ru
Feedback
Ethio-Kickoff

Ethio-Kickoff

Открыть в Telegram
3 514
Подписчики
-124 часа
-47 дней
-2030 день
Архив постов
⭕️የዋልያዎቹ አምበል በሰፈር ውድድር ዳኛ ደበደበ! : የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን (ዋሊያዎቹ) አምበል ጋቶች ፓኖም፣ በክረምት የሰፈር ውድድር ላይ ከጨዋታ ዳኛ ጋር በገባው አለመግባባት ዳኛውን መደብደ
⭕️የዋልያዎቹ አምበል በሰፈር ውድድር ዳኛ ደበደበ! : የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን (ዋሊያዎቹ) አምበል ጋቶች ፓኖም፣ በክረምት የሰፈር ውድድር ላይ ከጨዋታ ዳኛ ጋር በገባው አለመግባባት ዳኛውን መደብደቡ በማህበራዊ ሚዲያ እና በእግር ኳሱ ቤተሰብ ዘንድ ትልቅ ቁጣ እና ውዝግብ አስነስቷል። እንደ መረጃዎች ገለጻ፣ ተጫዋቹ በክረምቱ እረፍት ወቅት በተዘጋጀ የሰፈር ውድድር ላይ ተሳትፎ እያደረገ በነበረበት ወቅት፣ በመሀል ዳኛው ቢኒያም ወርቅአገኘሁ ቀይ ካር ተሰጥቶታል። በዚህ ሁኔታ የተበሳጨው ጋቶች ወደ ዳኛው በማቅናት አካላዊ ጥቃት አድርሷል። ተጫዋቹ ድርጊት ሲፈፅም የሚያሳይ ተንቀሳቃሽ ምስል በስፋት ተሰራጭቷል። ድርጊቱም በስፍራው የነበሩ ተመልካቾችን እና የስፖርት አፍቃሪዎችን በእጅጉ ያስገረመና ያሳዘነ ሆኗል። የጋቶች ፓኖም ድርጊት ይፋ ከሆነ በኋላ በርካታ ደጋፊዎች፣ ስፖርት ጋዜጠኞች እና የእግር ኳስ ተንታኞች ተጫዋቹን አጥብቀው እየኮነኑት ይገኛሉ። ጋቶች የሀገርን ትልቅ የብሔራዊ ቡድን አምበልነት በጥቁር እና ቢጫ ማሊያ የሚመራ፣ ለታዳጊዎች እና ለወጣት ተጫዋቾች መልካም አርኣያ (Role Model) መሆን የሚገባው አንጋፋ ተጫዋች ሆኖ ሳለ፣ በሰፈር ጨዋታ ላይ እንዲህ አይነት የስነ-ምግባር ጉድለት ማሳየቱ ጨርሶ የሚጠበቅ አይደለም ሲሉ ተችተውታል። በፕሮፌሽናል ደረጃ በሀገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጭ የተጫወተ ልምድ ያለው ተጫዋች፣ የስፖርታዊ ጨዋነት ህግጋትን ማክበር ሲገባው በቁጣ ተሸንፎ ዳኛ ላይ እጅ ለማንሳት መሞከሩ የሙያው ስነ-ምግባር አበክሮ ያፈነገጠ መሆኑን የብዙዎች አስተያየት ያመለክታል። @maleda

⭕️የ2019 የኢትዬጵያ ፕሪሚየር ሊግ መቼ ይጀመራል? የኢትዬጵያ ብሄራዊ ቡድን ወሳኝ ጨዋታዎች እና የአዲሱ ዓመት የኢትዬጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጠቅላላ ጉባኤው አዲስ ቀን አግኝቷል ክለቦች በይፋ መስኮቱ
⭕️የ2019 የኢትዬጵያ ፕሪሚየር ሊግ መቼ ይጀመራል? የኢትዬጵያ ብሄራዊ ቡድን ወሳኝ ጨዋታዎች እና የአዲሱ ዓመት የኢትዬጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጠቅላላ ጉባኤው አዲስ ቀን አግኝቷል ክለቦች በይፋ መስኮቱ ከመከፈቱ አስቀድሞ በተጨዋቾች የዝውውር ስራ ተጠምደው በሚገኙበት በአሁኑ ወቅት አወዳዳሪው አካል የአዲሱ ዓመት ሻምፒዮና የሚጀመርበትን ግዜ ይፋ ለማድረግ መቃረቡን በተለይ ለወርልድ ለስፓርት የደረሰው መረጃ አመላክቷል። ከወዲሁ እየወጡ ያሉት መረጃዎች የ2019 የኢትዬጵያ ፕሪሚየር ሊግ መስከረም ወር ይጀመራል በማለት ቢጠቁሙም አወዳዳሪው አካል ግን ሊጉ የሚጀመርበትን ቀርጥ ያለው ቀን በቀጣይ ሳምንት ይፋ እንደሚያደርግ አረጋግጠናል። ፕሪምየር ሊጉ በዝናብ መፈተኑ እና ክለቦች ለኢንተርናሽናል ዉድድር በቂ የመመዝገቢያ ግዜ እንዲያገኙ በተጨማሪ በቀጣዩ ዓመት የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን የአፍሪካ ዋንጫ ጨምሮ በርካታ ኢንተርናሽናል ጨዋታ ስለሚጠብቀው ሊጉን በግዜ መጀመር እንደሚገባ ወርልድ ያነጋገረቻቸው የክለብ አመራሮች ጠቁመዋል። የኢትዬጵያ ብሄራዊ ቡድን በመስከረም ወር ብቻ ከሱዳንና ከሴኔጋል ጋር የአፍሪካ ዋንጫ የማጣሪያ ጨዋታ ስለሚያደርግ ፕሪምየር ሊጉ በመስከረም የመጀመሩን ነገር ሲበዛ አጠራጣሪ ያደርገዋል። ዋሊያዎቹ እስከ መጋቢት የአፍሪካ ዋንጫ ወሳኝ የማጣሪያ ጨዋታ ስለሚያደርጉ ፕሪምየር ሊጉ ይሄንን ታሳቢ ያደረገ መርሃ ግብር ያስፈልገዋል። በሌላ በኩል የፊታችን እሁድ ይካሄዳል ተብሎ የነበረው የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ጠቅላላ ጉባኤ ለቀጣይ ሳምንት ቀን ተይዞለታል። ወርልድ እንዳረጋገጠችው ትላልቅ ውሳኔዎች የሚጠበቁበት ጠቅላላ ጉባኤ የዛሬ ሳምንት ሃምሌ 23/2018 ይካሄዳል።ለክለቦችም ደብዳቤ ደርሷቸዋል። @ወርልድ ስፖርት

➖️"በውጭ የሚኖሩ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ለሀገራቸው የሚጫወቱበትን አሰራር መዘርጋት ያስፈልጋል:"- ትውልደ ኢትዮጵያዊው አሊ አሕመድ 👇 የኢትዮጲያ እግርኳስ ፌደሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ባህሩ
+1
➖️"በውጭ የሚኖሩ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ለሀገራቸው የሚጫወቱበትን አሰራር መዘርጋት ያስፈልጋል:"- ትውልደ ኢትዮጵያዊው አሊ አሕመድ 👇 የኢትዮጲያ እግርኳስ ፌደሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ባህሩ ጥላሁን ከትውልደ ኢትዮጵያዊው የካናዳ ብሔራዊ ቡድን ተጨዋች አሊ አህመድ ጋር ውይይት አካሂደዋል። የፌዴሬሽኑ ዋና ስራ አስፈፃሚ ዲያስፖራ ተጨዋቾችን የመቀላቀል ሂደትን ወደ ሀገራችን ለማምጣት ከመንግስት ጋር ንግግር እንደተጀመረ የገለፁ ሲሆን አሊ አህመድ በዚህ ረገድ ለሌሎች ትውልደ ኢትዮጲያዊያን ተጨዋቾች ላይ ተነሳሽነት መፍጠር እንዲችል ጥሪ አቅርበውለታል። አሊ በበኩሉ ከሱ ውጪ ብዙ ቁጥር ያላቸው ትውልደ ኢትዮጲያዊያን እንዳሉ ገልፆ ዲያስፖራ ተጨዋቾች ወደ ሀገራቸው መጥተው የሚጫወቱበትን አሰራር መዘርጋት አስፈላጊ መሆኑን ሀገሬ ስፓርት ዘግቧል

🔄ዝውውር መረጃ ቧ2019 ዓ.ም. በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ እና የኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድሮችን ክለቦች ጠንካራ ሆነው ለመቅረብ እና ውጤታማ ለመሆን የተጨዋቾችና የአሰልጣኞች የተጨዋቾች ማስፈረም እና የ
+4
🔄ዝውውር መረጃ ቧ2019 ዓ.ም. በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ እና የኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድሮችን ክለቦች ጠንካራ ሆነው ለመቅረብ እና ውጤታማ ለመሆን የተጨዋቾችና የአሰልጣኞች የተጨዋቾች ማስፈረም እና የውል የማራዘም ሂደቱን በሠፊው ቀጥለዋል :: ✅️አዳማ ከተማ የ2018 የውድድር ዘመን የቅዱስ ጊዮርጊስን ክለቡን ከበርካታ ፈተናዎች አብሮ ያለፈው ኢንስትራክተር ፋሲል ተካልኝ ከአራት ዓመታት በኋላ ወደ አዳማ ከተማ መመለሱን ክለቡ በገፁ ላይ ይፋ አድርጓል። ✅️መቻል አሰልጣኝ ውበቱ አባተን የቀጠረው እና በዛሬው ዕለት ወደ ዝውውር በመግባት ያሬድ ካሳዬን የመጀመሪያ ፈራሚ ያደረገው መቻል ሁለት ተጨማሪ ተጫዋቾችን የግሉ አደረገ። ሁለተኛው ፈራሚ ረመዳን የሱፍ ሲሆን ሌላኛው የክለቡ ሦስተኛ ፈራሚ የመሐል ተከላካዩ አማኑኤል ተርፉ ነው። የቀድሞው የቅዱስ ጊዮርጊስ እና በኢራቁ አል ናፍጥር ክለብ ቆይታ የነበረው ይህ ተጫዋች ቀጣዩ መዳረሻው ወደ ኢትዮጵያ ተመልሶ መቻል ሆኗል። በተጨማሪም መቻል የአራት ወሳኝ ተጫዋቾችን ውል ያጠናቀቁ አራት ተጫዋቾችን ውል ማራዘሙን አሰልጣኝ ውበቱ አባተ ለሀገሬ ቴሌቪዥን ገልፀዋል።የቀድሞው የኢትዮጵያ ቡና እና በመቻል ያለፉትን ሁለት አመታት የቆየው የተከላካይ አማካዩ አማኑኤል ዮሐንስ ፣ የቀድሞው የአዳማ ከተማ እና ፋሲል ከነማ የመስመር አጥቂ በረከት ደስታ ፣ በኢትዮጵያ መድን ፣ ወልቂጤ ከተማ እና ኢትዮጵያ ቡና የተጫወተው አማካዩ አብዱልከሪም ወርቁ እና ከፋሲል ከነማ በኋላ በመቻል ላለፉት ሁለት አመታት ያሳለፈው የመስመር ተከላካዩ አለምብርሀን ይግዛው እና የግራ መስመር ተከላካዩ ዳዊት ማሞ ለተጨማሪ አመት በመቻል ለተጨማሪ አመታት ውላቸውን ያራዘሙ ተጫዋቾች ሆነዋል።

⭕️ኤፍሬም ታምራት ለሁለት ክለብ ፈርሟል? ትላንት ወላይታ ድቻን ለመቀላቀሉ ተስማምቶ በይፋዊ ማኅበራዊ ገጹ ይፋ ሆኖ የነበረው የግራ መስመር ተከላካዩ ኤፍሬም ታምራት በዛሬው ዕለት ለሲዳማ ቡና የሁለ
⭕️ኤፍሬም ታምራት ለሁለት ክለብ ፈርሟል? ትላንት ወላይታ ድቻን ለመቀላቀሉ ተስማምቶ በይፋዊ ማኅበራዊ ገጹ ይፋ ሆኖ የነበረው የግራ መስመር ተከላካዩ ኤፍሬም ታምራት በዛሬው ዕለት ለሲዳማ ቡና የሁለት አመት ውል ፈርሟል:: ተጫዋቹ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር በ2016 ዓ.ም የሊጉን ዋንጫ ካሸነፈ በኋላ ወደ አርባምንጭ መዘዋወሩ ይታወሳል። በአርባምንጭ የሁለት ዓመታት ቆይታ ያደረገው ኤፍሬም ወላይታ ድቻን በሁለት ዓመት ውል ተቀላቅሏል ተብሎ የነበረ ቢሆንም በዛሬው ዕለት ለሲዳማ ቡና ን መቀላቀሉ ተሰምቷል::

➖️ኢትዮጵያ ቡና በ8 ቢሊየን ብር ዘመናዊ ስታዲየም ሊገነባ ነው ➖️"ኢትዬጵያ ቡና ደሃ ክለብ አይደለም" ➖️"ይህን ታሪካዊ እና አንጋፋ ክለብ ለማሰልጠን ተመራጭ በመሆኔ ክብር ይሰማኛል" ➖️ጥራት
+2
➖️ኢትዮጵያ ቡና በ8 ቢሊየን ብር ዘመናዊ ስታዲየም ሊገነባ ነው ➖️"ኢትዬጵያ ቡና ደሃ ክለብ አይደለም" ➖️"ይህን ታሪካዊ እና አንጋፋ ክለብ ለማሰልጠን ተመራጭ በመሆኔ ክብር ይሰማኛል" ➖️ጥራት ያላቸው ተጨዋቾች ወደ ቡድናችን ይመጣሉ ከተመሰረተ ሃምሳኛ ዓመት ዕድሜው ላይ የሚገኘው ኢትዮጵያ ቡና እጅግ ዘመናዊ እና ግዙፍ ስታዲየም ሊገነባ መሆኑ ተሰማ። ይህ የተገለፀው ዛሬ ክለቡ በስካይ ላይት ሆቴል በሰጠው መግለጫ ላይ ሲሆን ይህንን ዘመናዊ ስታዲየም ለመገንባት ስምንት ቢሊዮን ብር እንደሚያስወጣው እና ዲዛይኑ ተሰርቶ መጠናቀቁን አዲሱ የክለቡ ፕሬዚዳንት ዶክተር እስራኤል ተናግረዋል። "ኢትዬጵያ ቡና ደሃ ክለብ አይደለም" ያሉት ዶክተር እስራኤል ክለባችን ተረጂ ሳይሆን ረጂ ክለብ ነው።ከራሳችን አልፈን ሌሎች ክለቦችን ለማገዝ የሚያስችል ጥናት ሰርተናል ብለዋል። አሰልጣኝ ገብረ መድህን ሃይሌ በበኩሉ ታላቁን የኢትዮጵያ ቡና ደጋፊ ይዤ የማይሳካ ነገር የለም ሲል ተናግሮ የትኛውም አሰልጣኝ ኢትዮጵያ ቡናን ማሰልጠን ይፈልጋል። ትልቅ እና አንጋፋ ክለብ ነው ።ታሪክ አለው።ሁሉም ቡድኑን ለማሰልጠን ይይፈልጋል።ይጉዋጋል።በመሆኑም የዚህ ዕድል ተመራጭ በመሆኔ ኩራት ይሰማኛል ብሉዋል። በቀጣዩ ዓመት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 68 ነጥብ ለማሳካት ማቀዱን የገለፀው አሰልጣኝ ገብረመድህን ወደ ኢትዮጵያ ቡና የመጣሁት ታሪክ ለማፃፍ ነው ደጋፊውን እና አመራሩን ይዤ ህልሜን፡አሳካዋለሁ ብለዋል በአስተያየቱ።

⭕️ቅዱስ ጊዮርጊስ ብሩክ እንዳለ እና ተመስገን ብርሃኑን አስፈርመዋል 👇 ቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ የ2019 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ እና የኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድሮችን በተሻለ ዝግጅትና
+1
⭕️ቅዱስ ጊዮርጊስ ብሩክ እንዳለ እና ተመስገን ብርሃኑን አስፈርመዋል 👇 ቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ የ2019 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ እና የኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድሮችን በተሻለ ዝግጅትና በጠንካራ ስብስብ ለመሳተፍና ውጤታማ ለመሆን ብሩክ እንዳለ እና ተመስገን ብርሃኑን ለማስፈረም መስማማቱን ክለቡ ይፋ አድርጓል ::

⭕️ተጠናቋል 🇪🇹ኢትዮጵያ 1-1 ዛምቢያ 🇿🇲 88' ምኅረት አየለ |46' ፕሪሽየስ ምዋዋ ድምር ውጤት: 🇪🇹2-3🇿🇲 የኢትዮጵያ ከ 17ዓመት በታች ሴቶች ብሔራዊ ቡድን ከዛምቢያ ጋር ያደረ
⭕️ተጠናቋል 🇪🇹ኢትዮጵያ 1-1 ዛምቢያ 🇿🇲 88' ምኅረት አየለ |46' ፕሪሽየስ ምዋዋ ድምር ውጤት: 🇪🇹2-3🇿🇲 የኢትዮጵያ ከ 17ዓመት በታች ሴቶች ብሔራዊ ቡድን ከዛምቢያ ጋር ያደረገውን ጨዋታ 1ለ1 በሆነ አቻ ውጤት አጠናቋል። ለኢትዮጵያ ታዳጊ ብሔራዊ ቡድን ምኅረት አየለ የአቻነት ጎል አስቆጥራለች። በሀገሯ 2ለ1 ያሸነፈችው ዛምቢያ በድምር ውጤት 3ለ2 በመርታት ለአለም ዋንጫ ውድድር አልፈዋል። የ 2026 ከ 17ዓመት በታች ሴቶች አለም ዋንጫ ውድድር በሞሮኮ አዘጋጅነት ይካሄዳል። @tikvahethsport

የመጨረሻ ዙር - የመልስ ጨዋታ እረፍት ከ17 ዓመት በታች ሴቶች የዓለም ዋንጫ ማጣርያ 🇪🇹 ኢትዮጵያ 0-0 ዛምቢያ 🇿🇲 (ድምር ውጤት: 1-2)
+3
የመጨረሻ ዙር - የመልስ ጨዋታ እረፍት ከ17 ዓመት በታች ሴቶች የዓለም ዋንጫ ማጣርያ 🇪🇹 ኢትዮጵያ 0-0 ዛምቢያ 🇿🇲 (ድምር ውጤት: 1-2)

⭕️ከ17 ዓመት በታች ሴቶች የዓለም ዋንጫ ማጣርያ 18' የመጨረሻ ዙር - የመልስ ጨዋታ 🇪🇹 ኢትዮጵያ 0-0 ዛምቢያ 🇿🇲 (ድምር ውጤት: 1-2)
⭕️ከ17 ዓመት በታች ሴቶች የዓለም ዋንጫ ማጣርያ 18' የመጨረሻ ዙር - የመልስ ጨዋታ 🇪🇹 ኢትዮጵያ 0-0 ዛምቢያ 🇿🇲 (ድምር ውጤት: 1-2)

⭕️የ2018 የሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኮከቦች ! ➖️የእርሶ የ2018 ኮከብ ማነው comments ላይ ከነ ምክንያቶ ያስቀምጡ
⭕️የ2018 የሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኮከቦች ! ➖️የእርሶ የ2018 ኮከብ ማነው comments ላይ ከነ ምክንያቶ ያስቀምጡ

🏆የ2018 የሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኮከብ አሰልጣኝ - ያሬድ ገመቹ ( ሲዳማ ቡና ) የዋንጫ እና የ200ሺህ ብር ተሸላሚ !
+3
🏆የ2018 የሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኮከብ አሰልጣኝ - ያሬድ ገመቹ ( ሲዳማ ቡና ) የዋንጫ እና የ200ሺህ ብር ተሸላሚ !

🏆የ2018 የሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኮከብ ግብ አስቆጣሪዎች 15 ግቦች የዋንጫ እና በጋራ የ200ሺህ ብር ተሸላሚ ! ⚽️ታምራት ኢያሱ ከ ፋሲል ከነማ ⚽️ናትናኤል ዳንኤል ከ ኢትዮጵያ ንግድ
+2
🏆የ2018 የሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኮከብ ግብ አስቆጣሪዎች 15 ግቦች የዋንጫ እና በጋራ የ200ሺህ ብር ተሸላሚ ! ⚽️ታምራት ኢያሱ ከ ፋሲል ከነማ ⚽️ናትናኤል ዳንኤል ከ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ

🏆የ2018 የሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኮከቦች ሽልማት ተካሄዷል! በኢሊሌ ሆቴል የ2018 የCBE ፕሪሚየር ሊግ የኮከቦች የሽልማት መርሐግብር ተካሄዷል :: በሽልማት መርሐግብሩ ላይ ተጨዋቾች
+4
🏆የ2018 የሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኮከቦች ሽልማት ተካሄዷል! በኢሊሌ ሆቴል የ2018 የCBE ፕሪሚየር ሊግ የኮከቦች የሽልማት መርሐግብር ተካሄዷል :: በሽልማት መርሐግብሩ ላይ ተጨዋቾች : አሰልጣኞች: የክለብ መሪዎች እና እንግዶች የታደሙበት ነበረ :: 🏆የ2018 የሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኮከብ ተጫዋች - ያሬድ ባየህ ( ሲዳማ ቡና ) ⭕️የዋንጫ እና የ250 ሺህ ብር ተሸላሚ ! 🏆የ2018 የሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኮከብ ተስፈኛ ተጫዋች - ሐብታሙ ጉልላት ( ቅዱስ ጊዮርጊስ ) ⭕️የዋንጫ እና የ100 ሺህ ብር ተሸላሚ 🏆የ2018 የሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኮከብ ግብ ጠባቂ - ፔፔ ሰይዶ ( ባሕር ዳር ከተማ ) ⭕️ዋንጫ እና የ150 ሺህ ብር ተሸላሚ ! 🏆የ2018 የሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ምስጉን ዋና ዳኛ - ሃይማኖት አዳነ ⭕️የዋንጫ እና የ150 ሺህ ብር ተሸላሚ 🏆የ2018 የሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ምስጉን ረዳት ዳኛ - ፋሲካ የኋላሸት ⭕️የዋንጫ እና የ125 ሺህ ብር ተሸላሚ

🏆 የ2018 የኢትዮጵያ ዋንጫ አሸናፊ 🏆 🥇 ወልዋሎ ዓ/ዩ ⚽ የፍፃሜ ውጤት ሲዳማ ቡና 0-2 ወልዋሎ ዓ/ዩ ⚽ 47' ኮንኮኒ ሀፊዝ ⚽ 90+9' በየነ ባንጃ
🏆 የ2018 የኢትዮጵያ ዋንጫ አሸናፊ 🏆 🥇 ወልዋሎ ዓ/ዩ ⚽ የፍፃሜ ውጤት ሲዳማ ቡና 0-2 ወልዋሎ ዓ/ዩ ⚽ 47' ኮንኮኒ ሀፊዝ ⚽ 90+9' በየነ ባንጃ

የ2018 የኢትዮጵያ ዋንጫ ፍፃሜ 70' ሲዳማ ቡና 0-1 ወልዋሎ ዓ/ዩ 47' ኮንኮኒ ሀፊዝ
+2
የ2018 የኢትዮጵያ ዋንጫ ፍፃሜ 70' ሲዳማ ቡና 0-1 ወልዋሎ ዓ/ዩ 47' ኮንኮኒ ሀፊዝ

⭕️የ2018 የኢትዮጵያ ዋንጫ እረፍት ሲዳማ ቡና 0-0 ወልዋሎ ዓ/ዩ
+5
⭕️የ2018 የኢትዮጵያ ዋንጫ እረፍት ሲዳማ ቡና 0-0 ወልዋሎ ዓ/ዩ

🏆የዛሬው ተጠባቂው የ2018 የኢትዮጵያ ዋንጫ የ2018 የውድድር ዘመን የኢትዮጵያ ዋንጫ ፍፃሜ በሲዳማ ቡና እና ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ መካከል ከቀኑ 5:00 ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም ይደረ
🏆የዛሬው ተጠባቂው የ2018 የኢትዮጵያ ዋንጫ የ2018 የውድድር ዘመን የኢትዮጵያ ዋንጫ ፍፃሜ በሲዳማ ቡና እና ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ መካከል ከቀኑ 5:00 ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም ይደረጋል። - ጨዋታው በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን (በሳተላይት እና ማህበራዊ ሚድያዎች) በቀጥታ ይተላለፋል የኢትዮጵያ ዋንጫን ማን ያነሳል ሲዳማ ቡና ወይስ ወልዋሎ ዓ/ዩ ? ?

ኢትዮጵያዊው አማካይ ጋቶች ፓኖም ከሳውዲው ክለብ አል አራቢ በኩዌት ፕሪምየር ሊግ ስድስተኛ ሆኖ ላጠናቀቀው አል ፉሂሉ መቀላቀሉን ተጨዋቹ በኢንስትግራም ገፁ አሳውቌል።
ኢትዮጵያዊው አማካይ ጋቶች ፓኖም ከሳውዲው ክለብ አል አራቢ በኩዌት ፕሪምየር ሊግ ስድስተኛ ሆኖ ላጠናቀቀው አል ፉሂሉ መቀላቀሉን ተጨዋቹ በኢንስትግራም ገፁ አሳውቌል።

⭕️ካፍ በኢትዮጵያ ስታዲዮምች ላይ ወሰነ ! ➖️ ሁለት የኢትዮጵያ ስታዲዬሞች ኢንተርናሽናል ጨዋታ እንዲያስተናግዱ የካፍን ይሁንታ አገኙ ➖️ሲዳማ ቡና እና ወልዋሎ ጨዋታቸውን የት ያደርጋሉ? ➖️ዋሊያ
+2
⭕️ካፍ በኢትዮጵያ ስታዲዮምች ላይ ወሰነ ! ➖️ ሁለት የኢትዮጵያ ስታዲዬሞች ኢንተርናሽናል ጨዋታ እንዲያስተናግዱ የካፍን ይሁንታ አገኙ ➖️ሲዳማ ቡና እና ወልዋሎ ጨዋታቸውን የት ያደርጋሉ? ➖️ዋሊያዎቹ ከአምስት ዓመት በኋላ ከስደት ይመለሳሉ 👇 የአፍሪካን እግር ኳስ በበላይነት የሚያስተዳድረው ካፍ ለአዲሱ የውድድር ዓመት ኢንተርናሽናል ጨዋታዎችን እንዲያስተናግዱ ይሁንታ የሰጣቸውን ሃገራት ይፋ አድርጓል። ኢትዬጵያም በሚያስገርም ሁኔታ ሁለት ስታዲዬሞች ኢንተርናሽናል ጨዋታ ኢንዲያስተናግዱ ፍቃድ አግኝተዋል ተብሏል። ካፍ ይፋ ባደረገው መረጃ መሰረት የድሬዳዋ እና የአበበ ቢቂላስታዲየም ኢንተርናሽናል ጨዋታ እንዲያስተናገዱ መፈቀዱ ይነገራል።ይህ ደግሞ ለክለቦቻችንና ለብሄራዊ ቡድኑ መልካም አጋጣሚ የሚፈጥር ከመሆኑ ባሻገር ከስደት የሚታደግ ይሆናል። በሚቀጥለው ወር መጨረሻ ኢንተርናሽናል ጨዋታ የሚጠብቃቸው ሲዳማ ቡና እና ወልዋሎ ጨዋታቸውን በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ለማድረግ መወሰናቸው ታውቋል። እግር ኳስ ፌዴሬሽኑ ሁለቱን ክለቦች ጠርቶ ባነጋገረበት ወቅት ነው የአበበ ቢቂላ ስታዲየምን ምርጫቸው ያደረጉት። ከአምስት ዓመት በኋላ ከስደት የሚመለሰው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን የአፍሪካ ዋንጫ የማጣሪያ ጨዋታውን ድሬዳዋ ላይም ያደርጋል። @ወርልድ ስፖርት