ru
Feedback
Ethiopian Private Higher Education & TVET Institutions' Association

Ethiopian Private Higher Education & TVET Institutions' Association

Открыть в Telegram

Tefera Gebeyehu Werku General Manager, EPHEIA Institutional email: info@ephetveta.com Website : https://ephetveta.com

Больше
5 379
Подписчики
-224 часа
Нет данных7 дней
-930 день
Архив постов
#NGAT አገር አቀፍ የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ነሐሴ 20 እና 21/2018 ዓ.ም ይሰጣል፡፡ ተመዝጋቢዎች Username፣ Password እና Entrance Ticket ለማግ
#NGAT   አገር አቀፍ የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ነሐሴ 20 እና 21/2018 ዓ.ም ይሰጣል፡፡     ተመዝጋቢዎች Username፣ Password እና Entrance Ticket ለማግኘት የኢሜይል አድራሻችሁን መጎብኘት አትዘንጉ። @tikvahuniversity

All Examinee Nehase 2018.zip7.20 MB

የብቃት ምዘና ፈተና ለምትወስዱ ጤና ባለሙያዎች በሙሉ ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በመጀመሪያ ዲግሪ ተመርቃችሁ የብቃት ምዘና ፈተናውን ለመውሰድ ምዝገባ ያጠናቀቃችሁ የጤና ባለሙያዎች በሙሉ፤ ፈተናው ከ
የብቃት ምዘና ፈተና ለምትወስዱ ጤና ባለሙያዎች በሙሉ ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በመጀመሪያ ዲግሪ ተመርቃችሁ የብቃት ምዘና ፈተናውን ለመውሰድ ምዝገባ ያጠናቀቃችሁ የጤና ባለሙያዎች በሙሉ፤ ፈተናው ከነሀሴ 13 እስከ 15/2018 ዓ.ም የሚሰጥ መሆኑን እየገለፅን፦ 1.የፈተናው መርሃ-ግብርም፦ -በ13/12/2018 ዓ.ም…… Medicine, Pharmacy, Anesthesia, Environmental Health, Human Nutrition, Emergency and Critical Care Nursing, Dental Medicine እና Optometry -በ14/12/2018 ዓ.ም…………, Medical Laboratory Science, Public Health, Midwifery, Medical Radiology Technology,  Pediatric and Child Health Nursing, Psychiatric Nursing,  Physiotherapy እና Surgical Nursing -በ15/12/2018 ዓ.ም…… Nursing ሁሉም ተፈታኝ ነሀሴ 12/2018 ዓ.ም ከሰዓት 8፡00 ሰዓት በመፈተኛ ጣቢያ በመገኘት ስለፈተናው አሰጣጥ ቅድመ ገለጻ (orientation) መከታተል፤ የቅድመ ፈተና መለማመጃ ጥያቄዎችን መስራትና፤ የመፈተኛ ክፍሉን መለየት ይኖርበታል::

የብቃት ምዘና ፈተና ለምትወስዱ ጤና ባለሙያዎች በሙሉ ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በመጀመሪያ ዲግሪ ተመርቃችሁ የብቃት ምዘና ፈተናውን ለመውሰድ ምዝገባ ያጠናቀቃችሁ የጤና ባለሙያዎች በሙሉ፤ ፈተናው ከ
የብቃት ምዘና ፈተና ለምትወስዱ ጤና ባለሙያዎች በሙሉ ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በመጀመሪያ ዲግሪ ተመርቃችሁ የብቃት ምዘና ፈተናውን ለመውሰድ ምዝገባ ያጠናቀቃችሁ የጤና ባለሙያዎች በሙሉ፤ ፈተናው ከነሀሴ 13 እስከ 15/2018 ዓ.ም የሚሰጥ መሆኑን እየገለፅን፦ 1.የፈተናው መርሃ-ግብርም፦ -በ13/12/2018 ዓ.ም…… Medicine, Pharmacy, Anesthesia, Environmental Health, Human Nutrition, Emergency and Critical Care Nursing, Dental Medicine እና Optometry -በ14/12/2018 ዓ.ም…………, Medical Laboratory Science, Public Health, Midwifery, Medical Radiology Technology,  Pediatric and Child Health Nursing, Psychiatric Nursing,  Physiotherapy እና Surgical Nursing -በ15/12/2018 ዓ.ም…… Nursing ሁሉም ተፈታኝ ነሀሴ 12/2018 ዓ.ም ከሰዓት 8፡00 ሰዓት በመፈተኛ ጣቢያ በመገኘት ስለፈተናው አሰጣጥ ቅድመ ገለጻ (orientation) መከታተል፤ የቅድመ ፈተና መለማመጃ ጥያቄዎችን መስራትና፤ የመፈተኛ ክፍሉን መለየት ይኖርበታል::

"ማህበሩ እያደረገ ያለው እንቅስቃሴ የሚመሰገን ነው ተባለ" ይህ የተባለው የኢፌዴሪ የትምህርትና ሥልጠና ባለስልጣን መመሪያ ቁጥር 990/2016 ማሻሻያ ላይ ለመወያየት ነሀሴ 1/2018 በትምህርት ሚ
+2
"ማህበሩ እያደረገ ያለው እንቅስቃሴ የሚመሰገን ነው ተባለ" ይህ የተባለው የኢፌዴሪ የትምህርትና ሥልጠና ባለስልጣን መመሪያ ቁጥር 990/2016 ማሻሻያ ላይ ለመወያየት ነሀሴ 1/2018 በትምህርት ሚኒስቴር መሰብሰቢያ አዳራሽ በጠራው የገፅ ለገፅ የውይይት መድረክ ላይ ነው። ለውይይት የቀረበው የመመሪያ ማሻሻያው ዋና ማጠንጠኛ ህግን በመተላለፍ ሲኦሲ ሳይመዘኑ የከፍተኛ ትምህርት የቀጠሉ ዜጎች ያጋጠማቸውን ችግር በዘላቂነት ለመፍታት ያለመ ነው። የማህበሩ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ሞላ ጸጋይ ከሲኦሲ ጋር በተያያዘ ያጋጠመውን ችግር መፍትሔ እንዲሰጠው ማህበሩ ለአመታት ጥረት ሲያደርግ እነደነበረ አስታውሰው ባለስልጣኑ የማህበሩን የአመታት ጥያቄና የዜጎችን እንግልት ከግምት ውስጥ በማስገባት መመሪያውን ለማሻሻል መወሰኑ ሊመሰገን ይገባዋል ብለዋል። በመቀጠል የመመሪያ ማሻሻያው በሚመለከት ከማህበሩ ለባለሥልጣኑ በጽሁፍ የቀረበውን አስተያየት በዝርዝር አቅርበዋል።  በውይይቱ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አመራሮች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ማህበሩ የተቋማትና የዜጎች ጥያቄ ምላሽ ያገኝ ዘንድ ላደረገው ብርቱ ጥረት ከልብ ያመሰገኑ ሲሆን ለወደፊቱም መልስ ያላገኙ ችግሮች እንዲፈቱ የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ አደራ ብለዋል። የውይይት መድረኩን የባለስልጣኑ ከፍተኛ አመራሮች አቶ ታምሩ መስፍን እና አቶ ሀብታሙ ገ/መድህን መርተውታል።

#Update የጤና ሙያ ተመራቂዎች የብቃት ምዘና ፈተና ከነሐሴ 13-15/2018 ዓ.ም ይሰጣል። ፈተናውን ለመውሰድ ስማችሁን ከፋይዳ ቁጥር ጋር አያይዛችሁ በመጠባበቅ ላይ የምትገኙ የጤና ሙያ ተመራቂ
#Update የጤና ሙያ ተመራቂዎች የብቃት ምዘና ፈተና ከነሐሴ 13-15/2018 ዓ.ም ይሰጣል። ፈተናውን ለመውሰድ ስማችሁን ከፋይዳ ቁጥር ጋር አያይዛችሁ በመጠባበቅ ላይ የምትገኙ የጤና ሙያ ተመራቂ ተመዛኞች ከሐምሌ 27- 30/2018 ዓ.ም ድረስ ብቻ https://hple.moh.gov.et/ ላይ በመግባት Fayda and Password በማስገባት የፈተና ጣቢያ እንድትመርጡ ጤና ሚኒስቴር አሳስቧል። እያንዳንዱ የፈተና ጣቢያ በየሙያ መስኩ ማስተናገድ በሚችለው ከፍተኛ የተመዛኝ ቁጥር መጠን ገደብ ስለተቀመጠለት የፈተና ጣቢያ ምርጫ ቀድማችሁ በማጠናቀቅ ተጠቃሚ መሆን የምትችሉ መሆኑ ተገልጿል። በምዝገባ ወቅት ለሚገጥማችሁ ማንኛውም ችግር በነጻ የስልክ መስመር 952 በመደወል ከዚያም 3 ቁጥርን በመጫን በቀጥታ እገዛ ማግኘት ትችላላችሁ፡፡

ማሰታወሻ ለሁሉም የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፦ የትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን (ETA) በክረምት የአረንጓዴ አሻራ እና በጎ ተግባራት ስራዎች ጉዳይ ለመወያየት የጠራው ስብሰባ ነገ ሐምሌ 28/2018 በትምህርት ሚኒስቴር መሰብሰቢያ አዳራሽ ከጠዋቱ 2፥30 ጀምሮ እንደሚደረግ ማስታወስ እንወዳለን። የማህበሩ ጽ/ቤት

+1
2018_EHPLE Information Booklet.zip20.92 MB

ለብቃት ምዘና ፈተና መረጃ በማስተሳሰር ላይ ለምትገኙ የጤና ሙያ ተመራቂዎች በሙሉ ___ የብቃት ምዘና ፈተና ለመውሰድ ስማችሁን ከብሄራዊ መታወቂያ መለያ ቁጥራችሁ (National ID FAN 16 Di
ለብቃት ምዘና ፈተና መረጃ በማስተሳሰር ላይ ለምትገኙ  የጤና ሙያ ተመራቂዎች በሙሉ ___ የብቃት ምዘና ፈተና ለመውሰድ ስማችሁን ከብሄራዊ መታወቂያ መለያ ቁጥራችሁ (National ID FAN 16 Digit) ጋር በማስተሳሰር ላይ የምትገኙ ነገር ግን በተለያዩ ምክንያቶች ያላገባደዳችሁ የጤና ሙያ ተመራቂዎች፤ የመረጃ ማስተሳሰሪያ ጊዜ ገደብ እስከ ሀምሌ 24/2018 ዓ.ም የተራዘመ መሆኑን እያሳወቅን ፣ በተጨማሪም ለፈተናው አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት ለማድረግ የሚረዱና ጠቃሚ መረጃዎችን የያዙ Information Booklets እንዲሁም Practice Test Booklets ከዚህ በታች በተቀመጡት Zip files ውስጥ ማግኘት የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡

የጤና ሙያ ፈቃድ ፈተናን ለመውሰድ በመጠባበቅ ላይ ለምትገኙ ተመዛኞች በሙሉ ____ የጤና ሚኒስቴር ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በመጀመሪያ ዲግሪ ለተመረቃችሁ ጤና ባለሙያዎች በነሀሴ ወር 2018 ዓ.ም
የጤና ሙያ ፈቃድ ፈተናን ለመውሰድ በመጠባበቅ ላይ ለምትገኙ ተመዛኞች በሙሉ ____ የጤና ሚኒስቴር ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በመጀመሪያ ዲግሪ ለተመረቃችሁ ጤና ባለሙያዎች በነሀሴ ወር 2018 ዓ.ም የጤና ሙያ ፈቃድ ፈተና ለመስጠት በዝግጅት ላይ ይገኛል፡፡ ስለዚህም መረጃችሁን ወደ ሲስተም ያላስገባችሁ ነባር እና አዲስ ተመዛኞች ከሰኔ 30/2018 እስከ ሃምሌ 17/2018 ዓ.ም ድረስ ብቻ ይህንን https://hple.moh.gov.et/ ማስፈንጠሪያ/Link/ በመጫን የብሄራዊ መታወቂያ መለያ ቁጥር (National ID FAN 16 Digit) በማስገባት አስፈላጊ መረጃዎችን በማሟላት ለምዝገባ እንድትዘጋጁ እናሳስባለን፡፡ ማሳሰቢያ፡- ▪ ይህ መረጃን የማስተሳሰር ሂደት እንዳለቀ የፈተና ጣቢያ መረጣ ሂደት እንደሚቀጥል እናሳውቃለን፡፡ ▪ በሰኔ 2018 ዓ.ም የመውጫ ፈተና ተፈትናችሁ ያለፉችሁ ተመዛኞች የስም ዝርዝራችሁን በተማራችሁበት ተቋም አማካኝነት ወደ ሲስተም ማስጫን የሚጠበቅባችሁ መሆኑን እናሳስባለን። ከጤና ሚኒስቴር የተገኘ መረጃ

የጤና ሙያ ፈቃድ ፈተና ለወሰዳችሁ የጤና ሙያ ፈቃድ ፈተና ለወሰዳችሁ ጤና ባለሙያዎች በሙሉ ___ በሰኔ 2018 ዓ.ም በጤና ሚኒስቴር በኩል የተሰጠውን የጤና ሙያ ፈቃድ ፈተና የወሰዳችሁ ተመዛኞች ከ
የጤና ሙያ ፈቃድ ፈተና ለወሰዳችሁ  የጤና ሙያ ፈቃድ ፈተና ለወሰዳችሁ  ጤና ባለሙያዎች በሙሉ ___ በሰኔ 2018 ዓ.ም በጤና ሚኒስቴር በኩል የተሰጠውን የጤና ሙያ ፈቃድ ፈተና የወሰዳችሁ ተመዛኞች ከሰኔ 27/2018 ዓ.ም ጀምሮ https://hple.moh.gov.et ላይ በመግባትና የብሄራዊ መለያ ቁጥር(FAN) እና Password በማስገባት የፈተና ውጤታችሁን መመልከት የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን በውጤታችሁ ላይ ቅሬታ ያላችሁ ተመዛኞች ውጤት ከተገለጸበት ዕለት አንስቶ ባሉት 10 (አስር) ተከታታይ የስራ ቀናት በስልክ ቁጥር 952 በስራ ሰዓት በመደወል ሙሉ ስም፣ ዲፓርትመንት እና የተማራችሁበትን የትምህርት ተቋም ስም በማሳወቅ ጥያቄዎቻችሁን ማቅረብ የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡ ማሳሰቢያ፦ የጤና ሙያ ፈቃድ ፈተናውን ያለፋችሁ ተመዛኞች ከሰኞ ሃምሌ 6/2018 ዓ.ም ጀምሮ ስም ዝርዝራችሁ ወደ ክልል የሚላክ ስለሆነ የሙያ ፍቃዳችሁን 12ተኛ ክፍል በተማራችሁበት ክልል ማውጣት የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡             የጤና ሚኒስቴር

ቅሬታዎን ያስገቡ! በመውጫ ፈተና ውጤትዎ ላይ ቅሬታ ካለዎት ቅሬታዎን በኦንላይን ያስገቡ፡፡ ➫ ውጤትዎ ያልተገኘ ከሆነ ➫ Disqualified የተባሉ ከሆነ ➫ ፊርማ ቢፈርሙም NG የተባሉ ከሆነ ➫ የተሳሳተ ጾታ ከመረጡና መሠል ቅሬታ ካለዎ ማቅረብ ይችላሉ፡፡ የመውጫ ፈተና ውጤት ባዩበት ሊንክ (https://result.ethernet.edu.et) ላይ Submit Complaint የሚለውን ይጫኑ፣ Complaint Category ከሚለው ይምረጡ፣ Description የሚለው ባዶ ቦታ ላይ ቅሬታውን አጠር አድርገው ይግለፁ፣ ስልክ ቁጥርዎን ያስገቡና Submit Complaint የሚለውን በመጫን ያጠናቅቁ፡፡

Greetings, Your 2018 End-Year Exit Examination result is now available. You can view your result by providing your username a
+2
Greetings, Your 2018 End-Year Exit Examination result is now available. You can view your result by providing your username and download a temporary certificate from the results portal using the link below: Link: https://result.ethernet.edu.et Please note: If you have any complaints regarding your result, you can submit them online while viewing your results, as indicated on the portal. You do not need to come in person to submit a complaint. @FDRE_EAES_Official

የብቃት ምዘና ፈተና ለምትወስዱ ጤና ባለሙያዎች በሙሉ ___ ጤና ሚኒስቴር ከሰኔ 17 እስከ 19/2018 ዓ.ም የብቃት ምዘና ፈተና ለመስጠት ዝግጅቱን አጠናቋል፡፡ ስለሆነም ሁሉም ተፈታኝ ሰኔ 16/2
የብቃት ምዘና ፈተና ለምትወስዱ ጤና ባለሙያዎች በሙሉ ___ ጤና ሚኒስቴር ከሰኔ 17 እስከ 19/2018 ዓ.ም የብቃት ምዘና ፈተና ለመስጠት ዝግጅቱን አጠናቋል፡፡ ስለሆነም ሁሉም ተፈታኝ ሰኔ 16/2018 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 ሰዓት በመረጣችሁት በመፈተኛ ጣቢያ በመገኘት ስለፈተናው አሰጣጥ ቅድመ ገለጻ (orientation) መከታተል፤ የቅድመ ፈተና መለማመጃ ጥያቄዎችን መስራትና፤ የመፈተኛ ክፍሉን መለየት የሚጠበቅባችሁ ሲሆን ወደ ፈተና ጣቢያ ስትመጡ የብሄራዊ መታወቂያ (National ID) እንዲሁም ሲስተሙ የሚሰጠውን QR code ያለው የፈተና መግቢያ /ስሊፕ/ print out ይዛችሁ መገኘት ይኖርባችኋል፡፡ ከጤና ሚኒስቴር የተገኘ መረጃ

የመውጫ ፈተና #በድጋሚ ተፈታኝ የሆናችሁ (Re-sitters) የፈተና መግቢያ ትኬታችሁን https://verify.ethernet.edu.et/ ላይ በመግባት አውርዳችሁ ፕሪንት ማለት ይኖርባችኋል። (ከላ
+2
የመውጫ ፈተና #በድጋሚ ተፈታኝ የሆናችሁ (Re-sitters) የፈተና መግቢያ ትኬታችሁን https://verify.ethernet.edu.et/ ላይ በመግባት አውርዳችሁ ፕሪንት ማለት ይኖርባችኋል። (ከላይ በምስል የተያያዘውን ቅደም ተከተል በመጠበቅ ያውርዱ።)

የ2018 ዓ.ም የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና መርሐግብር (Exit Exam Schedule) የቅድመ-ምረቃ የመውጫ ፈተና ከሰኔ 04-12/2018 ዓ.ም እንደሚሰጥ ይታወቃል

#ለሁሉም_የግል_ከፍተኛ_ትምህርት_ተቋማት #ባሉበት፤ በunified መሶብ አማካኝነት በግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚሰጡ አገልግሎቶችን በተመለከተ ዝርዝር ገለጻና እና ውይይት ለማድረግ እቅድ ተይዟ
#ለሁሉም_የግል_ከፍተኛ_ትምህርት_ተቋማት #ባሉበት፤ በunified መሶብ አማካኝነት በግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚሰጡ አገልግሎቶችን በተመለከተ ዝርዝር ገለጻና እና ውይይት ለማድረግ እቅድ ተይዟል። ስለሆነም በዚህ አገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ የሚደረገው ገለጻ እና ውይይት ላይ የተቋሙ የበላይ ኃላፊ እና ሬጅስትራር ኃላፊ አርብ፣ ግንቦት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ጠዋት 3:00 ሰዓት በትምህርት ሚኒስቴር መሰብሰቢያ አዳራሽ እንድትገኙ በጥብቅ እያሳወቅን ስብሰባው ላይ መገኘት የማይችሉ ሀላፊዎች ተወካይ መላክ እንዳለባቸው እናሳስባለን፡፡ የኢፊዲሪ ትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን