Ethiopian Private Higher Education & TVET Institutions' Association
رفتن به کانال در Telegram
Tefera Gebeyehu Werku General Manager, EPHEIA Institutional email: info@ephetveta.com Website : https://ephetveta.com
نمایش بیشتر5 360
مشترکین
+124 ساعت
+217 روز
+6530 روز
آرشیو پست ها
+2
የመውጫ ፈተና #በድጋሚ ተፈታኝ የሆናችሁ (Re-sitters) የፈተና መግቢያ ትኬታችሁን https://verify.ethernet.edu.et/ ላይ በመግባት አውርዳችሁ ፕሪንት ማለት ይኖርባችኋል።
(ከላይ በምስል የተያያዘውን ቅደም ተከተል በመጠበቅ ያውርዱ።)
የ2018 ዓ.ም የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና መርሐግብር (Exit Exam Schedule)
የቅድመ-ምረቃ የመውጫ ፈተና ከሰኔ 04-12/2018 ዓ.ም እንደሚሰጥ ይታወቃል
#ለሁሉም_የግል_ከፍተኛ_ትምህርት_ተቋማት
#ባሉበት፤
በunified መሶብ አማካኝነት በግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚሰጡ አገልግሎቶችን በተመለከተ ዝርዝር ገለጻና እና ውይይት ለማድረግ እቅድ ተይዟል።
ስለሆነም በዚህ አገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ የሚደረገው ገለጻ እና ውይይት ላይ የተቋሙ የበላይ ኃላፊ እና ሬጅስትራር ኃላፊ አርብ፣ ግንቦት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ጠዋት 3:00 ሰዓት በትምህርት ሚኒስቴር መሰብሰቢያ አዳራሽ እንድትገኙ በጥብቅ እያሳወቅን ስብሰባው ላይ መገኘት የማይችሉ ሀላፊዎች ተወካይ መላክ እንዳለባቸው እናሳስባለን፡፡
የኢፊዲሪ ትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን
ከጤና ሚኒስቴር የተላለፈ መልዕክት:-
የብቃት ምዘና ፈተና ለምትወስዱ ጤና ባለሙያዎች በሙሉ
___
"ጤና ሚኒስቴር በሰኔ ወር 2018 ዓ.ም ለሚሰጠው የብቃት ምዘና ፈተና ለመውሰድ ስማችሁን ከፋይዳ ቁጥር ጋር ያያያዛችሁ ተመዛኞች የተቀመጠውን https://hple.moh.gov.et/ ማስፈንጠሪያ /Link/ በመጫን የመፈተኛ ጣቢያ እየመረጣችሁ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ይህ የፈተና ጣቢያ መረጣ እስከ ግንቦት 26/2018 ዓ.ም ድረስ ብቻ መሆኑን አውቃችሁ ምርጫችሁን እንድታገባድዱ እያሳሰብን ከተጠቀሰው ቀን ውጭ ምዝገባው የማይራዘም መሆኑን እናሳውቃለን"፡፡
*የሬሜዲያል ፈተና ፕሮግራም*
የ2018 ዓ.ም የሪሚዲያል (አቅም ማሻሻያ) ፕሮግራም ፈተና ከግንቦት 27/2018 ዓ.ም እስከ ሰኔ 03/2018 ዓ.ም ለአምስት ቀናት እንደሚሰጥ ይታወቃል።
በተጠቀሱት ቀናት በሁለት ፈረቃ በጠዋት እና በከሰዓት መርሐግብር የሚሰጠው የሪሚዲያል ፕሮግራም (የተፈጥሮ ሳይንስ እና ማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች) የፈተና መርሐግብር ከታች ተያይዟል።
የብቃት ምዘና ፈተና ለምትወስዱ ጤና ባለሙያዎች በሙሉ
__
ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በመጀመሪያ ዲግሪ ተመርቃችሁ የብቃት ምዘና ፈተና ለመጀመሪያ ጊዜ ወይም በድጋሚ ለመውሰድ ስማችሁን ከፋይዳ ቁጥራችሁ ጋር አስተሳሰራችሁ በመጠባበቅ ላይ ለምትገኙ የጤና ሙያ ተመራቂዎች በሙሉ፤ ጤና ሚኒስቴር በሰኔ ወር 2018 ዓ.ም ፈተናውን ለመስጠት እየተዘጋጀ በመሆኑ ሁላችሁም ተመዛኞች ከግንቦት 20 – 26/2018 ዓ.ም ድረስ ብቻ https://hple.moh.gov.et/ ማስፈንጠሪያ /Link/ በመጫን FAYDA and Password በማስገባት የፈተና ጣቢያ እንድትመርጡ እናሳስባለን፡፡
ማሳሰቢያ፦
▪ እያንዳንዱ የፈተና ጣቢያ በየሙያ መስኩ ማስተናገድ በሚችለው ከፍተኛ የተመዛኝ ቁጥር ልክ ገደብ ስለተቀመጠለት የፈተና ጣቢያ ምርጫ ቀድማችሁ በማጠናቀቅ ተጠቃሚ መሆን የምትችሉ መሆኑን እያሳወቅን ከፍተኛው የተመዛኝ ቁጥር በደረሰበት የፈተና ጣቢያ ላይ ተጨማሪ ምዝገባ ማከናወን የማይቻል መሆኑን እናሳስባለን።
▪ ለብቃት ምዘና ፈተና የመፈተኛ ጣቢያ መምረጥ የምትችሉት ስማችሁን ከፋይዳ ቁጥር ጋር ያያያዛችሁ ተመዛኞች ብቻ ይሆናል፡፡
▪ በምዝገባ ወቅት ለሚገጥማችሁ ማንኛውም ችግር በነጻ የስልክ መስመር 952 በመደወል ከዚያም 3 ቁጥርን በመጫን በቀጥታ እገዛ ማግኘት የምትችሉ መሆኑን ከወዲሁ እናሳስባለን፡፡
▪ ለበለጠ ማብራሪያ ከስር የተያያዘውን ቪዲዮ መመልከት የምትችሉ መሆኑን እናሳስባለን፡፡
CALL FOR PAPER FROM QUEENS COLLEGE
ማስታወቂያ
የሪሜዲያል ፈተና እና የቅድመ ምረቃ ትምህርት መውጫ ፈተና (Exit Exam) የምሰጥበት ቀን የተቀየረ መሆኑ ተገለጸ።
ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር ምክክር በማድረግ የሪሜዲያል እና EXIT EXAM ፈተናዎች የምሰጥባቸው ቀናት እንደምከተለው የተሸጋሸጉ መሆኑን እናሳውቃለን።
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት
@FDRE_EAES_Official
🔔 #አስቸኳይ
የፊታችን ሰኞ መሠጠት የሚጀምረውን የሪሚዲያል ተማሪዎች ፈተና ለመውሰድ የተመዘገባቹ በአስቸኳይ የማረጋገጥ ሥራ እንድታደርጉ ትምህርት ሚኒስቴር አሳስቧል።
የማረጋገጥ ሥራው (Self Verification) ከ2-3 ደቂቃዎች ብቻ የሚወስድና የተፈታኞችን የትምህርት ሰነዶች ከፋይዳ መታወቂያ ጋር ለማስተሳሰር የሚያስችል መሆኑ ተመላክቷል።
ተከታዩን ሊንክ (https://verify.ethernet.edu.et/) ከተጫኑ በኋላ Remedial Examination የሚለውን ይጫኑ፣ Start Verification የሚለውን በመጫንና የሚያስፈልገውን በመሙላት ያረጋግጡ።
የሪሚዲያል ተማሪዎች ፈተና ከግንቦት 17-20/2018 ዓ.ም እእንደሚሰጥ ይታወቃል።
verify.ethernet.edu.et
Ministry of Education
Ministry of Education | Exit Exam Verification
#MoH
#የብቃት_ምዘና_ፈተና
የጤና ባለሙያዎች የብቃት ምዘና ፈተና በግንቦት ወር 2018 ዓ.ም ይሰጣል፡፡ - ጤና ሚኒስቴር
ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በመጀመሪያ ዲግሪ ተመርቃችሁ የብቃት ምዘና ፈተና ለመጀመሪያ ጊዜ ወይም በድጋሚ ለመውሰድ በመጠባበቅ ላይ የምትገኙ የጤና ባለሙያዎች በግንቦት ወር 2018 ዓ.ም የብቃት ምዘና ፈተና ለመስጠት በዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የጤና ሚኒስቴር ገልጿል፡፡
ስለዚህም ተፈታኞች ተቋሙ አዲስ ባለማው ሲስተም መረጃችሁን ለማስገባት የብሔራዊ መታወቂያ መለያ ቁጥር (16 Digit FAN) እና ስልክ ቁጥር አስፈላጊ በመሆኑ ተመዛኞች ከሚያዚያ 21/2018 ዓ.ም እስከ ሚያዚያ 30/2018 ዓ.ም ድረስ ብቻ https://hple.moh.gov.et/ ሊንክን በመጫን ከላይ የተገለፀውን እንዲሁም ሲስተሙ የሚጠይቃችሁን መረጃ በማሟላት ለምዝገባ ዝግጁ እንድትሆኑ ሚኒስቴሩ አስገንዝቧል፡፡
በተጨማሪ ነባር ተመዛኞች ሲስተሙ የጤና ሚኒስቴር መለያ ቁጥር (Registration Number) ስለሚጠይቃችሁ ተቋሙ በይፋዊ የቴሌግራም ገፁ ከለቀቀው የተፈታኞች ዝርዝር ውስጥ ስማችሁን በመፈለግ ከስማችሁ ትይዩ ያለውን መለያ ቁጥር (Registration Number) ተጠቅማችሁ መረጃችሁን እንድታያይዙ ሚኒስቴሩ አሳስቧል፡፡
@tikvahuniversity
Shape the Future of African Business Schools in Addis Ababa! 🌍✨
Join a landmark global summit at the UN ECA, Africa Hall. This is the premier academic networking bridge for Ethiopian institutions to connect with 60+ global universities and 150+ international delegates.
📍 Location: UN ECA, Africa Hall
📅 Date: 13–15 May 2026
🔥 High-Impact Sessions & Masterclasses:
The Future of Work: Exclusive Masterclass on modern career shifts.
AI in Education: Navigating the promise and pitfalls.
Powering Youth: Skills and mindsets for a digital global economy.
Quality & Innovation: Accreditation, ethics, and impactful research.
Teaching for Tomorrow: Rethinking learning for the next generation.
🎟 EXCLUSIVE LOCAL OFFER
Special discounted rates are available for local Ethiopian universities and colleges.
Registration:https://www.aabschools.com/events/aabs-2026-connect-conference
⚠️ URGENT: Seats for local delegates are strictly limited. Secure your institution’s on time.
📞 +251904848586
✅ከትምህርት ሚኒስቴር የተላለፈ መልዕክት
ለሁሉም የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት
ትምህርት ሚኒስቴር የሬሜዲያል ተማሪዎች በተመለከተ አፋጣኝ ምላሽ እንድትሰጡ ስለሚፈልግ ይህን ተግባራዊ እንድታደርጉ እንጠይቃለን።
+1
የኢትዮጵያ የግል ከፍተኛ ትምህርትና የቴ/ሙ/ስልጠና ተቋማት ማህበር ቅዳሜ ሚያዝያ 10ቀን 2018ዓ/ም ከማህበሩ አባላትና ከኢፌዲሪ ትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን በመጡ የስራ ሐላፊዎች አማካኝነት የምክክር መድረክና የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና አከናውኗል።
በምክክር መድረኩ በግል ትምህርት ዘርፉ ያሉ ዓበይት ጉዳዮችና የሚታዩ ተግዳሮቶችን ለመቅረፍ ምክክር የተደረገባቸው ሲሆን በስራ አስፈፃሚ ቦርዱ በኩል የ6ወር ስራእ አፈፃፀም ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
