917
Подписчики
Нет данных24 часа
+47 дней
-330 дней
Архив постов
ሚያዝያ 07/2018ዓ.ም
የተማሪዎች ስነ-ምግባር በማሻሻል ተወዳዳሪና ብቁ ዜጋ ለመፍጠር የመምህራን ሚና ከፍተኛ መሆኑ የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ትምህርት ፅህፈት ቤት ገለጸ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
ይህ የተገለፀው የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ትምህርት ፅ/ቤት ከገደባኖ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎችና መምህራን በተማሪዎች ስነ-ምግባርና ውጤት ማሻሻል ዙሪያ ውይይት በተደረገበት ወቅት ነው።
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳደር አቶ ሚፍታ ሁሴን በውይይቱ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት መንግስት ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራባቸው ከሚገኝባቸው ዘርፎች አንዱ ትምህር እንደሆነ ተናግረው በተስጠው ልዩ ትኩረት ልክ የሚፈልገው ውጤት ማምጣት እንዳልተቻለ አስታውሰው ተማሪዎች በውጤታቸው ላይ ትኩረት ሰጥተው መማር እንዳለባቸው ጠቅሰው የትምህርትጊዜያቸው በተገቢው በመጠቀም መምህራን የሚሰጡት የድጋፍ ትምህርት ፣ወርክ ሺት በመሰራትና ላይብረሪ ገብተው በማንበብ ሀገር አቀፍ በሚሰጡ ፈተናዎች ላይ የሚፈልገውን ከፍተኛ ውጤት ማምጣት እንደሚችሉ አስገንዝበዋል።
ዋና አስተዳዳሪው አክለው መወ ተማሪዎች ውጤታቸው ለማሻሻል ስነ ምግባር ከፍተኛ ሚና እንደሚጪወት ገልፀው የትምህርት ቤቱ ህግና ደንብ በማክበር ሀገር የምትጠብቀው ውጤት ማምጣት እንደሚገባቸው አስታውቀዋል።
ትምህርት ለአንድ ሀገር ሁለንትናዊ ብልፅግና መሰረት በመሆኑ መምህራን ተማሪዎቻቸውን በማገዝ ፣ወርክሺት በመስጠት ፣ የድጋፍ ትምህርት በመስጠት ትኩረት ስጥተው በመስራት እንዳለባቸው ተማሪዎች የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ ከመምህራን ብዙ መስራት እንደሚጠበቅባቸው በየደረጃው የሚዘጋጁ ፈተናዎች ላይ ልዩ ትኩረት በመስጠት የተማሪዎች የንባብ ክህሎት ለማሻሻል የቤተ መፅሐፍ የአገልግሎት አሰጣጥ ጊዜ ማሻሻል እንደሚገና የተማሪዎች ፍላጎት ያማከለ ስነ ዘዴ በመጠቀም ውጤታቸው ማሻሻል እንደሚገባ ገልጸዋል።
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ትምህርት ቤቶች ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አለማየሁ ኬኔ በበኩላቸው የተማሪዎች ውጤት እና ስነምግባር ለማሻሻል ትኩረት ሰጥተው እየሰሩ መሆኑን ገልፀው፤ተማሪዎች ለትምህርታቸው ጊዜ ሰጥተው መማር እንዳለባቸ ተናግረዋል።
በስነ ምግባር የታነፀ ዜጋ ለመፍጠር የመምህራን ድርሻ የጎላ በመሆኑ ውጤታቸውን እዲያሻሽሉ ልዩ እገዛ በማድረግ ፣ተማሪዎች በማብቃት የዕረፍት ቀናትን በመጠቀም ውጤታቸው ማሻሻል እንዲችሉ ተገቢውን ድጋፍ መስጠት ከመምህራን ይጠበቃል ብለዋል።
ሚያዝያ 07/2018 ዓ.ም
ባለፉት 5 አመታት ከ24,081 በላይ ወጣቶችን በቋሚና ጊዜያዊ የስራ ዕድል መፍጠር መቻሉ የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ልማት ፅ/ቤት አስታወቀ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ልማት ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ጂላሉ ወራቄ እንደገለፁት ባለፉት አምስት አመታት ስራ አጥ ወጣቶች በመለየት፣ግንዛቤ በመፍጠር፣በማደራጀትና የስራ ባለቤት በማድረግ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸው እያደገ መምጣቱን ገልፀዋል።
አቶ ጂላሉ አክለውም የስራ አጥ ቁጥርን ለመቀነስ ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ ባከባቢያችን ያሉ ፀጋዎችን መጠቀም እንደሚገባ አውስተው በዚህም ባለፉት 5 አመታት 26,436 ስራ አጥ ወጣቶች በመለየት አጫጭር የክህሎት ስልጠና በመስጠት 24,081 ወጣቶች በከተማና በገጠር ስራ እድል መፈጠሩን ጠቅሰው በግብርና ዘርፍ በመኸር ሠብል ልማት ፣መስኖ ፣ማደለብና ማሟከት እንዲሁም በዶሮ ሃብት ፣በንብ ማነብ፣በንግድ ዘርፍ እና በእንጨትና ብረታ ብረት ዘርፍ መሰማራታቸውን ገልጸዋል።
መንግስት ያመቻቸላቸው ከኦሞ ባንክ ከ47 ሚሊዮን ብር በላይ ብድር በመውሰድ ቢዝነስ ፕላን በመስራት ለተደራጁ ስራ አጥ ወጣቶች መሰራጨት መቻሉን የገለጹት አቶ ጅላሉ ወራቄ በከተማ ለተደራጁ ወጣቶች 22 የማምረቻና መሸጫ ሼድ በመገንባት ለተደራጁ ወጣቶች ማስተላለፍ እንደተቻለ ጠቅሰው በገጠር ስራ ዕድል ፈጠራ ለተደራጁ ወጣቶች 1 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በቤተሰብ፣በኪራይና የውል መሬት በማስተላለፍ ማስጠቀም መቻሉን ገልፀዋል።
ለኢንተርፕራይዞች ከ119 ሚሊዮን ብር በላይ የገበያ ትስስር የተፈጠረ ሲሆን ባለፉት 5 አመታት በገጠርና ከተማ ከተደራጁ ስራ አጥ ወጣቶች ከ38 ሚሊዮን ብር በላይ ዕዳ ማስመለስ መቻሉን ጠቅሰው የወጣቶች ሁለንትናዊ ተጠቃሚነት ሚያረጋግጡ የመንግስት ድጋፎች በማጠናከር ኢንተርፕራይዞች እንዲያሻሽሉ ለማድረግ በተሰራው ስራ በ5 አመታት ውስጥ ከ314 በላይ ኢንተርፕራይዞች የደረጃ ሽግግር ማድረግ መቻላቸውን አቶ ጅላሉ ተናግረዋል።
በመጨረሻም አቶ ጅላሉ ወራቄ ባስተላለፉት መልዕክት
ቋሚ ስራ ዕድል ፈጠራ ፣ ብድር አመለለስ ፣ ብድር ስርጭት፣ቁጣባ እና ኢንተርፕራይዞችን በELMIS ምዝገባ ተግባራት በጠንካራ ቅንጅታዊ አሰራር መተግበር እንዳለበት ገልጸው በአከባቢያችን ያሉ ጸጋዎቻችንን በአግባቡ በመለየት ወጣቶች የስራ ዕድል ፈጠራ በተጨባጭ ተጠቃሚ እንዲሆኑ በትኩረት እየተሰራ ሲሆን ዜጎች በሚፈጠሩት የስራ ዕድሎች ከራሳቸው ባለፈ ሌሎችንም ተጠቃሚ በማድረግ የስራ
አጥነትን ችግር መቅረፍ እንዳለባቸው አሳስበዋል።
ሚያዝያ 06/2018 ዓ.ም
በባለፉት 5 አመታት በህበረተሰቡ፣ በተወላጅ ባለሀብቶች፣ በመንግስትና ከ620 ሚልዮን ብር በላይ ሀብት በማሰብሰብ የትምህርት መሰረተ ልማት ማሻሻል መቻሉን የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ትምህርት ቤቶች ፅፈት ቤት አስታወቀ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
የተማሪዎች የመጽሀፍት አቅርቦት ለማሻሻል አዲሱ ስርአተ ትምህርት ተከትሎ በክልሉ በባለፉት 3 አመታት አንድ መጽሀፍት ለአንድ ተማሪ ንቅናቄ በወረዳው ከ1ኛ እስከ 8ኛ ክፍል ከ59 ሺህ 7 መቶ በላይ የመማሪያና ማስተማሪያ መጽሀፍት በማሳተም ለተማሪዎች ተደራሽ መደረጉን ጽ/ቤቱ አክሎ ገልጿል።
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ትምህርት ቤቶች ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አለማየሁ ኬኔ እንደገለፁት በመንግስት ልዩ ትኩረት ከተሰጠባቸው ዘርፎች አንዱና ዋነኛው የትምህርት ልማት መሆኑን ገልፀው ትምህርት ለአንድ ሃገር ሁለንተናዊ ዕድገት የማይተካ ሚና ያለው በመሆኑ በትውልድ ላይ በትኩረት መስራት እንደሚገባና መንግስት ለትምህርት ዘርፍ የሠጠውን ልዩ ትኩረት አጠናክሮ በማስቀጠል የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ
እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
አቶ አለማየሁ አክለው ባለፉት 5 አመታት በህብረተሰቡ፣ በተወላጅ ባለሀብቶች፣ በመንግስትና በአጋር ድርጅቶች 620 ሚሊዮን 890 ሺህ 530 ብር በላይ በማሰብሰብ የትምህርት መሰረተ ልማት ለማሻሻል ሰፊ ስራ መሰራት መቻሉን አስታውሰው ለዚህም ህብረተሰቡ፣ተወላጅ ባለሀብትና መንግስት በትምህርት ዘርፍ እያደረጉት ያለው ተሳትፎ ከጊዜ ወደ ጊዜ በከፍተኛ ደረጃ እያደገ መምጣቱን ገልፀዋል።
በ2013 ዓ.ም ከህብረተሰብ፣ ከተወላጅ ባለሀብቶች፣ ከመንግስትና ከአጋሮች በአመት ይሰበሰብ የነበረው 91 ሚሊዮን ብር እንደነበር አስታውሰው በ2018 በጀት አመት ከ620 ሚሊዮን ብር በላይ መድረሱን ተናግረዋል።
በዚህም ገለፃቸው 202 አዳዲስ የመማሪያ ክፍሎች 110 የቅድመ አንደኛ የመማሪያ ክፍል 8900 የተማሪዎች መቀመጫ ወንበር 1831 የተማሪዎች ጠረጴዛ ፣250 ክፍል የመምህራን መኖሪያ ቤት ፤46 አዲስ ቤተ ሙከራ ክፍሎች፣ 20 አዲስ ቤተ መጽሀፍት፣ 58 አዳዲስ IT ላብራቶሪ ኮምፒውተር ፣193 ጥቁር ሰሌዳ ፣16 ፕሪንተር ማሽን 32፣ከ59,723 የመማሪያና ማስተማሪያ መጽሀፍት፣የመጸዳጃ ብሎኮች መገንባት፣22 የሴት ተማሪዎች ሞዴስ ክፍሎች መገንባታቸውን ጠቅሰው 380 መማሪያ ክፍል ጥገና ፣191 ቅድመ አንደኛ ክፍል ጥገና ፣41ቤተ ሙከራ ጥገና ፣241 የመምህራን መኖሪያ ቤት ጥገና ፣6891 የተማሪዎች መቀመጫ ወንበር ጥገና በማድረግ አገልግሎት እንዲሰጡ ተደርጓል ሲሉ ተናግረዋል።
የመማር ማስተማር ስራ ለማሳደግ ወቅቱን የሚፈልገውን ቴክኖሎጂ ተጠቃሚ ለማድረግ ከተለያዩ አካላት ፤ኮምፒውተር ፤ፕሪንተር።፤የሶላር ፀሀይ ሀይል ድጋፍ መደረጉ ጠቅሰው የትምህርት ቤቶች ደረጃ በማሻሻል የንፁህ መጠጥና የማብራት ተደራሽ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑንና ምቹ የትምህርት አከባቢ ለመፍጠረወ በርካታ ስራዎች እንደተሰሩ የተናገሩት አቶ አለማየሁ አዲስ የስረዓተ ትምህርት ለውጥ መደረጉ ተከትሎ መምህራንና የትምህርት አመራሮች ከአዲሱ ስረዓተ ትምህርት ለመላመድና የማስተማሪያ ስነ ዘዴ ለማሻሻል በየደረጃው የተለያየ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ማግኘት መቻላቸውን ገልጸው የተጀመረው የተማሪዎች ውጤት ለማሻሻል ተጠናክሮ እንደሚቀጥልና የትምህርት ዘርፍ ውጤታማ ለማድረግ ሁሉም የበኩሉን እንዲወጣ ጥሪ አስተላልፈዋል።
የቀይ ባሕር ሰላም እና የኢትዮጵያ መልሕቅ
(የዕለቱ መልዕክት)
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
በአንድ መንደር ውስጥ የሚገኝ ትልቅ ግቢ ነበረ። የዚህ ግቢ ደጅ የሰፈሩ ሰዎች ወደ ገበያ እና ወደ ሥራ የሚወጡበት ዋናው መተላለፊያ መንገድ ነበር።
የግቢው ባለቤት ብርቱ እና ኃላፊነት የሚሰማው ሰው ስለነበር፣ ደጁን እንደ ቤቱ ይጠብቃል፤ ይከታተለውም ነበር። እርሱ ደጁ ላይ ሲቆም ሰፈሩ ሰላም ነው፤ ወንበዴ አይፈናጠጥም፤ አላፊ አግዳሚውም ያለ ስጋት ይመላለሳል።
ዘመናት ነጎዱ እና በታሪክ አጋጣሚ ይህ ብርቱ ባለቤት የገዛ ግቢው በር ተዘግቶበት፣ ደጁንም ተነጥቆ ወደ ጓሮ እንዲገባ ተደረገ። የቀይ ባሕር እና የኢትዮጵያ ጉዳይም እንደዚህ ነው።
የቀይ ባሕር የንግድ መስመር የዓለም ኢኮኖሚ የልብ ትርታ ነው። "ባሕርን የራቀ፣ ሰላምን አራቀ" እንዲሉ፣ ዛሬ ይህ የልብ ትርታ በባብ ኤል መንደብ ማነቆ ምክንያት እየተቆራረጠ ይገኛል።
"ጅብ ከሄደ ውሻ ጮኸ" እንደሚባለው ዓለም አቀፍ የባሕር ኃይሎች ጥበቃ ቢጀምሩም፣ ስጋቱ ግን አሁንም እንደ ቀጠለ ነው።
ኢትዮጵያ በጥንት ዘመን የአክሱም ሥልጣኔ ባለቤት በነበረችበት ወቅት፣ አዱሊስ የሰላም ወደብ፣ ንጉሥ ካሌብ ደግሞ የባሕር ላይ ወንበዴዎችን የሚቀጣ የቀይ ባሕር ዘብ ነበሩ። ዛሬ ግን 130 ሚሊዮን ሕዝብ ያላት እና በቀጣናው ግዙፍ ወታደራዊ አቅም ያላት ሀገር፣ የባሕር በር እጦት እጆቿን ታስራ እንድትቀመጥ አድርጓታል።
የቀይ ባሕር ዳርቻ ሀገራት የባሕር ላይ ውንብድናን እና ሽብርተኝነትን ለመቆጣጠር አቅም ማጣታቸው የደኅንነት ክፍተት ፈጥሯል። "ባለቤት የሌለው ቤት፣ ሌባ ይፈነጭበታል" እንደሚባለው፣ ቀጣናው የስጋት ማዕከል የሆነው ቀጥተኛ ባለቤት እና ጠንካራ ኃይል ስለሌለው ነው።
ኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤት መሆኗ ለራሷ የኢኮኖሚ ነፃነት ብቻ ሳይሆን ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብም አስተማማኝ መልሕቅ ነው።
የዓለም ዲፕሎማሲያዊ ማኅበረሰብ ሊረዳው የሚገባው ቁልፍ ጉዳይ ቢኖር፣ ኢትዮጵያ ወደ ቀይ ባሕር መመለሷ ለሀገራዊ ብልጽግና ብቻ ሳይሆን አደጋ ላይ ለወደቀው የባብ ኤል መንደብ ሰላም ዋስትና መሆኑን ነው።
“ከሩቅ ዘመድ፣ የቅርብ ጎረቤት” እንዲሉ፣ ከሩቅ ሀገር ከሚመጡ የባሕር ኃይሎች ይልቅ፣ በቀጣናው ያለችው ኢትዮጵያ ጠንካራ የባሕር ኃይል ኖሯት የቀይ ባሕርን ደኅንነት ብትጠብቅ፣ ዓለም አቀፍ ንግድ ከመታፈን ይድናል።
በመሆኑም የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ የፍትሕ፣ የታሪክ እና የዓለም አቀፍ ደኅንነት ጥያቄ በመሆኑ፣ ተገቢውን ዲፕሎማሲያዊ ድጋፍ ሊያገኝ ይገባል።
የቀይ ባሕር ሞገድ እንዲረጋጋ፣ የኢትዮጵያ መልሕቅ ማረፍ አለበት!
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
#EBC #Ethiopia #RedSea #SeaAccess #worldpeace
የሳምንቱ አበይት ዜናዎች
ሚያዚያ 04/2018 ዓ.ም
🎤 የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፍታ ሁሴን ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች
የትንሳኤን በዓል በማስመልከት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
🎤 በባለፉት 5 አመታት በህብረተሰቡ፣ በመንግስትና በባለሀብቶች ተሳትፎ 2 መቶ 45.6 ሚሊየን ብር ሀብት በመሰብሰብ በርካታ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎችን መከናወናቸውን የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ጽ/ቤት ገለጸ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨፨
🎤 የማህፀን በር ጫፍ ካንሰር መከላከያ ክትባት እንዲሳካ የባለድርሻ አካላት ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት አስታወቀ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
🎤 "ሳይንስ ይመራናል ቴክኖሎጂ ያስቀድመናል "
በሚል መሪ ቃል በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ
ለ5ኛ ዙር የሳይንስ ቴክኖሎጂ የፈጠራ ስራዎች አውደ ራዕይ ተካሄደ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
🎤 የማዕከላዊ ኢትዮጵያዊ ክልል ትምህርት ቢሮ የሙያ ፈቃድ ምዘና በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ለሚገኙ መምህራን እና ርዕሰ መምህራን በመሃል አምባ ከተማ ሰጥቷል።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
