917
المشتركون
+124 ساعات
+57 أيام
-330 أيام
أرشيف المشاركات
ሚያዝያ 06/2018 ዓ.ም
በባለፉት 5 አመታት በህበረተሰቡ፣ በተወላጅ ባለሀብቶች፣ በመንግስትና ከ620 ሚልዮን ብር በላይ ሀብት በማሰብሰብ የትምህርት መሰረተ ልማት ማሻሻል መቻሉን የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ትምህርት ቤቶች ፅፈት ቤት አስታወቀ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
የተማሪዎች የመጽሀፍት አቅርቦት ለማሻሻል አዲሱ ስርአተ ትምህርት ተከትሎ በክልሉ በባለፉት 3 አመታት አንድ መጽሀፍት ለአንድ ተማሪ ንቅናቄ በወረዳው ከ1ኛ እስከ 8ኛ ክፍል ከ59 ሺህ 7 መቶ በላይ የመማሪያና ማስተማሪያ መጽሀፍት በማሳተም ለተማሪዎች ተደራሽ መደረጉን ጽ/ቤቱ አክሎ ገልጿል።
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ትምህርት ቤቶች ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አለማየሁ ኬኔ እንደገለፁት በመንግስት ልዩ ትኩረት ከተሰጠባቸው ዘርፎች አንዱና ዋነኛው የትምህርት ልማት መሆኑን ገልፀው ትምህርት ለአንድ ሃገር ሁለንተናዊ ዕድገት የማይተካ ሚና ያለው በመሆኑ በትውልድ ላይ በትኩረት መስራት እንደሚገባና መንግስት ለትምህርት ዘርፍ የሠጠውን ልዩ ትኩረት አጠናክሮ በማስቀጠል የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ
እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
አቶ አለማየሁ አክለው ባለፉት 5 አመታት በህብረተሰቡ፣ በተወላጅ ባለሀብቶች፣ በመንግስትና በአጋር ድርጅቶች 620 ሚሊዮን 890 ሺህ 530 ብር በላይ በማሰብሰብ የትምህርት መሰረተ ልማት ለማሻሻል ሰፊ ስራ መሰራት መቻሉን አስታውሰው ለዚህም ህብረተሰቡ፣ተወላጅ ባለሀብትና መንግስት በትምህርት ዘርፍ እያደረጉት ያለው ተሳትፎ ከጊዜ ወደ ጊዜ በከፍተኛ ደረጃ እያደገ መምጣቱን ገልፀዋል።
በ2013 ዓ.ም ከህብረተሰብ፣ ከተወላጅ ባለሀብቶች፣ ከመንግስትና ከአጋሮች በአመት ይሰበሰብ የነበረው 91 ሚሊዮን ብር እንደነበር አስታውሰው በ2018 በጀት አመት ከ620 ሚሊዮን ብር በላይ መድረሱን ተናግረዋል።
በዚህም ገለፃቸው 202 አዳዲስ የመማሪያ ክፍሎች 110 የቅድመ አንደኛ የመማሪያ ክፍል 8900 የተማሪዎች መቀመጫ ወንበር 1831 የተማሪዎች ጠረጴዛ ፣250 ክፍል የመምህራን መኖሪያ ቤት ፤46 አዲስ ቤተ ሙከራ ክፍሎች፣ 20 አዲስ ቤተ መጽሀፍት፣ 58 አዳዲስ IT ላብራቶሪ ኮምፒውተር ፣193 ጥቁር ሰሌዳ ፣16 ፕሪንተር ማሽን 32፣ከ59,723 የመማሪያና ማስተማሪያ መጽሀፍት፣የመጸዳጃ ብሎኮች መገንባት፣22 የሴት ተማሪዎች ሞዴስ ክፍሎች መገንባታቸውን ጠቅሰው 380 መማሪያ ክፍል ጥገና ፣191 ቅድመ አንደኛ ክፍል ጥገና ፣41ቤተ ሙከራ ጥገና ፣241 የመምህራን መኖሪያ ቤት ጥገና ፣6891 የተማሪዎች መቀመጫ ወንበር ጥገና በማድረግ አገልግሎት እንዲሰጡ ተደርጓል ሲሉ ተናግረዋል።
የመማር ማስተማር ስራ ለማሳደግ ወቅቱን የሚፈልገውን ቴክኖሎጂ ተጠቃሚ ለማድረግ ከተለያዩ አካላት ፤ኮምፒውተር ፤ፕሪንተር።፤የሶላር ፀሀይ ሀይል ድጋፍ መደረጉ ጠቅሰው የትምህርት ቤቶች ደረጃ በማሻሻል የንፁህ መጠጥና የማብራት ተደራሽ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑንና ምቹ የትምህርት አከባቢ ለመፍጠረወ በርካታ ስራዎች እንደተሰሩ የተናገሩት አቶ አለማየሁ አዲስ የስረዓተ ትምህርት ለውጥ መደረጉ ተከትሎ መምህራንና የትምህርት አመራሮች ከአዲሱ ስረዓተ ትምህርት ለመላመድና የማስተማሪያ ስነ ዘዴ ለማሻሻል በየደረጃው የተለያየ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ማግኘት መቻላቸውን ገልጸው የተጀመረው የተማሪዎች ውጤት ለማሻሻል ተጠናክሮ እንደሚቀጥልና የትምህርት ዘርፍ ውጤታማ ለማድረግ ሁሉም የበኩሉን እንዲወጣ ጥሪ አስተላልፈዋል።
የቀይ ባሕር ሰላም እና የኢትዮጵያ መልሕቅ
(የዕለቱ መልዕክት)
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
በአንድ መንደር ውስጥ የሚገኝ ትልቅ ግቢ ነበረ። የዚህ ግቢ ደጅ የሰፈሩ ሰዎች ወደ ገበያ እና ወደ ሥራ የሚወጡበት ዋናው መተላለፊያ መንገድ ነበር።
የግቢው ባለቤት ብርቱ እና ኃላፊነት የሚሰማው ሰው ስለነበር፣ ደጁን እንደ ቤቱ ይጠብቃል፤ ይከታተለውም ነበር። እርሱ ደጁ ላይ ሲቆም ሰፈሩ ሰላም ነው፤ ወንበዴ አይፈናጠጥም፤ አላፊ አግዳሚውም ያለ ስጋት ይመላለሳል።
ዘመናት ነጎዱ እና በታሪክ አጋጣሚ ይህ ብርቱ ባለቤት የገዛ ግቢው በር ተዘግቶበት፣ ደጁንም ተነጥቆ ወደ ጓሮ እንዲገባ ተደረገ። የቀይ ባሕር እና የኢትዮጵያ ጉዳይም እንደዚህ ነው።
የቀይ ባሕር የንግድ መስመር የዓለም ኢኮኖሚ የልብ ትርታ ነው። "ባሕርን የራቀ፣ ሰላምን አራቀ" እንዲሉ፣ ዛሬ ይህ የልብ ትርታ በባብ ኤል መንደብ ማነቆ ምክንያት እየተቆራረጠ ይገኛል።
"ጅብ ከሄደ ውሻ ጮኸ" እንደሚባለው ዓለም አቀፍ የባሕር ኃይሎች ጥበቃ ቢጀምሩም፣ ስጋቱ ግን አሁንም እንደ ቀጠለ ነው።
ኢትዮጵያ በጥንት ዘመን የአክሱም ሥልጣኔ ባለቤት በነበረችበት ወቅት፣ አዱሊስ የሰላም ወደብ፣ ንጉሥ ካሌብ ደግሞ የባሕር ላይ ወንበዴዎችን የሚቀጣ የቀይ ባሕር ዘብ ነበሩ። ዛሬ ግን 130 ሚሊዮን ሕዝብ ያላት እና በቀጣናው ግዙፍ ወታደራዊ አቅም ያላት ሀገር፣ የባሕር በር እጦት እጆቿን ታስራ እንድትቀመጥ አድርጓታል።
የቀይ ባሕር ዳርቻ ሀገራት የባሕር ላይ ውንብድናን እና ሽብርተኝነትን ለመቆጣጠር አቅም ማጣታቸው የደኅንነት ክፍተት ፈጥሯል። "ባለቤት የሌለው ቤት፣ ሌባ ይፈነጭበታል" እንደሚባለው፣ ቀጣናው የስጋት ማዕከል የሆነው ቀጥተኛ ባለቤት እና ጠንካራ ኃይል ስለሌለው ነው።
ኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤት መሆኗ ለራሷ የኢኮኖሚ ነፃነት ብቻ ሳይሆን ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብም አስተማማኝ መልሕቅ ነው።
የዓለም ዲፕሎማሲያዊ ማኅበረሰብ ሊረዳው የሚገባው ቁልፍ ጉዳይ ቢኖር፣ ኢትዮጵያ ወደ ቀይ ባሕር መመለሷ ለሀገራዊ ብልጽግና ብቻ ሳይሆን አደጋ ላይ ለወደቀው የባብ ኤል መንደብ ሰላም ዋስትና መሆኑን ነው።
“ከሩቅ ዘመድ፣ የቅርብ ጎረቤት” እንዲሉ፣ ከሩቅ ሀገር ከሚመጡ የባሕር ኃይሎች ይልቅ፣ በቀጣናው ያለችው ኢትዮጵያ ጠንካራ የባሕር ኃይል ኖሯት የቀይ ባሕርን ደኅንነት ብትጠብቅ፣ ዓለም አቀፍ ንግድ ከመታፈን ይድናል።
በመሆኑም የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ የፍትሕ፣ የታሪክ እና የዓለም አቀፍ ደኅንነት ጥያቄ በመሆኑ፣ ተገቢውን ዲፕሎማሲያዊ ድጋፍ ሊያገኝ ይገባል።
የቀይ ባሕር ሞገድ እንዲረጋጋ፣ የኢትዮጵያ መልሕቅ ማረፍ አለበት!
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
#EBC #Ethiopia #RedSea #SeaAccess #worldpeace
የሳምንቱ አበይት ዜናዎች
ሚያዚያ 04/2018 ዓ.ም
🎤 የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፍታ ሁሴን ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች
የትንሳኤን በዓል በማስመልከት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
🎤 በባለፉት 5 አመታት በህብረተሰቡ፣ በመንግስትና በባለሀብቶች ተሳትፎ 2 መቶ 45.6 ሚሊየን ብር ሀብት በመሰብሰብ በርካታ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎችን መከናወናቸውን የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ጽ/ቤት ገለጸ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨፨
🎤 የማህፀን በር ጫፍ ካንሰር መከላከያ ክትባት እንዲሳካ የባለድርሻ አካላት ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት አስታወቀ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
🎤 "ሳይንስ ይመራናል ቴክኖሎጂ ያስቀድመናል "
በሚል መሪ ቃል በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ
ለ5ኛ ዙር የሳይንስ ቴክኖሎጂ የፈጠራ ስራዎች አውደ ራዕይ ተካሄደ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
🎤 የማዕከላዊ ኢትዮጵያዊ ክልል ትምህርት ቢሮ የሙያ ፈቃድ ምዘና በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ለሚገኙ መምህራን እና ርዕሰ መምህራን በመሃል አምባ ከተማ ሰጥቷል።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
ሚያዚያ 03/2018 ዓ.ም
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፍታ ሁሴን ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች
የትንሳኤን በዓል በማስመልከት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
ዋና አስተዳዳሪው በዓሉን ስናከብር የሀገራችን መለያ የሆነውን በመተጋገዝና በመደጋገፍ አብሮ የማሳለፍ ልማድን በማጠናከር አቅም ለሌላቸውና በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ወገኖቻችንን በማሰብና ማዕድ በማጋራት ሊሆን እንደሚገባም አሳስበዋል።
የትንሳኤ በዓል በክርስትና ሀይማኖት ተከታዮች ዘንድ የዐብይ ጾም መጠናቀቅን ተከትሎ በድምቀት ከሚከበሩና ትልቅ ትርጉም ከሚሰጣቸው ዐበይት ክብረ በአላት መካከል ተጠቃሽ ነው።
በየእምነቶቻችን አስተምህሮዎችና ድንጋጌዎች መሠረት የምናከናውናቸው ሃይማኖታዊ ክንዋኔዎች ውስጣዊና ውጫዊ ሠላምን በማጎናፀፍ የእርስበርስ ትስስራችን በፍቅር፣ በመከባበርና በመቻቻል ላይ እንዲመሠረትና እንዲጠናከር ድልድይ ሆነው የሚያገለግሉ ናቸው ሲሉም አቶ ሚፍታ ሁሴን በመልዕክታቸው ጠቁመዋል።
በመጨረሻም ዋና አስተዳዳሪው በዓሉን ስናከብር በፍቅር በመተሳሰብ፣ በመቻቻል በመደጋገፍና በመረዳዳት ባህላዊ እሴታችንን ባይበልጥ በማጠናከር ለተቸገሩ ወገኖች ካለን ላይ በማካፈል ሊሆን ይገባል ሲሉም ተናግረዋል።
በድጋሚ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች የትንሳኤ በዓል የሰላም፣ የደስታና የፍቅር እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን ገልፀዋል።
መልካም በዓል!!!
ሚያዝያ 03/2018 ዓ ም
በባለፉት 5 አመታት በህብረተሰቡ፣ በመንግስትና በባለሀብቶች ተሳትፎ 2 መቶ 45.6 ሚሊየን ብር ሀብት በመሰብሰብ በርካታ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎችን መከናወናቸውን የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ጽ/ቤት ገለጸ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨፨
በወረዳው ባለፉት አምስት አመታት 271.84 ኪ.ሜ በላይ የጠጠር መንገድ መስራት መቻሉን ጽ/ቤቱ አክሎ ገልጿል።
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ አሸብር ረጋ በባለፉት 5 አመታት በተቋሙ በመንገድ ልማት የተከናወኑ ተግባራት አስመልክቶ እንደገለጹት መንገድ ለአንድ ሀገርና አካባቢ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ብልጽግና የሚኖረው ፍይዳ ከፍተኛ መሆኑን ገልፀው የመንገድ ተደራሽነት በማሳደግ የምንፈልገውን ማህበራዊ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ እድገት ለማረጋገጥ የመንግስት፣ የህብረተሠቡና የባለሃብቱ ንቁ ተሳትፎ እንዲሁም የመንግስትና ቅንጅታዊ አሠራር በማጠናከር በርካታ ስራዎች መሰራተቸውን አስታውቀዋል።
አቶ አሸብር አክለውም መንግስት ባለፉት 5 አመታት የህብረተሰቡን የመንገድ ተደራሽነት ችግር ለመቅረፍ በረካታ ጥረት ሲያደርግ መቆየቱን ገልፀው ፣ቀበሌን ከቀበሌ፣ ቀበሌን ከወረዳና ከሌሎች አጎራባች አካባቢዎች ጋር በማስተሳሰር ሰፊ ርብርብ መደረጉን የተናገሩት ኃላፊው ባለፉት 5 ዓመታት ብቻ በወረዳው መንግስት፣ ተወላጅ ባለሃብቶችና ህብረተሰቡን በማስተባበር ከ2 መቶ 45.6 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ 271.84 ኪ.ሜ የጠጠር ስራ እና 151.3 ኪ.ሜ የአፈር ስራ በላይ የገጠር መንገድ ግንባታ፣ የተለያዩ ስትራክቸሮች ስራ፣ የድልድይ ግንባታ እና ሌሎች መሰረተ ልማቶች በማከናወን አ/አደሩን ማስጠቀም ስለመቻሉ ገልጸዋል።
በወረዳው በ2013 ዓ.ም በህብረተሰቡ በመንግስትና በባለሃብቶች ተሳትፎ 15 ሚሊዮን 950,000 ብር ተሰብስቦ የነበረ ሲሆን አሁን ላይ በአምስት አመቱ ሁለት መቶ 45.6 ሚሊዮን ብር መሰብሰብ ተችሏል።
ይህም በ2013 ዓ/ም ከነበረው 89.1ኪ.ሜ በ2018 ዓ.ም 271.84 ኪ.ሜ የጠጠር መንገድ ማደጉን አመላክተው ከዚህም በተጨማሪ የአፈር ስራ በ2013 ዓ.ም 43 ኪ.ሜ ከነበረበት 151.3 ኪ.ሜ መስራትና መፈፀም የተቻለ ሲሆን የወረዳችን የመንገድ ሽፋን በ2013 ዓ.ም ከነበረበት 28.13% በ2018 ዓ/ም ወደ 75.3% ማደጉን ገልጸዋል።
እንዲሁም በርካታ እስትራክቸሮች እና እጅግ ለመገናኘት አታካች የነበሩ ድልድዮች የመገንባት ስራ ተሰርቷል፡፡
በመንገድ ልማት ዘርፍ በህብረተሰብ ተሳትፎ ማደጉን ተከትሎ በተሰሩ ውጤታማ ስራዎች የህብረተሰቡ ተጠቃሚነት ማሳደግ መቻሉን ተናግረዋል፡፡
ቀጣይ የመንገዶች ማስተዳደር ስራዎች እንደሚሰራ እንደዚሁም የተሰሩ የመንገድ ልማት ስራዎች የረጅም ጊዜ እንዲያገለግሉ የመጠበቅ የመንከባከብ የመጠገን ስራ በትኩረት ይሰራል ብለዋል ሲል የዘገበው የወረዳው መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት ነው።
መጋቢት 30/2018 ዓ.ም
የማህፀን በር ጫፍ ካንሰር መከላከያ ክትባት እንዲሳካ የባለድርሻ አካላት ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት አስታወቀ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት እድሜያቸው ከ9-14 ዓመት ለሆኑ ልጃገረዶች የሚሰጠው የማህፀን በር ጫፍ ካንሰር ክትባት አስመልክቶ ለባለድርሻ አካላት ስልጠና ሰጥቷል።
የወረዳው ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኢብራሂም አብራር በመድረኩ ተገኝተው እንዳሉት ሴቶችን ከማህጸን በር ጫፍ ካንሰር በሽታ ተጋለጭነት ለመታደግ በሚደረገው ጥረት ሁሉም ባለድርሻ አካላት ሚናቸውን በአግባቡ መወጣት እንዳለባቸው ጠቅሰው ዕድሜያቸው ከ9 እስከ 14 ዓመት ለሆናቸው ሴቶች የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር መከላከያ ክትባት በጤና ተቋማት፣በትምህርት ቤት አና በክትባት መስጫ ቦታዎች ለመስጠት አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት መደረጉን አስታውቀዋል።
የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር በስፋት በወሊድ እድሜ ክልል የሚገኙ ሴቶችን የሚያጠቃና ለሞት የሚዳርግ በሽታ እንደሆነ የገለጹት አቶ ኢብራሂም ክትባቱ ምንም አይነት የጎንዮሽ ጉዳት የሌለው በመሆኑ ሁሉም ልጃገረዶች ያለምንም ፍራቻ በጤና ባለሙያ የሚሰጣቸውን ክትባት መውሰድ እንዳለባቸው ገልጸዋል።
በማህጸን በር ጫፍ ካንሰር መከላከያ ክትባቶች አጠቃቀም ላይ የግንዛቤ ስልጠና የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት የእናቶችና ህጻናት ስራ ሂደት አስተባባሪ አቶ ሚፍታ መቻል ቀርቦ ውይይት የተደረገበት ሲሆን የመድረኩ ተሳታፊዎችም ዘመቻውን ስኬታማ ለማድረግ አስፈላጊው ርብርበብ እንደሚያደርጉ ተናግረዋል።
በመድረኩም የወረዳው የወረዳው ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኢብራሂም አብራር ፣ የጤና ጣብያ ኃላፊዎች፣ የቀበሌ ጤና ኤክስቴንሽን፣ የጽ/ቤቱ ባለሙያዎችና ባለድርሸሰ አካላት ተገኝተዋል።
