ru
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Открыть в Telegram
1 076
Подписчики
+224 часа
+37 дней
+230 день
Архив постов
በድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ም/ኮምሽነር ማኦ ተሾመ የተመራ ልኡክ ቡድን በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የመስክ የስራ ጉብኝት አደረገ፡፡ ኮሌጁ ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ በመደበኛና በአጫጭር ስልጠናዎ
+4
በድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ም/ኮምሽነር ማኦ ተሾመ የተመራ ልኡክ ቡድን በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የመስክ የስራ ጉብኝት አደረገ፡፡ ኮሌጁ ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ በመደበኛና በአጫጭር ስልጠናዎች በርካታ ወጣቶችን የስራ ባለቤት ማድረግ የቻለ ተቋም ነው፡፡ኮሌጁ የህዝብ ሃብት እንደመሆኑ መጠን ሁሉም የአካባቢው ማህበረሰብ ይህን እምቅ ሃብት ሊጠቀሙበት ይገባል ያሉት የኮሌጁ ዲን አቶ ሰለሃዲን አብዱላሚድ ሲሆን ዲኑ ያይዘውም ኮሌጁ በቀጣይ የባቡር ምህንድስና እና የICT የልህቀት ማእከል እንደመሆኑ መጠን ከድሬዳዋ አስተዳደር እንዲሁም ከፖሊስ ጠቅላይ መምሪያው ጋር በርከት ያሉ ስራዎችን በጋራ የምንሰራ ይሆናል ብለዋል፡፡ በመስክ ምልከታው ወቅት ልኡክ ቡድኑን የመሩት ም/ኮምሽነር ማኦ ተሾመ እንዳሉት አጠቃላይ የኮሌጁ እንቅስቃሴ እጅግ በጣም ጥሩ የሚባልና በኮሌጁ ውስጥ እየተገነባ የሚገኘውም የምስራቅ አፍሪካ የልህቀት መአከል ግንባታ በከፍተኛ ፍጥነት ተከናውኖ ለሚፈለገው አላማ መዋል እንዲችል እየታየ ያለው ርብርብ በጣም አስደማሚ ነው በኮሌጁ የሚገኙ የተለያዩ ትምህርት ክፍሎች ያላቸው አቅም ከሌሎች ኮሌጆች አንጻር ከድሬዳዋ አልፎ ለምስራቁ የሀገራችን ክፍሎች የሚበቃ ነው ያሉ ሲሆን ይህንን አቅም በተገቢው መንገድ በጋራ እየተጠቀምን ከተማችንን በጋራ የምናለማ ይሆናል ብለዋል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ታህሳስ 23/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

በአስተደዳደሩ ኢንዱስትሪዎች ውስጥ ለሚሰሩ ሰራተኞች በስራ ቦታ ኤች አይ ቪ ኤድስት መከላከል ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተዘጋጀ። በመድረኩ በመልዕክት ያስጀመሩት የቢሮው ሴቶች ወጣቶችና ኤች አይ ቪ ኤድስ  ፎካል ፐርሰን (ተጠሪ) ወ/ሮ ማርታ በዛብህ ቢሮዉ ሰዉ ተኮር ስራዎችን በተለያየ ዘርፍ  የሚሰራ በመሆኑ የኤች አይ ቪ ተጋላጭነት እና ስርጭት ተገቢዉን ትኩረት እንዲያገኝ በተለይም የዛሬው መድረክ በአሰሪና ሰራተኛ ዘርፉ በኢንዱስትሪዎች ላይ የሚሰሩ ሰራተኞችን ግንዛቤ ያማስጨበጥ ስራው ማሳያ ነው ብለዋል። ከቢሮው በወረደዉ አቅጣጫ መሰረት ስልጠናዉ በአስተዳደሩ የተለያዩ ኢንዱስትሪዎች የሚሰሩ ሰራተኞች ኤች አይ ቪ ኤድስ አሁንም ድረስ ማህበራዊ ቀዉሱ ከፍተኛ  መሆኑን ተረድተው ትኩረት ሊሰጡት እንደሚገባና ጥንቃቄ እንዲያደርጉ በአፅዕኖት ተገልጿል:: በዕለቱ የቀረበዉን ሰነድ እና ተያያዥ ጉዳዮች በተመለከተ ከታሳታፊዎች ጋር ዉይይት የተካሄደ ሲሆን በዉይይቱ ለተነሱ ጥያቄዎች  የቢሮው የሴቶች ወጣቶችና ኤች አይ ቪ  ፎካል ፐርሰን (ተጠሪ) ወ/ሮ ማርታ በዛብህ  እና ስልጠናዉን የሰጡት አቶ ፈቲህ መሀመድ ምላሽ ሰጥተዉበታል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ታህሳስ 23/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+4

photo content
+9

የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የኢንተርፕራይዞች ልማት ዳይሬክቶሬት የብድርና ዋስትና ፈንድ አሰጣጥና አመላለስ ዙሪያ ለድሬ ማይክሮ ፋይናንስ እና ለቀበሌ አመራሮችና ባለሙያዎች የግንዛቤ ማስጨበጫና የውይይት መድረክ አዘጋጀ፡፡ በመድረኩም በድሬዳዋ አስተዳደር ከብድርና ዋስትና ፈንድ አሰጣጥና አመላለስ ጋር በተያያዘ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን መድፈን እንዲያስችል ከድሬዳዋ ማይክሮ ፋይናንስ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል፡፡ ከተሳታፊዎችም ከብድር ተጠቃሚዎች ምልመላ አንስቶ እስከ አመላለስ ድረስ የታዩ እና እየታዩ ያሉ ችግሮችና ተግዳሮቶችን በተለይም በብድር ተጠቃሚዎች ዘንድ ያለው ለሚያገኙት ብድር ያላቸው አመለካከት እና ተከታትሎ እንዲመለስ በማድረጉ ረገድ የሚመለከታቸው አካላት ቁርጠኝነት ላይ የሚታየው ከፍተት በሰፊው ተነስቷል፡፡ የቢሮው ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው በበኩላቸው የሚመለከታቸው አካላት በሚመለከታቸው ልክ ትኩረት በመስጠት ክፍተቶችን በመሙላትና እርምት በመውሰድ በቅንጅት የማስተካከሉን ስራ ቅድሚያ እንዲሰጡ በማሳሰብ የተጀመረውን ውጤታማ የማስመለስ ሂደት ማስቀጠል እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ታህሳስ 23/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+9

በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የተዘጋጀ የሞዴል ኢንተርፕራይዞች ኤግዚቢሽንና ባዛር ተጀመረ። ከታህሳስ 22/2017 ዓ.ም እስከ 27/2017 ዓ.ም ድረስ በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ድሬዳዋ ቅርንጫፍ ፊት ለፊት የሚገኘው ቦታ ላይ የሚካሄደውን ይህን ኤግዚቢሽን እና ባዛር የቢሮው ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በይፋ ተከፍቷል። በመክፈቻ ስነሥርዓቱ ላይ የአስተዳደሩ ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው እንደተናገሩት ቢሮው ለኢንተርፕራይዞች ከሚያመቻቻቸው የድጋፍ ማዕቀፎች ውስጥ የገበያ ትስስር አንዱ ሲሆን ኤግዚቢሽንና ባዛር ደግሞ በዚህ ረገድ ወሳኝ ሚና አለው በመሆኑም ኢንተርፕራይዞች ያመረቱትን ምርት ይዘው የሚቀርቡበት ገበያተኛውም በሚፈልገው ልክ ተገበያይቶ የሚወጣበት መድረክ መፍጠሪያ ዘዴ አንዱ ይህ በመሆኑ እንዲሁም  ያለውን የኑሮ ውድነት ለማረጋጋትም ከፍተኛ ሚና ይኖረዋል ብለዋል። በዚህም ኤግዚቢሽንና ባዛር ላይ ሞዴል ኢንተርፕራይዞች ምርትና አገልግሎቶቻቸውን ይዘው የሚቀርቡ ሲሆን ወቅቱም የበዓል ሰሞን እንደመሆኑ የአስተዳደሩ ነዋሪ በቦታው በመገኘት ሞዴል ኢንተርፕራይዞችን በማበረታታት ተጠቃሚ እንዲሆን በቢሮው የሥራ ዕድል ፈጠራና አንድ ማዕከል ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰኢድ አሊ መልዕክት አስተላልፈዋል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ታህሳስ 23/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+9

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በበጀት አመቱ የሩብ አመት የድጋፍ፣ክትትልና ግምገማ ተካሄደ:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በተቋሙ በሚገኙ ዋና ስራ ሂደቶችና ስራ ክፍሎች ላይ በበጀት አመቱት የሩብ አመት የድጋፍ፣ክትትልና ግምገማ መርሃ-ግብር አካሂዷል:: የድጋፍ፣ክትትልና ግምገማ መመሪያው በቼክሊስት መልክ የተዘጋጀ ሲሆን ይህን መነሻ በማድረግም በበጀት አመቱ ለዋና ስራ ሂደቶችና ስራ ክፍሎች በተሰጡ የቁልፍ ውጤት አመላካች እስትራቴጂክ ተግባራት አንፃር የተገኘውን አፈፃፀም ለመገምገም እንዲሁም በአተገባር ወቅት የተገኙ ምርጥ ተሞክሮዎችን በመቀመር ወደሌሎች ክፍሎች ለማስፋት የታለመ መሆኑ ተግልፇል:: የድጋፍ፣ክትትልና ግምገማውን የኮሌጁ ማኔጅመንትና የISO Task force በጋራ በመሆን እንዲሁም ቼክሊስቶችን በማዘጋጀት በስራ ሂደቶችና ክፍሎች በመገኘት የበጀት አመቱ የሩብ አመቱን ግምገማ ያካሄዱ ሲሆን በዚህም ከተሰጡ ዋና ቁልፍ እስትራቴጂክ ተግባራት በተጨማሪ የISO ትግበራን ከማስቀጠል አኳያ ስራ ሂደቶችና ክፍሎች ያሉበትን ነባራዊ ሁኔታ መመልከት ተችሏል:: በተካሄደው የድጋፍ፣ክትትልና ግምገማው መሰረት በስራ ሂደቶችና ክፍሎቹ የታዩ የአፈፃፀም ውስንነቶችን እንዲሁም የተለዩ ምርጥ ተሞክሮችን በመሰብሰብ ግብረ-መልስ የተሰጠ ሲሆን በቀጣይ የድጋፍ ክትትልና ግምግማውን መነሻ በማድረግ እንደ ተቋም የተመዘገበው የአፈፃፀም ሪፖርት የሚቀርብም ይሆናል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን ታህሳስ 22/2017 ዓ.ም

የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለከተማ ግብርና የሚያገለግል በዘመናዊ መልኩ ያመረተውን የንብ ቀፎ በከተማ ግብርና ላይ ለተሰማራ ማህበር በዛሬው እለት አስረከበ፡፡ ኮሌጁ በተሸሻለ እና የማር ምርትን በሚ
+1
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለከተማ ግብርና የሚያገለግል በዘመናዊ መልኩ ያመረተውን የንብ ቀፎ በከተማ ግብርና ላይ ለተሰማራ ማህበር በዛሬው እለት አስረከበ፡፡ ኮሌጁ በተሸሻለ እና የማር ምርትን በሚያሳድግ መልኩ ያመረተውን ዘመናዊ የንብ ቀፎ በከተማ ግብርና ላይ ለተሰማራ ማህበር 25 የንብ ቀፎዎችን ያስረከበ ሲሆን ይህም ወጣቶችን በዘመናዊ የከተማ የንብ እርባታ ላይ እንዲሰማሩና እራሳቸውን ብሎ ማህበረሰቡን መጥቀም እንዲችሉ ታስቦ የተደረገ ድጋፍ ነው ብለዋል የኮሌጁ ዲን አቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ፡፡አያይዘውም በቀጣይ በኮሌጁና በስራና ክህሎት ቢሮ በኩል ከ500 በላይ ዘመናዊ የንብ ቀፎዎችን በማምረት ለገጠሩ ማህበረሰብ ክፍል በዘመናዊ የማር ምርት ላይ እንዲሰማሩ ለማድረግ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ታህሳስ 22/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ  ስልጠና ኤጀንሲ በቴክኖሎጂ ሽግግርና በኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ዳይሬክቶሬት አዘጋጅነት  በዚህ አመት በሁለቱ የመንግስት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅና በግል ተቋማት ስልጠናቸውን ለሚያጠናቅቁ ሰልጣኝ ተማሪዎች የስራ ፈጠራ ባህል ግንባታ ስልጠና ተሰጠ። በዚህም ስልጠና ላይ በድሬዳዋ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ውስጥ ስልጠናቸውን አጠናቀው ስኬታማ የሆኑትን  የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ  በረጅም አመት የኮሌጅ አሰልጣኝ መምህርነትና አመራርነት  ያላቸውን ልምድና ተሞክሮአቸውን አነቃቂ በሆነ ንግግር  ለስልጠና አጠናቃቂዎች  አካፍለዋል ። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ታህሳስ 22/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+9

የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የአሰልጣኝ ልማትና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ለኢንደስትሪ ውስጥ ባለሙያዎች የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠን ስነ ዘዴ/ Industry Trainers Methodology / ስልጠና እየሰጠ ይገኛል፤ በዚህም ስልጠና ውጤትን መሰረት ያደረገ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና በንድፈ ሃሳብ እና በተግባር የተደገፈ እንደመሆኑ ስልጠናው በቴ/ሙ/ት/ስ ተቋማት ውስጥ እና  በኢንደስትሪው ውስጥ በሁለትዮሽ/ በትብብር ይሰጣል፤ ለዚህም በኢንደስትሪው ውስጥ ይህንን ስልጠና የሚሰጥ የኢንደስትሪ ባለሙያ ለማፍራት ታሳቢ ያደረገ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ስትራቴጂ ላይ ግንዛቤ በመስጠት፣ በ OBT Delivery System፣ Occupational Standard፣ Session Plan፣ Delivery Methods፣ TTLM፤ Plan and Conduct Assessment ሞጁልን በመሰልጠን ላይ ይገኛሉ፤ በመሆኑም ቢሮው ከዘርፍ መስሪያ ቤቶች ጋር ባደረገው የጋራ ዕቅድ/MoU/ ስምምነት መሰረት ኮሌጆች ለትብብር ስልጠና መስጫነት የመረጡአቸው ዘርፍ መስሪያ ቤት እና ኢንደስትሪዎች ውስጥ የሚሰሩ ቴክኒካል ባለሙያዎችን በማካተት ስልጠናው ለ5 ተከታታይ ቀናት የሚቆይ ሲሆን በስልጠናው ማጠናቀቂያ በሚኖራቸው ምዘና መሰረት ብቁ የሆኑትን ሰርቲፋይ በማድረግ በኢንደስትሪ ውስጥ የትብብር ስልጠናን የሚሰጡ የኢንደስትሪ ውስጥ አሰልጣኞች እንደሚሆኑ የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ ለገሰ ተናግረዋል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ታህሳስ 21/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+9

photo content

የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የአሰልጣኝ ልማት እና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት የአሰልጣኝ መምህራን የሙያ ብቃት ምዘና ለማስጀመር ከኮሌጆች ጋር የጋራ መድረክ አዘጋጀ፤ መድረኩ በአዲሱ የትምህርትና ስልጠና ፖሊሲ ከተሻሻሉ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና አሰራር ስርአቶች መካከል የሙያ ደረጃ እና የሙያ ብቃት ምዘና አተገባበር ስርአት መነሻ በማድረግ በአስተዳደሩ በግልና በመንግስት ኮሌጆች የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ዘርፍ የሚያሰለጥኑ አሰልጣኞችን በተያዘው የ2017 በጀት አመት ወደምዘና ለማስገባት የሚያስችል መግባባት ለመፍጠር ያለመ ሆኗል፡፡ በዚህም ከቢሮው የቴክኒክና ሙያ ትምህሮትና ስልጠና ኤጀንሲ እና የሙያ ብቃት ምዘናና ማረጋገጫ ማዕከል ባለሙያዎች እንዲሁም ከኮሌጆቹ አባል የሆኑበት የስትሪንግ ኮሚቴ ጋር የአሰልጣኝ መምህራን የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ምዘና ወጥነት ባለው፣ በተቀናጀ እና የስልጠና ስራውን በማይጎዳ አግባብ ለመፈጸም ውይይት የተደረገ ሲሆን በአስተዳደሩ ከሚገኙ ሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች እና የ5ቱ የግል ኮሌጆች ለምዘና የተለዩ አሰልጣኞች ምዘና ለማከናወን ለውሳኔ የሚረዱ ሃሳቦች መለየታቸውን የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ ለገሰ ገልጸዋል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ታህሳስ 18/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ኤጀንሲ የአሰልጣኝ ልማት እና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት የአሰልጣኝ መምህራን የሙያ ብቃት ምዘና ለማስጀመር ከኮሌጆች ጋር የጋራ መድረክ አዘጋጀ፤ መድረኩ በአዲሱ የትምህርትና ስልጠና ፖሊሲ ከተሻሻሉ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና አሰራር ስርአቶች መካከል የሙያ ደረጃ እና የሙያ ብቃት ምዘና አተገባበር ስርአት መነሻ በማድረግ በአስተዳደሩ በግልና በመንግስት ኮሌጆች የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ዘርፍ የሚያሰለጥኑ አሰልጣኞችን በተያዘው የ2017 በጀት አመት ወደምዘና ለማስገባት የሚያስችል መግባባት ለመፍጠር ያለመ ሆኗል፡፡ በዚህም ከቢሮው የቴክኒክና ሙያ ትምህሮትና ስልጠና ኤጀንሲ እና  የሙያ ብቃት ምዘናና ማረጋገጫ ማዕከል ባለሙያዎች እንዲሁም ከኮሌጆቹ አባል የሆኑበት የስትሪንግ ኮሚቴ ጋር የአሰልጣኝ መምህራን የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ምዘና ወጥነት ባለው፣ በተቀናጀ  እና የስልጠና ስራውን በማይጎዳ አግባብ ለመፈጸም ውይይት የተደረገ ሲሆን በአስተዳደሩ ከሚገኙ ሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች እና የ5ቱ የግል ኮሌጆች ለምዘና የተለዩ አሰልጣኞች ምዘና ለማከናወን ለውሳኔ የሚረዱ ሃሳቦች መለየታቸውን የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ ለገሰ ገልጸዋል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ታህሳስ 18/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+7