ru
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Открыть в Telegram
1 084
Подписчики
+524 часа
+107 дней
+530 день
Архив постов
photo content
+7

ኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የ2017 በጀት አመት እቅድ እና የዝግጁነት ምዕራፍ አፈፃፀም ሪፖርት በተመለከተ ኮሌጁ ማህበረሰብ በተገበት የውይይት መድረክ አካሂዷል። በመድረኩ በቅድሚያ በኮሌጁ የዝግጁነት ምዕራፍ ወቅት የተሰሩ ስራዎች አፈፃፀም የቀረበ ሲሆን በዋነኛነትም የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የአለም አቀፍ የጥራት ደረጃ የሆነውን የISO 9001:2015 የጥራት አስተዳደር ስርዓት እውቅና ያገኘበትን የላቀ ትግበራ ያከናወነበት ምዕራፍም ነበር:: በተጨማሪም በዝግጁነት ምዕራፍ ወቅት እንደ ተቋም የ2017 በጀት ዓመት እቅድ ከዋና ስራ ሂደቶች ጀምሮ እስከ ፈፃሚው ድረስ የጠራ እቅድ ዝግጅት የተከናወነበት ወቅት ሲሆን እንዲሁም የአረንጏዴ አሻራ፣የደም ልገሳን ጨምሮ የአቅመ ደካሞችን ቤት የማደስና መሰል ትግበራዎችም በዝግጁነት ምዕራፍ ወቅት እንደተከናወኑ ለኮሌጁ ማህበረሰብ ሪፖርት ቀርቧል:: በመጨረሻም የ2017 በጀት ዓመት መሪ እቅድ ለኮሌጁ ማህበረሰብ የቀረበ ሲሆን የቀረበውን እቅድ መነሻ በማድረግም ከመድረኩ ተሳታፊዎች ሀሳብ ተሰቶበት ሰፋ ያለ ውይይትም ተደርጎበታል:: በማጠቃለያውም በተጠናቀቀው በጀት አመት የታዩ ጠንካራ አፈፃፀሞችን በማስቀጠል እንዲሁም በ2017 በጀት አመት የተሻለ አፈፃፀም ለማስመዝገብ በጋራ መረባረብ እንደሚገባ ተገልፆ መድረኩ ፍፃሜውን አጊኝቷል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን ጥቅምት 21/2017 ዓ.ም

#ዜና በ2017 ዓ/ም ወደ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች የሚገቡ ሰልጣኝ ተማሪዎችን ለመቀበል ዝግጅት መጠናቀቁንና ኮሌጆች መቀበል መጀመራቸውን የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ አስታወቀ፤ በሀገር አቀፍ ደረጃ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት መለቀቅን ተከትሎ በ2017 ዓ/ም ወደ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች የሚገቡ ሰልጣኝ ተማሪዎችን ለመቀበል ዝግጅት መጠናቀቁንና ኮሌጆች ምዝገባ መጀመራቸውን የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ ምክትል ኃላፊና የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ በዛሬው ዕለት ለሚዲያ አካላት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቀዋል፡፡ የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮው አዳዲስ ሰልጣኝ ተማሪዎች ወደ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች እንዲገቡ በማድረግ ረገድ ሰፊ ስራ መሰራቱን ገልጸዋል፡፡ በዚህም በአስተዳደሩ 6 የግል እና 2 የመንግስት ኮሌጆች ሰልጣኝ ተማሪዎችን ለመቀበል ሙሉ ዝግጅቶች የተጠናቀቁ ሲሆን ሰልጣኝ ተማሪዎች ከምዝገባ በፊት አዋጭ የትምህርት ዘርፎችን የመለየት በተለይም አስተዳደሩ የኢንዱስትሪ ማዕከል እንደመሆኑ መጠን ሀገር አቀፍ እና አለምቀፍን የሚያስተሳስሩ  የዲጂታላይዜሽን ስልጠናዎችን ጨምሮ ስለሚሰጥ ሰልጣኞች አውቅና እና ብቃት ካላው ኮሌጆች ጋር ተገናገኝተው ዘርፉን መምረጥ እንደሚገባም ነው ኃላፊዋ ያብራሩት፡፡   በተጨማሪም ከዚህ ቀደም በደረጃ 3 እና 4 ላይ ብቻ ትኩረት አድርጎ የመቀበል አዝማሚያዎች እንዳሉ አንስተው በተያዘው በጀት አመት ሁሉም የግል እና የመንግስት ኮሌጆች ደረጃ 1 እና 2 ተቀብለው ምዝገባ እንዲያካሂዱም ነው ያሳሰቡት፡፡ ኃላፊዋ አያይዘውም ቢሮው እንደ ከዚህ ቀደሙ በአስተዳደር ደረጃ በደማቁ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ሳምንት(TVT Week) ለማክበር በዝግጅት ላይ መሆናቸውንና የዘርፉን ገጽታ ለመገንባት የሚያስችሉ በተጨባጭ የተሰሩ ስራዎችን ህብረተሰቡ እንዲመለከታቸው የማስተዋወቅ እና ከሚመለከታቸው የባለድርሻ አካላት ጋር ያለውን ግንኙነት እንደሚያጠናክረው ጨምረው ገልጸዋል፡፡  በመጨረሻም በቢሮው የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የሰልጣኝ ልማትና የተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶጨ ጀማል አደም ሰልጣኝ ተማሪዎች የሥራ ዕድል ፈጠራን  በክህሎት በመታጀብ የተመቻቸውን ዕድል ወደ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች በመምጣት እንዲጠቀሙ ጥሪ አቅርበዋል፡፡  ©️ DGC  ጥቅምት 20/2017

#ዜና በ2017 ዓ/ም ወደ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች የሚገቡ ሰልጣኝ ተማሪዎችን ለመቀበል ዝግጅት መጠናቀቁንና ኮሌጆች መቀበል መጀመራቸውን የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ አስታወቀ፤ በሀገር አቀፍ ደረጃ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት መለቀቅን ተከትሎ በ2017 ዓ/ም ወደ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች የሚገቡ ሰልጣኝ ተማሪዎችን ለመቀበል ዝግጅት መጠናቀቁንና ኮሌጆች ምዝገባ መጀመራቸውን የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ ምክትል ኃላፊና የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ በዛሬው ዕለት ለሚዲያ አካላት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቀዋል፡፡ የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮው አዳዲስ ሰልጣኝ ተማሪዎች ወደ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች እንዲገቡ በማድረግ ረገድ ሰፊ ስራ መሰራቱን ገልጸዋል፡፡ በዚህም በአስተዳደሩ 6 የግል እና 2 የመንግስት ኮሌጆች ሰልጣኝ ተማሪዎችን ለመቀበል ሙሉ ዝግጅቶች የተጠናቀቁ ሲሆን ሰልጣኝ ተማሪዎች ከምዝገባ በፊት አዋጭ የትምህርት ዘርፎችን የመለየት በተለይም አስተዳደሩ የኢንዱስትሪ ማዕከል እንደመሆኑ መጠን ሀገር አቀፍ እና አለምቀፍን የሚያስተሳስሩ  የዲጂታላይዜሽን ስልጠናዎችን ጨምሮ ስለሚሰጥ ሰልጣኞች አውቅና እና ብቃት ካላው ኮሌጆች ጋር ተገናገኝተው ዘርፉን መምረጥ እንደሚገባም ነው ኃላፊዋ ያብራሩት፡፡   በተጨማሪም ከዚህ ቀደም በደረጃ 3 እና 4 ላይ ብቻ ትኩረት አድርጎ የመቀበል አዝማሚያዎች እንዳሉ አንስተው በተያዘው በጀት አመት ሁሉም የግል እና የመንግስት ኮሌጆች ደረጃ 1 እና 2 ተቀብለው ምዝገባ እንዲያካሂዱም ነው ያሳሰቡት፡፡ ኃላፊዋ አያይዘውም ቢሮው እንደ ከዚህ ቀደሙ በአስተዳደር ደረጃ በደማቁ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ሳምንት(TVT Week) ለማክበር በዝግጅት ላይ መሆናቸውንና የዘርፉን ገጽታ ለመገንባት የሚያስችሉ በተጨባጭ የተሰሩ ስራዎችን ህብረተሰቡ እንዲመለከታቸው የማስተዋወቅ እና ከሚመለከታቸው የባለድርሻ አካላት ጋር ያለውን ግንኙነት እንደሚያጠናክረው ኃላፊዋ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ጨምረው ገልጸዋል፡፡  በመጨረሻም በቢሮው የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የሰልጣኝ ልማትና የተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶጨ ጀማል አደም ሰልጣኝ ተማሪዎች የሥራ ዕድል ፈጠራን  በክህሎት በመታጀብ የተመቻቸውን ዕድል ወደ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች በመምጣት እንዲጠቀሙ ጥሪ አቅርበዋል፡፡  ©️ DGC  ጥቅምት 20/2017

photo content
+3

#ዜና በ2017 ዓ/ም ወደ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች የሚገቡ ሰልጣኝ ተማሪዎችን ለመቀበል ዝግጅት መጠናቀቁንና ኮሌጆች መቀበል መጀመራቸውን የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ አስታወቀ፤ በሀገር አቀፍ ደረጃ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት መለቀቅን ተከትሎ በ2017 ዓ/ም ወደ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች የሚገቡ ሰልጣኝ ተማሪዎችን ለመቀበል ዝግጅት መጠናቀቁንና ኮሌጆች ምዝገባ መጀመራቸውን የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ ምክትል ኃላፊና የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ በዛሬው ዕለት ለሚዲያ አካላት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቀዋል፡፡ የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮው አዳዲስ ሰልጣኝ ተማሪዎች ወደ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች እንዲገቡ በማድረግ ረገድ ሰፊ ስራ መሰራቱን ገልጸዋል፡፡ በዚህም በአስተዳደሩ 6 የግል እና 2 የመንግስት ኮሌጆች ሰልጣኝ ተማሪዎችን ለመቀበል ሙሉ ዝግጅቶች የተጠናቀቁ ሲሆን ሰልጣኝ ተማሪዎች ከምዝገባ በፊት አዋጭ የትምህርት ዘርፎችን የመለየት በተለይም አስተዳደሩ የኢንዱስትሪ ማዕከል እንደመሆኑ መጠን ሀገር አቀፍ እና አለምቀፍን የሚያስተሳስሩ  የዲጂታላይዜሽን ስልጠናዎችን ጨምሮ ስለሚሰጥ ሰልጣኞች አውቅና እና ብቃት ካላው ኮሌጆች ጋር ተገናገኝተው ዘርፉን መምረጥ እንደሚገባም ነው ኃላፊዋ ያብራሩት፡፡   በተጨማሪም ከዚህ ቀደም በደረጃ 3 እና 4 ላይ ብቻ ትኩረት አድርጎ የመቀበል አዝማሚያዎች እንዳሉ አንስተው በተያዘው በጀት አመት ሁሉም የግል እና የመንግስት ኮሌጆች ደረጃ 1 እና 2 ተቀብለው ምዝገባ እንዲያካሂዱም ነው ያሳሰቡት፡፡ ኃላፊዋ አያይዘውም ቢሮው እንደ ከዚህ ቀደሙ በአስተዳደር ደረጃ በደማቁ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ሳምንት(TVT Week) ለማክበር በዝግጅት ላይ መሆናቸውንና የዘርፉን ገጽታ ለመገንባት የሚያስችሉ በተጨባጭ የተሰሩ ስራዎችን ህብረተሰቡ እንዲመለከታቸው የማስተዋወቅ እና ከሚመለከታቸው የባለድርሻ አካላት ጋር ያለውን ግንኙነት እንደሚያጠናክረው ኃላፊዋ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ጨምረው ገልጸዋል፡፡  በመሆኑም ሰልጣኝ ተማሪዎች የሥራ ዕድል ፈጠራን  በክህሎት በመታጀብ የተመቻቸውን ዕድል ወደ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች በመምጣት እንዲጠቀሙ ጥሪ አቅርበዋል፡፡  ©️ DGC  ጥቅምት 20/2017

#ዜና በ2017 ዓ/ም ወደ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች የሚገቡ ሰልጣኝ ተማሪዎችን ለመቀበል ዝግጅት መጠናቀቁንና ኮሌጆች መቀበል መጀመራቸውን የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ አስታወቀ፤ በሀገር አቀፍ ደረጃ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት መለቀቅን ተከትሎ በ2017 ዓ/ም ወደ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች የሚገቡ ሰልጣኝ ተማሪዎችን ለመቀበል ዝግጅት መጠናቀቁንና ኮሌጆች ምዝገባ መጀመራቸውን የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ ምክትል ሀላፊና የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ በዛሬው ዕለት ለሚዲያ አካላት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቀዋል፡፡ የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮው አዳዲስ ሰልጣኝ ተማሪዎች ወደ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች እንዲገቡ በማድረግ ረገድ ሰፊ ስራ መሰራቱን ገልጸዋል፡፡ በዚህም በአስተዳደሩ 6 የግል እና 2 የመንግስት ኮሌጆች ሰልጣኝ ተማሪዎችን ለመቀበል ሙሉ ዝግጅቶች የተጠናቀቁ ሲሆን ሰልጣኝ ተማሪዎች ከምዝገባ በፊት አዋጭ የትምህርት ዘርፎችን የመለየት በተለይም አስተዳደሩ የኢንዱስትሪ ማዕከል እንደመሆኑ መጠን ሀገር አቀፍ እና አለምቀፍን የሚያስተሳስሩ  የዲጂታላይዜሽን ስልጠናዎችን ጨምሮ ስለሚሰጥ ሰልጣኞች አውቅና እና ብቃት ካላው ኮሌጆች ጋር ተገናገኝተው ዘርፉን መምረጥ እንደሚገባም ነው ኃላፊዋ ያብራሩት፡፡   በተጨማሪም ከዚህ ቀደም በደረጃ 3 እና 4 ላይ ብቻ ትኩረት አድርጎ የመቀበል አዝማሚያዎች እንዳሉ አንስተው በተያዘው በጀት አመት ሁሉም የግል እና የመንግስት ኮሌጆች ደረጃ 1 እና 2 ተቀብለው ምዝገባ እንዲያካሂዱም ነው ያሳሰቡት፡፡ የቴ/ሙ/ት/ስ ሳምንት ሲከበርም በተለይም አጫጭር ስልጠናዎች ለስራ እድል ሰፊ እድሎችን ስለሚያመጣ ከነበረው ከአጫጭር ስልጠናዎች ውጪ በማኒፋክቸሪንግ ዘርፍ  ሌሎች ተጨማሪ ስልጠናዎችን ለመስጠት ሰፊ ስራ መሰራታቸውንም ኃላፊዋ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ጨምረው ገልጸዋል፡፡  በመሆኑም ሰልጣኝ ተማሪዎች የሥራ ዕድል ፈጠራን  በክህሎት በመታጀብ የተመቻቸውን ዕድል ወደ ተቋማቸው በመምጣት እንዲጠቀሙ ጥሪ አቅርበዋል፡፡  ©️ DGC  ጥቅምት 20/2017 ዓ.ም

photo content
+1

photo content
+2

photo content

photo content

የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ በማስተር ካርድ ፋውንዴሽን ስር የሚገኙ የተለያዩ ፕሮግራሞችን ከሚያስተባብሩ በአስተዳደሩ ከሚገኙ የፕሮግራም አስተባባሪዎች ጋር በሥራ ፈጠራና ክህሎት ልማት ላይ ያተኮረ ውይይት አካሂዷል፤ በመድረኩ የሥራና ክህሎት ቢሮ ም/ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ቢሮው ከተቋቋመ ጊዜ ጀምሮ ባለፉት ሦስት ዓመታት የተከናወኑ አበይት ተግባራትና የተገኙ ውጤቶች ላይ የአጋር አካላት ሚና ቀላል የማይባል መሆኑንና በቀጣይም ተቀራርቦ እና በየጊዜው ስራዎችን እየገመገሙ መሄድ አስፈላጊ በመሆኑ የዛሬው መድረክ መዘጋጀቱን ገልጸዋል፡፡ በአስተዳደሩ ከተማና ገጠር ፍትሃዊ ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የአጋር አካላት ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን የገለፁት የሥራ ዕድል ፈጠራ እና የአንድ ማዕከል ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት አቶ ሰኢድ አሊ በማስተር ካርድ ፋውንዴሽን እየተተገበሩ የሚገኙ ፕሮግራሞችን ከዘርፉ እሳቤ ጋር የተቀናጀ እንዲሆኑ ለማስቻል ብሎም ጠንካራ ትብብር ለመፍጠር በትኩረት ይሰራል ብለዋል፡፡ በማስተር ካርድ ፋውንዴሽን ስር የሚገኙ የተለያዩ ፕሮግራሞች ሲኖሩ በዛሬው ዕለት ስራዎቻቸውን ለቢሮው አቅርበው የተገመገሙት የመስራት ስራ ፈጣሪዎች ፕሮግራም፣ ሳፊ ፕሮግራም፣ መስመር ፕሮግራም እና ሲድ ፕሮግራም ናቸው፡፡ የመስራት ስራ ፈጣሪዎች ፕሮግራም : 5 ዓመት የሚቆይ ፕሮግራም ሲሆን፣ 100 ጊግ ሞዴል ያላቸውን ቢዝነሶችን መርጦ ሁለ ገብ ድጋፍ ይሰጣል፤ ሳፊ ፕሮግራም ፋይናንሻል ቴክኖሎጂ ላይ የሚሰራ ሲሆን መደበኛ እና ኢ-መደበኛ ብድሮችን ያቀርባሉ በተለይ ለኢ-መደበኛ ተበዳሪዎች በመታወቂያ ብቻ ብድሮችን ከእጅ ንክኪ ነጻ የሆነ በAI ታግዘው ብድሮችን ያመቻቻሉ፤በዚህም በዋናነት 80% ሴቶች፣ 10% ለአካል ጉዳተኞች እና 10% ለተፈናቃዮች ትኩረት አድርጎ ይሰራል፤ መስመር ፕሮግራም የብድር አገልገሎት ሴቶችና ወጣት ሥራ ፈጣሪዎችን ለማበረታታትና ሥራቸውን ለማስፋፋት የብድር አገልገሎት ይሰጣል አገልገሎቱ በአስተዳደራችን የሚገኙ በተለይም በወጣት ሴቶች የሚመሩ የጥቃቅን፣ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞችን በመጠነኛ ዋስትናና በአነስተኛ የወለድ መጠን እንዲሁም የሸሪአ መርህን የተከተለ ከወለድ ነጻ የብድር አገልገሎት ተጠቃሚ በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡ ሲድ ፕሮግራም እንደ ኢትዮጵያ ለአንድ ሚሊዮን ወጣቶች እና ሴቶች የሥራ ዕድል ለመፍጠር ይፈልጋል፡፡ አንድ መቶ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኮሌጆችን በማጎልበት ለውጥ አምጭ የንግድ ሞዴሎችን በማስተዋወቅ፣ የንግድ መፈልፈያ ማዕከላትን በማቋቋምና ወደ ስራ በማስገባት እንዲሁም ፍላጎትን መሰረት ያደረጉ ልማቶችን በማጎልበት የወጣቶች የስራ እድል ፈጠራን ለመደገፍ በማለም የሚተገበር ነው፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጥቅምት 18/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+6