ru
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Открыть в Telegram
1 064
Подписчики
-224 часа
-77 дней
+130 день
Архив постов
photo content
+9

የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ከግራንድ ግሩፕ እና ከሲድ ፕሮጀክት ጋር በመቀናጀት በE - Money ላይ የተደራጁ ስራ ፈላጊ ወጣቶችን ስራ ለማስጀመር የተዘጋጀ የስልጠና መድረክ ተካሄደ። ግራንድ ግሩፕ በድሬዳዋ የመጀመሪያው የሆነ በዲጂታል ማርኬቲንግ እና የበቃ የሰው ሀይል ለኢንዱስትሪዎች አቅራቢ ኢንተርፕራይዝ ሲሆን በለይም ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር በመተባበር ስራ ፈላጊ ወጣቶች በኢ መኒ ዘርፍ ተደራጅተው ወደ ስራ እንዲገቡ ማድረግ የቻለ ሲሆን ከሲድ ፕሮጀክት ጋር በመተባበርም የስልጠና እና የብድር ምችችት እንዲያገኙ መደረጉም ታውቋል። የቢሮው ም/ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም በስልጠና መድረኩ ላይ በመገኘት ባስተላለፉት መልዕክት ለዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር ማስቀጠር ላይ የሚቆም አለመሆኑና ዘላቂ የሆነ የሥራ ዕድል መፍጠር ላይ ቢሮው ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸው ለዚህም መሰል ኢንተርፕራይዞች በአስተዳደሩ መፈጠራቸውና ወደ ስራ መግባታቸው ትልቅ አቅም የፈጠረ ሆኗል ብለው ቢሮው ለተደራጁት ኢንተርፕራይዞች በE-LMIS እንዲመዘገቡ በማድረግ የእድገት ሽግግር ሰርተፍኬት እንዲያገኙ ማድረጉን ተናግረዋል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጥቅምት 27/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+9

በአስተዳደሩ የሚገኙ የግል ኮሌጆች የ2018 ዓ.ም የአዲስ ተማሪዎች ምዝገባ ሂደት አፈጻጸም ምልከታ ተደረገ። የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ  የሰልጣኝ ልማትና ተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ጀማል አደን የሚመራ የባለሙያዎች ቡድን በአስተዳደሩ የግል ኮሌጆች በመገኘት የአዲስ ሰልጣኝ ተማሪዎች የምዝገባ ሂደትን ጎብኝተዋል። አቶ ጀማል እንደተናገሩት ይህ የምዝገባ ሂደት ምልከታ ቀጣይነት ያለውና የእለት ተእለት መረጃ ልውውጥ የሚደረግበት መሆኑን ገልጸው ባሉት ጥቂት የምዝገባ ጊዜያት ዜጎች ወደ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች በመሄድ እንዲመዘገቡም ጥሪ አስተላልፈዋል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጥቅምት 27/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+7

የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የአሰልጣኝ ልማት እና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት የአሰልጣኝ ልማት እና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ለኮሌጆች የውስጥና የውጭ ጥራት ኦዲት ሰነድ ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አዘጋጀ፤ መድረኩ በአስተዳደሩ የሚገኙ የመንግስትና የግል ኮሌጆች ትምህርትና ስልጠናዉን በተቀመጠዉ የስልጠና ጥራት ስታንዳርድ መሰረት እንዲተገብሩ የውስጥ ጥራት ኦዲት ፎካል ፐርሰኖች በውስጥና በውጭ ጥራት ኦዲት ሰነዶች ላይ ግንዛቤ እንዲፈጠርላቸው ያለመ ሲሆን በዚህም አግባብነት ያለዉ ስልጠና ከቅበላ እስከ ምረቃ ለማካሄድ እንዲሁም ዜጎች ለትምህርትና ስልጠና የተሰጣቸዉን ፍትሃዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተቋማት የስልጠና ጥራትና አግባብነቱን ለመጠበቅ አቅም የሚፈጥር መሆኑን የቢሮው ም/ኃላፊ እና የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ተናግረዋል፡፡ በዚሁ መሰረት የሥራና ክህሎት ቢሮ በመንግስት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጆች እና በግል ኮሌጆች በተለይም በ2018 ዓ.ም የስልጠና ዘመን  የሚቀበሏቸዉን ሰልጣኞች በቅበላ መመርያ መሰረት ቅበላዉን ስለማከናወናቸው መመዝገብ በሚገባቸዉ የሙያ ደረጃ መመዝገብ ላይ ትኩረት ሰጥተው እንዲፈጽሙና ከዚሁ ጋር በተያያዘ በቀጣይ በቢሮው የተዋቀረ የባለሙያ ቡድን መረጃዎችን ከኮሌጆች በማሰባሰብ የሰልጣኝ ቅበላ የጥራት ኦዲት ሥራዉን የሚያከናወንና ለተቋማት ግብረ-መልስ የሚሰጥ መሆኑን የአሰልጣኝ ልማት እና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ ለገሰ ተናግረዋል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጥቅምት 26/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+9

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በ2018 ዓ.ም የስልጠና ዘመን አዲስ ለተቀበላቸው ሰልጣኞች የህይወት ክህሎት(Life Skill) ስልጠና እየሰጠ ይገኛል:: የህይወት ክህሎት(Life skill )ስልጠናው ብቁ በሆኑ የኮሌጁ አሰልጣኝ መምህራን አማካኝነት ለቀጣይ 3ቀናት ለአዲስ ሰልጣኞች እየተሰጠ እንደሚቆይ የተገለፀ ሲሆን ይህ ስልጠናም ሰልጣኞች የቀጣይ ህይወታቸውን በእቅድ እዲመሩ እንዲሁም ራሳቸውን ፈልገው እንዲያገኙና ስልጠናቸውን በዓላማ እንዲሰልጥኑ የሚያስችላቸውን ክህሎት የሚያገኙበት ስልጠና እንደሆነም ተገልፇል:: ሰልጣኞቹ የህይወት ክህሎት ስልጠናቸውን አጠናቀው ሲጨርሱ በቀጣይ የEntrepreneurship ስልጠና የሚወስዱ መሆኑም ተገልፇል:: ኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ጥቅምት 26/2018 ዓ.ም

የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከሀገር ውስጥ አልፎ በአለም ተወዳዳሪ መሆን የሚችሉ ስልጣኛችን እያፈራ እንዳለ ገለጸ፡፡ #ዜና| የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የአዲስ ገቢ ተማሪዎች ቅበላ መርሃ ግብር በዛሬው እለት አከናወነ፡፡ በመርሃ ግብሩ ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ም/ኃላፊና የቴክኒክና ሙያ ኤጀንሲ ዳይሬክተር የሆኑት ክብርት ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ሲሆኑ በንግግራቸውም ድሬዳዋ ከተማችን የኢንዱስትሪ ከተማ እንደመሆኗ መጠን በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ውስጥ ይህን ኢንዱስትሪ የሚያንቀሳቅስ ባለሙያ ማፍራት የሚጠበቅብን ዋና ስራ ነው ያሉ ሲሆን፤ ወ/ሮ ፈጡም አያይዘውም በዛሬው እለት በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ስልጠና ለመውሰድ የተመዘገባችሁ የከተማችን ወጣቶች ይህንን መልካም እድል በመጠቀም እራሳችሁን በእውቀትና በክህሎት ልታጎለብቱ ይገባል ብለዋል፡፡ የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከሀገር ውስጥ አልፎ በአለም ተወዳዳሪ መሆን የሚችሉ ስልጣኛችን እያፈራ ነው ያሉት ደግሞ የኮሌጁ ዲን አቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ ናቸው፡፡ አቶ ሰለሃዲን አያይዘውም ሙያ የማይነጥፍ ሀብት ነው፡፡ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ደግሞ ፍላጎትና ተሰጥዎን ወደ ወደማይነጥፍ ሀብትነት የሚቀይር ትልቅ መንገድ ነው ብለዋል፡፡በመጨረሻም ኮሌጁን በመምረጥ እውቀትና ክህሎትን ፍለጋ የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ስለተመዘገባችሁ እጅግ ደስተኛ ነኝ በእውቀትና ክህሎት ሰልጣኞችን እንዲዳብሩ ከማድረግ በዘለለ ኢኮኖሚው ላይ ትልቅ ተጠቃሚ እንድትሆኑ በርካታ ስራዎችን የምንሰራ ይሆናል ብለዋል፡፡ በዛሬው እለት በኮሌጁ ከተደረገው የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባበል በተጨማሪ በPsychometric Test ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራ የተከናወነ ሲሆን ከግንዛቤ ማስጨበጫ መርሃ ግብሩ በማስቀጠል በኮሌጁ ትምህርትና ስልጠና ለመውሰድ ለተመዘገቡ ሰልጣኞች የመጀመሪያ ዙር የPsychometric Test መስጠት ተችሏል፡፡በቀጣይ ቀናትም አዲስ የሚመዘገቡ እዲሁም በምዝገባ ሂደት ላይ ላሉም ሰልጣኞች ሁለተኛ ዙር ፈተና የሚሰጥ ይሆናል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ጥቅምት 26/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከ ከEntrepreneurship Development Inistitut(EDI) ጋር መተባበር በBusiness Incubation center ዙሪያ ለሚመለከታቸው ባለሙያዎችና አስተባባሪዎች ስልጠና ሰጠ:: ስልጠናውን በንግግር ያስጀመሩት የቴክኒክና ሙያ ኤጀንሲ ሀላፊና የስራና ክህሎት ቢሮ ም/ል ሀላፊና ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ሲሆኑ በንግግራቸውም የቴክኒክና ሙያ ዘርፋችን ክህሎት መር የስራ እድልን የሚመራ በመሆኑ ወጣቶች ቢዝነሳቸውን እዚሁ ኮሌጆቻችን ውስጥ እንዲያጎለብቱ ማድረግ ይጠበቅብናል ያሉ ሲሆን አክለውም ሰልጣኞች ተሰጥዕኦዋቸውን እያሳደጉ ከቢዝነሱም ተጠቃሚ የሚሆንበትን የኢንኩቤሽን ማዕከል እንዲፈጠር ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው ይህ ስልጠና የተዘጋጀበት አላማም ይህኑ ታሳቢ እድርጎ እንደሆነም ገልፀዋል:: EDI ወደ እኛ ዘርፍ ከተቀላቀለ ጊዜ ጀምሮ በርካታ ስራዎች በመስራት ዘርፉ ላይ መነቃቃት እየፈጠረ እንደሚገኝ የገለፁት ደግሞ የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ሲሆኑ በ2018 ከኢንስቲትዩቱ ጋር ዘርፈ ብዙ ስራዎችን በጋራ ለማከናወን ሰፊ እቅድ መያዙንም ገልፀዋል:: ስልጠናው ከሁለቱ ፖሊ ቴክኒኮች እና ከኤጀንሲ ለተወጣጡ ባለሙያዎች እንዲሁም አስተባባሪዎች የተሰጠ ሲሆን በዚህ ስልጠናም የBusiness Incubation center (BIC) ታሪካዊ አመጣጥ/አጀማመርና ፅንሰ-ኃሳብን ጨምሮ የቢዝነስ ኢንኩቤሽን ሴንተር ለማቋቋም እና ለማስተዳደር  መከተል የሚያስፈልገውን መሰረታዊ መርሆዎች ን ከEDI በመጡ አሰልጣኞች አማካኝነት በጥሩ አቀራረብ ለተሳታፊዎች ስልጠናውን መስጠት ተችሏል:: በዛሬው እለት ለባለሙያዎችና አስተባባሪዎች የተጀመረው ስልጠና ነገም ቀጥሎ የሚሰጥ ሲሆን በቀጣይ ለኮሌጁ ፑል አመራር አባላትና ለተመረጡ ሰልጣኝ ተማሪዎች የEntrepreneurship ስልጠና በመስጠት እንደሚቀጥልም ማወቅ ተችሏል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ጥቅምት 25/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

ዜጎችን በኢኮኖሚው እንቅስቃሴ የሚፈጠሩ በርካታ እድሎችን ተጠቃሚ ለማድረግ  በክህሎት ልማቱ አቅጣጫ በሚደረገው ርብርብ የወላጆች እና የአካባቢው ማህበረሰብ ሚና የላቀ መሆኑ ተገለፀ:: የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ስለ አጠቃላይ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ዘርፍ እንዲሁም የ2018 ዓ.ም የአዲስ ሰልጣኝ ተማሪዎችን ቅበላ አስመልክቶ ለአስተዳደሩ ወረዳዎች የብሎክ አደረጃጀት አባላት የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አዘጋጀ:: የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩን በንግግር የከፈቱት የሥራና ክህሎት ቢሮ ም/ኃላፊ እና የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ባስተላለፉት መልዕክት ያደጉ ሀገራት ዛሬ ለደረሱበት እድገት መነሻ የሆናቸው በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ላይ ያሳደሩት እምነትና ዘርፉ ላይ በሰሩት ጠንካራ ስራ መሆኑን ጠቅሰው የአስተዳደሩን ነዋሪ በዚህ ረገድ ግንዛቤ ተፈጥሮለት የክህሎት ስልጠናዎች ላይ እንዲሰማራ እንዲሁም እንዱስትሪውን እንዲያንቀሳቅስ የማድረጉ ተግባርና ኃላፊነት የሁላችንም ድርሻ ነውም ብለዋል:: በመድረኩ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ዘርፍ ገጽታ ግንባታ የአካባቢ ማህበረሰብ ውይይት በሚል ሃሳብ ሰነድ የቀረበ ሲሆን በማጠቃለያውም ከመድረኩ የተነሱ ጉዳዮችን መነሻ በማድረግ በተሳታፊዎች በርካታ ሀሳቦች ላይ ውይይት የተካሄደ ሲሆን በቀጣይ በቅንጅት በሚሰሩ ተግባራት ላይ ከመግባባት መድረስ መቻሉን በቢሮው የሰልጣኝ ልማትና ተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ጀማል አደን ገልጸዋል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጥቅምት 25/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+9

የኮሌጁን የግዢ ስርአት ለማዘመን ሁሉም ባለድርሻ አካላት በጋራ በመሆን ሊሰሩ ይገባል ተባለ፡፡ #ዜና|በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በአለም ባንክ የግዢና ውል አስተዳደር ላይ ትኩረቱን ያደረገ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በዛሬው እለት ተጀመረ፡፡ በስልጠናው ማጀመሪያ ላይ በመገኘት መድረኩን የከፈቱት የኮሌጁ EASTRIP ፕሮጀክት አስተባባሪ የሆኑት ወ/ሮ አሽረፊያ አብዲ እንዳሉት ይህ በዛሬው እለት ለሁሉም የኮሌጁ ባለድርሻ አካላት እየተሰጠ የሚገኘው ስልጠና በአለም ባንክ የግዢ ስርአት እና ውል አስተዳደር ላይ ትኩረቱን ያደረገ ግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ነው ያሉ ሲሆን የኮሌጁን የግዢ ስርአት ለማዘመን ሁሉም ባለድርሻ አካለት በጋራ ሊሰሩ ይገባል ብለዋል፡፡ወ/ሮ አሽረፊያ አያይዘውም ይህ ስልጠና ሲጠናቀቅ በኮሌጁ ውስጥ የሚደረጉ የግዢ አሰራራችን ላይ የተሸለ ለውጥ ማምጣት የሚያስችል ነው ብለዋል፡፡ በዛሬው እለት የተጀመረው ይህ ስልጠና በአለም ባንክ ከፍተኛ የግዢ ባለሙያ በመሆን እየሰሩ ባሉ ኢ/ር ቀጀላ ፉፋ አማካኝነት በ EASTRIP ፕሮጀክት አስተባባሪነት እየተሰጠ ሲሆን በስልጠናው ላይ ኮሌጁ ኃላፊዎች፣የትምህርት ክፍል ተጠሪዎች፣የግዢና ፋይናንስ ባለሙያዎች፣የጨረታ አጽዳቂ ባለሙያዎች እንዲሁም ሌሎች ተጋባዥ እንግዶች ተሳታፊ ሆነውበታል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ጥቅምት 25/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ ለወቅታዊ ትኩስ የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ መረጃ You tube: Dire Dawa Polytechnic College(DDPTC) Facebook: https://web.facebook.com/Dire Dawa Polytechnic College Regional Flagship TVET Institute Telegram: t.me/Dire Dawa Polytechnic College TikTok: tiktok.com/@diredawapolytechnicollege

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ለአዲስ ገቢ ሰልጣኞቹ የPsychometric Test እየሰጠ ይገኛል:: ይህ የPsychometric Test በሀገር አቀፍ ደረጃ በተሰጠ አቅጣጭ መሰረት በኮሌጃችንም ተ
+9
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ለአዲስ ገቢ ሰልጣኞቹ የPsychometric Test እየሰጠ ይገኛል:: ይህ የPsychometric Test በሀገር አቀፍ ደረጃ በተሰጠ አቅጣጭ መሰረት በኮሌጃችንም ተግባራዊ እየተደረገ የሚገኝ ሲሆን በኮሌጁ የICT ዲፓርትመንት በሚገኝ Lab በOnline አማራጭ አዲስ ኮሌጁን ለሚቀላቀሉ ሰልጣኞች እየተሰጠ ይገኛል:: ፈተናው አዲስ ሰልጣኞች ከራሳቸው፣ከቤተሰቦቻቸውና ከጓደኞቻቸው ጋር ተመካክረው ለመምረጥ ከሚመጡት የስልጠና ዘርፍ በተጨማሪ የሰልጣኞችን የግንዛቤ፣ የስብዕናና ያላቸውን ተሰጥኦ የሚያመላክታቸው በመሆኑ ለወደፊት ውጤታማ የሚሆኑበትን የስልጠና ዘርፍ ከወዲሁ አውቀው እንዲወስኑ የሚያግዛቸው መሆኑም ተገልፇል፡፡ በእለቱ የኮሌጁ ዲን የሆኑት አቶ ታደለ አሰፋ የPsychometric Test አሰጣጡን በአካል ተገኝተው ያስጀመሩ ሲሆን ፈተናውን ለሚወስዱት ሰልጣኞችም ግንዛቤ የመስጠት ስራ አከናውነዋል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ጥቅምት 25/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ