1 071
Подписчики
+224 часа
+37 дней
+230 день
Архив постов
በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና የአሰልጣኝ ልማትና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት የአሰልጣኝ ልማት ቡድን የAUTOMOTIVE ዘርፍ አሰልጣኝ መምህራን በMOENCO ድሬዳዋ ቅርንጫፍ ላለፉት ሁለት ወራት የቆየው የኢንዱስትሪ ላይ ተግባራዊ ስልጠና ቆይታ ማጠቃለያ በቢሮው ም/ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ምልከታ ተደረገ፡፡
በምልከታው የካምፓኒው ኃላፊዎች እና አስተባባሪዎችም ለአሰልጣኞች ያላቸውን ክህሎት እያካፈሉ መቆየታቸውንና ይህ ግንኙነትም ከፍ ብሎ ለዘርፉ አጠናቃቂ ሰልጣኞች የስራ ዕድል ምችችት በር የከፈተ መሆኑን ማረጋገጥ የተቻለ ሲሆን ከዚህ ጎን ለጎን ቢሮው ከኢንደስትሪው ጋር ያለውን ግንኙነት ለአሰልጣኝ መምህራን አቅም መገንባት እና ለአጠናቃቂ ሰልጣኞች የስራ ዕድል ፈጠራ ምቹ ሁኔታን መፍጠር ብቻ ሳይሆን በአሰሪና ሰራተኛ ጉዳዮች በተለይም ከሙያ ጤንነት እና ደህንነት አኳያ የተሰሩ ስራዎችን ተመልክተው በቀጣይ ተቋማቱ በትብብር በሚሰሩበት አግባብ ላይ ከካንፓኒው ኃላፊዎች ጋር መግባባት ፈጥረዋል፤
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
መጋቢት 2/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
+6
#ዜና| በሀገር አቀፍ ደረጃ ለ4ኛ ጊዜ ለሚካሄደው የክህሎት ውድድር የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የተለያዩ ዝግጅቶችን አጠናቆ ለውድድሩ ዝግጁ መሆኑን አስታወቀ፡፡
በዘንድሮ በጀት ዓመት ለ4ኛ ጊዜ ‹‹ ብሩህ አዕምሮዎች ፣በክህሎት የበቁ ዜጎች!››በሚል መሪ ሀሳብ ለሚካሄደው ሀገር አቀፍ የክህሎት ውድድር የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች ተጠናቆ ወደ ተግባር ተሸጋግሯል ያሉት የኮሌጁ ዲን አቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ ሲሆኑ ዲኑ አያይዘውም ውድድሩ ለሀገር የሚተርፉ ዜጎችን ወደፊት ለማምጣት የሚጠቅም ነው። ይህ የክህሎት ውድድሩ ክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራን ወደ ተግባር በመለወጥ ሂደት የበቁ ዜጎችን ለመፍጠር ያስችላል ብለዋል። ለውድድሩም የተለያዩ ዝግጅቶችን በማድረግ አሰልጣኞችና ሰልጣኞች በተለያዩ የሞያ ዘርፎች ብቃታቸውን የሚያሳድጉ ስራዎችን ስንሰራ ቆይተናል ብለዋል፡፡
በአሰልጣኞችና ሰልጣኞች እንዲሁም ኢንተርፕራይዞች ኮሌጁን ብሎም የከተማ አስተዳደሩን የሚወክሉ ተወዳዳሪዎችን ለመለየት በኮሌጅ ደረጃ የተለያዩ ውድድሮችን ከመጋቢት 10 ጀምሮ መካሄድ እንደሚጀምር የገለጹት ደግሞ የኮሌጁ ም/ዲንና የኢ/ኤ/ቴ/ሽግግር ኃላፊ የሆኑት ወ/ሮ ትግስት በዙ ሲሆኑ ወ/ሮ ትግስት አያይዘውም ይህ ውድድር በኮሌጁ በአሰልጣኞች እና ሰልጣኞች መካከል የፉክክር መንፈስ በመፍጠር እና ተወዳዳሪነታቸውን በማሳደግ በቀጣይ በከተማ እና በሀገር አቀፍ እንዲሁም በዓለም ዓቀፍ ደረጃ በሚካሄዱ ውድድሮች ላይ ተሳታፊ እንዲሆኑ ያስችላል ብለዋል፡፡
መጋቢት 15/2017 ዓ.ም መካሄድ የሚጀምረው የሰልጣኞች የክህሎት ውድድር በ6 የሙያ ዘርፎች በኮሌጅ ደረጃ በርካታ ሰልጣኞች እንደሚወዳደሩ ከኮሌጁ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
መጋቢት 02/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ EASE ፕሮጀክት የስርዓተ-ፆታ እና አካታችነትን ለማሳደግ በተዘጋጀው ጥናት ላይ ከፑል አመራር አባላትና ሴት አሰልጣኝ መምህራን ጋር የውይይት መድረክ አካሄደ::
መድረኩን በንግግር የከፈቱት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ባስተላለፉት መልዕክት በቅድሚያ በአለም አቅፍ ደረጃ ለ114ኛ ጊዜ በሀገራችን ደግሞ ለ49ኛ ጊዜ ለሚከበረው የሴቶች ቀን(March 8) እንኳን አደረሳችሁ ያሉ ሲሆኑ በዚህ ቀን ስርዓተ-ፆታን በኮሌጃችን ለማዳበር በተዘጋጀ ጥናት ላይ ውይይት ማድረጋችን ቀኑን ልዩ ያደርገዋልም ብለዋል::
የኮሌጁ ዲን አክለውም በተቋማችን በስርዓተ-ፆታ እና በአካታችነት በርካታ ፍላጎቶች መኖራቸውን አስታውሰው ከዚህ ቀደም የተወሰኑ ስራዎች ቢሰሩም በሚነሱት ፍላጎቶች ልክ በአግባቡ ምላሽ መስጠት የሚያስችሉ እንዳልነበሩ ጠቅሰው በዚህም በስርዓተ ፆታ እና አካታችነት ላይ መስራት በሚገባን መጠን ለመንቀሳቀስ የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት አድርጎ መነሻ የሚሆን መመሪያ ማዘጋጀት አስፈልጏልም ብለዋል::
በተጨማሪም በሁለቱ ጉዳዮች ላይ የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት ለማድረግ በተመረጡ ቡድኖች አማካኝነት ጥናቱ ሲደረግ መቆየቱን አስታውሰው በዛሬው እለትም የጥናት ቡድኑ የደረሰበት በመድረኩ አቅርቦ በቀረበው ጥናት ላይ አስተያየት እንዲሰጥበትና መካተት የሚገባቸውን ጉዳዮች ማካተት እንዲቻል የተዘጋጀ መድረክም ነው ብለዋል::
የስርዓተ ፆታ እና እካታችነትን ለማሳደግ በEASE ፕሮጀክት በቀጣይ 5አመት ውስጥ ለሚኖረው ትግበራ መነሻ ሚሆነውን መመሪያ ለማዘጋጀት የተደረገውን የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት አዘጋጆቹ የደረሱበትን ለተሳታፊዎች ያቀረቡ ሲሆን በቅድሚያ በአካታችነት ላይ የተደረገውን የፍላጎት ዳሰሳ በአሰልጣኝ መምህር ዮናስ ሙሉጌታ ለተሳታፊዎች ቀርቦ በጥናቱ ከጉዳዩ ጋር ተያይዞ እንደ ተቋም የተለዩ ክፍተቶችን በዝርዝር አመላክቷል::
ቀጥሎም በስርዓተ-ፆታ ላይ የተዘጋጀውን የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት በወ/ሮ ራሄል እሸቱ እና ኢንጂነር ህይወት እሸቱ አማካኝነት ለመድረኩ ተሳታፊዎች የቀረበ ሲሆን በቀረበው ጥናትም በስራ እካባቢ ለሴቶች የሚያስፈልጉ ማቴሪያሎች የማሟላት ክፍተት፣ ስርዓተ ፆታ ላይ በቂ ግንዛቤ ለኮሌጁ ሰራተኞች አለመፍጠር፣ ሴቶችን የማበረታታትና ወደ አመራርነት እንዲመጡ ተገቢውን ድጋፍ ያለማድረግ እንዲሁም የማማከር አገልግሎት ሚያገኙበት አግባብ ያለመኖሩ የሚሉት በጥናቱ ከተገለፁት ውስጥ ተጠቃሽ ነጥቦችም ነበሩ::
በመጨረሻም በቀረቡት ጥናቶች መነሻነት ከተሳታፊዎ በርከት ያሉ ሀሳቦች ተነስተው ውይይት የተደረገበት ሲሆን ጥናቱንም ለማዳበር ተጨማሪ ግብአቶች የተገኙበት መድረክም ነበር::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን
የካቲት 29/2017 ዓ.ም
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ዋና ስራ ሂደት በተቋሙ ከሚገኙ አሰልጣኝ መምህራን ጋር የውይይት መድረክ አካሄደ::
የውይይት መድረኩ የመሩት የኮሌጁ የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ም/ዲን አቶ ኤሊያስ አህመድ በንግግራቸው እንደግለፁት በአካዳሚክ ካላንደሩ መሰረት የትምህርትና ስልጠናው የመጀመሪያ ተርም ተጠናቆ ሁለተኛውን ተርም ምንጀምርበት ወቅት ላይ እንደመሆናችን የነበሩ ክፍተቶችን በሚገባ ለይቶ መፍትሄ ለማበጀትና በሁለተኛው ተርም ላይ በድጋሚ እንዳይስተዋሉ ለማድረግ ይህ የውይይት መድረክ አስፈልጎናልም ብለዋል::
ም/ዲኑ አክለውም ቀደም ብለው ከአካዳሚክ አባላት ጋር ተመሳሳይ ውይይት ማድረጋቸውን አስታውሰው ከዛ በተገኘው ግብዓት መነሻነት እንዲሁም ከአሰልጣኝ መምህሩ የሚነሱ ሀሳቦችንም ጨምሮ በመወያየትና መፍትሄዎችንም በማስቀመጥ ለሁለተኛው ተርም በቂ ዝግጅት ማድረግ እንደሚገባም ገልፀዋል::
በመድረኩ ተሳታፊ ከነበሩት አሰልጣኝ መምህራንም የትምህርትና ስልጠና ሂደቱን አስመልክቶ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን በዝርዝር ያስቀመጡ ሲሆን ከተነሱት ሀሳቦች ውስጥም የትምህርትና ስልጠና ማቴሪያል ውስንነት፣ ከትብብር ስልጠና ጋር ተያይዞ የሚያጋጥሙ ችግሮችን እንዲሁም በምሽት ስልጠና ላይ ያልተመጣጠነ የመምህራን ክፍያ ችግርን ጨምሮ ትምህርትና ስልጠናውን ውጤታማ እንዳይሆን መንስኤ ናቸው ያሏቸውን በርካታ ክፍተቶችን በመጥቀስና አያይዘውም የመፍትሄ ሀሳብ ይሆናሉ ያሏቸውንም በመድረኩ አቅርበዋል::
በመጨረሻም አጠቃላይ ከመድረኩ በተነሱ ሀሳቦች ላይ ውይይት በማድረግ እንዲሁም ሰፊ ማብራሪያና ምላሽ ተሰጥቶባቸው መድረኩ ፍፃሜውን አጊኝቷል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን
የካቲት 28/2017 ዓ.ም
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ሴት አመራሮችና ሰራተኞች ዘንድሮ በዓለም ለ114ኛ በሃገራችን ለ49ኛ ጊዜ እየተከበረ የሚገኘው ዓለማቀፉ የሴቶች ቀንን "ፈጣንና ቀጣይነት ያለው ሁሉን አቀፍ ለውጥ በሴቶች ተሳትፎ ይረጋገጣል!" በሚል መሪ ቃል በተለያዩ መርሃ-ግብሮች አከበሩ፡፡
በመርሃ-ግብሩ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የቢሮው ም/ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ በዓሉን ስናከብር የሴቶችን ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ በመስራት ሊሆን ይገባል ብለዋል፡፡
ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ አክለውም የሴቶችን ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ተጠቃሚነትና ተሳታፊነት ለማሳደግ በርካታ ስራዎች በመሰራት ላይ መሆኑን ጠቅሰው የሴቶችን ቀን በዓመት 1 ቀን ከማክበር ባሻገር የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነታቸውን በማረጋገጥ መሆን እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
ቀኑን አስመልክቶም የመወያያ ሰነድ በወ/ሮ ማርታ በዛብህ የሴቶች ወጣቶችና ኤች አይ ቪ ኤድስ ባለሙያ ቀርቦ ውይይት ተካሂዶበታል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
የካቲት 28/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
+5
#ዜና|የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለአካል ጉዳተኞች ምቹ እና ተደራሽ እንዲሁም አካታች የሆነ ተቋም እንዲሆን እየተሰራ እንደሆነ ተገለጸ፡፡
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለአካል ጉዳተኞች መልካም መደላድልን ለመፍጠር ያለመ ለኮሌጁ ትምህርት ክፍል ተጠሪዎች እንዲሁም ለተለያዩ የኮሌጁ ሰራተኞች ለ10 ቀን የሚቆይ ስልጠና ተጀመረ፡፡
በሃገራችን ከሚገኙ ኮሌጆች መካከል ሁሉን አካታች ኮሌጅ የሆነው የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በግንባር ቀደምትነት የሚጠቀስ ነው ያሉት በስልጠናው ላይ በመገኘት መልእክት ያስተላለፉት የኮሌጁ ም/ዲንና የኢ/ኤ/ቴ/ሽግግር ኃላፊ የሆኑት ወ/ሮ ትግስት በዙ ሲሆኑ አያይዘውም ኮሌጃችን የህብረተሰባችን ክፍል የሆኑ የአካል ጉዳት ያለባቸው ሰልጣኞችን ተቀብሎ እንደማሰልጠኑ መጠን መልካም መደላደል ለአካል ጉዳተኞች መፍተር ይኖርብናል ይህንንም መልካም መደላደል ለመፍጠር ደግሞ አካታች የሆኑ እቅዶችን በማዘጋጀትና ምቹ የስልጠና ቦታዎችን በማመቻቸት እየሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡
በዛሬው እለት የተጀመረው ስልጠና ለሁሉም የኮሌጁ አካላት በቀጣይነት የሚሰጥ ሲሆን ስልጠናው ሲጠናቀቅ ደግሞ አካል ጉዳት ያለባቸው ሰልጣኞችን ያለ አስተርጓሚ ስልጠናቸውን በጥራት እንዲከታተሉ ያስችላል ያሉት ደግሞ የኮሌጁ ልዩ ፍላጎት አስተባባሪ አቶ መሰለ ወ/ጊዮርጊስ ናቸው፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
የካቲት 28/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ
በአስተዳደሩ የገጠር አራቱም ክላስተሮች ስር የሚገኙና በቢሮው ኢንተርፕራይዞች ልማት ዳይሬክቶሬት የተለያዩ ድጋፎች የሚደረግላቸው ኢንተርፕራይዞችን ወደ ሞዴል ኢንተርፕራይዝነት ለማሳደግ የሚያስችል የመስክ ምልከታና ልየታ መደረግ ጀመረ።
በዛሬው ዕለትም በቢዮአዋሌ ክላስተር የተለዩ ሞዴል ኢንተርፕራይዞች ምልከታ የተደረገ ሲሆን ቀሪ የአስተዳደሩ ገጠር ክላስተሮች ላይ የሚገኙ ኢንተርፕራይዞች በተመሳሳይ ምልከታ እና ልየታ የሚደረግ ይሆናል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
የካቲት 26/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
የአምራችና አገልግሎት ሰጪ ኢንዱስትሪውን ፍላጎት መሰረት ያደረጉ ባለሙያዎችን ማፍራት እንደሚገባ ተገለፀ::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ EASE ፕሮጀክት በአስተዳደሩ ከሚገኙ አምራችና አገልግሎት ሰጪ ድርጅቶች ጋር በኢንዱስትሪ ፍላጎት ዳሰሳ ጥናት ላይ የምክክር መድረክ አካሄደ::
የምክክር መድረኩን በንግግር ያስጀመሩት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ሲሆኑ ባስተላለፉት መልዕክትም የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ወደ ኢንዱስትሪ የሚገቡትን ብቻ ሳይሆን ኢንዱስትሪው ላይ እየሰሩ የሚገኙትን ባለሙያዎችን ጭምር የሚፈለገው ደረጃ ላይ እንዲደርሱ አሰልጥኖ ማብቃት እንዱ ተግባሩ መሆኑን ጠቅሰው ለዚህም እንዲረዳ በየትኛው ዘርፍ ላይ ትኩረት ተደርጎ ቢሰራ የሚስተዋለውን ችግር መቅረፍ ይቻላል የሚሉትን ጉዳዮች በቀጥታ ከእናንተ ከጉዳዩ ባለቤቶቹ ጋር ለመወያይትና መረጃዎችን ለመሰብሰብ ይህ የምክክር መድረክ መዘጋጀቱንም ገልፀዋል::
የኮሌጁ ዲን አክለውም በሚኖረን የምክክር መድረክ ላይ ብዙ ግብዓቶች ከተሳታፊዎች እንደሚጠብቁ ገልፀው በኢንዱስትሪው ውስጥ ምርታማነትን ከማስፋፋት አንፃር እንዲሁም በትክክል የኢንዱስትሪውን እድገት እየጎተቱ ያሉ ጉዳዮችን ከቴክኒክና ሙያ ዘርፉ አኳያ ሊፈቱ የሚችሉትን በዝርዝር መረጃ እዲሰጡም ጠይቀዋል::
የዳሰሳ ጥናት ሰነዱን ለተሳታፊዎች ሰፋ ባለ ማብራሪያ ያቀረቡት የኮሌጁ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር ም/ዲን አቶ ተሾመ ሸዋዬ ሲሆኑ በንግግራቸውም በዚህ ጉዳይ እስካሁን በነበረው የተናጠል እንቅስቃሴ የሚጠበቅውን ውጤት ማስመዝገብ እንዳልተቻለ አስታውሰው ከጅምሩ በቅንጅት ሲሰራ ብዙ አዳዲስ ነገሮችን መፍጠር እንደሚቻልና ለሚስተዋሉ ችግሮችም የመፍትሄ አካል መሆን ስለሚቻል ሁላችንም በንቃት ልንሳተፍ ይገባልም ብለዋል::
ከመድረኩ በተደረገው ገለፃ መሰረትም አምራችና አገልግሎት ሰጪ እንዱስትሪዎች እንደየዘርፋቸው በቡድን ተከፋፍለው የምክክር መድረኩ የተካሄደ ሲሆን ተሳታፊዎች በየድርጅቶቻቸው የተለዩ ፍላጎቶችን እንዲሁም የመፍትሄ ሃሳቡ ይሆናሉ ያሏቸውን ለመድረኩ አወያዮች በማቅረብ ለፍላጎት ዳሰሳ ጥናቱ ግብዓት ማግኘትም ተችሏል::
በተጨማሪም በመድረኩ የዳሰሳ ጥናት ፎርም አጠቃቅም በተመለከት በኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት አስተባባሪ አሰልጣኝ መ/ር አቤል ዘገየ አማካኝነት ለተሳታፊዎች ግንዛቤ የተሰጠ ሲሆን በቀጣይም ለዚህ ተግባር በተመደቡ ባለሙያዎች አማካኝነት በየኢንዱስትሪዎቹ በመሄድ ለዳሰሳ ጥናቱ የሚያስፈልገውን መረጃ የሚያደረራጁ መሆኑም በመድረኩ ተገልፇል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን
የካቲት 27/2017 ዓ.ም
ለቅድመ ሞዴል ኢንተርፕራይዞች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተዘጋጀ፡፤
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኢንተርፕራይዞች ልማት ዳይሬክቶሬት በ2017 ዓ.ም ከተለዩት ቅድመ ሞዴል ኢንተርፕራይዞች መካከል ስራቸውን በመመልከት ለሞዴልነት እጩ የሆኑ 47 ኢንተርፕራይዞችን በመምረጥ በሞዴል መመሪያውና በቀጣይ ሞዴል ሆነው የሚያበቃቸው ሃሳቦች ዙሪያ ግንዛቤ እንዲያገኙ የተደረገ ሲሆን በተጨማሪም የኢንተርፕራይዞችን አቅም ለማሳደግና የፋይናንስ ፍላጎታቸውን ለመደገፍ የተቋቋመው የሲድ ፕሮጀክት ተጠቃሚ በሚሆኑበት አግባብ ላይ ገለጻ ተደርጎላቸዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
የካቲት 25/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የሥራ ዕድል ፈጠራና አንድ ማዕከል ዳይሬክቶሬት በአጠቃላይ የሥራ ዕድል ፈጠራ ስራዎች እንቅስቃሴን አስመልክቶ ለከወረዳ ምክትል ሥራ አሥፈጻሚዎች፣ የአንድ ማዕከል እና የቢሮው ባለሙያዎች ጋር ውይይት ተካሄደ።
በዚህም መድረክ ለተሳታፊዎች ገለጻ የተደረገላቸው ሲሆን የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ ሮቤል ጌታቸው በአስተዳደሩ የተፈጠሩ ዕድሎችን በተለይም የኢንደስትሪዎች መስፋፋት የኮሪደር ልማት ስራዎችን ተከትሎ የሚፈጠሩ የሥራ ዕድሎችን የአስተዳደሩ ሥራ ፈላጊዎች እንዲጠቀሙ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ተቀራርቦ መስራት እንዲሁም የሥራ ፈላጊዎችና የኢንተርፕራይዞች ምዝገባ፤ በየመንደሩ የቤተሰብ ቢዝነሶች እንዲፈሩ ከማድረግ አኳያ በየጊዜው መሰል ውይይቶች እንደሚደረጉ አብራርተዋል፡፡
ዳይሬክተሩ አክለውም በኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት ላይ https://lmis.gov.et የሚከናወነው ምዝገባ በተለያዩ ህብረተሰቡ በስፋት በሚገኝባቸው ቦታዎች ድረስ በመሄድ ተደራሽ የማድረግ ስራዎች እንደሚሰሩ የገለጹ ሲሆን በመጨረሻም "ብቃት" የወጣቶች ሥራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም ሶስተኛ ዙር ትግበራ መጀመሩን አስመልክቶ ሁሉም አካላት በቅንጅት በመስራት ከዚህ በፊት በሁለቱ ዙሮች የተገኘውን ውጤት በማሻሻል መድገም እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተው አሳስበዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
የካቲት 25/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Уже доступно! Исследование Telegram 2025 — ключевые инсайты года 
