ru
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Открыть в Telegram
1 076
Подписчики
+224 часа
+37 дней
+230 день
Архив постов
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በጫኝና አውራጅ ስራ ላይ ለተሰማሩ ወጣቶች ለተከታታይ 5 ቀናት ሲሰጥ የነበረው በህይወት ክህሎት ላይ ትኩረቱን ያደረገ ስልጠና ተጠናቀቀ፡፡ ወጣቶችን በህይወት ክህሎት የበ
+4
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በጫኝና አውራጅ ስራ ላይ ለተሰማሩ ወጣቶች ለተከታታይ 5 ቀናት ሲሰጥ የነበረው በህይወት ክህሎት ላይ ትኩረቱን ያደረገ ስልጠና ተጠናቀቀ፡፡ ወጣቶችን በህይወት ክህሎት የበቁና በስራ ቦታቸው ለሚገጥማቸው ጉዳዮች ሁሉ ፈጠራ የተሞላበት እና ተገቢውን ተግባራት እንዴት ማከናወን እንደሚችሉ ትኩረቱን ያደረገው ይህ ስልጠና ወጣቶቹን ለስራ ዝግጁ እንዲሆኑና ፈጠራ የታከለበት ስራዎችን መስራት እንዲችሉ የሚያደርግ ስልጠና እንደሆነ በስልጠናው ወቅት ለማወቅ ተችሏል፡፡ በተጨማሪም ሰልጣኞቹ ከሚሰሩት ስራ ጎን ለጎን ትምህርትና ስልጠናዎችን በኮሌጁ በኩል ማግኘት እንደሚችሉ ለሰልጣኞቹ ገለጻ ተደርጓል፡፡ በኮሌጁ የተሰጠው ይህ ስልጠና በድሬዳዋ ስራ ክህሎት ቢሮ እና በኮሌጁ የተዘጋጀ ሲሆን በቀጣይም እንዲህ አይነት ስልጠናዎች በከተማና በገጠር ክላስተሮች በሰፊው የሚሰጥ ይሆናል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ጥር 27/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

የቢሮው ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ዘርፍ ከኢንደስትሪው ጋር ያለውን ግንኙነት ለአሰልጣኝ መምህራን አቅም መገንባት እና ለአጠናቃቂ ሰልጣኞች የስራ ዕድል ፈጠራ ምቹ ሁኔታን እየፈጠረ እንደሚገኝ ተገለጸ፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና የአሰልጣኝ ልማትና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት የአሰልጣኝ ልማት ቡድን የAUTOMOTIVE ዘርፍ አሰልጣኝ መምህራን  በMOENCO ድሬዳዋ ቅርንጫፍ ለሁለት ወራት የሚቆይ የኢንዱስትሪ ላይ ተግባራዊ ስልጠና ያለበት ሂደት ላይ ምልከታ አደረገ፡፡ በምልከታው የካምፓኒው  ኃላፊዎች እና አስተባባሪዎችም ለአሰልጣኞች  ያላቸውን ክህሎት እያካፈሉ መሆኑንና ይህ ግንኙነትም ከፍ ብሎ ለዘርፉ አጠናቃቂ ሰልጣኞች የስራ እድል ምችችት በር የከፈተ መሆኑን ማረጋገጥ ተችሏል፤ የካምፓኒው አመራሮች የዘርፉን ስትራቴጂ በመረዳት አሰልጣኞቹን ተቀብለው እያደረጉ ላሉት የቴክኖሎጂ እና እውቀት ሽግግር በዘርፉ ያለን የስልጠና ጥራት እና የኢንዱስትሪውን አጋርነት እያረጋገጠ ያለ ቅንጅታዊ አሰራር መፈጠሩ ተመላክቷል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጥር 27/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

የቢሮው ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ዘርፍ ከኢንደስትሪው ጋር ያለውን ግንኙነት ለአሰልጣኝ መምህራን አቅም መገንባት እና ለአጠናቃቂ ሰልጣኞች የስራ ዕድል ፈጠራ ምቹ ሁኔታን እየፈጠረ እንደሚገኝ ተገለጸ፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና የአሰልጣኝ ልማትና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት የአሰልጣኝ ልማት ቡድን የAUTOMOTIVE ዘርፍ አሰልጣኝ መምህራን  በMOENCO ድሬደዋ ቅርንጫፍ ለሁለት ወራት የሚቆይ የኢንዱስትሪ ላይ ተግባራዊ ስልጠና ያለበት ሂደት ላይ ምልከታ አደረገ፡፡ በምልከታው የካምፓኒው  ኃላፊዎች እና አስተባባሪዎችም ለአሰልጣኞች  ያላቸውን ክህሎት እያካፈሉ መሆኑንና ይህ ግንኙነትም ከፍ ብሎ ለዘርፉ አጠናቃቂ ሰልጣኞች የስራ እድል ምችችት በር የከፈተ መሆኑን ማረጋገጥ ተችሏል፤ የካምፓኒው አመራሮች የዘርፉን ስትራቴጂ በመረዳት አሰልጣኞቹን ተቀብለው እያደረጉ ላሉት የቴክኖሎጂ እና እውቀት ሽግግር በዘርፉ ያለን የስልጠና ጥራት እና የኢንዱስትሪውን አጋርነት እያረጋገጠ ያለ ቅንጅታዊ አሰራር መፈጠሩ ተመላክቷል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጥር 27/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+8

ለውጥ መፍጠር እና ለውጥን መምራት... ከቃል እስከ ባህል! #prosperity

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ EASE ፕሮጀክት የሩብ አመት አፈፃፀምና የቀጣይ ስድስት ወር እቅድ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ተወያየ:: በዛሬው እለት በተካሄደው መድረክ የEASE ፕሮጀክት ወደ ትግበራ ከገባበት ጊዜ ጀምሮ እስከ እሁን የነበረውን የአፈፃፅም ትግበራ እንዲሁም በፕሮጀክቱ የቀጣይ ስድስት ወራት እቅድን መነሻ በማድረግ ከፕሮጀክቱ ኢንዱስትሪ እድቫይዘሪንግ ቦርድ አባላት ጋር የውይይት መድረክ በሀረር ተካሂዷል:: መድረኩን በንግግር ያስጀመሩት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ በንግግራቸው እንደገልፁት ምንም እንኳን የEASE ፕሮጀክትን ወደ ትግበራ ከገባ አጭር ጊዜ ቢሆንም እስካሁን በደረስንበት አፈፃፀም መሰረት ወቅቱን ጠብቆ ከባለድርሻ አካላት ጋር መወያየት አስፈላጊ በመሆኑ ይህን መድረክ ተዘጋጅቷል ያሉ ሲሆን በተጨማሪም በመድረኩ በሚቀርበው የEASE ፕሮጀክት የቀጣይ ስድስት ወር እቅድ ላይ ከኢንዱስትሪው አኳያ ማካተት ሚገባንና የተዘነጉ ጉዳዮች ካሉ ከመድረኩ በሚገኘው ግብዓት መሰረት እቅዱን ለማሻሻል ተቋማችን ዝግጁ እንደሆነም ገልፀዋል:: የኮሌጁ ዲን አክለውም ይህ ፕሮጀክት ሲነደፍ እንደ ሀገር ማስመዝገብ የተፈለገው ውጤት እንዳለ ጠቅሰው በዚህም መሰረት Result Framework በሚኒስቴር መ/ቤቱ ፀድቆ ሲመጣ በፕሮጀክቱ ትግበራ ወቅት የኛ መመዘኛ እሱ ይሆናልም ብለዋል:: በፕሮጀክቱ የእስካሁን አፈፃፀም ሪፖርት በEASE ፕሮጀክት የሞኒተሪንግና ኢቫሉዌሽን አስተባባሪ ወ/ሮ ህይወት እሸቱ አማካኝነት ለተሳታፊዎች የቀረበ ሲሆን በቀረበው አፈፃፀምም የኢንዱስትሪ አድቫይዘሪንግ ቦርድ ከማቋቋም ጀምሮ የፕሮጀክቱ አመራሮችንና ባለሙያዎችን በልምድ ልውውጥና ስልጠናዎች የማብቃት እንዲሁም 65 ለሚሆኑ የተቋሙ አገልግሎት ሰጪ ሰራተኞች የአቅም ግንባታ ስልጠና እንዲወስዱ ማድረግ መቻሉም ተገልፇል:: በተጨማሪም በቀረበው ሪፖርት በአስተዳደሩ ለሚገኙ የሚዲያ ባለሙያዎች እና የአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት አመራሮችና ተማሪዎች ስለ ዘርፉ ያለውን የተዛባ አመለካከት መቀየር የሚያስችል የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ መካሄዱም በሪፖርቱ ከቀረቡት ነጥቦች ይገኙበታል:: በመቀጠልም የEASE ፕሮጀክት የቀጣይ ስድስት ወራት እቅድ በፕሮጀክቱ አስተባባሪ አቶ ፋሲል ማዘንጊያ አማካኝነት ለተሳታፊዎች የቀረበ ሲሆን በዚህም በቀጣይ ዘርፈ ብዙ ተግባራትን ለመፈፀም በእቅዱ ላይ የተመላከት ሲሆን ከነዚህም ውስጥ በተቋሙ የሪኢኖቬሽን ስራዎች ፣ የአሰልጥኞች ስልጠና፣ የኢንተርፕሩነርሺፕ ስልጠናዎች እንዲሁ የተለያዩ የአቅም ግንባታ ስልጠዎችን ተግባራዊ ለማድረግ መያዙ ከብዙ ጥቂቱ መሆኑን በቀረበው እቅድ ተመላክቷል:: የመድረኩ ተሳታፊዎች በቀረበው የፕሮጀክቱ አፈፃፀምና የቀጣይ እቅድን መነሻ በማድረግ ለፕሮጀክቱ ውጤታማነት የሚረዱ ገንቢ እስተያየቶችና ምክረ ሃሳቦችን በስፋት አንስተው ውይይት የተካሄበት ሲሆን ኮሌጁን ጨምሮ የኢንዱስትሪ እድቫይዘሪንግ ቦርድ አባላትም ለቀጣይ የየድርሻቸውን አሳይመንቶችን በመውሰድ መድረኩ ፍፃሜውን አጊኝቷል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን ጥር 24/2017 ዓ.ም ሀረር

በአስተደዳደሩ ኢንዱስትሪ ፓርክ በተለያዩ ኢንዱስትሪዎች ውስጥ ለሚሰሩ ሰራተኞች በስራ ቦታ ኤች አይ ቪ ኤድስን መከላከል ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተዘጋጀ። በመድረኩ በመልዕክት ያስጀመሩት የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ም/ኃላፊ እና የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ኢንዱስትሪዎች ከፍተኛ ቁጥር ያለው የሰው ሃይል ከተለያዩ ቦታዎች በስራ የሚገናኙበት እንደመሆኑ መጠን ለኤች አይ ቪ ኤድስ ተጋላጭነቱን ለመቆጣጠር ቢሮዉ ተከታታይነት ያላቸውን ስልጠናዎች እያዘጋጀ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በተጨማሪ የሙያ ጤንነትና ደህንነት ባለሙያዎችን በማሰልጠን በኢንዱስትሪዎች ውስጥ እንዲቀጠሩ መደረጉ በቢሮው በኩል ትልቅ ስራ እንደተሰራ አስታውሰው ጤንነቱና ደህንነቱ የተጠበቀና የተረጋገጠ አምራች ሃይል የሆነውን ወጣት  ቢሮው ባለሙያ በማዘጋጀት የሚሰሩበት ኢንዱስትሪ ድረስ በመሄድ ግንዛቤ እንዲፈጠር መደረግ መቻሉንም ኃላፊዋ አክለው ተናግረዋል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጥር 24/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+9

ኢ-መደበኛ አንቀሳቃሾችን ወደ መደበኛ ኢንተርፕራይዝ እንዲሸጋገሩ ከአበዳሪ ተቋማት ጋር በመተባበር በቀጣይም ብድር የሚያገኙበትን ሁኔታ ለማመቻቸት የሚያስችል የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጠ፤ የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የኢንተርፕራይዞች ልማት ዳይሬክቶሬት ይህን የስልጠና መድረክ ለኢ-መደበኛ አንቀሳቃሾች ሲያዘጋጅ የሥራን ጠቀሜታ በመረዳትና ለሥራ ያላቸውን ተነሳሽነት በመጨመር የራሳቸውንና የቤተሰቦቻቸውን ህይወት እንዲለውጡ አስፈላጊና ጠቃሚ የሆኑ መሠረታዊ የንግድ ክህሎቶች እንዲጨብጡ ታሳቢ ያደረገ ነው፤ የኢንተርፕራይዞች ልማት ዳይሬክቶሬት ቡድን መሪ የሆኑት ወ/ሮ መቅደስ ከፈለኝ እንደገለጹት አንቀሳቃሾቹ ይህን ስልጠና ከወሰዱ በኋላ በሥራ ፈጠራና ሥራ ፈጣሪነት ላይ ግንዛቤያቸውን የሚጨምር ሲሆን በንግዱ ሙያ ውስጥ ውጤታማ ሊያደርጉ የሚያስችላቸውን ባህሪ በመላበስና ብቃቶችን እንዲያዳብሩ የሚያግዛቸው እንደሚሆን ተናግረዋል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጥር 23/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+9

በድሬዳዋ ነጻ ንግድ ቀጠና ውስጥ አጫጫር የሙያ ስልጠና ለመስጠት የተደራጀው የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ የእሳትና ድንገተኛ አደጋ መከላከል እና መቆጣጠር እንዲሁም የመጀመሪያ የህክምና እርዳታ አሰጣጥ ስልጠና በአዲሱ የሙያ ደረጃ መሰረት አጫጭር የቴክኒክና ሙያ ስልጠና እንዲሰጥ የእውቅና እድሳት ለማድረግ ያለበትን ደረጃ ለማወቅ ምልከታ ተደረገ። በአጠቃላይ ለስልጠናው አስፈላጊ የሆኑ የሰው ሃይልና የማሰልጠኛ መሣሪያዎች  ስለመሟላታቸው እንዲሁም የስልጠና አሰጣጥ አቅምን በምልከታ ለማረጋገጥ በባለሞያዎች የተዋቀረ ቡድን ማሰልጠኛውን ከሚመሩ እና ከሚያስተባብሩ ባለሙያዎች ጋር ውይይት የተካሄደ ሲሆን በቀጣይ ማሰልጠኛው ለአንድ አመት የተሰጠውን የምዝገባ ፈቃድ አፈጻጸም ጥሩ መሆኑ መመልከት የተቻለ ሲሆን የቀጣይ ሶስት አመታት የስልጠና የእውቅና ፈቃድም በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ በኩል የሚያገኝ ይሆናል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጥር 23/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+9

በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ስር የሚገኘው የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የአሰልጣኝ ልማትና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት የኮሌጆችን አቅም ለማሳደግና የአሰልጣኝ መምህራንን የክህሎት ክፍተት መሙላት የሚያስችል ተከታታይነት ያለው ስራ በመስራት ላይ እንደሚገኝ ተገለጸ፡፡ በኢትዮጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አሰልጣኝ መምህራን የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠናን ዲጂታላይዝ ለማድረግ የሚያስችሉ ስራዎችን በአይ ሲ ቲ ትምህርትና ስልጠና ክፍል ተግባራዊ ተደረገ፤ ይህም አሰልጣኝ መምህራኑ እርስ በእርስ የክህሎት ሽግግር በማድረግ በተቋሙ የሚሰጡ ስልጠናዎችን በኢ-ለርኒንግ ለመስጠት የሚያስችሉ ግብዓቶችን በራስ አቅም በመስጠት SSD RAM Upgrade  በማድረግና ወርክሾፖችን በማደራጀትና በቀጣይ የሶፍትዌር በተለይም ፎቶሾፕ ስልጠናዎችን ሊያሰጡ የሚችሉ ስራዎች ተሰርቷል፡፡ በዚህም የኮሌጁን አሰልጣኝ መምህራንን አቅም ከመገንባቱ ባሻገር እና በወጪ አንጻር ኮሌጁ ሊያወጣ የሚችለውን ከፍተኛ በጀት የቀነሰ ሆኗል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጥር 22/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+7

ለሥራ ፈላጊዎች የማይንድ ሴት ስልጠና ተሠጠ። ስልጠናው የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የሥራ ዕድል ፈጠራና አንድ ማዕከልማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት ሥራ ፈላጊዎች ተቀጥሮ መስራት ላይ ብቻ ሳይሆን በግልም ሆነ ተደራጅተው ሥራ እንዲፈጥሩ በሚያነሳሳ መልኩ ቀርቧል። በዚህም ተሳታፊ የሆኑ ከአስተዳደሩ ወረዳዎች የተወጣጡ ሥራ ፈላጊዎች ከዚህ በፊት ተቀጥሮ ለመስራት ብቻ ይጠብቁ የነበሩ ከስልጠናው ባገኙት ግንዛቤ በግልም ሆነ ተደራጅቶ ለመስራት መነሳሳት እንደተፈጠረባቸው ገልጸዋል። ቢሮው በአስተዳደሩ ትኩረት  የተሰጠውን የስራ አጥ ቁጥር ለመቀነስ የተጀመሩ የተለያዩ ስራዎችን በተለይም በኮሪደር ልማቱ እና ከኢንዱስትሪዎች ጋር ግንኙነት በመፍጠርና ሥራ ፈላጊዎች ተደራጅተው ወደ ሰራ እንዲሰማሩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በጋራ በመስራት ላይ ይገኛል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጥር 22/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+9

#በመካከላችን “አንድ  በቁጥር፤ ብዙ በግብር!” ተወልዶ ያደገው እዚሁ በተወዳጇ ድሬዳዋ ሲሆን ከልጅነቱ በተለያዩ የጥበብ ስራዎች ዝንባሌ ትኩረት በመስጠትና ደስ ስለሚያሰኘው እየሞከረ እንዳደገ ይናገራል፤ እራሱን ካወቀበት ጊዜ ጀምሮ በውስጡ የሚብላላ ቁጭት እንዳለው ይህም ድሬዳዋ የብዙ ጠቢባን መፍለቂያና መናኸሪያ የመሆኗን ቅርስነት ቅብብሎሽ አንጸባራቂ ሆኖ መመልከት አካልም መሆን መሻቱና ናፍቆቱ መሆኑን ይገልጻል፡፡ ዛሬ ልናስተዋውቃችሁና አብልጠን ልናበረታታው ይዘን የቀረብነው የሥራና ክህሎት ቤተሰብ አሰልጣኝ መምህር ዳንኤል በላይ ይባላል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክሎህት ቢሮ ስር በሚገኘው የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የአይ ሲ ቲ ትምህርትና ስልጠና ክፍል ውስጥ በአሰልጣኝ መምህርነት ዜጎችን እያበቃ የሚገኝ ግን በቃ የማያውቀው የባለ ብዙ ሞያዎችና ተሰጥኦ ባለቤት ድንቅ ቤተሰብ ነው፡፡ እናም ጥበበኛው በቁጥር አንድ ሰው ነው ግና በክህሎትና ግብር ብዙ ሆኖ አሰልጣኝ መምህር ነው ስትሉት ሰዓሊ ሆኖ ታገኙታላችሁ እኛ ለማበረታታትና ለመደገፍ ቅንነታችንን አብዝተን እንግለጥ እንጂ ከሙዚቃው መንደር ብትሄዱ እርሱ በዚያም ይገኛል መቼ በዚህ ብቻ ተገድቦ የተለያዩ የቅርጻቅርጽ ስራዎችን ሲሰራ ከተፈጥሮ ውበት ጋር አፍቃሪየ መናኝ ሆኖ በንመለከተው አንታዘበው እናበረታታው ነገ ብዙ ክህሎት ላላቸውና ለሚሰሩ አዕምሮዎችና እጆች አርዓያ ይሆናል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጥር 21/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+4