ru
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Открыть в Telegram
1 091
Подписчики
+324 часа
+257 дней
+1730 день
Архив постов
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የቴክኖሎጂ ሽግግር እና ኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ስራ ሂደት በዳይመንድ ሚስማር ፋብሪካ የመስክ ምልከታ አካሄደ:: በፋብሪካው በነበረው ጉብኝት በቅድሚያ ከድርጅቱ ሀላፊና ባለቤቶች ጋር በስራ ላይ ስለሚገጥሟቸው ችግሮች እንዲሁም ከተቋሙ በሚደረግላቸው የድጋፍ አይነቶች ዙሪያ ውይይቶች የተደረጉ ሲሆን የሚስማር ማምረቻ ወርክ ሾፖችንም ተዘዋውረው ተመልክተዋል:: በምልከታው ወቅትም ድርጅቱ በማሽን ጥገና ወቅት የመለዋወጫ እጥረት እንዳለበትና ለረጅም ጊዜ በብልሽት ምክንያት ያለ ስራ የቆሙ ትልልቅ ማሽነሪዎችም እንዳሉ መታዘብ ተችለዋል:: ተቋሙ በቀጣይ በድርጅቱ የተለዩ ችግሮች ላይ በኮሌጁ ሊፈቱ የሚችሉትን በዝርዝር በመለየትና ከድርጅቱ ጋር የጋራ ስምምነት በመፈፀም የዕውቀትና የቴክኖሎጂ ሽግግር ድጋፍ እንደሚይደርግም ተገልጿል:: ኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን ህዳር 28/2016 ዓ.ም

የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሊጂ ልማት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ኤጀንሲ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት ለ20 ቀናት የሚቆይ ስልጠና የሁለቱ ኮሌጅ አሰልጣኝ መምህራን በሞዴል ኢንተርፕራይዞች ላይ የካይዘን ትግበራ ተጀመረ፡፡ በዚህም ለኢንተርፕራይዞች ሠራተኞች የጥራትና ምርታማነት ማሻሻያ (ከይዘን) ትግበራ ስልጠና/ድጋፍ በመስጠት ማብቃት እና የመስሪያ/ ማምረቻ ወርክሾፖችን በከይዘን እንዲደራጁ በማድረግ ኮሌጆች ከኢንተርፕራይዞች ጋር የሚኖራቸዉን የስራ ትስስር ለማጠናከርና የኢንተርፕራይዞችን ሠራተኞች መሰረታዊ የካይዘን እዉቀትና ክህሎትን በኢንተርፕራይዙ ማምረቻ/የስራ ቦታ በመተግበር ደረጃዉን የጠበቀ ማምረቻ ቦታ ለመፍጠር እና በአጠቃላይ የከይዘን ፍልስፍናን በመተግበር የአሰልጣኝ መምህራኑን አቅም በመገንባት የኢንተርፕራይዞችን አላስፈላጊ ብክነቶችን በማስወገድ ምርትና ምርታማነትን ለማሻሻል አቅም የሚፈጥር ስልጠና ይሆናል፡፡ ዳይሬክቶሬቱ ከኮሌጆች ጋር በመሆን የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ድጋፍ በመስጠት በአስተዳደሩ ጉልህ ስራዎችን እየሰራ ሲሆን በተለይም በ4ቱ የድጋፍ ማእቀፎች የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞችን  የምርትና ምራታማነት በማሻሻልና  ብቁ የሆነ የሰዉ ሐይል በማፍራትና የሥራ እድል እንዲፈጥሩ ለማድረግ ድጋፍ እየሰጠ ይገኛል፤ በዚህም በአስተዳደሩ ዘጠኙም ወረዳዎች ለሚገኙ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ድጋፍ ለሚደረግላቸው  ኢንተርፕራይዞች የድርጊት መርሀ ግብር በማዘጋጀት ወደ ትግበራ መገባቱን የዳይሬክቶሬቱ ኬዝቲም ወ/ሮ ሰላም ደሳለኝ ገልጸዋል፡፡ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ህዳር 28/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+9

ከዘመኑ ጋር የሚሄድ ስልጠና መስጠት ለተሻለ ውጤት እንደሚያበቃ ተገለፀ፤ **************** የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን እና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት በሴቶችና፣ በአካል ጉዳተኛ ለሚመሩ  ኢንተርፕራይዞች  የንግድ ክህሎት እና የሂሳብ መዝገብ አያያዝ የአቅም ግንባታ ስልጠና ሰጠ፡፡ በስልጠናው ላይ የኢንተርፕሩነርሺፕ ምንነትና የንግድ ክህሎታቸውን ሊያዳብሩ የሚችሉና የሂሳብ መዝገብ አያያዝ ጋር ያለባቸውን ክፍተት ከመሙላት አንጻር ያለው አስተዋፅኦ በሰፊው የተዳሰሰ ሲሆን ሰልጣኞች ከዚህ በፊት የነበራቸውን እውቀትና ግንዛቤ እንዳሳደገላቸውም ሰልጣኞች ተናግረዋል፡፡ ኢንተርፕራይዞቹ እርስ በእርስ ያላቸውን መስተጋብር ይበልጥ በማጠናከር የልምድ ልውውጥና የእውቀት ሽግግር እንዲያደርጉ ያስቻለ ሲሆን  ለኢንተርፕራይዞች የተሻለ ትኩረት በማድረግ ውጤት ተኮር ተግባር ማስመዝገብ የሚቻለው ከጊዜው ጋር የዘመነ ስልጠና በመስጠት እንደሆነም የዳይሬክቶሬቱ ባለሙያ ወ/ሮ ውልታ ትልቅሰው  ተገልጿል፡፡ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ህዳር 28/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+9

ብቁ የሆኑ ሥራ ፈጣሪዎችን ለማፍራት በክህሎት ሥራዎች ላይ ትኩረት አድርጎ በፍጥነት ወደ ሥራ በመግባት ብሎም የሥራ አጥ ቁጥርን ለመቀነስ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና የጎላ ሚና እንዳላቸው የብልጽግና ፓርቲ ድሬዳዋ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኢብራሂም ዩሱፍ ተናገሩ፡፡ የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ በቀጣይ ወደ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች የሚገቡ አዲስ ሰልጣኝ ተማሪዎች ቅበላ ዝግጅት እና የብቃት የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ፕሮጀክት የሥራ አፈጻጸም ምን እደሚመስል ከወረዳ አመራሮችና ባለሙያዎች ጋር ተወያይቷል፡፡ ለውይይቱም መነሻ የሚሆን የቴክኒክና ሙያ ትምርትና ስልጠናን በተመለከት ኤጀንሲውን የሚመሩት ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ገለጻ የቀረበ ሲሆን ዘርፉን ለማስተዋወቅ የተሰሩና ወደፊት በስፋት ሊከናወኑ ስለሚገባቸው ሥራዎች አብራርተዋል፤ በተመሳሳይ ብቃት የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ፕሮጀክት የመጀመሪያ ዙር የማጠቃለያ ሥራዎች አፈጻጸም ሪፖርት የፕሮጀክቱ ስፔሻሊስት አቶ ፈጠነ ተክሉ አቅርበዋል፡፡ የቢሮው ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው አክለው እዳስገነዘቡት ኮሌጆቻችን ያላቸውን የአሰልጣኝ መምህራን አቅም፣ የግብዓት አቅርቦት በተለይ ደረጃቸውን የጠበቁ ማሽነሪዎችና ከጊዜው ጋር የሚሄዱ አዳዲስ ዘርፎችና ሙያዎችን ማሰልጠናቸውን ሊጠቀምና ሊመርጥ የሚፈልግ ሰልጣኝ ወደ ኮሌጆች ማምጣት የሁሉንም ርብርብ የሚጠይቅ ይሆናል ብለዋል፡፡ በመድረኩም ማጠቃለያ የብልጽግና ፓርቲ ድሬዳዋ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኢብራሂም ዩሱፍ  የሥራ ዕድል ፈጠራውንና የክህሎት ልማቱን ጉዳይ የወረዳ አመራሩና ባለሙያው የዕለት ከዕለት ስራው አድርጎ ከዚህ በፊት የተሰሩትን መልካም ስራዎች በተሞክሮ በማስፋት በአፈጻጸም ሂደት የተመላከቱ ክፍተቶችንና ተግዳሮቶችን ከቢሮው ጋር በመቀናጀት በሚሰራው ስራ አስተዳደሩ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚከታተል ተናግረዋል፡፡ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ህዳር 28/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+8

The special leadership training program for Senior Managers of Technical and Vocational education in East Africa currently ta
+6
The special leadership training program for Senior Managers of Technical and Vocational education in East Africa currently taking place in Guangzhou, China has so far covered a number of topics including TVET governance and quality assurance, change management, greening #TVET, industry collaborations, innovation and sustainable financing, experience sharing, among others. #Skills4Transformation

Repost from N/a
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እና የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ በዩኒቨርሲቲ፣ ቴሙትስና ኢንዱስትሪ ትስስር ጽንሰ ሃሳብን መሰረት ያደረገ ሁሉ-አቀፍ ቅንጅት/በጋራ ለመስራት የሚያስችል የጋራ መግባቢያ ሰነድ ተፈራረሙ:: ተቋማቱ ከዚህ ቀደም በዘርፉ የሚታዩ ችግሮችን ለመቅረፍ በተናጠል ብዙ ስራዎችን ለመስራት መሞከራቸውን ገልፀው ይህ ግን መርሀ-ግብር ከማሟላት በዘለለ በሚፈለገው ልክ ውጤት እንዳላስገኘላቸውም ገልፀዋል:: ይሁንና በዚህ አመት ሁለቱ ተቋማት በቅንጅት ሊያሰራቸው የሚችል የጋራ የስምምነት ሰነድ በማዘጋጀት እንዲሁም የሚታዩ ችግሮችን ከስር መስረታቸው በትክክል ለይቶ በማስቀመጥ ውጤታማ በሚያደርጋቸው ተግባራቶች ላይ እንደሚያተኩሩና እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል:: በተጨማሪም በኢንዱስትሪዎች ላይ ከመለዋወጫ ግብአት አንስቶ የተለያዩ የሚታዩ ችግሮች ያሉ በመሆናቸው እነዚህ ላይም ከተናጠል ይልቅ በቅንጅት ቢሰራባቸው ለችግሮቹ የመፍትሄ አካል መሆን እንደሚቻልም መግባባት ላይ የተደረሰ ሲሆን በአጠቃላይ በሰ/ኃ/ልማት፣ በቴ/ጂ ሽግግር፣ በጥናትና ምርምር... ወዘተ ትኩረት የሚደረግ መሆኑም ተገልጿል። በቀጣይ ከሁለቱ ተቋማት የተወጣጣ ቴክኒካል ቡድን ተቋቁሞ በስምምነቱ መሰረት ስራዎች በተቀመጠላቸው ጊዜ እና በሚፈለገው ደረጃ እንዲተገበሩ ክትትልና ድጋፍ የሚያደርግም ይሆናል:: ኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን ህዳር 27/2016 ዓ.ም

Repost from N/a
photo content
+2

የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎት እና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ከ2016 ዓ.ም. እስከ 2018 ዓ.ም የሚተገበር ከትኩረት ዘርፍ መሪ መ/ቤቶች እና ከልማት ፕሮግራም ፈፃሚ አካላት ጋር የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ(Memorandum of Agreement) ተፈራረመ፤  የፊርማ ሥነ ስርዓቱን ያካሄዱት የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎት እና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸውና በአስተዳደሩ የሚገኙ የትኩረት ዘርፍ መሪ መ/ቤቶች እና ከልማት ፕሮግራም ፈፃሚ ድርጅቶች ኃላፊዎችና ተወካዮች ናቸው:: ስምምነቱ በአስተዳድራችንና በልማት ቀጠናው በየዘርፉ የተቀመጡ ግቦችን ለማሳካት ብቃቱ የተረጋገጠ የሰው ሃይልና ምርጥ ቴክኖሎጂ የሚቀርብበትን ዘዴ በማመቻቸት በኢኮኖሚውም ረገድ፣ እንደ አገር ና እንደ አስተዳደር ተወዳዳሪ ሆኖ ለመዝለቅና በባለድርሻ አካላትንና የዘርፍ መሪ መስሪያ ቤቶች ንቁ ተሳትፎና ቅንጅታዊ አሰራር  ማረጋገጥ ሲሆን በቢሮው እና በተቋማቱ መካከል ትስስር በመፍጠር ምቹ ግንኙነት እንዲኖር ማድረግ ላይ ያተኮረ ነው፡፡ በዚህም የጋራ ዕቅድ ባለቤትና ከፍተኛ አመራር ሰጭ ዓብይ ኮሚቴ የተደራጀ ሲሆን ኦፐሬሽናል ኮሚቴ በማደራጀት የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ማስተዋወቅ፤ በኢንዱስትሪው ፍላጎት መሰረት በየሙያ ደረጃው ብቁ ሙያተኛ ማፍራት እና  ከስራ ጋር በማስተሳሰር የኢንዱስትሪውን የምርት እና የስራ ላይ ስልጠና ፍላጎትን ማሟላትና የስልጠናውን ጥራት የሚያስጠብቅ የትብብር ስልጠናን ተግባራዊ በማድረግ የተሟላ የቴክኖሎጂ ሽግግርና የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ማቅረብ በቀጣይ በትኩረት ተሰጥቶት የሚተገበር ይሆናል፡፡ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ህዳር 27/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+9

photo content
+9

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ  በዘንድሮ የትምህርትና ስልጠና ዘመን የተቀበላቸውን አዲስ ገቢ ሰልጣኝ ተማሪዎች ወደ መደበኛ ስልጠና ከመግባታቸው አስቀድሞ ሰልጣኞችን በሁሉም ረገድ ዝግጁ የሚያደርጋቸውን የLife Skill ስልጠና በዛሬው እለት መስጠት ጀመረ።  በስልጠናው ሰልጣኝ ተማሪዎቹ ከ Life skill ስልጠናው በተጨማሪም ስለ ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ፖሊሲና እስትራቴጂ እንዲሁም በዘርፉ ስለሚሰጡ የሙያ መስኮች ሰፉ ያለ ማብራርያ የሚሰጣቸው መሆኑም ተገልጿል:: በዚህም ሰልጣኝ ተማሪዎቹ ሰለ ቴ/ሙ/ት/ስ ዘርፍ እንዲሁ እሁን ላይ ያለውን የገበያ ፍላጎት በጥልቅ ከተረዱና ግንዛቤውን ካገኙ በኃላ ለመሰልጠን የወሰኑትን የሙያ መስክ ምርጫቸውን ለማስተካከል በእጅጉ እንደሚረዳቸውም ይትመናል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን ህዳር 24/2016 ዓ.ም

የድሬዳዋ አስተዳደር የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ "ብቃት" የወጣቶች ስራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም ለወጣቶች በተከታታይ ስድስት ዙር ሲደረግ የነበረው የአቻ ለአቻ ውይይት ተጠናቀቀ፤ ወጣቶቹ በየወ
+9
የድሬዳዋ አስተዳደር የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ "ብቃት" የወጣቶች ስራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም ለወጣቶች በተከታታይ ስድስት ዙር ሲደረግ የነበረው የአቻ ለአቻ ውይይት ተጠናቀቀ፤      ወጣቶቹ  በየወሩ የአቻ ለአቻ  ውይይት  በማድረግ  በየጊዜው ያገኙትን እውቀት  የገጠማቸውን ችግሮች  ለይተው የተወያዩበት መድረክ  ሲሆን ይህ  ለስድስተኛ ጊዜ የተዘጋጀ እና የመጨረሻው  ውይይት የተደረገ ሲሆን የስራ ላይ ልምምዱን ሲያጠናቅቁ  በተቀጠሩበት ወይም በሚቀጠሩበት ድርጅቶች በሰለጠኑት ሞያ መሰረት የሚያገለግሉ ይሆናል፡፡      በአስተዳደሩ ከ1700 በላይ ሰልጣኞች ተመዝግበው 1500 በላይ የሚሆኑት የ10 ቀን የህይወት ክህሎት ሰልጠና ወስደው 972 የሚሆኑ ወጣቶች ተግባራዊ የሥራ ላይ ልምምድን የተቀላቀሉ ሲሆን በተለያዩ በአስተዳደሩ የሚገኙ ኢንደስትሪዎች ላይ ስድስት ወራት የሚፈጀውን ውጤታማ ቆይታ እያደረጉ ሲገኝ ከዚሁ ጎን ለጎን የአቻ ለአቻ ውይይቶችን በየወሩ ሲወያዩ ቆይተዋል፡፡      በዚህም ውይይት ላይ ተሳታፊ የሆኑ ወጣቶች በአጠቃላይ በፕሮግራሙ ተጠቃሚነታቸው በአመለካከት፣ በክህሎት እንዲሁም በዕውቀት ከዚህ በፊት ከነበሩበት የተሻለ ነገሮችን የመረዳትና የማድረግ አቅም ማዳበራቸውን የተናገሩ ሲሆን በተለይ እርስ በዕርስ በመነጋገር ችግሮችን የፈቱበትና የተሻለ ዕውቀት የቀሰሙበት እንደነበር ተናግረዋል፡፡ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ህዳር 22/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

ጠቃሚ ሀገር በቀል እውቀቶችና ክህሎቶች ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫና የውይይት መድረክ ተካሄደ። በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የኢን
+8
ጠቃሚ ሀገር በቀል እውቀቶችና ክህሎቶች ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫና የውይይት መድረክ ተካሄደ።       በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የኢንዱሰትሪ ኤክስቴንሽንና የቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት ጠቃሚ ሀገር በቀል እውቀቶችና ክህሎቶች ዙሪያ ግንዛቤ መፍጠር የሚያስችል መድረክ ለአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህራንና ተማሪዎች ጋር አዘጋጀ።      በግንዛቤ ማስጨበጫና በውይይት መድረኩ ላይ የተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች የተነሱ ሲሆኑ ሀገርበቀል እውቀቶችንና ክህሎቶችን  በትምህርት ቤቶች ውስጥ ተማሪዎች እያዳበሩ የሚያድጉበት አመቺ ሁኔታ ማመቻቸት ላይ በተለይ በአዲሱ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ፖሊሲና ስትራቴጂ ላይ በተመላከተው መሰረት ለሀገርበቀል እውቀቶችንና ክህሎቶችን ማልማት ትኩረት መሰጠቱ ትልቅ አቅም መሆኑም ተገልጿል። የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ህዳር 22/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

ህገወጥ የሰዎች ዝውውርን የመከላከል ስራ ላይ የትምህርት ቤቶችን ተሳትፎ ማሳደግ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ ተገለጸ፤ የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የውጪ አገር ስራ ስምሪት
+8
ህገወጥ የሰዎች ዝውውርን የመከላከል ስራ ላይ የትምህርት ቤቶችን ተሳትፎ ማሳደግ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ ተገለጸ፤ የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የውጪ አገር ስራ ስምሪትና የሰራተኞች ደህንነት ጥበቃ ዳይሬክቶሬት በተለያዩ አዋጆች ዙሪያ ለአስተዳደሩ የመንግስት አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መምህራን የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሄደ። በመድረኩም ተሳታፊ ለሆኑ መምህራን በሰዎች መነገድ፣ ሰዎችን በህገወጥ መንገድ ድንበር ማሻገር እና ለስራ ወደ ውጭ ሀገር መላክ ወንጀል አዋጅ ቁጥር 1178/2012 እና ህጋዊ የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት አዋጅ ቁጥር 1246/2013 ላይ ግንዛቤ ተፈጥሮላቸዋል። በዚህም አዋጆቹን በመረዳት በሰዎች የመነገድ፣ በህገወጥ መንገድ ድንበር ማሻገር እና በህገወጥ መንገድ ለስራ ወደውጭ ሀገር መላክ ወንጀልን በመከላከል ረገድ የመምህራኑን ግንዛቤ ማሳደግ ዓላማው አድርጎ ከዚህ ጎን ለጎን ህጋዊው የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት አካሄድ ላይ ግንዛቤ መፍጠር ተችሏል። በማጠቃለያውም ከዚህ በፊት ከትምህርት ቤቶቹ ርዕሰ መምህራን ጋር በነበረ መድረክ ክበቦችን ለማቋቋም በተደረሰው ስምምነት መሰረት እየተሰሩ ባሉ ስራዎች ላይ ውይይት የተደረገ ሲሆን በአስተዳደሩ የሚገኙ ትምህርት ቤቶችን ከቢሮው ጋር በማቀናጀት ስራዎችን አጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባ በቢሮው የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ መሐመድ ኢብራሂም አሳስበዋል። የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ህዳር 22/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ