ru
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Открыть в Telegram
1 091
Подписчики
+324 часа
+257 дней
+1730 день
Архив постов
በድሬዳዋ አስተዳደር የድሬዳዋ ደወሌ ምድር ባቡር የባለሞያዎች ልኡክ ቡድን በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የመስክ የስራ ጉብኝት አደረጉ፡፡ በመስክ ጉብኝቱ ላይ በመገኘት የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር
+7
በድሬዳዋ አስተዳደር የድሬዳዋ ደወሌ ምድር ባቡር የባለሞያዎች ልኡክ ቡድን በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የመስክ የስራ ጉብኝት አደረጉ፡፡ በመስክ ጉብኝቱ ላይ በመገኘት የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ም/ዲን አቶ ሰልሃዲን አብዱልሃሚድ ሲሆኑ በንግግራቸውም እንኳን ወደ ምስራቅ አፍሪካ የልህቀት ማእከል ወደ ሆነው የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በደህና መጣችሁ፡፡ ኮሌጁ ከተመሰረተበት ጊዜ አንስቶ ብዙ ሺህ ወጣቶች የሙያና የክህሎት ባለቤት ያደረገ ኮሌጅ ነው ኮሌጁ አሁን ለደረሰበት ስኬትም የከተማ አስተዳደሩ እንዲሁም የኮሌጁ ማህበረሰቦችና ባለድርሻ አካላቶች የማይተካ ሚና አላቸው ያሉ ሲሆን ኮሌጁ በቀጣ የባቡር ምህንድስና የልህቀት ማእከል እንደመሆኑ መጠን ከድሬዳዋ ደወሌ ምድር ባቡር ተቋም ጋር በርከት ያሉ ስራዎችን በጋራ የምንሰራ ይሆናል ብለዋል፡፡አጠቃላይ ኮሌጁ በትምህርትና ስልጠና እንዲሁም ከስራ ፈጣሪነትና ለኮሌጁ ተጨማሪ ገቢን ከማፈላለግ አንጻር የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከሌሎች አቻ ኮሌጆች አንጻር የተሸለ አፈጻጸም እንዳለው ያብራሩ ሲሆን በቀጣይም የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከድሬዳዋ ደወሌ ምድር ባቡር ጋር መምህራንን ከማብቃት እንዲሁም ኮሌጁ ላይ ያለውን እምቅ አቅም ከመጠቀም አንጻር ሁለቱም ተቋማት አብረው በጋራ መስራት ይኖርባቸዋል ለዚህም ደግሞ ኮሌጁ ቁርጠኛ ነው ብለዋል፡፡ በመስክ ጉብኝቱ ወቅት የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የEASTRIP ፕሮጀክት እስካሁን የደረሰበት የፕሮጀክት አፈጻጸም ሪፖርት በአቶ መሳይ ጥላሁን የቀረበ ሲሆን በመቀጠልም በኮሌጁ የተለያዩ የትምህርት ክፍሎች ጉብኝት ተደርጓል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ጥቅምት 9/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት ከአራቱ የድጋፍ ማእቀፍ አንዱ የሆነውን የኢንተርፕሩነርሽፕ ስልጠና እየሰጠ ነው። ቢሮው በተያዘው የበጀት አመት ከሚያከናውናቸው ተግባራት መካከል አንዱ የአቅም ግንባታ ስልጠና መስጠት ነው። ይህን መሰረት በማድረግ ለመንግስት ፖሊ ቴክኒክና ለግል ኮሌጅ አሰልጣኝ መምህራኖች Business planning skills( የንግድ እቅድ ክህሎት እና Entrepreneural Culture(የስራ ፈጣራ ባህል ክህሎት ግንባታ) ላይ እየወሰዱ ይገኛል፡፡ በስልጠናው  ላይ ንግግር ያደረጉት የዳይሬክቶሬቱ ባለሙያ የሆኑት ወ/ሮ ውልታ ትልቅሰው ለመንግስት ፖሊ ቴክኒክና ለግል ኮሌጅ አሰልጣኝ መምህራኖች የኢንተርፕርነር ሺፕ ስልጠና መሰጠቱ ስራዎችን በተለይም የሚሰጡ ድጋፎችን በዕውቀትና በክህሎት ለመስራት  የሚያስችል እንደሆነ ገልጸዋል ። የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጥቅምት 8/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+6

የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት የበጀት ኢኮኖሚ ንግድና ኢንዱስትሪ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የመስክ ምልከታውን ማድረግ ጀመረ በዛሬው እለት መካሄድ በተጀመረው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴዎች የመደበኛ የመስክ ምልከታ የምክር ቤቱ የበጀት፣ ኢኮኖሚ፣ ንግድና ኢንዱስትሪ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በድሬዳዋ አስተዳደር የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ በመገኘት የመጀመሪያ ቀን መደበኛ የመስክ ምልከታውን ያካሄደ ሲሆን በተቋሙ የ2016 በጀት አመት የ1ኛ ሩብ አመት የዝግጅት ምእራፍ ስራዎች የሚገኙበትን ሁኔታ የተመለከተ ሲሆን የተቋሙን የ1ኛ ሩብ አመት የስራ አፈጻጸም ያለበትን ደረጃ በቢሮው አመራሮች በዝርዝር ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል ፡፡ በመሆኑም የተቋሙ የ2016 በጀት አመት እቅድ ተዘጋጅቶ እስከ ግለሰብ መውረዱንና የእቅድ ኦረንቴሽን ለተቋሙ ሰራተኞችና ለሁሉም ባለድርሻ አካላት መሰጠቱን ፣ የአቅመ ደካማ ቤቶችን ግንባታ ፣ የበጎ አድራጎት ስራዎች ፣ የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ ፣ የማእድ ማጋራት ስራዎች የተከናወኑ ሲሆን የስራ እድል ፈጠራ በተመለከተ በዝግጅት ምዕራፍ የግንዛቤ ማስጨበጫ እና የስልጠና መድረኮች መካሄዳቸውን፣ የስራ አጥ ልየታና ምዝገባን አውቶሜት የማድረግ ስራዎች የተከናወኑ ሲሆን በተቋሙ በ2016ዓ/ም የተያዙ ካፒታል ፕሮ ጀክቶች በዝግጅት ምዕራፍ ስራዎች እየተከናወኑ ሲሆን የካፒታል ፕሮጀክቶች ፈጥነው ወደ ትግበራ እንዲገቡ በወቅቱ በጀት መለቀቅ እንዳለበት እና አንዳንድ በቢሮው መሟላት የሚገባቸው ግብአት እንዲሟላላቸው ከሚመለከተው አካል መስራት እንዳለባቸው ገልጸዋል፡፡ በመጨረሻም የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ የተከበሩ ወ/ሮ አይናለም ተዘራ ባደረጉት ንግግር የተቋሙ የ1ኛ ሩብ አመት የዝግጅት ምዕራፍ እና የሪፎርም ስራዎች የስራ አፈጻጸም በጥሩ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ገልጸው የገጠርና የከተማ የስራ እድል ፈጠራ በቅንጅት መሰራት እንደሚገባው ፣ የወጣቶች ስልጠና ከቀበሌዎች ጋር በተቀናጀ መልኩ እንዲቀጥል እንዲሁም ተቋሙ ከሌሎች ተቋማት ጋር የሚያካሂደው የድጋፍና ክትትል ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ አቅጣጫ ሰጥተዋል፡፡ በአዲሱ ካሳ ጥቅምት 8/2016 ዓ.ም

photo content
+7

የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት በኦፊስ ካይዘን ትግበራ ዙሪያ ለቢሮው ሰራ
+9
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት በኦፊስ ካይዘን ትግበራ ዙሪያ ለቢሮው ሰራተኞች ስልጠና አዘጋጀ። በዚህም ስልጠናውን ከአስተዳደሩ የካይዘን ኢንስቲትዩት በመጡ ባለሙያዎች የተሰጠ ሲሆን በቀጣይም በቢሮው የሚገኙ ዳይሬክቶሬቶችና ክፍሎች በቀጥታ ወደ ትግበራ ከዛሬ ጀምሮ የሚገቡ ይሆናል። ቢሮው ለሪፎርም ስራዎች ትኩረት ሰጥቶ ሲሰራ መቆየቱ የሚታወቅ ሲሆን እነዚህም ስራዎች የሆነ ጊዜ ብቻ ተግባር አለመሆኑ በሚያሳይ መልኩ የዚህ ትግበራ አካል የሆነው ኦፊስ ካይዘንን በሁሉም የቢሮው ዳይሬክቶሬቶችና ክፍሎች ላይ ተግባራዊ ማድረግ በተለየ መልኩ ቦታ ተሰጥቶታል። በመሆኑም መጀመር ብቻ ሳይሆን ማዝለቅ እንደሚገባና ጥሩ አፈጻጸም የሚያስመዘገቡ ዳይሬክቶሬቶች፣ ክፍሎችና ሰራተኞችን ቢሮው እንደሚያበረታ በቢሮው የውጪ አገር ስራ ስምሪትና የሰራተኞች ደህንነት ጥበቃ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ መሀመድ ኢብራሂም ተናግረዋል፡፡ የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጥቅምት 6/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

በድሬደዋ አስተዳደር ከተለያዩ ቢሮዎችና ከሚመለከታቸው አካላት የተወጣጣ የሱፐርቪዥን ቡድን የድሬዳዋ እና የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጆችን የ2016 በጀት የመጀመሪያ ሩብ አመት የእቅድ አፈጻጸም ገ
+6
በድሬደዋ አስተዳደር ከተለያዩ ቢሮዎችና ከሚመለከታቸው አካላት የተወጣጣ የሱፐርቪዥን ቡድን የድሬዳዋ እና የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጆችን የ2016 በጀት የመጀመሪያ ሩብ አመት የእቅድ አፈጻጸም ገመገመ፤ የድሬዳዋ እና የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጆች የ2016 በጀት አመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ሪፖርት ቀርቦም ሰፊ ውይይት ተካሂዶበታል። በመጨረሻም የሱፐርቪዥን ቡድን አባላቱ የቀረበው ሪፖርት አቀራረቡንና የተከናወኑ ስራዎችን አድንቀው በቀጣይ ሊተኮርባቸውና ሊስተካከሉ የሚገባቸውን ጉዳዮች ሀሳብና አስተያየቶች አክለው አቅጣጫ ሰጥተዋል። የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጥቅምት 6/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content

"የሰንደቅ ዓላማችን ከፍታ ለሕብረ-ብሔራዊ አንድነታችንና ለሉዓላዊነታችን ዋስትና ነው" በሚል መሪ ቃል የሰንደቅ ዓላማ ቀን ተከበረ፡፡ በዓሉንም የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢ
+9
"የሰንደቅ ዓላማችን ከፍታ ለሕብረ-ብሔራዊ አንድነታችንና ለሉዓላዊነታችን ዋስትና ነው" በሚል መሪ ቃል የሰንደቅ ዓላማ ቀን ተከበረ፡፡ በዓሉንም የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ እና በስሩ የሚገኙ የድሬዳዋ እንዲሁም የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አመራሮችና ሰራተኞች በፓናል ውይይት አክብረዋል፡፡ ከመድረኩም ማጠናቀቂያ በአንድነት ለሰንደቅ ዓላማ  ክብር በሰጠና የህብረ-ብሄራዊነታችን መገለጫ እንዲሁም የብሔር ብሔረሰቦች የብሩህ ተስፋ ምልክት መሆኑን በሚያሳይ በኢትዮጵያ ህዝብ መዝሙር የታጀበ የባንዲራ መስቀል ስነ-ሥርዓት ተካሂዷል፡፡ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጥቅምት 5/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content

ከSIFA ፕሮጀክት ማስተባበሪያ ጽ/ቤት እንዲሁም ከዋናው የ SIFA ፕሮጀክት ጽ/ቤት የተውጣጡ የSIFA ተወካዮችና የስራ ሀላፊዎች በድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የፕሮጀክት አፈጻጸም ግምገማና እና የእቃ ግዢ አካሄዶች ላይ ውይይት ተካሄደ፡፡ በግምገማ ሂደቱ ላይ በመገኘት የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ም/ ዲን አቶ ሰልሃዲን አብዱልሃሚድ እንዳብራሩት እንኳን ወደ በረሀዋ ንግስትና የፍቅር ከተማ ወደ ሆነችው ድሬዳዋ ከተማ በደህና መጣችሁ ፡፡ ይህ በጀርምን መንግስት ድጋፍ የሚተገበረው የSIFA ፕሮጀክት ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ሲደረግ እንደ ሀገር የሚጠቅመው ጥቅም የላቀና ብዙ ወጣቶችን የክህሎት፣የስራ ባለቤት እንዲሁም የስራ ፈጣሪ የሚያደርግ እንደሆነ እና ከተማችንን ደግሞ ዲጂታል አሰራሮች ያሉባት ምርጥና ሳቢ ለማድረግ ለሚደረገው ጥረት ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው እተማመናለሁ፡፡ ኮሌጃችን አሁን ያለውን አሰራር ወደ ዲጅታል ለመቀየር በሚያደርገው ስራ ላይ ይህ ፕጀክት በኮሌጃችን በመጀመሩ እጅግ የላቀ ስራ ለኮሌጃችን ፣ለከተማችን ብሎም ለሃገራችን ኢትዮጵያ ማበርከት እንደንችል ያግዘናል፡፡በተጨማሪም በኮሌጁ እየተተገበረ ያለው ይህ የSIFA ፕሮጀክት መሳካት የከተማችን አስተዳደር እንዲሁም የአስተዳደሩ የስራና ክህሎት ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ፕጀክቱ ከግብ እንዲደርስ ማቺንግ ፈንድ በመመደብ ለሌሎች ከተሞች አርአያ የሆነ ተግባር ፈጽመዋል ይህም ፕሮጀክቱ ከግብ እንዲደርስ በቁርጠኝነት እንደሚሰራ ማሳያ ነው፡፡ በተጨማሪም የኮሌጁ ማኔጅመንት ቁርጠኛ ሆኖ ለሚያጋጥሙ ችግሮች ሁሉ ፈጣን ምላሽ በመስጠት ፕሮጀክቱ ከግብ እንዲደርስ በቁርጠኝነት እንደሚሰራ ገልጸዋል፡፡ በግምገማ ሂደቱ ወቅት የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የSIFA ፕሮጀክት የእቃ ግዢ ሂደቱ እንዲሁም እስካሁን የደረሰበት የፕሮጀክት አፈጻጸም ሪፖርት ቀርቦ ውይይት የተደረገ ሲሆን በግዢ ሂደቱ እና በአቅም ግንባታ እንዲሁም በህንጻ ግንባታው ሂደት ከSIFA ፕሮጀክት ማስተባበሪያ ጽ/ቤት እንዲሁም ከዋናው የ SIFA ፕሮጀክት ጽ/ቤት የመጣው ልኡክ ቡድን ከኮሌጁ አመራሮች እና ከፕሮጀክት ማስፈፀሚያ ዩኒት ጋር ውይይት ከተደረገ በኃላ በቀጣይ የእቃ ግዚው፣የመምህራን የአቅም ግንባታውና የልህቀት ማእከሉ የህንጻ ግንባታ ለማስጀመር ከስምምነት ላይ በመድረስ የግምገማ ሂደቱ ተጠናቋል፡፡ የ SIFA ፕሮጀክት በኢትዮጵያ በሚገኙ ሁለት ኮሌጆች የሚተገበር ሲሆን በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የICT የልህቀት ማእከል እንዲሁም በሚዛን ቴፒ ኮሌጅ ደግሞ የግብርና የልህቀት ማእከልነት የሚተገበር ፕሮጀክት ነው፡፡ፕሮጀክቱ በዋናነት የእቃ ግዢ፣የመምህራን የአቅም ግንባታ እንዲሁም የህንጻ ግንባታን ያካትታል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ጥቅምት 3/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

‹‹የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የምስራቅ አፍሪካ ተማሪዎችን በመቀበል እና አሰልጥኖ በማብቃት ለቀጠናው ትስስር ከፍተኛውን ሚና እየተጫወተ ይገኛል።›› አቶ ሰልሃዲን አብዱልሃሚድ የኮሌጁ ም/ዲን እና የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ኃላፊ **** የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከሶማሊያ የመጡ 18 አልጣኞችን በኤሌክትሪክ ኢንስታሌሽንና በፋሽን ዲዛይን የሰለጠኑ ሰልጣኞችን በዛሬው እለት አስመረቀ፡፡ በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት እና ለሰልጣኞች ሰርተፊኬት የሰጡት የኮሌጁ ም/ዲንና የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ኃላፊ አቶ ሰልሃዲን አብዱልሃሚድ ትምህርት እና ስልጠና ለአንድ ሀገር ኢኮኖሚያዊ ፖለቲካዊ እና ማህበራዊ እድገት ቁልፍ መሳሪያ ነው። ይህን መሳርያ ደግሞ ለከተማችን ወጣቶች ብቻ ሳይሆን ለምስራቅ አፍሪካ ወጣቶችም ማድረስ ይኖርብናል፡፡ለዚህም በዛሬው እለት በኤሌክትሪክ ኢንስታሌሽንና በፋሽን ዲዛይን ለ2 ወር ያክ ስልጠናቸውን የተከታተሉ የሶማሊያ ዜግነት ያላቸው ወጣቶች አንዱ ማሳያው ናቸው ብለዋል፡፡ የኮሌጁ ም/ዲን በማስቀጠል የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የምስራቅ አፍሪካ ተማሪዎችን በመቀበል እና አሰልጥኖ በማብቃት ለቀጠናው ትስስር ከፍተኛውን ሚና እየተጫወተ ይገኛል።በቀጣይም ከሌሎች የምስራቅ አፍሪካ ሀገሮች የተለያዩ ሰልጣኞችን በመቀበል የምስራቅ አፍሪካን በትምህርትና ስልጠናው የማዋሃድ ስራን የሚሰራ ይሆናል፡፡ለዛሬ የምርቃት ቀን የደረሳችሁ ሰልጣኖች ለድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ አባሳደር ናችሁ እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል፡፡ በመቀጠልም ንግግር ያደረጉት የEASTRIP የኢንዱስትሪ ላይዘን ከፍተኛ ባለሙያ የሆኑት መሀመድአወል ጠሃ ሲሆኑ ድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከጎረቤት ሀገራት ሶማሌላንድ፣ ጅቡቲ፣ከኬንያ፣ከታንዛንያ እንዲሁም ከሌሎች የምስራቅ አፍሪካ ሃገራት ጋር በትምህርትና ስልጠና ለማዋሃድ በንቃት ሲሰራ መቆየቱ የሚታወስ ነው ያሉ ሲሆን አያይዘውም በዛሬው እለት ስልጠናችሁን አጠናቃችሁ ለምርቃት የበቃችሁ የሶማሊያ ሰልጣኝ ተማሪዎች ለዚህ ውህደት ማሳያ ናችሁ ብለዋል፡፡ከዚህ ኮሌጅ ስልጠናችሁን ጨርሳችሁ ወደ ሀገራችሁ ስትሄዱ በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ያገኛችሁትን ስልጠና ሌሎች ወጣቶች እንዲያገኙ የአባሳደርነት ሚናችሁን እንድትወጡ አደራ እላለሁ ብለዋል፡፡ በመጨረሻም ንግግር ያደረጉት የEASTRIP M&E የሆኑት አቶ መሳይ ጥላሁን ሲሆኑ በንግግራቸውም ድሬዳዋን እንደ ሁለተኛው ሀገራችሁ በመቁጠር የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅን ደሞ እንደ ምርጥ ኮሌጅ በመምረጥ ስልጠናችሁን ያለምንም እንከን ስላጠናቀቃችሁ እንኳን ደስ አላችሁ ያሉ ሲሆን በመጨረሻም ለዚህ ስልጠና መሳካት ትልቁን ሚና ለተወጣችሁ አካላቶች ምስጋና ማቅረብ እወዳሉ ብለዋል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ጥቅምት 3/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም መረጃዎችን ወደ ዲጂታል መቀየር ላይ በኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ እየተሰሩ የሚገኙ ስራዎች ተገመገመ። በኮሌጁ ውስጥ ከዚህ ቀደም ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም መረጃዎችን ከመያዝ ጋር
+7
ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም መረጃዎችን ወደ ዲጂታል መቀየር ላይ በኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ እየተሰሩ የሚገኙ ስራዎች ተገመገመ። በኮሌጁ ውስጥ ከዚህ ቀደም ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም መረጃዎችን ከመያዝ ጋር ተያይዞ የነበሩ ክፍተቶችን የነበሩ ሲሆን ነገር ግን ባለፍት አመታት በተሰሩ ዘርፈ-ብዙ ስራዎች መረጃዎችን በቴክኖሎጂ በመታገዝ ዲጂታላይዜሽን የማድረጉ ስራ በአካዳሚክና በአስተዳደር ዘርፉ በስፋት እየተሰራ ይገኛል ። የኢ.ፌ.ድ.ሪ የስራና ክህሎት ሚኒስቴር የመንግስት ቴክኒክና ሞያ ስልጠና ተቋማትን መረጃዎች ወደ ዲጂታል ለመቀየር ይቻል ዘንድ የመንግስት የቴክኒክና ሞያ ስልጠና ተቋማትና የክልል የብቃት ማረጋገጥ ኤጀንሲ ሀላፊና ባለሞያች ተሳታፊ የሆኑበት የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ መካሄዱ ይታወሳል። በአስተዳደራችን ላይ ያሉ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጆች እና የመንግስት ተቋማት ኮሌጆች ላይ ያሉ መረጃዎችን ወደ ዲጂታል በመቀየር ከዚህ ቀደም ከመረጃ አያያዝ ጋር ተያይዞ ይስተዋሉ የነበሩትን ክፍተቶች ማሻሻል ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ እንደሚገኝ የሰልጣኝ ልማትና ተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት የሆኑት አቶ ጀማል አደም ገልጸዋል። የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጥቅምት 2/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

የሰንደቅ ዓላማ ቀን የፊታችን ሰኞ ጥቅምት 5 ቀን 2016 ዓ.ም እንደሚከበር የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አስታውቋል፡፡ ቀኑ “የሰንደቅ ዓላማችን ከፍታ ለሕብረ-ብሔራዊ አንድነታችንና ለሉዓላዊነታችን
የሰንደቅ ዓላማ ቀን የፊታችን ሰኞ ጥቅምት 5 ቀን 2016 ዓ.ም እንደሚከበር የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አስታውቋል፡፡ ቀኑ “የሰንደቅ  ዓላማችን ከፍታ ለሕብረ-ብሔራዊ አንድነታችንና ለሉዓላዊነታችን ዋስትና ነው” በሚል መሪ ሃሳብ ለ16ኛ ጊዜ ነው የሚከበረው፡፡ ሀገራዊ ወቅታዊ ሁኔታን በዋጀ መልኩ ከሰንደቅ ዓላማ መርሆች ጋር ተገናዝቦና ሀገራዊ ሪፎርሙን በሚያስቀጥሉ ውይይቶች ታጅቦ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መሪነት በመላ ሀገሪቷ እንደሚከበር ተጠቁሟል፡፡ የበዓሉ መከበር ለሕብረ-ብሔራዊ አንድነት እና ለሉዓላዊነት መጠናከር መነቃቃትን ለመፍጠር ትልቅ ትርጉም እንደሚኖረው ተጠቅሷል፡፡ ለሀገር ክብር እና ጥቅም ሁላችንም የበኩላችንን ለመወጣት እኛ የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ እንዲሁም ሁለቱ የመንግስት ኮሌጅ አመራሮችና ሠራተኞች  በኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ቅጥር  ግቢ  ዉስጥ በሰንደቅ ዓላማ ፊት ዳግም ቃላችንን የምናድስበት ዕለት ይሆናል ::

photo content

photo content

photo content

የድሬዳዋ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሀብት ልማት ቢሮን ጨምሮ የሚመለከታቸው ሌሎች አካላትን ያካተተ በአስተዳደሩ የሚገኙ የመንግስት ተቋማት በ2016 በጀት አመት የዝግጅት ምዕራፍ ያከናወኗ
+5
የድሬዳዋ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሀብት ልማት ቢሮን ጨምሮ የሚመለከታቸው ሌሎች አካላትን ያካተተ በአስተዳደሩ የሚገኙ የመንግስት ተቋማት በ2016 በጀት አመት የዝግጅት ምዕራፍ ያከናወኗቸውን ተግባራት እንዲሁም አጠቃላይ የአገልግሎት አሰጣጣቸው ያለበትን ነባራዊ ለመገምገም ያለመ ድጋፋዊ ሱፐርቪዥን በማድረግላይ የሚገኝ ሲሆን በዛሬው ዕለትም የሱፐርቪዥን ቡድኑ በሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ በመገኘት ድጋፋዊ ሱፐርቪዥን አድርገዋል። የሱፐርቪዥን ቡድን አባላቱም በሩብ አመቱ በቢሮው ያለውን የዝግጅት ምዕራፍ ዕቅድ አፈፃፀም በዝርዝር የተመለከቱ ሲሆን በአፈፃፀም የታዩ ጥንካሬዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ እና የታዩ ክፍተቶችም በቀጣይ ሊስተካከሉ በሚችሉበት አግባብ አስፈላጊውን ድጋፍ የሚያደርጉ መሆኑንም ነው የገለፁት። ጥቅምት 1/2016 ዓ.ም