cookie

Мы используем файлы cookie для улучшения сервиса. Нажав кнопку «Принять все», вы соглашаетесь с использованием cookies.

avatar

ጋርባዶና አካባቢው የሱና ቻናል

✅ደረጃችን ከፍ ሚለው ለአላህ ባለን ፍራቻ በተውሂዳችን ልክ ነው👉👇 🌲🌲🌲إن رحمة الله قريب من المحسنين🌹🌹🌹

Больше
Рекламные посты
198
Подписчики
Нет данных24 часа
Нет данных7 дней
Нет данных30 дней

Загрузка данных...

Прирост подписчиков

Загрузка данных...

⭐️ ከኢማሙ አሕመድ ህይወት ነፀብራቅ ክፍል አንድ ኢማሙ አሕመድ ኢብኑ ሙሐመድ ኢብኑ ሐንበል ( አቡ ዐብዲላህ ) ከአራቱ አኢማዎች አንዱ የሆነው ሲሆን ከሕይወቱ ነፀብራቅ ቀንጨብ እናድርግ ። ኢማሙ አሕመድ ኢማሙ አህሉ አስ–ሱናህ በመባል ይታወቃል ። አባቱ አንዳንዶች በእናቱ ሆድ እያለ ነው የመተው ይላሉ ከፊሎች በተወለደ በሶስት አመቱ ነው ይላሉ ። ሁሉም በእናቱ እጅ ማደጉ ላይ ይስማማሉ ። ኢማሙ አሕመድ የቲም ሆኖ ነበር ያደገው ። የተወለደው 164 እንደ ሂጅሪያ አቆጣጠር ሲሆን ቁርኣንን በ11ኛው አመቱ አካባቢ ነበር የሐፈዘው ። በመቀጠል የዐረብኛ ቋንቋ ጥናት አስከትሎ ወደ ሸሪዓ እውቀት ፍለጋ በ15ኛ አመቱ 179ኛ አመተ ሂጅሪያ ወጣ ። ይህ አመት ኢማሙ ማሊክ የሞቱበት አመት ነበር ። ወደ አንቱታ ተሸጋገርን ። ለእውቀት ራሳቸውን አግልለው ሐዲስ ፣ ፍቅህ ፣ ተፍሲር እና ሌሎችም የሸሪዓ እውቀቶችን ከየምንጫቸው መጠጣት ጀመሩ ። በነበራቸው ፍጥነትና የአእምሮ ምጥቀት በሁሉም የሸሪዓ እውቀቶች አንቱ ለመባል በቁ ። የሰለፎችን አሰርና ( ፋና ) ትክክለኛውን የኢስላም አስተምሮ በመከተል ከቢዳዓ አንጃዎች ብዥታ ሱናን በማፅዳት ለኢስላም ትልቅ ውለታ ውሏል ። ኢማሙ አሕመድ በዒልሙ ጠልቆ መሄዳቸው ከሌሎች ዒባዳዎች አላዘናጉዋቸውም ። ይልቁንም በሌሎች ዒባዳዎች የባሱ ሆኑ እንጂ ። በጣም አላህን የሚፈሩ ፣ ሐራም እንዳይነካቸው ጥንቁቅ ፣ ዓቢድ ፣ ዛሂድ ፣ ሙኽሊስ ፣ ለይላቸውን በዚክርና በሶላት ( በአንድ ለሊት ሶስት መቶ ረካዐ ይሰግዱ ነበር ይባላል ) በዱዓእና በለቅሶ ቀናቸውን በማስተማርና በማጥናት ለጥያቄዎች መልስ ( ፈታዋ ) በመስጠት ያሳልፋሉ ። ሀብትና ስልጣን ሲመጡላቸው ከአንበሳ እንደሚሸሽ ሰው በመሸሽ ርቀው ድህነትን መርጠው የኖሩ ናቸው ። ብዙ ቀናት ምንም ሳይቀምሱ ያሳልፉ ነበር ። ልብሳቸውን ገዝተው ሳይቀይሩ ያላቸውን አጥበው ሲቀደድ አሰለጥፈው ይለብሱ ነበር ። በዚህ ሁኔታ አመታት ያልፋሉ ። እውቀት ፍለጋ ወደ የመን በሄዱበት ጊዜ ቂጣ ሊገዙበት ጫማቸውን አሲዘው በእግራቸው ነበር የሄዱት ። ይህ ሁሉ ሲሆን ልባቸው በአላህ ፍራቻና በኢማን ተሞልቶ በተቅዋ ብርሃን ይበራ ነበር ። ሞትን ሲያስታውሱ ራሳቸውን ይስቱ ነበር ። ለብዙ ቀን ምግብና ውሃ እንቢ ይላቸው ነበር ይላሉ ። ድሆችን በጣም የሚወዱና ከንጉስና ከባለስልጣን በላይ የሚያከብሩና ቦታ የሚሰጡ ነበሩ ። መታወቅን በጣም የሚጠሉና ልታወቅ ባይነትን የሚዋጉ ነበሩ ። በዚህ ማንነታቸው እልህ ውስጥ ገብተው የጠሉዋቸውና ለበቀል የተነሱባቸው የሙዕተዚላ ዑለማዎች ቁርኣን የአላህ ቃል አይደለም በል ተብለው በወቅቱ መሪዎች እንዲፈተኑ አደረጉ ። ፈተናው ምን ይመስል ነበር እንዴት ተወጡት የሚለውን አላህ ካለ በሚቀጥለው ክፍል እናያለን ። https://t.me/bahruteka
Показать все...
ባህሩ ተካ - Bahiru Teka

السلام عليكم ورحمة الله وبركاته قناة رسمية لمحاضرات ودروس الأستاذ بحرو تكا (أبو عبيدة) الدعوة السلفية በአላህ ፈቃድ በዚህ ቻናል የአማርኛ ትምህርቶችን እንዲሁም አጫጭር የአረብኛና የአማርኛ ፁሁፎችን እንለቃለን ከዚህ ቻናል ውጪ ከሌላ ቦታ ተወስደው ለሚለቀቁ ኦዲዮዎች እውቅና አልሰጥም

https://telegram.me/bahruteka

🚫 ማን ነው በጂሃድ የሚያዘው ? በመጀመሪያ ደረጃ ሁሉም ሊያወቀው የሚገባው ጂሃድ በኢስላም ትልቅ ቦታ ያለው ለአላህ ተብሎ አንገት የሚሰጥበት የአምልኮት አይነት ነው ። ጂሃድ ምእራባዊያን እንደሚያስቡት አላማው ዝም ብሎ የሰው ሕይወት ማጥፋት አይደለም ። ኢስላም ጂሃድን አስመልክቶ በጣም ግልፅ መርሕ ነው ያለው ። እንደሚታወቀው በእስልምና የአምልኮ ድንጋጌ አይነቶች በሁለት ይከፈላሉ : – ↪️ በቀጥታ ለራሳቸው ተብለው የታዘዙ በመስፈርታቸው ሁሌም የሚሰሩ ( መቅሱድ ሊዛቲሂ ) የሆኑ እንደ ሶላትና ፆምና ሐጅ የመሳሰሉ የአምኮ አይነቶች እና ↪️ በቀጥታ ለራሳቸው ተብሎ ሳይሆን ለሌላ አምልኮ መዳረሻ ተብሎ የታዘዙ ( መቅሱድ ሊጘይሪሂ ) የሆኑ ለምሳሌ ውዱእ ማድረግ :– ውዱእ የታዘዘው በዋነኝነት ለሶላት ሲሆን ያለ ውዱእ አይሰሩም ለተባሉ የአምልኮት አይነቶችም ይሆናል ። በመሆኑም አንድ ሰው ውዱእ ማድረግ ግዴታ የሚሆንበት ሶላት መስገድ በሚፈልግ ጊዜ ወይም የፈርድ ሶላት ወቅት ሲደርስ ይሆናል ። ይህ ማለት ውዱእ በራሱ ዒባዳ ከመሆኑ ጋር ። ነገር ግን የሚፈለገው በቀጥታ ለራሱ ሳይሆን ለሌላ የዒባዳ አይነት ነው ። እንደዚሁ ጂሃድም በቀጥታ ለራሱ ሳይሆን የታዘዘው ለሌላ አምልኮት ነው ። እሱም አላህ ለሰው ልጆች የሕይወት መመሪያ ይሆን ዘንድ ቁርኣንን አውርዷል ። ይህንን መለኮታዊ የህይወት መመሪያ የሆነው ቁርኣን ለሰው ልጆች እንዲያደርሱ መልእክተኞችን ልኳል ። ይህ መለኮታዊ የሕይወት መመሪያ የሆነው የአላህ ቃል መልእክተኞቹ ለሰው ልጅ ሊያደርሱና የሰውም ልጅ ይህ መለኮታዊ የህይወት መመሪያ ሊደርሰው መብቱ ነው ። በሱና በመብቱ መካከል የሚቆም አካል ሊኖር አይገባም አይ ብሎ በዚህ መለኮታዊ የህይወት መመሪያ በማድረሱ መንድ ላይ የሚቆም አሜኪላ ወይም ጋሬጣ በሚኖር ጊዜ ይህን ለማስወገድ ነው ጂሃድ የታዘዘው ። ከመሆኑም ጋር እንደ ሌሎቹ ህግጋቶች ሁሉ የራሱ የሆነ መስፈርቶች አሉት ። ልክ ዘካ አቅም ያለው ሰው እንደሚያወጣውና ሐጅም አቅም ያለው ሰው ሌሎች መስፈርቶችን አሟልቶ እንደሚያደርገው ሁሉ ። ጂሃድም አቅም ያለው መሪ ነው የሚያዝበት ። ኢስላም አቅም የሌለውን ዘካ አውጣ ወይም ሐጅ አድርግ እንዳላለው ሁሉ በዳዕዋ መንገድ ላይ የተጋረጠውንም አሜኪላ ለማስወገድ አቅም የሌለውን ጂሀድ አድርግ አላለውም ። ወደ ርእሴ ስመለስ የዚህ አይነቱ ትልቅ የሸሪዓ አካል የሆነውን ጂሃድ ማን ነው የሚያዝበት ከተባለ የሙስሊም መሪ መስላሐና መፍሰዳውን አይቶ አቅሙን መዝኖ በመንገዱ ላይ የቆመውን አሜኪላ አቅም አመዛዝኖ ከሚመለከታቸው የዲኑና የሀገር ህልውና አደራ ከተጣለባቸው አጋሮቹ ጋር በመሆን የሚያዝበት ነው ። በመሆኑም በኢስላም ጂሃድ ማንም ሰው ተነስቶ የሚያውጀው ወይም ተነሱ የሚልበት ሳይሆን በጣም ትልቅ ጥንቃቄ የሚፈልግ ነው ። ለዚህ ነው የአላህ መልእክተኛ ወሕይ እየወረደላቸውም ሙሃጅሮችንንና አንሷሮችን ያወያዩበት የነበረው ። እነ አቡበከር ዑመር በዚሁ መልኩ ትላልቅ የሙሃጅርና የአንሷር ሶሓቦችን ሰብስበው ያወያዩ የነበረው ። በጣም የሚገርመው ዛሬ ሀገራችን ላይ ማን እንደሆኑና የት ሆነው እንደሚያዙ የማይታወቁ አካላት ጂሃድ እያወጁና ተነሱ እያሉ ነው !!!!!! ። እነዚህ አካላት ሊያውቁት የሚገባው ወይ የኢስላም ጠላት ተላላኪዎች ናቸው ። ሙስሊሞችን ለማጥቃት ይህን ምክንያት አድርገው መንቀሳቀስ የሚፈልጉ የኢስላም ጠላቶች ወይም በስሜት ፈረስ የሚጋልቡ ከጂሃጅ ስሙን እንጂ ርቀቱንና ሸሪዓዊ ብይኑን የማያውቁ ። የሚያሳዝነው እነዚህ ሙስሊሙን ወጣት ለጂሀድ ተነስ የሚሉ አካላት ሚስቶቻቸው ወይም እህቶቻቸው በየወሩ ወይም በወሊድ ጊዜ ስለሚፈሳቸው ደም ሸሪዓዊ ብይን ቢጠይቁዋቸው መመለስ የማይችሉ ናቸው ‼። ነገር ግን በተሽከርካሪ ወንበር ላይ ቁጭ ብለው ማኪያቶ እየጠጡ በኡማው ደም ላይ ፈትዋ ይሰጣሉ ። ሙስሊሞች ሆይ በፖለቲካ ወይም በመሬት ስራ የከሰሩ ማንነታቸው የማይታወቁ የኢስላም ጠላት ተላላኪዎች ተነሱ ጂሃድ ስላሉዋችሁ ወይም በእንቅፋት አለያም ትንታ ትሞታላችሁ እቺን እርካሽ ህይወት ለዲን ሰጥታችሁ በጀነት በራፍ ላይ የጀነት ሙሽራ አበባ ይዛ ብተቀበላችሁ ይሻላችኋል ‼ ብለው እያሰከሩ እንዳይነዱዋችሁ ። የወንድምነት ምክሬ መጀመሪያ ዲናችሁን እወቁ ተማሩ ስሩበት አውቃችሁ የሰራችሁበትን እውቀት ለሌሎች በማድረስና ከሽርክና ቢዳዓ እንዲወጡ ሰበብ በመሆን በነፍሳችሁ ላይ ጂሃድ አድርጉ ይህ ለናንተ ትልቅ ጂሃድ ነው ። ስለሺርክና ቢዳዓ ሳታውቁ ስለጣሃራና ሶላት ሳታውቁ ወደ አኼራ እንዳትሄዱ ተጠንቀቁ ። የሱና ዑለሞች ፣ ኡስታዞችና ዱዓቶች ሙስሊሙን ከእነዚህ አካላት መጠበቅና ግንዛቤ ማስጨበት ወቅታዊ ግዴታችሁ ነውና አማናችሁን ተወጡ ኡማውን ታደጉ ። አላህ ሐቅን አውቆን የምንሰራበትና ባጢልን አውቆን የምንርቀው ያደርገን ። https://t.me/bahruteka
Показать все...
አንዳንድ ጊዜ በትክክለኛው ሀይማኖት በኢስላም የካዱም ብቻ ሳይሆን ኢስላምን ለማጥፋት ህልም አድርገው የተነሱ ካፊሮችን ሩጫ ስንመለከት፣ ምነው ወደ ታች የዘቀጠውም ወደላይ ድንበር አላፊውም ወደ ትክክለኛው አካሄድ ተመልሰው በመንሀጀ ሰለፍ ላይ አንድ ሆነን ኩፍር የተባለን፣ በጥሩ አንደበት፣ በትህትና አገላለፅ፣ ሀቅን በማብራራት፣ አርስን፣ ዘርተን፣ ኮትኩተን፣ አርመን፣ አጭደን፣ አበጥረን፣ ፈጭተን፣ አቡክተን፣ ጋግረን፣ ፈርፍረን፣ አጥበን፣ አስጥትን፣ ተኩሰን፣ ድልን ተጎናፅፈን፣ የዲል ልብስ ለብሰን፣ ባሳየናቸው ያስብላል። የቴሌግራም ቻናል ይቀላቀሉ https://t.me/Abdurhman_oumer -
Показать все...
ያልገባኝ ምሳሌ፣ አጣሁ አብጠርጥሬ፣ ተረት ዝባ-ዝንኬ፣ ትርጉም አልባ ወሬ፣ የውስጥ ጥላቻ፣ የላይ-ላይ ዝማሬ ጭብጥ የሌለው ስብከት፣ አያለሁ ዟዙሬ! ሊበሏት ያሰቧትን፣ የሰማይ አሞራ፣ ቆቅ ናት አሏት አሉ፣ ሥሟ ተቀይራ፣ ምሳሌው እንዲህ ነው፣ ያገራችን ሴራ፣ ታፔላን መቀየር፣ ተንኮል አዘል ሥራ! መስጅድን ሊያወድሙ፣ ከኢትዮ ምድር፣ በግለሰብ ቤቶች፣ ነበረ ሲጀመር፣ አላማው ታርጌቱ፣ ወጣ ሲውል ሲያድር፣ ህዝቡን ማዘናጊያ፣ ቃላት ሲደረደር! ደግሞም      ማሳመኛ፣            ማስፈራሪያም                        ጭምር፣ ሊነቅሉት ሲሻቸው፣ እስልምናን ከሥር፣ ምክንያቱን አስጠጉት፣ ከህግ ከሀገር! ህጉ የበላይ ነው፣ መስጅድም ያወድማል፣ ቁርአን ረጋግጦ፣ ቀዳዶ ይጥላል፣ ምክንያት አፈላልጎ፣ ሙስሊም ይጨቁናል፣ ህገ-ወጥ የምትል፣ ታፒላም አግኝቷል፣ አውቆ ተኝቶ እንጅ፣ ታሪኩን ያውቀዋል፣ ህጉ የበላይ ነው፣ የሻውን ይሰራል፣ ጠያቂም የለበት፣ ወንጀልም ይሰራል፣ ይህ ነው ትልቅነት፣ ለሰሚው ይገርማል! ይልቅ ከተግባባን፣ መረዳዳት ከቻልን፣ ከአሁንም በኋላ፣ አቁሙት ጫናውን፣ ተንኮል አጥንታችሁ፣ ሙስሊም ማመናመን፣ ጥፋት ማደራጀት፣ ይቅርባችሁ በቃን፣ ምንም ልትነኩት፣ የማይገባችሁን፣ ረብሻ ሲያምራችሁ፣ አትንኩት ኢስላምን! ምነው ሀገር ማክበር፣ ህጉን ለማስከበር፣ ሀገር አጥፊዎችን፣ ብትይዙልን የምር፣ አክቲቪቱን ሁሉ፣ በሰው ደም የሚያድር፣ ረብሻ ሚያስፋፉ፣ ዩትዩበር ቲክቶከር፣ ሌት ቀን ሥራ ፈቶ፣ የሚያጋጭ ዘር-ከዘር፣ ሁሌ ፖለቲካ፣ እያወራ ሚኖር፣ ማንጅራት መቺውን፣ የሚኖር በሰው ብር፣ ሚስኪን በማስለቀስ፣ ያለን በየ ሰፈር፣ መስጅድን ከማፍረስ፣ የሰላም መሀደር፣ ቁርአን ቀዳችሁ፣ ሙስሊም ከማሸበር፣ ዱርየ ከመሆን፣ ጣጣ ቢሶች ነገር፣ ምነው ብትሰሩ፣ ለሀገር ቁም ነገር! ✍ አብዱረህማን ዑመር የቴሌግራም ቻናል ይቀላቀሉ ሼር ያድርጉ https://t.me/Abdurhman_oumer/4902 -
Показать все...
بِسْمِ اللَّهِ الرَّحْمَٰنِ الرَّحِيمِ ብዬ ጀመርኩት ግጠም ግጠም አለኝ ፥ ነሻጣው መጣ 'ሚፃፍ ሀሳብ አጣሁ ፥ ውሃ የሚያነሳ! እንግዲህ ጀመርኩት ÷ልፅፈው ከሰማሁት ሁሉ ÷ መርጬ ልፅፈው ያየሁት ሁሉ ÷ አሳጥሬ ላቀርበው ቁርአን ሀዲሱ÷አሳምሬ ልፅፈው ብዕሬ ጀመርኩት በአላህ ስም በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በኾነው፡፡ ------------//------------- አቡ አብደላህ (ቶፊቅ) https://t.me/TofikGarbado
Показать все...
الشاعر

ግጥም

Показать все...
ጋርባዶና አካባቢው የሱና ቻናል

✅ደረጃችን ከፍ ሚለው ለአላህ ባለን ፍራቻ በተውሂዳችን ልክ ነው👉👇 🌲🌲🌲إن رحمة الله قريب من المحسنين🌹🌹🌹

ሰላማዊ ሰልፍ እና በዳይ አካል ከበደሉ እንዲቆጠብ ማድረጊያ ስልት የጅሐድ መዳረሻ ነውን? ✅📝 መልስ፡- ይህ ትክክል አይደለም፡፡ የነብዩ ﷺ መመሪያ ከሁሉም መመሪያ የበለጠ ነው፡፡ በረሡል ﷺ ዘመን ያልነበረ አዲስ የጅሐድ ስልት የሚፈጥርን አካል ሰለፎች ይቃወሙ ነበር፡፡ ሸይኹል ኢስላም ኢብን ተይሚያህ - ረሂመሁሏህ - የሚከተለውን ተናግረዋል፦ (ጦርነትን አስመልክቶ ሱናው ድምጽን መቀነስ ነው፤ ይህ እየዘለሉ መሬትን በእግር መደብደብ፤ ልክ እንደአይሁዶች ጡሩንባ መንፋት፤ ልክ እንደነሷራዎች ደዎል መደወል፤ በኹለፋኡ ራሽዲን (በቅን መሪዎች) ዘመን እና ከእነርሱ በኋላ በነበሩ የሙስሊም መሪዎች አልነበረም፤ ይህን ቢድዓ በምስራቅ የነበሩ የፋሪስ ንጉሶች የፈጠሩት ይመስለኛል፤ ንግስናቸው በዓለም በሰፊው ተሰራጭቶ ስለነበር ያን ጊዜ በመሪዎች ላይ ሲያምጹና ሲያስገድሉ በርካታ አዳዲስ ነገሮችን ፈጥረዋል፤ በዚሁ ቢድዓ ላይ ህጻኑም አደገ ትልቁም አረጀ፤ ከዚህ ውጭ ሌላ አያውቁም፤ እንዴውም በእነርሱ ተቃራኒ አንድ ሰው ከተናገረ ወዲያውኑ ይቃወማሉ፤ እንዴውም አንዳንድ ሰዎች ይህን ቢድዓ ዑስማን ኢብን አፋን እንደፈጠረው አድርገው የሚሞግቱ አሉ፤ ነገሩ ግን እንደዚህ አይደለም፤ እንዴውም ከዑስማን በኋላ የመጡ መሪዎች ሁሉ ያልፈጸሙት ተግባር ነው፡፡ ነገር ግን በአሁኑ ሰዓት ነብዩ ﷺ የተናገሩት ትንቢት ይፋ ሆኖ እየተመለከትን ነው ረሡል ﷺ የሚከተለውን ተናግረዋል፡- “ከእናንተ በፊት የነበሩ ማህበረሰቦች የያዙትን በእርግጥ ትይዙታላችሁ፤ ስንዝር በስንዝር፤ ክንድ በክንድ፤ “ፋርስ እና ሮም ነው እንዴ?” በማለት ሶሃቦች ጠየቁ፤ “እነርሱ ካልሆኑ ማን ሊሆን ይችላል?” በማለት ምላሽ ሰጡ፡፡ ቡኻሪ በሌላም ሐዲስ ረሡል ﷺ የሚከተለውን ተናግረዋል፡- “ከዚህ በፊት ያለፉ ህዝቦችን መንገድ ላባ በላባ በእርግጥ ትከተላላችሁ፤ የአርጃኖ (የወከሎ) ጉድጓድ ቢገቡ እንኳ በእርግጥ ትገባላችሁ፤” በማለት ተናገሩ፤ ከዚያም “የአላህ መልክተኛ ሆይ! አይሁድ እና ነሷራን ነውን?” በማለት ሶሃቦች ጥያቄ አቀረቡ፤ “እንግዲያ ማንን ነው?” በማለት ምላሽ ሰጡ፡፡ አህመድ፡ 17135, አልባኒ አስሶሂሃ 7/915 ኢብኑ ከሲር በተፍሲራቸው፣ ሀይሰሚይ መጅሙዑ ዘዋኢድ ላይ ዘግበውታል ሐዲሡ ሶሂህ ነው፡፡) ሁለቱም ሐዲሶች ከረሡል ﷺ የተሰሙ ትክክለኛ ሐዲሶች ናቸው፡፡ ረሡል በዚህ ማህበረሰብ ውስጥ አይሁድ እና ነሷራን ወይም ፋርስ እና ሮማዎችን የሚመሳሰሉ ማህበረሰቦች እንደሚኖሩ ነው የጠቆሙት፡፡ ይህን ርዕስ የምናብራራበት ቦታ ከዚህ ባይሆንም በመሪዎች በንጉሶች በርካታ አዳዲስ ነገሮች ተፈጥረዋል፡፡ ነገር ግን በዚህ ቦታ ዋናው አላማችን ጅሐድን አንስተው የጩኸት ቢድዓን በፈጠሩ ሰዎች ላይ ነው፤ አመዛኝ ጥቅም ሊኖረው ይችላል ብለው ገምተው እንኳ ቢሆን መልካሙን ነው አጥብቀው መያዝ ያለባቸው፤ አመዛኙ ጥቅም የዚክር ድምጾች፤ ሶላት እና ከእርሱ ጋር የተያያዙ ዱዓዎች፤ ቁርኣን መቅራት እና መስማት ናቸው፤ ሌሎች ጥቅም የሚያስገኙ ሸሪዓዊ ጉዳዮች አሉ…. ከዚህ በፊት የነበሩት ቀዳሚዎች ታብዒዮች በማንኛውም ነገር ከኋለኞች የተሻሉ፤ የሚከተሉት መንገድም የተሟላ ነው፤ ነገር ግን አንድ ሙስሊም ስራዎችን በአቅሙ ሊፈጽም ይገባል፡፡ አላህ የሚከተለውን ተናግሯል፦ فَاتَّقُوا اللَّهَ مَا اسْتَطَعْتُمْ “አላህንም የቻላችሁትን ያህል ፍሩት፤” ተጋቡን 16 ነብዩ ﷺ የሚከተለውን ተናግረዋል፡- “አንድ ነገር ካዘዝኳችሁ የቻላችሁትን ያህል ፈጽሙት፡፡” ቡኻሪና ሙስሊም https://t.me/AbuImranAselefy/6935
Показать все...
Abu Imran Muhammed Mekonn

❌ ሰልፍ ❌ 📁 ይህ ሸይኽ ዓብዱረህማን ብን ሰዕድ ብን ዓልይ አሽሸስሪ “አልሙዟሀራት ፊ ሚዛኒ አሽሸሪዓቲ አልኢስላምየቲ” በሚል ርዕስ ካዘጋጁት መጽሐፍ ከገጽ 84-108 የተወሰደ አጭር ትምህርት ነው፡፡ አጠቃላይ የመጽሐፉ ይዘት ሰላማዊ ሰልፍን በቁርኣን እና በሐዲስ የሚገመግም ሲሆን በዚህ መጽሐፍ የሰላማዊ ሰልፍ ቋንቋዊና ሸሪዓዊ ትርጉም፤ በመሪዎች ላይ ማፈንገጥ ያለው ሸሪዓዊ ብይን፤ ሰላማዊ ሰልፍ እያስከተለ ያለው አደጋ፤ ሰላማዊ ሰልፍ መቸ ተጀመረ?፤ ማን ጀመረው?፤ የሰላማዊ ሰልፍ ብዥታዎችና መልሶቻቸው እና የመሳሰሉ ርዕሶች የተዳሰሱበት በመሆኑ በተለያዩ ቋንቋዎች ቢተረጎም ለሙስሊሙ ህብረተሰብ ከፍተኛ ፋይዳ ያስገኛል ብየ አስባለሁ፡፡ ይህችን አጠር ያለች ጽሁፍ ለመክተብ ያነሳሳኝ በአሁኑ ሰዓት በአገራችን ብሎም በአለም የስንት ሙስሊም ወንድሞቻችንን ህይወት ያስቀጠፈ፤ ከአገር ያሰደደ፤ ያስገረፈ፤ ክብራቸው እንዲጣስና አካለ ስንኩላን እንዲሆኑ ያስደረገ ፤ ያለአግባብ የሙስሊሞች ገንዘብ እንዲወድም እንዲዘረፍ እና በአጠቃላይ የሙስሊሞችን አገር የበታተነ ስለሆነው “ሰላማዊ ሰልፍ” በኢስላም ይፈቀዳል? ወይስ አይፈቀድም? በሚል በየመንደሩና በየጓዳው ማስረጃን መሰረት ያላደረገ ክርክርና ብዥታዎችን ከአንዳንድ ወጣቶች በማስተወሌ ነው፤ በመሆኑም ምንም እንኳ የሚያጠግብ ባይሆንም የወጣቱን ግለት በተወሰነ መልኩ ያበርዳል፤ የተንሻፈፈውን አመለካከት ያቃናል፤ ያለእውቀት በዚህ አውዳሚ እንቅስቃሴ ላይ ጠንካራ አቋም ያላቸው ወንድሞቻችን እና እህቶቻችን እነዚህን 18 ብዥታዎች እና መልሶቻቸው ሲያስተውሉ በአላህ ፈቃድ ከነበራቸው ጠንካራ አቋም ይመለሳሉ ብየ ስላሰብኩ ነው፡፡ አላህ ሁላችንንም ወደሐቁ መስመር ይምራን! 📝 ሸይኽ ዩሱፍ አህመድ ሀፊዘሁሏህ

https://t.me/AbuImranAselefy/5069

👉 በአንድ ጉድጓድ ሁለቴ መነደፍ    ሙእሚን በአንድ ጉድጓድ ሁለቴ አይነደፍም ። እንደሚታወቀው ከዚህ በፊት ኢኽዋን አሕባሽን በመቃወም ስም ሙስሊሙን ማህበረሰብ ሰላማዊ ትግል ብሎ ዋጋ አስከፍሎታል ። በዚህ ሰላማዊ ትግል ስም ብዙ ወንድሞቻችንን አጥተናል ። አብዛኛዎች የአልጋ ቁራኛ ሆኗል ። ሌሎች ሀገር ለቀው ተሰደዋል ። ብዙ እህቶች ክብራቸውን አጥተዋል ። አደባባይ ላይ ኒቃብና ጅልባባቸው ጫማ ተጠርጎበት ወደ እሳት ተወርውሯል ። ያለ ምንም ርህራሄ አናታቸው ተሰንጥቋል ። ጥቂት የማይባሉ ተረጋግጠው ህይወታቸውን አጥተዋል ። ከሴት እህቶቻችን ውስጥ አንዷ በጡቶቿ ላይ ኤሌክትሪክ ተለቆባት ደርቃ የሞተች አለች ። ኢኽዋኖች በዚህ መልኩ ዋጋ አስከፍለው መጨረሻ ላይ ከአሕባሽ ጋር አንድ ነን ብለው አሕባሽን አንግሰዋል ። የኋላ ኋላ በመጅሊስ ስልጣን ተጣልተው አይንህ ላፈር ተባብለው ተለያይተዋል ።   ኢኽዋን መጅሊሱን ሲዝ የፈለገ መውሊድ ያውጣ የፈለገ ጫት ይቃም ብሎ የዐቂዳና የአመለካከት ነፃነት አውጇል ። በዚህም ትልቁን ወላእና በራእ የሚለውን እንዲሁም በመልካም ማዘዝና ከመጥፎ የመከልከል የኢስላም መርህ ንደዋል ። ያ ቁስል ሳይድን ትካዜው ሳይረሳ አሁንም ሙስሊሙን ዋጋ ሊያስከፍሉ ይመስላል ። በመሆኑም ሙስሊሞች ባጠቃላይ ሰለፍዮች በተለይ በየአንዳንዱ እንቅስቃሴያችን ኢስላም ምን ይላል ብለን ልንጠይቅ ይገባል ።     ድንጋይ በመወረወር ፣ መንገድ በመዝጋት ፣ ንብረት በማውደም በንፁሃን አካልም ሆነ ንብረት ላይ ወሰን በማለፍ የሚጠየቅ መብት የለም ። ገጠርም ይሁን ከተማ የሚደርሱ በደሎች ካሉ መጀመሪያ ወደ አላህ መመለስና በደላችንን ምንም ለማይሰወርበት አምላካችን ማቅረብ ፍትህ ከሱ መጠበቅ ይኖርብናል ። ከዚህ ካለፈ እስከሚቻለው ድረስ በሰላማዊ መንገድ በመነጋገር ጥያቄ በማቅረብ መብትን መጠየቅ ይቻላል ። መልስ አላገኘሁም ብሎ የሚደረጉ ረብሻዎች ጉዳት እንጂ ጥቅም የላቸውም ። ተጎጂው ደግሞ ሁሌም ምስኪኑ ሙስሊም ማህበረሰብ ነው ። የንቅናቄው መሪዎች ፊት ለፊት ሆነው አይደለም የሚመሩት መመሪያ ሰጥተው መስመሩን ዘርግተው የሚሆነውን ሩቅ ሆነው ነው የሚከታተሉት ። ይህ በተደጋጋሚ በዩንቨርሲቲ ተማሪዎች ንቅናቄ ታይቷል ።     እንደ ምሳሌ በ2001 ላይ ሚዛን ቴፒና ወሎ ዩንቨርሲቲ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ሒጃብ ተከልክለዋል በሚል የአ/አ ዩንቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ለሶስት ቀን የምግብ ማቆም አድማ እንዲያደርጉና በሶስተኛው ቀን ሁሉም ተማሪ ጁሙዓ ፒያሳ ኑር መስጂድ ሰግዶ ሰላማዊ ሰልፍ እንዲያደርግ መመሪያ ተሰጥቶ ሰላማዊ ሰልፉ ተጀምሮ ጥቂት ሳይጓዝ ተማሪው በላእ ወርዶበት ሰማይና ምድር ጠቦት እርስ በርሱ እየተረጋገጠ የወደቀው ወድቆ የተነሳው ቆመጥ እየተቀበለው ሲታመስ መመሪያ ሰጪዎቹ የአ/አ ጥግ ላይ ሰግደው ምን ላይ ደረሰ እያሉ ሲጠይቁ ነበር።‼     የድምፃችን ይሰማን ንቅናቄ ሲመሩ የነበሩት አብዛኞቹ ኳታር፣ ካናዳና አሜሪካ ሆነው ነበር ሲመሩ የነበሩት። በመሆኑም ሙስሊሞች ማን ለምን ተነሱ እንደሚላቸው ሊጠይቁና ሊያውቁ ይገባል ። በስሜት መነዳት በዱንያም በአኼራም ጉዳት እንጂ ጥቅም የለውም። ያለፈው ይበቃል በአንድ ጉድጓድ ሁለቴ መነደፍ የለም።  https://t.me/bahruteka    
Показать все...
Abu Imran Muhammed Mekonn

በመጀመሪያው ሰልፍ ➲ ይህንን ኡለሞች ያልፈቀዱት ሰላማዊ (የተቃውሞ) ሰልፍ ተው ቢባሉ አሻፈረኝ ያሉት የስሜት ተከታዮች ዛሬም ህዝቡን ወደ ጥፋት እየማገዱት ነው

https://t.me/AbuImranAselefy/6933

❌ ሰልፍ ❌ 📁 ይህ ሸይኽ ዓብዱረህማን ብን ሰዕድ ብን ዓልይ አሽሸስሪ “አልሙዟሀራት ፊ ሚዛኒ አሽሸሪዓቲ አልኢስላምየቲ” በሚል ርዕስ ካዘጋጁት መጽሐፍ ከገጽ 84-108 የተወሰደ አጭር ትምህርት ነው፡፡ አጠቃላይ የመጽሐፉ ይዘት ሰላማዊ ሰልፍን በቁርኣን እና በሐዲስ የሚገመግም ሲሆን በዚህ መጽሐፍ የሰላማዊ ሰልፍ ቋንቋዊና ሸሪዓዊ ትርጉም፤ በመሪዎች ላይ ማፈንገጥ ያለው ሸሪዓዊ ብይን፤ ሰላማዊ ሰልፍ እያስከተለ ያለው አደጋ፤ ሰላማዊ ሰልፍ መቸ ተጀመረ?፤ ማን ጀመረው?፤ የሰላማዊ ሰልፍ ብዥታዎችና መልሶቻቸው እና የመሳሰሉ ርዕሶች የተዳሰሱበት በመሆኑ በተለያዩ ቋንቋዎች ቢተረጎም ለሙስሊሙ ህብረተሰብ ከፍተኛ ፋይዳ ያስገኛል ብየ አስባለሁ፡፡ ይህችን አጠር ያለች ጽሁፍ ለመክተብ ያነሳሳኝ በአሁኑ ሰዓት በአገራችን ብሎም በአለም የስንት ሙስሊም ወንድሞቻችንን ህይወት ያስቀጠፈ፤ ከአገር ያሰደደ፤ ያስገረፈ፤ ክብራቸው እንዲጣስና አካለ ስንኩላን እንዲሆኑ ያስደረገ ፤ ያለአግባብ የሙስሊሞች ገንዘብ እንዲወድም እንዲዘረፍ እና በአጠቃላይ የሙስሊሞችን አገር የበታተነ ስለሆነው “ሰላማዊ ሰልፍ” በኢስላም ይፈቀዳል? ወይስ አይፈቀድም? በሚል በየመንደሩና በየጓዳው ማስረጃን መሰረት ያላደረገ ክርክርና ብዥታዎችን ከአንዳንድ ወጣቶች በማስተወሌ ነው፤ በመሆኑም ምንም እንኳ የሚያጠግብ ባይሆንም የወጣቱን ግለት በተወሰነ መልኩ ያበርዳል፤ የተንሻፈፈውን አመለካከት ያቃናል፤ ያለእውቀት በዚህ አውዳሚ እንቅስቃሴ ላይ ጠንካራ አቋም ያላቸው ወንድሞቻችን እና እህቶቻችን እነዚህን 18 ብዥታዎች እና መልሶቻቸው ሲያስተውሉ በአላህ ፈቃድ ከነበራቸው ጠንካራ አቋም ይመለሳሉ ብየ ስላሰብኩ ነው፡፡ አላህ ሁላችንንም ወደሐቁ መስመር ይምራን! 📝 ሸይኽ ዩሱፍ አህመድ ሀፊዘሁሏህ https://t.me/AbuImranAselefy/5069
Показать все...
ሰላማዊ ሰልፍ ብዥታዎቹና መልሶቹ.pdf2.68 MB
Фото недоступноПоказать в Telegram
በመጀመሪያው ሰልፍ ➲ ይህንን ኡለሞች ያልፈቀዱት ሰላማዊ (የተቃውሞ) ሰልፍ ተው ቢባሉ አሻፈረኝ ያሉት የስሜት ተከታዮች ዛሬም ህዝቡን ወደ ጥፋት እየማገዱት ነው https://t.me/AbuImranAselefy/6933
Показать все...
Выберите другой тариф

Ваш текущий тарифный план позволяет посмотреть аналитику только 5 каналов. Чтобы получить больше, выберите другой план.