ru
Feedback
ፍኖተ መጻሕፍት 📚FinoteBooks1623 ➮አድራሻ አዲስ አበባ ፒያሳ ገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ማኅበረ በኩር ሰንበቴ ፊት ለፊት ለበለጠ መረጃ ፦በ0913083816 ይደውሉ።

ፍኖተ መጻሕፍት 📚FinoteBooks1623 ➮አድራሻ አዲስ አበባ ፒያሳ ገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ማኅበረ በኩር ሰንበቴ ፊት ለፊት ለበለጠ መረጃ ፦በ0913083816 ይደውሉ።

Открыть в Telegram

📚ፍኖተ መጻሕፍት @finoteBooks1623 ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 t.me/FinoteBooks1623

Больше
3 295
Подписчики
-324 часа
-167 дней
-3730 день
Архив постов
"ዐራተኛው ሰው" ማን ነው? መጋቢት ፲፱ ቀን የቅዱስ ገብርኤል ወርኃዊ  በዓል በቤተክርስቲያን ታሪክ "የሠለስቱ ደቂቅ" በዓል ተብሎ ይከበራል። ታሪኩ የጥንቷ ባቢሎን ቢሆንም፣ መልእክቱ ግን የዛሬው የሁላችንም የዕለት ተዕለት የሕይወት ትግል ነው። ዛሬም እንደ ባቢሎን ሜዳ፣ በዙሪያችን የሚነዱ "የእሳት እቶኖች" ሞልተዋል። ​🔥 የዘመናችን እቶኖች፦ ሲነዱ የማናያቸው እሳቶች ​የባቢሎኑ እሳት ቁሳዊና የሚታይ ነበር፤ የዛሬው እሳት ግን ረቂቅና የሚሰማ ነው። የጭንቀት እቶን፦ "ነገ ምን እሆናለሁ?" የሚል ስጋት፣ የኢኮኖሚ ጫና እና የቤተሰብ ኃላፊነት ልክ እንደ ሰባት እጥፍ እሳት ትውልዱን እየለበለቡት ይገኛሉ። የብቸኝነት እቶን፦ በሰው መካከል እየኖሩ "ሰው ማጣት"፣ ማንም የማይረዳው ውስጣዊ ስቃይና የሐዘን ነበልባል ብዙዎችን እያቃጠለ ነው። የጥላቻና የክፋት እቶን፦ በሥራ ቦታ፣ በማኅበራዊ ሕይወትና በምንኖርበት ዓለም ውስጥ በቅናትና በክፋት የሚለኮሱ እሳቶች ሕይወታችንን ፈታኝ አድርገውታል። ​📜እሳቱ ለምን አልጠፋም? ​ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን አንድ ድንቅ ምስጢር ይነግሩናል። ቅዱስ ገብርኤል ወደ እቶኑ ሲወርድ እሳቱን አላጠፋውም፤ ይልቁንም "ባሕርዩን ለወጠው" እንጂ። ለሕፃናቱ እሳቱ ወደ በረድነት ተቀየረላቸው፤ ለገዳዮቻቸው ግን እንደነደደ ነበር። ​ይህ ለሕይወታችን ትልቅ ትርጉም አለው፦ እግዚአብሔር መከራውን ከዓለም ላይ ላያጠፋው ይችላል፤ ነገር ግን በመከራው ውስጥ እንድንጸና፣ መከራው እንዳያቃጥለንና እንዲያውም መከራው ለበረከት እንዲሆንልን "ባሕርዩን የመለወጥ" ኃይል አለው። ​✨ "አራተኛው ሰው" — የድላችን ምሥጢር ​ናቡከደነጾር እቶኑን ሲመለከት ደነገጠ። "የጣላቸው ሦስት ሰዎች ነበሩ፤ አሁን ግን አራተኛው በመካከላቸው ይታየኛል" አለ። በሕይወትህ ውስጥ ብቻህን አይደለህም ፤ በደረሰብህ መከራና በወደቅክበት እቶን ውስጥ ብቻህን አይደለህም። ያ "አራተኛው ሰው" — ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል — በእግዚአብሔር ትዕዛዝ ከጎንህ ቆሟል። መከራው መሸጋገሪያ ነው፦ ሦስቱ ሕፃናት ወደ እሳቱ ባይጣሉ ኖሮ፣ የመልአኩን ተራዳኢነት ባላዩ ነበር። ዛሬ የሚያቃጥልህ መከራ ነገ የምስክርነትህ መድረክ ይሆናል። የእምነት ጽናት፦ "አምላካችን ቢያድነንም ባያድነንም..." የሚለው የሕፃናቱ ቃል፣ ዛሬ ላለን ሰዎች ትልቅ ትምህርት ነው። ለእውነት ስትቆም እሳቱ የበረድ ጠል የመሆን ግዴታ አለበት። ​✍️ ወደ በረድነት የሚለወጥ ሕይወት ​የመጋቢት ፲፱ ወርሐዊ በዓል መልእክቱ ግልጽ ነው፦ "እሳቱ ይነዳል፤ ገብርኤል ግን ያበርደዋል።" ዛሬ በኑሮህ፣ በጤናህ ወይም በሐሳብህ እቶን ውስጥ ከሆንክ ተስፋ አትቁረጥ። በባቢሎን ሜዳ የደረሰው መልአክ፣ ዛሬም በቤትህና በልብህ አለ። ​ጭንቀታችን ወደ ደስታ፣ መከራችን ወደ በረከት የሚለወጥበት የመጋቢት የብሥራት ወር ይሁንልን ​📜ሰላም ለከ ገብርኤል ኃይለ እግዚአብሔር ልዑል፤ ዘአድኃንኮሙ ለሠለስቱ ደቂቅ እም እሳተ ነበልባል!" ​እንኳን ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ወርኃዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! ​----------------------- ©️ደምፀ በቀለ ፥ የጉባኤ ደብረ ምጥማቅ የሐዲስ ኪዳን ደቀመዝሙር

📚#ጉባኤያተ ቤተ ክርስቲያን ከ50-380ዓ.ም .....የወንድማችን የዲያቆን አዶንያስ ብርሃነ «የቤተ ክርስቲያን ጉባኤዎች» መጽሐፍ ለተዋሥኦና ጥናት ብዙ ርቀት የሚያስጉዝ ስንቅ እንደሆነ ይሰማኛል፡
📚#ጉባኤያተ ቤተ ክርስቲያን ከ50-380ዓ.ም .....የወንድማችን የዲያቆን አዶንያስ ብርሃነ «የቤተ ክርስቲያን ጉባኤዎች» መጽሐፍ ለተዋሥኦና ጥናት ብዙ ርቀት የሚያስጉዝ ስንቅ እንደሆነ ይሰማኛል፡፡ከኢየሩሳሌሙ የሐዋርያት ጉባኤ እስከ ቊስጥንጥንያ የነበሩትን ጉባኤያት በግሩም አቀራረብ ቃኝቶ በመልካም ትርጓሜ አቅርቦልናል። መልካም ንባብ!      በአማን ነጸረ [ደብተራና የሕግ ባለሙያ] 📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 Join us ◉Telegram t.me/FinoteBooks1623 ◉Facebook facebook.com/FinoteBooks1623 ◉Tiiktok tiktok.com/@finotebooks1623

📚#አውቴዝራማ “የንታ...እንደው አንድ ጥያቄ ነበረችኝ” “ምንድናት የኔ ዓለም?” “እውነት ግን ሀገራችን ትንሣኤ አላት?” “ይህ ነው ጥያቄህ?” “አዎ! ቴዎድሮስ ይመጣል የሚሉትስ እውነት ነው? ማ
📚#አውቴዝራማ “የንታ...እንደው አንድ ጥያቄ ነበረችኝ” “ምንድናት የኔ ዓለም?” “እውነት ግን ሀገራችን ትንሣኤ አላት?” “ይህ ነው ጥያቄህ?” “አዎ! ቴዎድሮስ ይመጣል የሚሉትስ እውነት ነው? ማነው ቴዎድሮስ? ምን ዓይነት ሰው ነው?” “እንዴት ስትል ጠየቅኸኝ ግን የኔ ልጅ?” “የንታ ድርሳነ ዑራኤል ሳነብ ነው ጥያቄው የተፈጠረብኝ።የጥቅምቱ ድርሳን ላይ የስሙ ምልክት «ቴ» ተብሎ የተመለከተው ይነግሳል ይላል። አሁን ላይ ሁሉም በየፊናው ቴዎድሮስ ይመጣል ይላል። የኢትዮጵያ ትንሣኤ ቀርቧል ይላል። አንዳንዱም ፈጽሞ ይቃወመዋል። ድርሳኑ ምን እንዳለ አስረዱኝ የንታ?” ❲ከውስጥ ገጽ❳ 📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 Join us ◉Telegram t.me/FinoteBooks1623 ◉Facebook facebook.com/FinoteBooks1623 ◉Tiiktok tiktok.com/@finotebooks1623

📚#የማምሻ_ዕድሜ_ወግ ይህን መጽሐፍ የሚያነብብ ሰው ሁሉ በኢትዮጵያ ታሪክ ላይ የሚጨምረው ዕውቀት እንደሚያገኝ ርግጠኛ ሆኜ መናገር እችላለሁ:: ይልቁንም ደግሞ በመደበኛ ታሪክ ውስጥ የማይገኙ ነገር
📚#የማምሻ_ዕድሜ_ወግ ይህን መጽሐፍ የሚያነብብ ሰው ሁሉ በኢትዮጵያ ታሪክ ላይ የሚጨምረው ዕውቀት እንደሚያገኝ ርግጠኛ ሆኜ መናገር እችላለሁ:: ይልቁንም ደግሞ በመደበኛ ታሪክ ውስጥ የማይገኙ ነገር ግን ደግሞ በማኅበረሰቡ ዘንድ ዋጋ ያላቸውና በተለይ መጪው ትውልድ በአግባቡ ስለማይገነዘባቸው ብዙ ነገሮች ከዚህ መጽሐፍ ማግኘት ይችላል:: ባለታሪኩ ታላቁ ሊቅ እና አስተዋዩ ዳኛ ሊቀ ኅሩያን በዛብህ ወልደ ዮሐንስ እና ባለቤታቸው ወ/ሮ ወለተ ማርያም ታፈሰ የመተረክ ችሎታቸውም ያስደንቃል:: ስለዚህ ለታሪክ፣ ለማኅበረሰብ ሥሪት እና በማኅበረሰባችን ውስጥ ስለነበሩ አንዳንድ ሳንካዎች ብቻ ሳይሆን አንዳንድ ለየት ያሉ ነገሮችንም ለማወቅ የሚፈልግ ሰው ሁሉ ሊያመልጠው የማይገባ መጽሐፍ ነው ብዬ አምናለሁ:: ✍️ዲያቆን ብርሃኑ አድማስ 📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 Join us ◉Telegram t.me/FinoteBooks1623 ◉Facebook facebook.com/FinoteBooks1623 ◉Tiiktok tiktok.com/@finotebooks1623

📚#የማምሻ_ዕድሜ_ወግ ይህን መጽሐፍ የሚያነብብ ሰው ሁሉ በኢትዮጵያ ታሪክ ላይ የሚጨምረው ዕውቀት እንደሚያገኝ ርግጠኛ ሆኜ መናገር እችላለሁ:: ይልቁንም ደግሞ በመደበኛ ታሪክ ውስጥ የማይገኙ ነገር
📚#የማምሻ_ዕድሜ_ወግ ይህን መጽሐፍ የሚያነብብ ሰው ሁሉ በኢትዮጵያ ታሪክ ላይ የሚጨምረው ዕውቀት እንደሚያገኝ ርግጠኛ ሆኜ መናገር እችላለሁ:: ይልቁንም ደግሞ በመደበኛ ታሪክ ውስጥ የማይገኙ ነገር ግን ደግሞ በማኅበረሰቡ ዘንድ ዋጋ ያላቸውና በተለይ መጪው ትውልድ በአግባቡ ስለማይገነዘባቸው ብዙ ነገሮች ከዚህ መጽሐፍ ማግኘት ይችላል:: ባለታሪኩ ታላቁ ሊቅ እና አስተዋዩ ዳኛ ሊቀ ኅሩያን በዛብህ ወልደ ዮሐንስ እና ባለቤታቸው ወ/ሮ ወለተ ማርያም ታፈሰ የመተረክ ችሎታቸውም ያስደንቃል:: ስለዚህ ለታሪክ፣ ለማኅበረሰብ ሥሪት እና በማኅበረሰባችን ውስጥ ስለነበሩ አንዳንድ ሳንካዎች ብቻ ሳይሆን አንዳንድ ለየት ያሉ ነገሮችንም ለማወቅ የሚፈልግ ሰው ሁሉ ሊያመልጠው የማይገባ መጽሐፍ ነው ብዬ አምናለሁ:: ✍️ዲያቆን ብርሃኑ አድማስ 📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 Join us ◉Telegram t.me/FinoteBooks1623 ◉Facebook facebook.com/FinoteBooks1623 ◉Tiiktok tiktok.com/@finotebooks1623

📚#ሦስቱ_መጻሕፍተ_መነኰሳት #በተስፋ_ገብረሥላሴ_ዘብሔረ_ቡልጋ የተዘጋጀ.... ...#ታሪክ ፤ የሙሴ ፡ ጸሊም ፡ ጌቶቹ ፡ ፀሐይ ፡ ጨረቃ ያመልኩ ፡ ነበር ፤ እነዚያ ፡ ሙተው ፡ ለልጆቹ ፡ ይገዛ
📚#ሦስቱ_መጻሕፍተ_መነኰሳት #በተስፋ_ገብረሥላሴ_ዘብሔረ_ቡልጋ  የተዘጋጀ.... ...#ታሪክ ፤ የሙሴ ፡ ጸሊም ፡ ጌቶቹ ፡ ፀሐይ ፡ ጨረቃ ያመልኩ ፡ ነበር ፤ እነዚያ ፡ ሙተው ፡ ለልጆቹ ፡ ይገዛል ልጆቹም ፡ ፀሐይ ፡ ጨረቃ ፡ ያመልካሉ ፡ ከዕለታት አንድ ፡ ቀን ፡ ከባልንጀሮቹ ፡ ጋራ ፡ ሊሠርቁ ፡ ሊቀሙ ፡ በረኃ ፡ ለበረኃ ፡ ሲሄዱ ፡ ዋዕየ ፡ ፀሐይ ጸናባ ቸው ፡ ከጥላ ፡ አርፈው ፡ ሳለ ፡ ቀና ፡ ብሎ ፡ ፀሐይን፡ ስትባክን ፡ አይቶ ፡ አሁን ፡ ይች ፡ ፀሐይ ፡ ምን ፡ ምላክ ፡ ናት ፤ አምላክስ ፡ የኔ ፡ ጌቶች ናቸው ፡ በል ተው ፡ ጠጥተው ፡ ከጥላ ፡ አርፈው ፡ የሚውሉ አላቸው ። እነሱም አሻግረው ፡ አይተው ፡ አምላክ አምላክ ፡ ትላለህ ፡ አምላክማ ፡ ከፈለገህ ፡ ያባ ኤስ ድሮስ ፡ ገዳም ፡ ያውልህ አትሄድምን ፡ አሉት ያው ፡ ተነሥቶ ፡ ሄደ ፤ ከገዳሙ ፡ ቢደርስ ፡ ግብሩን፡ ያውቃሉና ፡ ማኅበሩ ፡ ተሸበሩ ፣ አበ ፡ ምኔቱ ፡ አባ ኤስድሮስ ፡ ነው ፤ ጸጋ ፡ እግዚአብሔር ፡ ጠርታ ፡ አ ምጥታዋለችና ፡ ይልቅ ፡ ተቀበሉት ፡ አላቸው : ተቀብለው ፡ አገቡት ፣ ከዚያ ፡ በኋላ ፡ ልጄ ፡ ምን ፡ አመ ጣህ ፡ አለው ፡ ትመክረኝ ፡ ብዬ ፡ አለ። መከረው አስተማረው ፤ አመነ ፡ ተጠመቀ ፤ ደግ ሰው ሆነ አመንኩሶታል። 📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 Join us ◉Telegram t.me/FinoteBooks1623 ◉Facebook facebook.com/FinoteBooks1623 ◉Tiiktok tiktok.com/@finotebooks1623

📚#ተግሣፅ ዘ #ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ #በተስፋ_ገብረሥላሴ_ዘብሔረ_ቡልጋ የተዘጋጀ። « . . . ተግሣፅ ፡ ማለት፡ ስሕተትን ፡ ማረሚያ ፡አቋምን ፡ ማስተካከያ መናፍቃንን ፡ መቃወሚያ ፡መጭውን ፡
📚#ተግሣፅ #ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ #በተስፋ_ገብረሥላሴ_ዘብሔረ_ቡልጋ የተዘጋጀ። « . . . ተግሣፅ ፡ ማለት፡ ስሕተትን ፡ ማረሚያ ፡አቋምን ፡ ማስተካከያ መናፍቃንን ፡ መቃወሚያ ፡መጭውን ፡ የሕይወት ፡ ጐዳና ፡ የሚተልም መንፈሳዊ፡መሐንዲስ ፡ ማለት ፡ ነው። ስለዚህ ፡ በዚህ ፡ የመጽ ሐፍ ፡ ቃለ ፡ ምዕዳን የሚመራውን ፡ ሁሉ ፡ እግዚአብሔር' ለከፋ ሞት ፡ አሳልፎ አይሰጠውም ። » መዝ ፻፲፯ ፲፰ ። ኢሳ. ፳፮ ፲፮ " 📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 ◉Telegram t.me/FinoteBooks1623 ◉Facebook facebook.com/FinoteBooks1623 ◉Tiiktok tiktok.com/@finotebooks1623

➮አዲስ መጽሐፍ 📚#ኦርቶዶክሳዊ_ነገረ_ሥላሴ📚 በዲያቆን ዮሐንስ ጌታቸው «እግዚአብሔር አምላካችን ሕያው መሆኑ የታወቀ ሲሆን ባሕርዩና አኗኗሩ ምን እንደሆነ ግን እርሱ ለእኛ በሚጠቅመንና በምንችለው
አዲስ መጽሐፍ 📚#ኦርቶዶክሳዊ_ነገረ_ሥላሴ📚 በዲያቆን ዮሐንስ ጌታቸው «እግዚአብሔር አምላካችን ሕያው መሆኑ የታወቀ ሲሆን ባሕርዩና አኗኗሩ ምን እንደሆነ ግን እርሱ ለእኛ በሚጠቅመንና በምንችለው ልክ ከገለጠልን ውጭ እኛ ተመራምረን ልንደርስበት አንችልም። ምክንያቱም እግዚአብሔር “ከህልውና/ከመኖር ሁሉ በላይ” “above existence/being'' ነውና። መቼም ቢሆን ውስን (inite) የሆነው የፍጡራን አእምሮ ያልተወሰነ (Infinite) የሆነውን እግዚአብሔርን መርምሮ ሊደርስበት አይችልም። እግዚአብሔር አምላካችን አንድ አምላክ ሲሆን ልዩ ሦስትነት ያለው ነው፡፡ ይህን የገለጠልንም እርሱ ራሱ ነው፡፡ ይህ የእግዚአብሔር የአንድነትና የልዩ ሦስትነት ነገር በሒሳባዊ ወይም ፍልስፍናዊ መንገድ የሚታወቅ ወይም የሚደረስበት አይደለም፡፡ “ምስጢረ ሥላሴ” ተብሎ የሚገለጸው ይህ በሰዎችና በመላእክት አእምሮ ሊደረስበት የማይችለው፣ በራሱ በእግዚአብሔር ብቻ ለእኛ የተገለጠው እውነት ነው፡፡ “የእርሱን ነገር መስማት እንደሚቻለን መጠን እርሱ ራሱ ነገረን'' እንዳለ ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ፡፡ ዲያቆን ዮሐንስ ጌታቸው መሠረታዊ የቤተ ክርስቲያን ትምህርቶችን ለማብራራትና አንባቢዎችን ለማገዝ እያደረገ ባለው ጥረት ሊመሰገንና ሊበረታታ ይገባዋል፡፡ በነገረ ቅድስት ሥላሴ ዙሪያ ያዘጋጀውን ይህን መጽሐፉንም አንብበን እንጠቀምበት እላለሁ፡፡» ✍️[ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ] 📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 ◉Telegram t.me/FinoteBooks1623 ◉Tiiktok tiktok.com/@finotebooks1623

#ተወዳጆች.... ➮የዕቅበተ እምነቷ ቅመም ባለማወቅ ለተነጠቁት ዓይነተኛ መፍትሔ (መድኃኒት) በመኾን የጠቀመ በእውር ድንብር ለሚመሩት ደግሞ ከዳተኝነታቸው የተነሳ የሚፈሩት የ*መ*ና*ፍ*ቃ*ን 🔨 በ
#ተወዳጆች.... ➮የዕቅበተ እምነቷ ቅመም ባለማወቅ ለተነጠቁት ዓይነተኛ መፍትሔ (መድኃኒት) በመኾን የጠቀመ በእውር ድንብር ለሚመሩት ደግሞ ከዳተኝነታቸው የተነሳ የሚፈሩት የ*መ*ና*ፍ*ቃ*ን 🔨 በጉምቱ መምህራችን በዲያቆን ያረጋል አበጋዝ የተቀመመው ድንቁ መጽሐፋችን #መድሎተ ጽድቅ ቅጽ-፩ #ለ20ኛ_ጊዜ_ታትሟል!! ''ለሰው ልጆች መዳኛ ትሆን ዘንድ ከእግዚአብሔር የተሰጠችው አንዲቷ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ክርስትና  በሰዎች ግለሰባዊ አስተሳሰብና 'መሰለኝ' በሚል ግምትና መላ ምት የተገኘች ሳትሆን ከራሱ ከእግዚአብሔር የተሰጠች ናት፡፡''            [ከውስጥ ገጽ....] 📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 Join us ◉Telegram t.me/FinoteBooks1623 ◉Facebook facebook.com/FinoteBooks1623 ◉Tiiktok tiktok.com/@finotebooks1623

➧ጌታ ኾይ... መቼ ነው የምትመጣው?" ✔️ ይህ ጥያቄ ዛሬ በአንድ እምነት ተከታዮች አንደበት ብቻ የሚሰማ አይደለም። ✔️ ዛሬ ዓለም በምትቃጠልበት ሰብአዊነት በጠፋበትና ፍቅር በበረደበት በዚኽ ዘመን የሰው ልጅ ኹሉ የጋራ ጩኸት ኾኗል። ✔️ ደብረ ዘይት ክርስቶስ በተራራው ላይ ተቀምጦ ስለ መጨረሻው ዘመን ያስተማረበት፣ ስለ ፍቅር መቅዘቅዝና ስለ መከራ መብዛት የተናገረበት ዕለትነው ። ✔️ዛሬ ግን ያ'' ትምህርት ከታሪክ በላይ ኾኖ በቤታችን አንኳክቷል። 👉እስኪ ቆም ብለን እናስተውል፦ ✔️ እናቶች "ልጄ የት ገባ?" ብለው ደጃፍ ላይ ሲቀሩ... ✔️ንጹሐን "ለምን?" የሚል ጥያቄ ሳይመለስላቸው በከንቱ ሲረግፉ... ✔️ወንድም ለወንድሙ ማረፊያ ሳይኾን መከራ ሲኾንበት... ✔️ ዓለም በረኀብ ፣ በጦርነትና በጭካኔ ስትናወጥ... በቃላችን "ጌታ ኾይ መቼ ነው የምትመጣው?" እንላለን። ✔️ ነገር ግን እርሱ መጥቶ የሚያርፍበት "የፍቅር ልብ" በውስጣችን አለ ወይ? . ✔️ የደብረ ዘይት ትምህርት ዛሬ የሚገሥጸን ስለ መለያየታችን ነው። እርሱ "ኹላችኹም ወንድማማቾች ናችኹ" ሲለን እኛ ግን በሰውነታችን መተያየት አቅቶን በልዩነት ግንብ ታጥረናል። ✔️ ይህ ጽሑፍ የሁላችንም ይኹን፦ ዛሬ የምናፈሰው ዕንባ የሃይማኖት ወይም የዘር ዕንባ አይደለም። የሰው ልጅነት ዕንባ እንጂ። ደብረ ዘይት የፍርድ ቀን መታሰቢያ እንደመሆኑ ''ነገ በፊቱ ስንቆም" ወንድምኽ የታለ?" ተብለን ስንጠየቅ ምን እንመልሳለን? ✔️"ጌታ ኾይ... ዓለም ጨለመችብን። ✔️ብርሃንኽ ይውጣላት። በልባችን የፈሰሰው የጥል መርዝ ደርቆ የፍቅር ምንጭ ይፍለቅ። ✔️በሰውነታችን ብቻ እንድንከባበር '' በስቃያችን ብቻ እንድንተዛዘን አድርገን።" 👉 ሙሽራው መጣ! ሲባል መብራታችን የበራው በሃይማኖት ስም በመከፋፈል ሳይኾን፣ ሰውን በመውደድና በምሕረት ዘይት ይኹን። ©️ነቅዐ-ጥበብ ገሰሰ ፥ የጉባኤ ደብረ ምጥማቅ የብሉይ ደቀመዝሙር

💧 አዲስ መጽሐፍ በቅርብ ቀን #ጸሐፊ፦ አባ ማቴዎስ ምስኪኑ #ትርጉም - ገ/እግዚአብሔር ኪደ 📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት
💧 አዲስ መጽሐፍ በቅርብ ቀን #ጸሐፊ፦ አባ ማቴዎስ ምስኪኑ #ትርጉም - ገ/እግዚአብሔር ኪደ 📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 ◉Telegram t.me/FinoteBooks1623 ◉Facebook facebook.com/FinoteBooks1623 ◉Tiiktok tiktok.com/@finotebooks1623

➮አዲስ መጽሐፍ በገበያ ላይ 📚#ሳምራዊቷ_ሴት📚 [በመምህር ኢዮብ በቀለ ዘገነተ ጽጌ ] «ጌታ ሆይ! ብዙ ጊዜ ጥማቴን ለመቁረጥ ከኃጢአት ኩሬ ጠጣሁ፤ ነገር ግን ይበልጥ ተቃጠልኩ። ደስታን ፍለጋ ወ
አዲስ መጽሐፍ በገበያ ላይ 📚#ሳምራዊቷ_ሴት📚 [በመምህር ኢዮብ በቀለ ዘገነተ ጽጌ ] «ጌታ ሆይ! ብዙ ጊዜ ጥማቴን ለመቁረጥ ከኃጢአት ኩሬ ጠጣሁ፤ ነገር ግን ይበልጥ ተቃጠልኩ። ደስታን ፍለጋ ወደ ዓለም ሄድኩ ነገር ግን በደረቅ ምድረ በዳ እንደቆመ ዛፍ ሆንኩ። አቤቱ መሐሪው ጌታ ሆይ በጨው ውሃ የተመሰለውንና በጠጣሁት ቁጥር ይበልጥ የሚያስጠማኝን የክፋትና የዝሙትን መንገድ ከእኔ አርቅ። ልቤ በዓለም ፍቅር እንዳይደርቅ በጸጋህ ጠል (ዝናብ) አርጥበው። በደካማነቴ ምክንያት የደረቀችውንና የጠወለገችውን ሕይወቴን አንተ በቃለ ወንጌልህ አቅልምልኝ። የሕይወት ውሃ ሆይ! በሳምራዊቷ ሴት ልብ ውስጥ እንደፈለቅህ በእኔም ልብ ውስጥ የፍቅር የትዕግሥትና የቅድስና ምንጭ ሆነህ ፍለቅ። ዛሬም ሆነ ዘወትር ለነፍሴ የምሰጠው መጠጥ አንተን መውደድና አንተን ማገልገል ይሁን። አንተን ያገኘ ከቶ አይጠማም በአንተ ያረፈም ዳግመኛ አይራብም። ጌታ ሆይ! በቃላት ልገልጸው ከምችለው በላይ ለምህረትህ የጠማሁ ነኝና በቸርነትህ ውሃ ሕይወቴን ቀድሳት።ልቤም አንተን በማግኘት ትርካ ሕሊናዬም በአንተ ቅዱስ ቃል ይረሰርስ።ለዘላለም ለማይጠማው የሰላም ምንጭ ለሆነው ለአንተ ክብርና ምስጋና ይሁን።» [ከውስጥ ገጽ] 📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 ◉Telegram t.me/FinoteBooks1623 ◉Facebook facebook.com/FinoteBooks1623 ◉Tiiktok tiktok.com/@finotebooks1623

➮አዲስ መጽሐፍ በገበያ ላይ 📚#ሳምራዊቷ_ሴት📚 [በመምህር ኢዮብ በቀለ ] «ጌታ ሆይ! ብዙ ጊዜ ጥማቴን ለመቁረጥ ከኃጢአት ኩሬ ጠጣሁ፤ ነገር ግን ይበልጥ ተቃጠልኩ። ደስታን ፍለጋ ወደ ዓለም ሄድ
አዲስ መጽሐፍ በገበያ ላይ 📚#ሳምራዊቷ_ሴት📚 [በመምህር ኢዮብ በቀለ ] «ጌታ ሆይ! ብዙ ጊዜ ጥማቴን ለመቁረጥ ከኃጢአት ኩሬ ጠጣሁ፤ ነገር ግን ይበልጥ ተቃጠልኩ። ደስታን ፍለጋ ወደ ዓለም ሄድኩ ነገር ግን በደረቅ ምድረ በዳ እንደቆመ ዛፍ ሆንኩ። አቤቱ መሐሪው ጌታ ሆይ በጨው ውሃ የተመሰለውንና በጠጣሁት ቁጥር ይበልጥ የሚያስጠማኝን የክፋትና የዝሙትን መንገድ ከእኔ አርቅ። ልቤ በዓለም ፍቅር እንዳይደርቅ በጸጋህ ጠል (ዝናብ) አርጥበው። በደካማነቴ ምክንያት የደረቀችውንና የጠወለገችውን ሕይወቴን አንተ በቃለ ወንጌልህ አቅልምልኝ። የሕይወት ውሃ ሆይ! በሳምራዊቷ ሴት ልብ ውስጥ እንደፈለቅህ በእኔም ልብ ውስጥ የፍቅር የትዕግሥትና የቅድስና ምንጭ ሆነህ ፍለቅ። ዛሬም ሆነ ዘወትር ለነፍሴ የምሰጠው መጠጥ አንተን መውደድና አንተን ማገልገል ይሁን። አንተን ያገኘ ከቶ አይጠማም በአንተ ያረፈም ዳግመኛ አይራብም። ጌታ ሆይ! በቃላት ልገልጸው ከምችለው በላይ ለምህረትህ የጠማሁ ነኝና በቸርነትህ ውሃ ሕይወቴን ቀድሳት።ልቤም አንተን በማግኘት ትርካ ሕሊናዬም በአንተ ቅዱስ ቃል ይረሰርስ።ለዘላለም ለማይጠማው የሰላም ምንጭ ለሆነው ለአንተ ክብርና ምስጋና ይሁን።» [ከውስጥ ገጽ] 📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 ◉Telegram t.me/FinoteBooks1623 ◉Facebook facebook.com/FinoteBooks1623 ◉Tiiktok tiktok.com/@finotebooks1623

📚#የልቡና_ችሎት [የክርስትና~እስልምና ተዋሥኦዎች በመካከለኞቹ ዘመናት ] .....አሁን አሁን የክርስትና~አስልምና ተዋሥኦዎች መቀስቀሳቸውን ተከትሎ የቀደሙ ድርሳናት አየተፈለጉ እየተጠኑና አየተተረ
📚#የልቡና_ችሎት [የክርስትና~እስልምና ተዋሥኦዎች በመካከለኞቹ ዘመናት ] .....አሁን አሁን የክርስትና~አስልምና ተዋሥኦዎች መቀስቀሳቸውን ተከትሎ የቀደሙ ድርሳናት አየተፈለጉ እየተጠኑና አየተተረጎሙ ናቸው።#ይህ_መጽሐፍም የዚህ ዐለም አቀፍ የክርስቲያኖች አንድ ተግባር አንድ አካል አንደሆነ ይሰማኛል። መጽሐፉ በተለያዩ ዘመናት የነበሩ የዐረቡ ዐለም የአስልምና እና የክርስትና ሊቃውንት መካከል የተመረጡትን ታሪካቸውን፣ የተከራከሩባቸውን ጉዳዮች አና በተለይም ደግሞ ከአስልምና ሊቃውንት በተነሡ መሠረታዋ ጥያቄዎች የዐረብ ክርስቲያን ሊቃውንት የመለሷቸውን አስደናቂ መልሶች የያዘ ግሩም መጽሐፍ ነው። በዚህ ዘመን ያለነው ክርስቲያኖች በዘመናት የተንሸራሸሩትን ጥያቄዎችና መልሶች ብቻ ሳይሆን በየዘመናቱ የነበሩትም ሰላማዊ አና ዕውቀታዊ ክርክሮች ተረድተን በመዘጋጀት ከፈለግን በምንም መንገድ ሊያመልጡን ከማይገቡት መጸሕፍት አንዱና ዋናው ይህ በወንድማችን በረከት አዝመራው የተዘጋጀው «የልቡና ችሎት» መጽሐፍ አንደሆነ አምናለሁ። [✍️ብርሃኑ አድማስ በሥነ ድርሳን ሁለተኛ ዲግሪ] 📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 ◉Telegram t.me/FinoteBooks1623 ◉Facebook facebook.com/FinoteBooks1623 ◉Tiiktok tiktok.com/@finotebooks1623

በድጋሚ ታትሟል.. 📚#ማስያስ 📚 ....ረከብናሁ ለማስያስ” ሐዋርያው በሲቃ የተናገረው ቃል ነው (ዮሐ.1፡41)፡፡ ባሕርያችንን ባሕርይ አድርጎ፣ ከእኛ እንደ አንዱ ሆኖ አገኘነው፡፡ ቃል ሥጋ ሆነ
በድጋሚ ታትሟል.. 📚#ማስያስ 📚 ....ረከብናሁ ለማስያስ” ሐዋርያው በሲቃ የተናገረው ቃል ነው (ዮሐ.1፡41)፡፡ ባሕርያችንን ባሕርይ አድርጎ፣ ከእኛ እንደ አንዱ ሆኖ አገኘነው፡፡ ቃል ሥጋ ሆነ፡፡ ረቂቁ ገዘፈ፡፡ በሥነ ፍጥረት የምናውቀው አምላክ በሥጋ ብእሲ ታየ፤ ተዳሰሰ፡፡ ቃል ሥጋ ሆነ፡፡ በእርሱ ሥጋን መዋሐድ የሥሉስ ቅዱስ አንድነትና ሦስትነት ታወቀ፤ ተረዳ፡፡ ወደመለኮታዊ ክብሩ በቸርነቱ ሳበን። በተወደደ ሥርዓተ አምልኮ በምንሳተፍበት ቅዱስ ቍርባኑ አቀረበን፡፡ በቸርነቱ የመለኮታዊ ክብሩ ተካፋዮች አደረገን፡፡ በየዘመናቱ በልዩ ልዩ አምሳል በመገለጥ፣ ኋላም ባሕርያችንን ባሕርይ በማድረግ ሥጋውን ቆርሶ ደሙን አፍስሶ ይኸው ምሥጢር የሚፈጸምባትን ቤተ ክርስቲያን በመመሥረት ወደራሱ አቀረበን፡፡ ቀድሞ በጥላ የምናውቀውን በአካል አገኘነው፤ ረከብናሁ ለማስያስ፡፡ የዚህ የታናሽ ወንድማችን መጽሐፍ ማጠንጠኛዋ እንደዚህ ይመስለኛል፡፡ መጽሐፏ ከብሉይ እስከ ሐዲስ፤ ከአእምሮ ጠባይዕ እስከ አእምሮ መንፈሳዊ፤ ከሃይማኖተ ሰሚዕ እስከ ሃይማኖተ ርእይ፤ ከምሳሌ እስከ ፍጻሜ ክርስቶስን ለማሳየት መሞከር፡፡ አስቀድማ በጥንተ ተፈጥሮ፤ በዕውቀትና ሃይማኖት፤ በብሉይ አምሳላት ሁሉ ጥላውን ታሳየናለች፤ ኋላ ደግሞ በኩነተ ሥጋ በአካል “ረከብናሁ ለማስያስ” ታሰኘናለች፡፡ መጽሐፏ ረቂቅ የነገረ መለኮት ሐሳቦችን በውብ፣ ቀላልና ለዚህ ትውልድ በሚገባ ቋንቋ በምጥን ይዘት ታቀርባለች፡፡ አንብቦ ለመጠቀም ያብቃን፡፡ መልካም ንባብ! ✍️[በአማን ነጸረ ደብተራና የሕግ ባለሙያ] 📚ፍኖተ መጻሕፍት [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 Join us ◉Facebook facebook.com/FinoteBooks1623 ◉Tiiktok tiktok.com/@finotebooks1623