ru
Feedback
The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus - EECMY

The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus - EECMY

Открыть в Telegram

The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus (EECMY) is a national Lutheran church with more than 10 million members.

Больше
3 498
Подписчики
-124 часа
+97 дней
+10930 дней
Архив постов
Ayyaana Yaadannoo Dhaloota Gooftaa Keenya Yesuus Kiristoos kan bara 2018 ilaalchisee Ergaa Uummata biyyattii maraaf darbe Waldaa Kiristiyaanaa Warra Wangeelaa Makane Yesus Itiyophiyaa Luba Dr. Yonas Yigazu Pirezedaantii Waldaa WWMI Muddee 27/2018

የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የ2018 ዓ.ም የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት መታሰቢያ በዓል የመልካም ምኞት መልዕክት ቄስ ዶ/ር ዮናስ ይገዙ የቤተ ክርስቲያኒቱ ፕሬዚዳንት ታህሳስ 27 / 2018

ሁለንተናዊ የልጆችና ወጣቶች አገልግሎት ስልጠና በማዕከላዊ ሰሜን ኢትዮጵያ ሲኖዶስ ተሰጠ። 'ሁለንተናዊ ዕድገት ለልጆች እና ወጣቶቻችን' በሚል ርዕስ የተዘጋጀው ስልጠና በማዕከላዊ ሰሜን ኢትዮጵያ ሲኖዶስ በሲኖዶሱ ማዕከል ደሴ ከተማ ተሰጥቷል። ስልጠናው የተሰጠው ከሲኖዶሱ ጋር በመተባበር በዋናው ጽ/ቤት የልጆች እና ወጣቶች አገልግሎት መምሪያ በኩል ሲሆን ከሲኖዶሱ ሁሉም ማ/ምዕመናናት የተወጣጡ መሪዎች እና የልጆችና ወጣቶች አገልጋዮች ተሳትፈዋል:: ከስልጠናው ጎን ለጎን ለልጆች እና ወጣቶች አገልግሎት የሚጠቅሙ ታቅዶ እየተሰራበት ላለው ቤተመጻህፍትን በእያንዳንዱ ማህበረ ምዕመናን የማስጀመር ራዕይ የሚረዱ የልጆች መጽሐፍ ቅዱሶች፣ የወጣቶች ማስተማርያ መጽሐፍቶች፣ ለአገልጋዮች እና ምዕመናን፣ ለደቀመዛሙርትነት እና ለሌሎች ለቤተክርስቲያን ስነ መለኮታዊ አስተምህሮ የሚረዱ የተለያዩ መጽሐፍቶች በመምሪያው በኩል በድጋፍ መልክ ተሰጥቷቸዋል:: የቤተክርስቲያኒቱ የልጆች እና ወጣቶች አገልግሎት መምሪያ ዳይሬክተር ቄስ ወንድማገኝ ኡዴሣ የተለያዩ መንፈሳዊ መጽሐፍትን ለቤተክርስቲያኒቱ ድጋፍ ያደረጉትን ተቋማት ' Rafiki Foundation' እና ' Lutheran Heritage Foundation ' እና ሌሎችንም በማመስገን : መጽሐፍቶቹን ለቤተክርስቲያኒቱ ማ/ምዕመናናት፣ ሴሚናሪዎች፣ መጽሐፍ ቅዱስ ኮሌጆች እና ት/ቤቶች ከተባባሪ ድርጅቶች ጋር በመሆን ድጋፍ የማድረጉ ስራ እንደሚቀጥል ገልጸዋል። በስልጠናው የተሳተፉ የሲኖዶሱ መሪዎችም ስልጠናው የልጆች እና ወጣቶች አገልግሎትን ጊዜው በሚፈልግ መልኩ ለማሳደግ አስፈላጊ እና ወቅቱን ያገናዘበ መሆኑን ገልጸው ሰልጣኞች በወሰዱት ስልጠና መሰረት ወደ ተግባር መቀየር እንዳለባቸው አጽንኦት ሰጥተው መልዕክት አስተላልፈዋል:: ከስልጠናው በኃላ በደሴ መካነ ኢየሱስ ሁሉንም ምዕመናን ያሳተፈ በቤተሰብ፣ ልጆች እና ወጣቶች ላይ ትኩረት ያደረገ ትምህርታዊ ኮንፈረንስ ተካሂዷል። በተቀሩት የቤተክርስቲያኒቱ ሲኖዶሶችም ተመሳሳይ ስልጠና ከሲኖዶሶች ጋር በመተባበር የሚቀጥል ይሆናል:: 📷 : Nahom, Dessie Congregation 🙏! EECMY Youth Ministry EECMY Children Ministry - MY Sunday School

የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የሴቶች አገልግሎት መምሪያ የመሪዎችና አገልጋዮች ሥልጠና በሆሳህና ከተማ አካሂዷል። ጎጂ ባህላዊ ልምምዶችን እና ህገወጥ የሰው ልጅ ዝውውርን መከለካል ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ለሲኖዶስ አመራሮች እና ከተለያዩ ሰበካዎች ለተወጣጡ አገልጋዮች ከታህሳስ 9-10, 2018 ዓ.ም በሆናህና ከተማ ተሰጥቷል። በስልጠናው ሶስት የሥራ ዘርፎች የተካፈሉ ሲሆን የሲኖዶሱን ጽሕፈት ቤት በሆሳህና ከተማ ያደረገው ማዕከላዊ ደቡብ ሲኖዶስ፣ አርባ ምንጭ እና ምዕራብ ጊቤ ሲኖዶሶች ተካፍሏል። ስልጠናውም ጎጂ ባህላዊ ድርጊቶችን እና በከፍተኛ ደረጃ እየተስተዋለ የሚገኘውን ህገወጥ የሰዎች ሀገር አቀፍ እና አለም አቀፍ ዝውውሮችን ምዕመናን መከላከል እንዲችሉ በአገልጋዮቻቸው በኩል ግንዛቤን የማስጨበጥ አላማ ያደረገ ሥልጠና መሆኑን የመምሪያው ዳይሬክተር ቄስ ታገሰች ዳኘው ገልጸዋል።

የ"ድንቅ መካር" የመዝሙር አልበም ምርቃት ጥሪ በልዩ የዝማሬ አገልግሎቱ የምናውቀው የኮተቤ መካነ ኢየሱስ ማህበረ ምዕመናን አገልጋይ የሆነው ዘማሪ ታማኝ ሙሉነህ ከሁለት አመት በላይ በዝግጅት ላይ የነበረውን ሁለተኛ ቁጥር አልበሙን ያስመርቃል። "ድንቅ መካር" በሚል ርዕስ የተዘጋጀው አልበም በውስጡ 13 ዝማሬዎችን የያዘ ሲሆን የቤተ ክርስቲያናችን አባላት እና መላው የወንጌል አማኞች በተጋበዙበት መርሃ ግብር የፊታችን ቅዳሜ ታህሳስ 26 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 10:00 ሰዓት ጀምሮ በኋልዎት አማኑኤል አጥቢያ የአምልኮ አዳራሽ በድምቀት ይመረቃል። ሙሉ ሥነ-ሥርዓቱም በተለያዩ የሚድያ አማራጮ በቀጥታ ሥርጭት የሚተላለፍ መሆኑን ዘማሪው አስታውቋል።