5killo Jem'a official Channel
Открыть в Telegram
This is the official channel of AAiT jem'a where we provide info abt 👉Jem'a Tutors 👉Trainings and Da'ewa programs 👉Weekly lunches and halaqas(circles) 👉qira'ts (Qur'an and other Kitabs) 👉Weekly Q&A sessions Group: https://t.me/+cw97UaRUF1YzMTg0
Больше1 161
Подписчики
Нет данных24 часа
+37 дней
+730 день
Архив постов
ከፓናሊስቶቻችን 3 - ኡስታዝ ሺሐቡዲን ሸይኽ ኑራ!
የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን በባህርዳር ዩኒቨርስቲ በሰሩበት ወቅት የጀመዓው አሚር ነበሩ። የዚያኔ ስለሙስሊም ተማሪዎች የታገሉ ሲሆን ደማቅ አሻራን አሳርፈው አልፈዋል። ወደ ሌሎች ዩኒቨርስቲዎች በማምራትም የተለያዩ ድግሪዎችን ሰርተዋል። በአራት የተለያዩ ዲፓርትመንቶች የማስተርስ ዲግሪ አላቸው። በአሁኑ ሰዓትም የPHD ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ነው።
ከዚህም ባሻገር የአዲስ አበባ መጅሊስን በምክትል ፕሬዚዳንትነት፤ ኢምፓክት ሜከርስ ፋውንዴሽንን በዳይሬክተርነት እየመሩ ጉልህ አስተዋፅዕ በማበርከት ላይ ናቸው። ለተለያዩ ተቋማትም የአመራርነት ስልጠናን በመስጠት ብቁ መሪዎች ይኖሩ ዘንድ ተግተው እየሰሩ ነው።
ኡስታዝ ሺሐቡዲን ሸህ ኑራ
የኢትዮጵያ ሙስሊም ተማሪዎች በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ ያላቸው መብቶች በሚል ርዕስ በመጪው እሁድ ከጧቱ 2:30 ጀምሮ ጦርሓይሎች በሚገኘው ረያን መስጂድ በተዘጋጀው የፓናል ውይይት ላይ ፓናሊስት ናቸው።
ቀጠሯችንን ከዚያው እናድርግ። በሰዓቱ እንገኝ! ለተሻለ ነገ መሠረት የምንጥልበትን ዛሬ እንያዝ!!
ዝግጁ ?! የኢማም አሕመድ ልጆች ዝግጁ?! የጦልሓ ጀዕፈር ምትኮች ዝግጁ?! የኡሙአይመን ልጆች _ ዝግጁ?!!!
@aaumsu
የፓናሉ መሪ _ ዲኑ ዓሊ !
የሚዲያ ባለሙያ ነው። በሙስሊሞች ላይ አንዳች የመብት ጥሰት ሲፈፀም ከፊት ለፊት ይገኛል። ኸይር ፈላጊ የሚልን ተቋም አቋቁሞ ማህበረሰቡን በማስተባበር ብዙ መስጂዶችን እና መድረሳዎችን ገንብቷል። በርካታ የውሐ ጉድጓዶችንም በገጠሩ የሀገራችን ክፍል በማስቆፈር ለብዙዎች ደርሷል።
ከዚህም ባሻገር በተለያዩ ኸይር ስራዎች ተፅዕኖ ሲፈጥር ይታወቃል። "የኢትዮጵያ ሙስሊም ተማሪዎች በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ ያላቸው መብቶች!" - በሚል ርዕስ ያዘጋጀነው የፓናል ውይይት ላይ የፓናሉ መሪ ሆኖ ቀርቧል። እሁድ ሰኔ 7 / 2018 ዓ.ል ከጧቱ 2:30 ጀምሮ ጦርሓይሎች በሚገኘው ረያን መስጂድ በሚካሄደው ፕሮግራም ላይ ማለት ነው።
በሰዓቱ እንገኝ! ከቀደምቶች የሚገኝን ልምድ በመቅሰም ስለአሁኑ በደንቡን የምንሰራበትን ስንቅ እንሸምት ዘንድ። በዳዮችን በመጋፈጥ ረገድ ሊያገለግለን የሚችልን እውቀት እንይዝ ዘንድ። ፍትሕ እንዲሰፍን በምናደርገው ትግል ውስጥ የሚጠቅመንን ነገር እናገኝ ዘንድ።
ዝግጁ? ያኡመተ-ሙሐመድ! የሱመያ ልጆች ... የቢላል ወራሾች _ ዝግጁ?!
@aaumsu
በፍትሕ ይመሩን ዘንድ ከቦታው የተቀመጡ ባለከፍተኛ ማዕረግተኞች የማይመስል ምክንያትን አቅርበው መብታችንን በመመሪያ አገዱ። ዶክተር የሚልን ማዕረግ የያዙ ሰዎች ተሰብስበው ሐይማኖታዊ መገለጫችንን የደህንኑት ስጋት ነው፤ መማር ማስተማርን ያደናቅፋል፤ ለአገልግሎት አያመችም የሚልን ምክንያት በመደርደር ሐይማኖታችንን ሰደቡ፤ ተማሪዎቻችንንም አንገላቱ፤ ከትምህርት እንደናቀፍ ዘንድ፤ የደህንነት ስጋት ይሰማን ዘንድ፤ አገልግሎት በአግባብ እንዳናገኝ ሰሩ። ጥያቄያችንን በሰላማዊ መንገድ ልንጠይቅ ስንሰበሰብ ንቀውን ዝም አሉ። ሆኖም በፅናት እስከ ምሽት ቀጠልን። በጥያቄያችን ስንገፋም "ሰብስበን አባረን ገበሬ ትሆናላችሁ!" አሉን።
አልደረስንባቸውም .. የደረሱብን እነርሱ ናቸው። የጣስነው ሕግ የለም ... ሕገ-መንግስቱን የሚጥስ መመሪያ ያወጡት እነርሱ ናቸው። መብቱን የነካንበት አካል የለም ... መብታችንን የጣሱት እነርሱ ናቸው።
ይህ የለመዱት ቢሆንም ... ልማድ አይሆንም ብለን ተነስተናል። በእኛ ቀደምቶች ላይ የደረሰ ቢሆንም ... ልጆቻችን ላይ አይደርስም ብለናል። ሀላፊነቱ የእኛ ነው ... መመሪያውን ያወጡበትን ቀን እስኪረግሙ፤ ተፀፅተውም መመሪያውን እስኪያሻሽሉ፤ መብቶቻችንን የጣሱ አካላት እስኪጠየቁ ድረስ እንሰራለን፤ ሳንታክት ... ሳንደክም ... ሳናርፍ እንሰራለን።
"የኢትዮጵያ ሙስሊም ተማሪዎች በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ ያላቸው መብቶች !"
ጦርሓይሎች
ረያን መስጂድ
እሁድ 07 / 2018 ዓ.ል
ከጧቱ 2:30 ጀምሮ
እንሰባሰብ!
አላህ ይጨመርበት!! ለዚህ መንገድ የማንሰስተውን ጥንካሬም ያድለን!!!
@aaumsu
በባለቤቱ የተበደለ ፈረስ እያነባ ለነቢ ስሞታ አቀረበ ... እርሳቸውም ዝም አላሉትም ... ፍትሕ ይሰፍን ዘንድ ከባለቤቱ በመሄድ መደረግ ያለበትን አደረጉ --- የእኛ ነብይ እንዲህ ናቸው ... ከሰው ዘር አልፈው ለተበደሉ እንስሳት ጥብቅና የሚቆሙ ... ፍትሕ እንዲሰፍንላቸው የሚተጉ ነብይ ነበሩ ...
በደልን እንድንፀየፍ አስተማሩን
ከበዳይ ፊት ሐቅን መናገር ከጂሐድ እንደሆነ አስተማሩን
ፍትሕ ይሰፍን ዘንድ በአንድነት እንድንሰባሰብ አስተማሩን
በእርሳቸው ላይ ሰለዋት አውርዱ
አላሁመ ሶሊ ወሰሊም ወባሪክ ዓላ ሙሐመድ !😍!
የእርሳቸው ኡማ እንደመሆናችን በትምህርት ተቋማት ውስጥ በሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ስላለው የመብት ጥሰት ዝም አንልም። ፍትሕ እስኪሰፍን እንጠይቃለን ... ፍትሕ እስኪሰፍን እንሰራለን ... ፍትሕ እስኪሰፍን እንሰባሰባለን ... ፍትሕ እስኪሰፍን መደረግ ያለበትን ሁሉ እናደርጋለን!!
በመጪው እሁድ ሰኔ 07 / 2018 ዓ.ል ከጧቱ 2:30 ጀምሮ ጦርሓይሎች በሚገኘው ረያን መስጂድ እንገናኝ ! !
©aaumsu
ከፓናሊስቶቻችን 2 - አብዱልጀሊል ሸህ ዓሊ ካሳ !
የመጀመሪያ ዲግሪውን ከሀረማያ ዩኒቨርስቲ ወስዷል። ሁለተኛ ዲግሪውን ባህር ማዶ ተሻግሮ በጣሊያን ሰርቷል። ኪነት-ያገነነው አፄ፤ ተምኔታዊት ደሴት እና እስልምና በኢትዮጵያ ከቅድመ ክርስቶስ እስከ ዛሬ የሚሉ ዘመን ተሻጋሪ መፅሐፍትን ለማህበረሰቡ በማበርከት ጉልህ አስተዋፅዖ አበርክተዋል።
ከዚህ ባሻገር በተለያዩ የሚዲያ ፕላትፎርሞች ላይ ሕዝበ ሙስሊሙን በማንቃት ይታወቃሉ። "የኢትዮጵያ ሙስሊም ተማሪዎች በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ ያላቸው መብቶች!" - በሚል ርዕስ በመጪው እሁድ ከጧቱ 2:30 ጀምሮ ጦርሓይሎች በሚገኘው ረያን መስጂድ ያዘጋጀነው የፓናል ውይይት ላይ ከፓናሊስቶች መካከል ሲሆኑ ስለሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥሰት ታሪካዊ ዳራ እና አሁናዊ መፍትሔ ጥልቅ እይታቸውን ያጋሩናል።
በሰዓቱ እንገኝ ... ታሪክን ከማወቅ ባሻገር ታሪክ እየሰሩ ካሉ ምሁራን ትላንታችንን እንወቅ፤ ዛሬያችንን እንረዳ፤ ስለነጋችን እናልም። የትላንቶቹ የሰሩትን እውቅና በመስጠት ዛሬን በመስራት ልናልፍ ቃልኪዳን አለንና ቃላችንን እንሞላ ዘንድ ከሚያሰባስበን መድረክ እንክተም።
ሁሉም ይገኝ ... ከሀይስኩል እስከ ኮሌጅ ... ከመድረሳ እስከ ዩኒቨርስቲ ተማሪ ይገኝ ... የተማሪ ወላጅም ይገኝ ... ወላጅ ያልሆነም ይገኝ ... ሁሉም ይገኝ! ስለጋራ አጀንዳችን በጋራ ተሰባስበን በጋራ እንምከር!!!
ዝግጁ?!
@aaumsu
ከፓናሊስቶቻችን 2 - አብዱልጀሊል ሸህ ዓሊ ካሳ !
የመጀመሪያ ዲግሪውን ከሀረማያ ዩኒቨርስቲ ወስዷል። ሁለተኛ ዲግሪውን ባህር ማዶ ተሻግሮ በጣሊያን ሰርቷል። ኪነት-ያገነነው አፄ፤ ተምኔታዊት ደሴት እና እስልምና በኢትዮጵያ ከቅድመ ክርስቶስ እስከ ዛሬ የሚሉ ዘመን ተሻጋሪ መፅሐፍትን ለማህበረሰቡ በማበርከት ጉልህ አስተዋፅዖ አበርክተዋል።
ከዚህ ባሻገር በተለያዩ የሚዲያ ፕላትፎርሞች ላይ ሕዝበ ሙስሊሙን በማንቃት ይታወቃሉ። "የኢትዮጵያ ሙስሊም ተማሪዎች በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ ያላቸው መብቶች!" - በሚል ርዕስ በመጪው እሁድ ከጧቱ 2:30 ጀምሮ ጦርሓይሎች በሚገኘው ረያን መስጂድ ያዘጋጀነው የፓናል ውይይት ላይ ከፓናሊስቶች መካከል ሲሆኑ ስለሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥሰት ታሪካዊ ዳራ እና አሁናዊ መፍትሔ ጥልቅ እይታቸውን ያጋሩናል።
በሰዓቱ እንገኝ ... ታሪክን ከማወቅ ባሻገር ታሪክ እየሰሩ ካሉ ምሁራን ትላንታችንን እንወቅ፤ ዛሬያችንን እንረዳ፤ ስለነጋችን እናልም። የትላንቶቹ የሰሩትን እውቅና በመስጠት ዛሬን በመስራት ልናልፍ ቃልኪዳን አለንና ቃላችንን እንሞላ ዘንድ ከሚያሰባስበን መድረክ እንክተም።
ሁሉም ይገኝ ... ከሀይስኩል እስከ ኮሌጅ ... ከመድረሳ እስከ ዩኒቨርስቲ ተማሪ ይገኝ ... የተማሪ ወላጅም ይገኝ ... ወላጅ ያልሆነም ይገኝ ... ሁሉም ይገኝ! ስለጋራ አጀንዳችን በጋራ ተሰባስበን በጋራ እንምከር!!!
ዝግጁ?!
@aaumsu
ከፓናሊስቶቻችን ! - 1
በሕግ ትምህርት ረዳት ፕሮፌሰር ናቸው። በሕገ-መንግስታዊ ሕጎች ዙሪያ አሉ ከሚባሉ ምሁራን ነው። በወሎ ዩኒቨርስቲ ሕግን እያስተማሩ ከመሆናቸው ባሻገር በፕሪቶሪያ ዩኒቨርስቲ እጩ የሕግ ዶክተር ናቸው። በ Ethiopian Civil Society Organizations Council ፖሊሲ ዳይሬክተር በመሆን እያገለገሉ ነው።
ፕሮፌሰር ዘላለም እሸቱ ...
በተለያየ መድረክ በተለይም በሴኩላሪዝም እና መሠል ርዕሶች ዙሪያ ጥልቅ የሕግ እውነታዎችን በማቅረብ ይታወቃሉ። "የኢትዮጵያ ሙስሊም ተማሪዎች በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ ያላቸው መብቶች!" - በሚል ርዕስ በመጪው እሁድ ከጧቱ 2:30 ጀምሮ ጦርሓይሎች በሚገኘው ረያን መስጂድ ያዘጋጀነው የፓናል ውይይት ላይ ከፓናሊስቶች መካከል ሲሆኑ መሠረት የሚሆኑንን ምልከታዎች ያጋሩናል።
ለመገኘት፣ ለመማር፣ ለመጠየቅ ዝግጁ ናችሁ? ደግሞም እርሳቸው ብቻ አይደሉም። ሌሎች ምሁራንም ተጋብዘዋል። የምናሳውቅ ይሆናል።
የሀይስኩል ተማሪዎች ዝግጁ?
የAAU እንቁዎች ዝግጁ?!
የኮሌጅ ተማሪዎች ዝግጁ?!!
ያኡመተ-ሙሐመድ ዝግጁ?!!!
እንሰባሰብ፣ ድምፃችንን እናዋህድ፤ ስለአንድ አላማ በአንድነት እንሰለፍ፤ በሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለውን በደል ታሪክ እናድርግ!!!
@aaumsu
ክቡራን የ2018 ዓ.ም የAAU ሙስሊም ተመራቂ ተማሪዎች፤ ቀደም ሲል ያሳወቅናችሁ የልዩ የምረቃ ሪቫን ምዝገባ አሁንም በከፍተኛ ሁኔታ ቀጥሎ የሚገኝ መሆኑን እያበሰርን፣ ካባችሁን በባዶ አንገት ከመልበስ ይልቅ ከሪቫኑ ጋር አብሮ የተዘጋጀውን ውብ ባይንደር (Binder) ጨምረው ማዘዝ እንደሚችሉ እናስታውሳለን።
ምዝገባው ከመጠናቀቁ በፊት ዕድሉን በመጠቀም ስምዎን ከነ አባት ስም ጋር፣ ካምፓስዎን እና ስልክ ቁጥርዎን ለቴሌግራም ቦታችን @Niqab_issueBot በመላክ በፍጥነት ይመዝገቡ። ሌላ ቦታ በመሄድ ሳይንገላቱ የራሳችንን መለያ የያዘውን ጥራት ያለው ሪቫንና ባይንደር በአንድ ላይ በመረጡት ካምፓስ ድረስ እናቀርባለን።
የዩኒቨርሲቲ ቆይታችሁን በታላቅ ድል ለምትደመድሙት ተመራቂዎቻችን በሙሉ አላህ መልካም የምረቃ ዕለት እንዲያደርግላችሁ እንመኛለን።
©aaumsu
ታሪካዊው መድረክ ጥቂት ቀናት ቀርተውታል!
ቅስቀሳው ቀጥሏል፤ ዝግጅቱም ደምቋል! በመጪው እሁድ ሰኔ 07/2018 ዓ.ል በጦር ኃይሎች ረያን መስጂድ የሚካሄደው ታላቅ የፓናል ውይይት እንደተጠበቀ ነው። ይህ መድረክ የሙስሊም ተማሪዎች ሕገ-መንግስታዊ መብቶች የሚከበሩበትን፣ እንደ ኒቃብና ሒጃብ ያሉ የእምነትና የማንነት መገለጫዎች ላይ የሚሰነዘሩ ጥቃቶች በሕጋዊ መንገድ የሚመከቱበትንና ዘላቂ መፍትሔ የሚቀመጥበትን አቅጣጫ የሚያሳይ ነው። ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ (ትራንስፖርት በተዘጋጀላቸው ካምፓሶች) ጀምሮ በከተማዋ የምትገኙ የከፍተኛ ትምህርት፣ የኮሌጅና የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች በሙሉ የዚህ ታሪክ አካል እንድትሆኑ ጥሪያችን የፀና ነው። እምነታችን፣ መብታችንና ምርጫችን ይከበር ዘንድ፣ ሰኔ 7 ከጧቱ 2፡30 ጀምሮ ልባችንና አቅጣጫችን ወደ ረያን መስጂድ ይሁን። ሁላችንም ለአንድ ዓላማ በአንድነት እንሰባሰብ።
ዝግጁ ናችሁ?!👍🫡
@aaumsu
اسلام عليكم ورحمة الله وبركاته أحبابي ،
How y'all doing ?
So first of all, congrats ahbabi,am happy that the day y'all have been waiting is here and am proud of y'all like really proud of how far you've come cuz yeah those 5 years of aait was never easy but y'all did it , Allah ybarik
Second, I just wanted to say something cuz yeah
I don't want y'all to leave us before I say what I gotta say and y'all really mean a lot to me , y'all did help alot so that I become the person I am today ( I mean it ),
I don't know a lot of seniors but those whom I know and those who were with me in the campus till this year, y'all were my blessings ymr , Allah blessed me with you guys, alhamdulillah,
I really got no words to express how much you guys mean to me , you made my campus life easy, and enjoyable, I wish I could mention y'all one by one and thank you but yeah bezu nachu ena mnm bl lenante yalegnn wudeta ena kbr aygeltsm ,
You guys were like the kinda people that becomes part of our qadar after an accepted Duas , yeah and imma say it again, y'all are my accepted Duas
Am glad that I met y'all fr 😊,
Becha mn elalew Allah kenante gar yhun ,
I wish I could write more but yeah, got no words and I prefer to talk to Allah about y'all ☺️ and I'll defo talk to him ,
Happy and sad at the same time, sad cuz y'all leaving us here and going but happy cuz it's finally your happy day and the day you've been waiting for has already come, the struggle came to an end,
Ameen belu Dua lareglachu new😁 , and it's from the deepest buttom of my heart eshi 😊,
May Allah be with y'all, may Allah bless your every steps ahead,
الله يحفظكم ، ويكون معاكم، ويرزقكم من حيث تحتسبونه ومن حيث لا تحتسبونه، ربي يجعلكم من عباده الصالحين ، ربي يفتح لكم ابواب رحمته ، ربي يغفر ما تقدم من ذنبكم وما تأخر ، وربي يجزيكم عنا خير الجزاء وخاصة عني خير الجزاء 😊،
جعلنا الله واياكم من اصحاب الفردس الاعلى ،
في امان الله ورعايته ،
اختكم فالله
መልካም ምኞቶች ለተመራቂ ተማሪዎች ከታናናሾች እንደቀጠለ ነው 🎓🎓
መልካም ምኞታችሁን ፣ ትውስታ እና አስቂኝ ገጠመኞቻችሁን አጋሩን
📩 መልዕክቶቻችሁን በዚህ ቦት ብትልኩልን እዚህ channel ላይ የምናጋራው ይሆናል ፦
👇👇👇
@fivekjemaa_bot
السلام عليكم ورحمة الله وبركاته
በቅድሚያ ለመላው የ5 ኪሎ ግቢ ሙስሊም ተመራቂ ተማሪዎች በሙሉ እንኳን ለዚህ ታላቅ ቀን አደረሳችሁ ‼️‼️‼️
Congratulations 🎓🎓🎓🎓✨✨✨✨🎉
ጊዜው ሳናስበው ከዚህ አደረሰን እና እኔም ይሄዉ እናተን መሰናበቻ ጽሑፌን እፅፍ ገባሁ ይገርማል አይደል‼️ ጊዜው ሩቅ አነበረም እኮ ግቢ ስንገባ ልክ እንደ ትላንት ቅርብ ሆኖ ይታየኛል፤ ምን እንደምል አላውቅም ብቻ እስቲ አላህ ያገራልኝን ውስጤ የቋጠረውን ልበላችሁ...
👉 የ5 አመት ትግል ፣ ጥረት፣ ከፍታ_ዝቅታ ፣ ጭንቀት፣ ሐሴት ፣ ድካም እና ጥንካሬ ሕይወታችሁ ላይ አንዣበው ከዚህ አደረሷችሁ ፤ ሐቂቃ ዞር ተብሎ ሲታሰብ ቀላል አይደለም ይሄን ሁላ አልፋችሁ ለዚህ ቀን በቃችሁ አልሃምዱሊላህ ሱመ አልሃምዱሊላህ ምርቃት ቀናችሁ ደረሰኮ ያ አላህ...እስቲ በአላህ ደስ ይበላችሁ በቃ ለኔ ስትሉ ተደሰቱ 😄😄
👉 ወላህ እኔ ለእዚህ ተመራቂዎች ምለው ያጥረኛል
ግርም እኮ ነው የሚሉኝ ሰው እንዴት በዚ ደረጃ ጠንካራ ይሆናል እስቲ አስቡት ማታ 6, 7 ሰዓት ድረስ ሹራ ፣ ጠዋት ከሱብሂ በኃላ ጥናት ቀን ክላስ አልያም ክላስ ተቀጥቶ ቢሮ ለቢሮ መንከራተት ፣ፀሐይ ታክሲ....ብቻ ምን አለፍችሁ መዘርዘር ከጀመርን እኔም ስፅፍ እናተም ስታነቡ መክረማችን ነው ብቻ ይገርማል ከነዚ ብርቅዬ ወንድም/እህቶቼ ምን ትልቅ ነገር ተማርኩኝ መሰላችሁ❓ ቁዋ
አንዳንዴ እኮ ሰውነት ብቻ አይደለም ነገሮች ሲደራረቡብን ውስጣችንም ይደክማል አይደል "እንደው.. ኡፍፍፍ አሁንስ በቃኝ በቃ" እንደው የት ልግባ ማንም የማያቀኝ ማንንም ማልሰማበት ቦታ ልሂድ አይነት ስሜት እኮ feel እናደርጋለን አይደል🥹 እነዚ ግሩም ልጆች ግን በዚ ሁሉ ነገር ውስጥ አልፈው እንኳን ያላቸው energy ተስፋ ልዩ ነው በል እንደውም አብረሃቸው ስትሆን ጥንካሬያቸው ይጋባብሃላ እነሱ ፊት ደከመኝ ማለት እራስህ ላይ እፍረትን እንጂ ሌላ አይፈጥርብህም እንደው እንዲህ ስል ትዝ አለኝ አንዱ ጓደኛዬ ምንም ሳያጠና ፈተና ሲደርስበት ለማጥናት ይሞክርና አልገባ ሲለው ውይይይ አሁንስ በቃኝ ‼️ ለነፍሴ ነው ለስጋዬ ብሎ ይተወዋል 🤣🤣 ብቻ ምን ልላችሁ መሰላችሁ ሐቂቃ እነዚ ልጆች የማይደገሙ አላህ ጥንካሬን ያላበሳቸው ለኛ ደግሞ በልጅነታችን teacher እንዳስተማሩን non- Renewable Resource አችን ናቸው አላህ ለኛ ከሰጠን ድንቅ ፀጋዎች መሃል ናቸው አላህ ይጠብቃቸው::
👉በዚህ አጋጣሚ ሳላነሳቸው ብቀር ቅር ይለኛል እና ላንሳቸው ውድ ጓደኞቼ የ4 ኪሎ ኡስታዝ ኡስታዝ ኢብን አቢ ዱንያ (ስሙን ሲጠሩት አይወድም ለዛ ነው) እና አብዱል ሐኪም በሕይወቴ ውስጥ ትልቅ ቦታ አላችሁ አባት ልጁን እጁን ይዞ ትምህርት ቤት እንደሚወስደው ሲያጠፋ ገስፆ እንደሚመልሰው ሲደክም እንደሚያበረታው ሁሉ ጓደኞቼ ለኔ እንደዛ ናቸው እኔን በማነፅ ውስጥ ትልቅ ሚና አላቸው አላህ ይጠብቃቸው እና 4 ኪሎ ያለው ጓደኛዬ ሊመረቅ ነው...
" ኡስታዜ እንኳን ደስ አለህ ሁሌም በሄድክበት ለኢስላም ምታገለግል ያድርግህ አላህ ሃላልህን በጊዜ ጀባ ይበልህ ከሐላሉ ሪዝቅ ጋር መልካም ምርቃት ብኛለው 🫡🫡 ሁሌም በልቤ ውስጥ ትልቅ ስፍራ አላችሁ...
👉ታዲያ እኚን ወንድም/እህቶቼን መሰናበት ከባድ ቢሆንም ይህ የሕይወት አንድ ክፍልም አይደል የሰው ልጅ ሁሌም በለውጥ ዑደት ላይ ነውና ከምርቃታችሁ ጭማሪ እኔም የታናሽ ምርቃት ልጨምርበት እና እንሰነባበት.... ሁሌም በሄዳቹበት ለሰው የምትጠቅሙ በናንተ መኖር ሌላው የሚደሰትባችሁ ለኢስላም መከታ ለሀገር አለኝታ ምትሆኑ ያድርጋችሁ::በሉ በቃ በዚሁ ላብቃ 5ኪሎ ተማሪ ረጅም ፅሁፍ ማንበብ አይወድም😄😄
👋👋👋 ደህና ቆዩኝ አላህ በኸይር ያገናኘን✨✨✨✨✨✨✨✨
በድጋሚ ለመላው የ5 ኪሎ ግቢ ሙስሊም ተመራቂ ተማሪዎች በሙሉ 🎉🎉🎉Congratulations 🎓🎓🎓
✍️ፅሁፉ ከእኔ ለተመራቂ ውንድም/ እህቶቼ
እምነቷ ነው
መብቷ ነው
ምርጫዋ ነው ... ኒቃብ !
የሴራ ጉንጉን ጎንጉነው ክብሯን ሊነኩ የሚሞክሩ አካላትን ተው ብሎ እጃቸውን መሰብሰብ የሁሉም ሀላፊነት ነው። የመንግስትን መዋቅር ተጠቅመው ሕዝብ የሰጣቸውን ሀላፊነት በመተላለፍ መብቷን የሚረግጥ መመሪያ በማውጣት በደል የፈፀሙ አካላትን ተጠያቂ ማድረግ የሁሉም ሀላፊነት ነው።
ኒቃብ ምርጫዋ ነው ... መብቷ ነው ... እምነቷ ነው። ሊነካ ሊደፈር አይችልም። ይህንን ተላልፎ መምጣት እስልምና እና ሙስሊሞችን መዳፈር ነው።
ለዚህም ሲባል ሁሉም ግንዛቤው ይኖረው ዘንድ ስለ ሁላችን በሁላችን የሆነን መድረክ አሰናድተናል።
እሁድ ሰኔ 7 ልባችንን ከአንድ ቦታ ይሁን ... አቅጣጫችን ወደ ረያን መስጂድ ይሁን ... በአንድነት ስለአንድ አላማ እንሰባሰብ ... አላህ ብሎ መፍትሔውን የሚያመጣው ትውልድ አካል እንሆናለን!!!
ዝግጁ ?!
@aaumsu
ታላቁ መድረክ ደረሰ .... የኢትዮጵያ ሙስሊም ተማሪዎች በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ ያላቸው መብቶች!
እንደ ሙስሊም ተማሪ ስላሉን ሕገ-መንግስታዊ መብቶች በተጋባዥ ምሁራን በጥልቀት ይዳሰሳል። ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ጀምሮ ድሮም ዛሬም መመሪያ በማውጣትም ሆነ እንደ ግል ሒጃብን በመከልከል ሙስሊም ተማሪዎችን ከትምህርት ስለሚያሰናክሉ ተቋማት እና ግለሰቦች ፍላጎት እና አንደምታ ብሎም ዘላቂ መፍትሔ በፓናሊስቶች ይብራራል። የሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥያቄ የእኛ ትውልድ ሀላፊነት ነው ብለን የገባነውን ቃል እናድሳለን፤ ቀጣይ የቤት ስራዎቻችንም ግልፅ ይደረጋሉ።
የሁሉም ካምፓስ ተማሪዎች (ትራንስፖርት ተመቻችቷል) የዚህ ታሪካዊ ፕሮግራም አካል ትሆኑ ዘንድ ተጋብዛችሗል። አዲስ አበባ ውስጥ ያላችሁ ሀይስኩል እና ኮሌጅ ተማሪዎች የዚህ ታሪክ አካል ትሆኑ ዘንድ በክብር ተጠርታችሗል። ሁላችንም የሁላችንም አጀንዳ በሆነው ጉዳይ ዙሪያ እንሰባሰብ ዘንድ ግድ ሆኗል። መታደልም ነው!
ቦታ፦ ጦርሓይሎች በሚገኘው ረያን መስጂድ
ቀን፦ በመጪው እሁድ ሰኔ 07 / 2018 ዓ.ል
ሰዓት፦ ከጧቱ 2:30 ጀምሮ
አዘጋጁ፦ የእናንተው የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ነው። ለጓደኞቻችን፣ ለቤተሰቦቻችን፣ ለእህት ወንድሞቻችን ማሰራጨት ግዴታ ነው።
@aaumsu
አሰላሙ አለይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካቱህ
✨ለዚህ ታላቅ ቀን ለምርቃታችሁ ስለበቃችሁ ውድ እህት ወንድሞቻችን ✨
ዛሬ የአመታት ልፋታችሁን ውጤት የምታጣጥሙበት ብቻ ሳይሆን በእያንዳንዷ ለሊት ጭንቅ ውስጥ የገባችሁበትን፣ መጠራጠር እና ግራ መጋባት ውስጥ የሆናችሁበትን እንዲሁም ተስፋ ለመቁረጥ ጫፍ የደረሳችሁበትን ግን በዛ ሁኔታ ውስጥ አላህ እናንተ የቀረፀበትን እና ያስተካከለበትን ሁኔታ የምታስታውሱበት ነው።
ይህን ጉዞ ስትጀምሩ የነበራችሁ ማንነት እና አሁን ያላችሁበት ሁኔታ አንድ አይደለም። ትላንት እንደ ህልም ያያችሁትን ደረጃ ዛሬ ላይ በቅታችኋል እና አልሀምዱሊላህ። ግን ይህን እንደ ስኬት ብቻ ሳይሆን እንደተጣለባችሁ እምነት መውሰድ ይኖርባችኋል ።
እውቀት ታላቅ አማና ነው። ይህን አደራ ወደፊት በሚኖራችሁ ጉዞ ላይ እንደምትወጡት በአላህ ላይ እምነት አለኝ።
ወደፊት የሚጠብቃችሁ አዲስ ህይወት አላህ በሲሳይ የተሞላ ያድርግላችሁ❤️! ያማረ ትዳር እና ሀላል ሪዝቅን ይወፍቃችሁ❤️!
💐💐💐በድጋሜ እንኳን ለዚህ ታላቅ ጊዜ አላህ አበቃችሁ !!! 💐💐💐
መብሩክክክክክ 🎉🎉
መብሩክክክክክ 🎉🎉
መብሩክክክክክ 🎉🎉
✨🎓✨🎓✨🎓✨
አሰላሙ አለይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካቱህ
ተመራቂ እህት ወንድሞቸ እንዴት ናችሁ?
ጌታችን ፈቅዶ እዚህ ደርሳቹ እንኳን ደስ አላቹ 🥹ለመባባል ስለደረስን ተቆጥሮ የማያልቅ ምስጋና ለአሏህ ይገባው ።
ግቢ ስንገባ ትምህርት ብቻ ልንማር መስሎን ብንገባም ከአካዳሚ ትምህርት ባሻገር ብዙ ነገሮችን ተምረን እንወጣለን ከሁሉም በላይ ደግሞ ሶብርን: የሰውን አመል መቋቋም ፣የፈተና ጭንቀት፣የዱንያ ጣጣ ፣ ስሜትን ማሸነፍ፣ያለምንም ብር መክረም ፣አንዳንዴም ስለሚበሉት ብር ማሰብ (እንዴት ላብቃቃው ፣መች ባዝ ቶሎ ይደርስልኛል.....) ብቻ ብዙ ብዙ እናም ይሄን ለምን አነሳሁት መሰላቹ እስቲ ንገሩኝ የቱ አላለፈም??በአሏህ
በቃ ዱንያ እንዲ ናት ችግር ይመጣል ይሄዳል ፣የሰው ልጅ “ም ረሺ ነውና ውድ እህት ወንድሞቼ 😊ይህን ትምህርት በቀሪ ሂወታቹ ላይ ሰንቃቹ ተጓዙ
الصبر من الإيمان بمنزلة الرأس من الجسدነውና የተባለው ስራም ስትፈልጉ ሆነ ዱንያን ስትትታገሉ فَاصْبِرُوا መልክቴ ነው። እንዳይበዛ ካለኝ ስጋት ላሳጥረው የመጨረሻው መልእክቴ ሙስሊም በያለበት በየሄደበት ሁሉ የኢስላምን ባንዲራ ከፍ ሊያረግ ይገባልና ወታቹም አኩሩን የኛ ታላቅ እኮ ናት ✨አንድ ላይ እኮ ነው ከሱ ጋ የተማርነው✨እያልን ልባችን እንዲሞቅ አርጉን ። የኢትዮጵያ ሙስሊም ቀዳዳው ችግሩ ብዙ ነውና አደራቹን አትርሱት !አማናቹን ተወጡ !በደረሳቹበት ሁሉ አሻራ ይኑራቹ ተደራጁ አትበታተኑ 🥺አሏህ ይጠብቃቹ።🥺 በድጋሚ እንኳን ደስ ያላቹ✨🎓✨🎓✨🎓✨🎓✨🎓✨ ✍️✍️✍️✍️
የምስራች ለ2018 ዓ.ም የAAU ሙስሊም ተመራቂ ተማሪዎች በሙሉ! 🎓✨
ከ6 ኪሎ፣ 5 ኪሎ፣ 4 ኪሎ እንዲሁም በሁሉም ካምፓሶች የምትገኙ የፊታችን ተመራቂዎች፤ ለዚህ ታላቅ የውጤት ቀን ያበቃችሁን አላህ (ሱ.ወ) እጅግ የላቀ ምስጋና ይድረሰው። አልሐምዱሊላሂ ረቢል ዓለሚን!
የመጀመሪያውን የዩኒቨርሲቲ ጉዟችሁን አስታውሳችሁ “መቼ ይሆን የምመረቀው?” ስትሉ የነበራችሁበት የትናንት ድካም አልፎ፣ አሁን የድል ምልክት የሆነውን የካባ መለኪያ ሰዓት በአላህ ፈቃድ ደርሷል።
የምረቃ ቀን በህይወት ውስጥ ትልቅ ስፍራ የሚሰጠው የትዝታ ማህደር ሲሆን፣ የምረቃ ሪቫን ደግሞ ለዕለቱ ፎቶዎች ልዩ ድምቀትና ውበት የሚሰጥ ዋናው አካል ነው። በመሆኑም፣ ሪቫን ሌላ ቦታ ሄደው ለማዘዝ ከመቸኮልዎ በፊት ጥቂት ሰከንዶችን ይውሰዱና ይህንን መልዕክት ያንብቡ።
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት (AAUMSU)፣ ሁላችንም የምንኮራበትን፣ እሴቶቻችንን እና አንድነታችንን በኩራት የምንገልጽበትን ልዩ የምረቃ ሪቫን በታላቅ ጥራት አዘጋጅቶላችኋል።
ሌላ ቦታ ሄዶ መጨናነቅ እና መጉላላት ቀርቷል፤ የራሳችንን መለያ ይዘን ውብ በሆነ መንገድ ደስታችንን እናከብራለን! 😎🎉
ሪቫኑን ለማዘዝ @Niqab_issueBot በዚህ ላይ ይዘዙን
@aaumsu
