5killo Jem'a official Channel
Открыть в Telegram
This is the official channel of AAiT jem'a where we provide info abt 👉Jem'a Tutors 👉Trainings and Da'ewa programs 👉Weekly lunches and halaqas(circles) 👉qira'ts (Qur'an and other Kitabs) 👉Weekly Q&A sessions Group: https://t.me/+cw97UaRUF1YzMTg0
Больше1 161
Подписчики
-124 часа
+17 дней
+530 день
Архив постов
🚨👀 SOMETHING BIG IS COMING... 🚨
Not just a campus event.
Not just a university program.
A powerful, historic, and highly engaging initiative that reaches far beyond the boundaries of campuses is on the horizon.
Prepared by AAUMSU in relation to the Niqab issue, this upcoming program will bring together voices, perspectives, and participants on a scale you won't want to miss.
🔥 Bigger than expected.
🔥 More impactful than imagined.
🔥 An event everyone will be talking about.
💭 Curious?
💭 Excited?
💭 Ready to be part of something significant?
The countdown has begun...
Keep your eyes open...
⏳ COMING SOON...
📣 STAY TUNED...
#AAUMSU #ComingSoon #StayTuned #NiqabIssue
@aaumsu
•በባህር ላይ እየሰመጠ ያለ ሰው ዱዓ ሲያደርግ አይተህ ታውቃለህ?! ከአላህ ውጪ ሌላ ተስፋ ቀልቡ ውስጥ ይኖራል?! በእንዲህ አይነት ዱዓ ብቻ ለችግራችን መፍትሄ ለበሽታችን ፈውስ እናገኛለን!
ሑዘይፋ ኢብኑል‐የማን -ረዲየላሁ ዐንሁ- እንዲህ ይላሉ፦«ወደፊት እንደሰጠመ ሰው ዱዓ ከሚያደርግ ሰው በስተቀር ማንም የማይድንበት ዘመን በሰዎች ይመጣል!»
©
السلام عليكم ورحمة الله وبركاته
በነገው ዕለት final exam ለምትጀምሩ ወንድምና እህቶች ሁሉ መልካም እድል እንመኛለን።
ወደ ፈተና ከመግባታችሁ በፊት አላህ ፈተናውን እንዲያገራላችሁ ዱዓ ማድረጋችሁን አትዘንጉ!!!!!!
እነዚህን እና መሰል ዱኣዎችን ብታደርጉ መልካም ነው ።
{ رب اشرح لي صدري ويسر لي أمري واحلل عقدة من لساني يفقهوا قولي } اللهم لا سهل إلا ما جعلته سهلا وأنت تجعل الحزن إذا شئت سهلا. يا حي يا قيوم برحمتك أستغيث أصلح لي شأني كله ولا تكلني إلى نفسي طرفة عين.🌟🌟ለሁላችሁም መልካም ፈተና 🌟🌟
Those of U who gonna take exit exam, kindly check this site, it'll help U to get previuos exam👇👇
exitexamstudio.app
I wish U good luck🤞
መልካም ምኞቶች ለተመራቂ ተማሪዎች ከታናናሾች እንደቀጠለ ነው 🎓🎓
እህቶቻችን እና ወንድሞቻችን ሊለዩን ቀናቶችን እየቆጠርን ነው 😢
መልካም ምኞታችሁን ፣ ትውስታ እና አስቂኝ ገጠመኞቻችሁን አጋሩን
📩 መልዕክቶቻችሁን በዚህ ቦት ብትልኩልን እዚህ channel ላይ የምናጋራው ይሆናል ፦
👇👇👇
@fivekjemaa_bot
بسم الله 😊
✨🎓✨🎓✨🎓✨🎓
በዚህ ምርጥ ዲን ላስተሳሰረን ውዱ ጌታችን ምስጋና ይገባው
እናንተ! አዎ እናንተ! በዚህ ፈታኝ environment ውስጥ እኛ መመረቃችሁን ስናስብ አስቀድመንም አብረንም እስልምናና ጀማዐን ከስብእናዎቻችሁ ጋር እናስብ ዘንድ ውለታን የዋለላችሁ ✨የሆነው የአላህ ሰላም፣ እዝነትና ረድኤቱ በእናንተ ላይ ይስፈን
ውድ ተመራቂዎች ይታወቃልና ችግር፣ ሀዘን፣ ደስታ ገጠመኝ ብዬ ጉዳዩን ለቀባሪ አላረዳም። እና እንኳን ተመረቃችሁ! ህይወታችሁ ውስጥ የኸይረኛ ምርቃት ሁሉ አይለፋችሁ፣እናንተም በህይወታችሁ ላይ ሁሌ ኸይርን ለመመረቅ ምንም እንቅፋት አይሁንባችሁ። ዱአዬ ነው😊
ብዙ ምታነቡት ስለሚኖር እኔም ማስረዘምን ልመርቅላችሁ 😅እና ወደ መልእክቴ ልግባ።
1ኛው ያው ይህን ለእናንተ መናገር ቢከብድም
وَذَكِّرْ فَإِنَّ الذِّكْرَىٰ تَنْفَعُ الْمُؤْمِنِينَ
ነውና
ሲጨንቃችሁ፣ ሲጠባችሁ ቤተሰብ ከጎናችሁ በራቀ ሰአት መንገዳችሁን ደግሞ ገና ሳትጀምሩት እንደቆመ የተሰማችሁ እለት የደላችሁም የከፋችሁም እለት ገለጥ ስታደርጉት ስሜታችሁን በቀየረላችሁ፣ ሰላምን ባሰፈነላችሁ፣ እውነተኛ ደስታን ለልባችሁ ባገራላችሁ ቁርአን ላይ አደራ።
ከዛ ደግሞ ያው እውነታው እኛ ለኢስላም ብዙ ማድረግ ይጠበቅብናል። ስለዚህ ለዲኔ ምን ላድርግ በሚል ተግባራዊ የሆነ መስመር ፣ አደረጃጀት and something worthy ታቅዱና ጉዞውን ትጀምሩት፤ የጀመራችሁትን ካለም ትቀጥሉት ዘንድ ምኞቴ ነው።
إِلَّا تَنْفِرُوا يُعَذِّبْكُمْ عَذَابًا أَلِيمًا وَيَسْتَبْدِلْ قَوْمًا غَيْرَكُمْ وَلَا تَضُرُّوهُ شَيْئًا ۗ وَاللَّهُ عَلَىٰ كُلِّ شَيْءٍ قَدِيرٌ
በመጨረሻም በዚህ university አለም ውስጥ ለምታገኟቸው ታናናሽ እህትና ወንድሞቻችሁ የመጨረሻ የሆነውን ስሜት ምክር፣ ዱአና ማስጠንቀቂያ ትንፍስ ትሉ ዘንድ ቢያንስ ከዚህ ሳልከለክል በዚህ ሳላዝ ወጣሁ እንዳይመጣ 😅
well go ላይ well stay አድርጋችሁ well talk ,well teach ,well advice & well dua ብታደርጉ we will happily wish for u a well exit 😊 honestly ባታደርጉም we will😊
እውነትም የኢስላም ሰላምታ ውድና ውብ ናት። ዛሬ ነገ ሳይሆን ሁልጊዜም የአላህ ሰላም እዝነትና ረድኤቱ አይለያችሁ።በድጋሚ እንኳን ተመረቃችሁ!✨🎓🎓🎓
✍️ just Some1
ፈገግ በሉ 😄😄
የሆነ ጊዜ የአንድ ሃገር ንጉስ ሁሉም ወንዶች ሁለተኛ ሚስት ማግባት አለባቸው አለበለዚያ ይገደላሉ ሚል አዋጅ ያወጣል፣
እናም ባል ይሄን ሰምቶ ፊቱን አጨፍግጎ ወደ ቤቱ ይገባል ታዲያ የባሏን ፊት መቀያየር ያየች ሚስት ግራ በመጋባት ለባሏ ጥያቄ ታቀርባላች
ሚስት :- ዛሬ ምን ሆነህ ነው ውዴ?
ባል :- ዛሬ ንግሱ ሁላችንንም ሰብስቦ አንድ ጉድ ነገረን
ሚስት :- "ሚስት በድንጋጤ" ምን አሏችሁ?
ባል :- ሁሉም ወንድ ሁለተኛ ሚስት ማግባት አለበት አሉ እና የማላገባ ከሆነ ንጉሱ ይገለኛል ሲላት
ምን ብትለው ጥሩ ነው ❓❓
" አንተ በጣም እድለኛ ነህ አላህ ለሸሂድነት መርጦሃል :: " አለችው ይባላል😄😄
#ከወሳኝ ነቢያዊ ዱዓዎች ውስጥ!
ከዘይድ ቢን አርቀም (رضيﷲ عنه)ተይዞ ረሱል (ﷺ) ይህን ዱዓ ያደርጉ ነበር፡‐
”اللَّهمَّ آتِ نفسي تقواها وزكِّها أنت خيرُ من زكّاها أنت
وليُّها ومولاها“
“አላህ ሆይ! ለነፍሴ ተቅዋን ለግሳት:: አጽዳትም። ከአንተ የትሻለ የሚያፀዳት የለምና፡፡ አንተ አስዋቢዋም
አምላኳም ነህ።”
📚 ሙስሊም ዘግበውታል: 2722
✨🎓 ውድ ተመራቂዎችን በልባዊ ስሜት እንሰናበት! 🎓✨
በአምስት ኪሎ ቆይታችሁ አሻራቸውን ላሳረፉ፣ በደስታና በችግር አብረዋችሁ ለነበሩ ወንድም እህቶቻችሁ ያላችሁን ልባዊ ምስጋና፣ ትዝታ እና መልካም ምኞት መግለጽ ይፈልጋሉ❓
"አንድ ሰው ወንድሙን ከወደደ እንደሚወደው ይንገረው።"
የተመራቂ ጓደኞቻችሁን ልብ የሚያሞቅ መልዕክትና ዱዓ በዚህ ቦት ላኩልን
📩 —>@fivekjemaa_bot
አብረን እንሰናበት፤ ትዝታችሁን ስንቅ እናድርግላቸው! ❤️✨አካዳሚክ ሴክተር አሚራህ እንዲህ ባማረ መልኩ ትውስታ፣ መልዕክትና ምኞቷን ለተመራቂዎች አስተላልፋለች ሌሎቻችሁስ❓
በዚህ ቦት ላኩልን👇👇👇
@fivekjemaa_bot
📩 የላካችሁልንን መልዕክት 5 ኪሎ ጀመዓ channel ላይ ለሁሉም የምናጋራ ይሆናል።
ቢስሚላህ
.......እንዴ!! type ማድረግ ከበደኝ ሀቂቃ🥹
ምን ልበል?! ብዙ የሚባልላቸው ናቸው....🤔
ምርጡ ፅሁፍ ሁሉ የሚገባቸው ዕንቁዎች ናቸውና አሪፉን ሁሉ ለነሱ በመፈለግ ነፍሴ ተጨነቀች'ኮ.....
"ሰዎች ልብህ ውስጥ የሚገቡት አብራችሁ ባሳለፋችሁት የጊዜ ብዛት ሳይሆን፣ ባሳለፋችሁት ጊዜ ጥራትና ጥልቀት ነው" ይባላል፣ በጣም እውነት ነው።
1፣2፣3ኛ አመት ጊዜው ረጅምና ማይገፋ እንደሆነ እየተሰማኝ አለፈ። 4ተኛ አመትስ?! ነጎደ ነው ምላችሁ!
ለካ በዙሪያችሁ ያለው ነገር ሁሉ ያማረ ሲሆን ጊዜው ሳታውቁት ይከንፋል! በዚች አጭር ጊዜ ውስጥ በህይወቴ ላይ የማይፋቅ ተፅዕኖ ማሳረፋችሁን ስገልፅ በታላቅ መገረም እና ደስታ ነው!😁
ቁም ነገር!....ሀቂቃ ምክራችሁ ለህይወቴ የማያልቅ ስንቅ ሆኖኝ ይኸው እስካሁን አንግቤው አለሁ።
ቆይ ግን ታናሾች! ታላላቆቻችሁ ታላቅ በመሆናቸው አብዛኛውን ሊገጥማችሁ ስለሚችል ነገር ቀደመው ስለሚያውቁ እንዴት notify እንደሚያደርጓችሁ ታውቁ የለ? በቃ! እነዚህ ልጆች ማለት notificationኖቼ በሏቸው!
ከአላህ በታች እንደናንተ ሳጠፋ እየመለሰ፣ ደግ ስሰራ እያበረታታ፣ ጫና ከብዶኝ ዘመም ስል እየደገፈ የሚያፀናኝ እህትና ወንድም ከወዴት አገኝ ይሆን?
የናንተን ኸይር ለማውራት ቃላቶች ይሰንፉብኛል...
"በዚህ ግቢ ውስጥ ለነሱ ያለናቸው እኛው ነን" ብላችሁ ምክርና ድጋፋችሁን ሳትሰስቱ ለግሳችሁናል፣ ቃል ከአንደበታችሁ ሳይወጣ እንኳን በሚያምረው ስብዕናችሁ አርአያ ሆናችሁ ቀርፃችሁናል።
ደከመኝ ሰለቸኝ ሳትሉ ለኛ ምርጡን በመፈለግ በጀምዐ ታቅፈን በዲን እንድንታነፅ ዳዕዋና ቂርአት፣ በዱንያ እንድንታገዝ Academic Sector፣ ኡኹዋችንን እንድናጠነክር social sector እንዲሁም ለነዚህ sectoroch ድጋፍ finance sector ብላችሁ ለጀምዐው ያላችሁን ሁሉ ሰጥታችኋል። በለጋ እድሜያችሁ እኛ ላይ ደክማችኋል፣ ብዙ ብዙ...
በአንዲት አመት ውስጥ ያሳለፍነው የ10 አመት ያህል ትዝታ አስታቅፎን መገባደጃው ደረሰ...
መሰናበት ሁሌም ይከብዳል፣ እንደናንተ ደግሞ በልብ ውስጥ ትልቅ ዋጋ ያለው ሰው ሲሆን........አላህ!........እጅጉን ይከብዳል።
መመረቅ...
2ተኛው "መ" ሲጠብቅ እና "ረ" ሲጠብቅ recipientu የተለያየ አካል ይሆናል።
ለመጀመሪያው እናንተ ተመራቂዎች ከዚህ ግቢ በሰላም እንወጣ ዘንድ ዱዐ እንድታረጉልን፣ እንድትመርቁን ነው።
ለሁለተኛው ደግሞ እኛ እናንተን እንድንመርቅ ነው። አላህ በግቢ ሀያታችሁ ኸይር ለሰራችሁት ሁሉ አብዝቶ ይመንዳችሁ፣ እኛ ላይ ለለፋችሁብን ልፋት በጀነት ቤትን ይገንባላችሁ፣ ከክፉ ነገር ሁሉ ጠብቆ፣ መንገዳችሁን እንዲሁም ኻቲማችሁን አሳምሮ አላህ በጀነቱ ያገናኘን!
እናንተን በጀነት ማግኘት..........
ወላሂ ነው ምላችሁ፣ ብዙ ማወራው ነበረኝ ግን "ሁሉንም ካወሩት ሆድ ባዶ ይቀራል" ይባላል፣ ስለዚህ የተቀረው እኔው ጋር ቢቀመጥ ወደድኩ።
ተመራቂዎች፣ አንድ አደራ 'ምላችሁ ነገር ቢኖር ይህንኑ ያማረ ምግባራችሁን እንደያዛችሁ ከግቢ ውጪ በሚገጥማችሁ ሁሉ ኢስላምን የምታስጠሩ ውድ የአላህ ባሮች መሆናችሁን እንድትቀጥሉ ነው።
ጌታችን አላህ ጀምዐችን ላይ በረከቱንና እዝነቱን እንዲያፈስ እለምነዋለሁ።
✍አካዳሚክ ሴክተር አሚራህ
የመጀመሪያው መልዕክት ለተመራቂ ተማሪዎች ከአሚራችን ተላልፏል ሌሎችም ትውስታ፣ መልዕክትና ምኞታችሁን ማስተላለፍ ትችላላችሁ።
በዚህ ቦት ላኩልን👇👇👇
@fivekjemaa_bot
📩 የላካችሁልንን መልዕክት 5 ኪሎ ጀመዓ channel ላይ ለሁሉም የምናጋራ ይሆናል።
بِسْـــــــــــــــــــــــــــــــــمِ اللهِ الرَّحْمَنِ الرَّحِيمِ
🎓 ለዘንድሮው ተመራቂዎች በሙሉ የተበረከተ የእንኳን ደስ አላችሁ መልክት ! 🎓 🎓🎓
አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካትሁ 👋
✍️ውድ ተመራቂ ወንድምና እህቶች ጊዜው ነጉዶ አምስት ዓመታት ተገባደው ለዚህ ቀን ደረሳችሁ፤ አልሃምዱሊላህ ብዙ ውጣ ውረድ አልፋችሁ እዚህ ላደረሳችሁ ጌታ አላህ ላቅ ያለ ምስጋና የተገባው ይሁን።
በግቢ ቆይታችሁ ብዙ ትዝታዎችን አሳልፋችኃል ንባብ፣ አሣይመንት፣ ፈተና እንዲሁም የዲን እውቀት ለማግኘት ላይ_ታች በማለት ፣ በኸይር ሥራዎችም በመታገል ሁሌም ከፊት ነበራችሁ ፤ ሳትሰስቱ ለታናናሽ ወንድም እህቶቻችሁ የተቻላችሁን አበርክታችኃልና አላህ በስራችሁ ላይ በረካ ያድርግላችሁ🤲።
አብረን በጀምዓ ጥላ ስር ሆነን ያሳለፍነው የሳቅ ፣ የደስታ ፣ የውዴታ እና የመረዳዳት ጊዜያቶች ሁሌም በልባችን ማህደር ውስጥ ሰፍረው የሚቀሩ ድንቅ ትውስታዎቻችን ናቸው።
በተለይ ጀምዓ ስራ ላይ ስትሳተፉ ለነበራችሁ ማህፉዝ ፣ አንዋር ፣ አብዱልፈታህ እንዲሁም ሌሎችም ስማችሁን ያልጠቀስኳችሁ ወንድምና እህቶች ሁሉ ልዩ ምስጋና አቀርባለሁ።
🔖መላ ተመራቂ ተማሪዎች ከቀናት በኃላ የምትፈተኑት exit exam በጥሩ ውጤት እንድታልፉ መልካም ምኞቴ ነው።
እኛም ከሁለት ሳምንት በኃላ ለሚኖረው well go ፕሮግራም ውዶቻችንን ባማረ ሁኔታ ለመሸኘት በዝግጅት ላይ ነን፤ ተገኝታችሁ ደስታውን በጋራ እናሳልፈው ዘንድ ጥሪዬ ነው።
✍️በአዲስ አበባ ዩንቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች 5 ኪሎ ጀመዐ ዋና አሚር
ወንድማችሁ ሙሐመድ ኢድሪስ‼️
🚨ጭንቅና መከራ የገጠመው…
ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦
﴿أَلا أُخْبِرُكُمْ بشيءٍ إذا نزلَ برجلٍ منكم كربٌ، أو بلاءٌ، مِنْ أمرِ الدنيا دعا بِهِ فَفُرِّجَ عنه؟ دُعاءُ ذي النونِ:
لا إِلهَ إلّا أَنتَ سُبْحانَكَ إِنَّي كُنتُ مِنَ الظّالِمِينَ﴾
“አንድ ሰው ላይ ጭንቅ ሲደርስበት ወይም ከዱኒያ ጉዳዮች ፈተና ሲደርስበት ዱዓእ ቢያደርግበት የሚገላገልበትን ነገር አልነገራችሁምን? የዘንኑን (የነቢዩ ዩኑስ) ዱዓእ ነች። ‘ካንተ በስተቀር የሐቅ አምላክ የለም። ጥራት ይገባህ እኔ ከበዳዮቹ ነኝ።’”
📚 ሶሂህ አልጃሚ፡ 2605
ይህ ከቄራ መስጂድ የተላለፈው ኹጥባ ነው። ባስተላለፈው ጥልቅ መልዕክትም የሚከተለውን አስታውሰዋል፦
“ሙስሊም ሴት እህቶቻችንና ተማሪዎቻችን በትምህርት ተቋማትና በብሔራዊ ፈተና ወቅት በሂጃብ፣ በጅልባብና በኒቃብ ምክንያት የሚደርስባቸው እንግልትና ከትምህርት ገበታ መገለል ፍፁም የማይገባና ማህበረሰቡን የሚያሳዝን ሰቆቃ መሆኑን አስቀምጠዋል። ቀደም ሲል በጉንችሬና በአክሱም፣ አሁን ደግሞ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የታዩት መሰል ችግሮች የሀይማኖት መብትንና ክብርን የሚነኩ በመሆናቸው ፈጣን እልባት ሊሰጣቸው እንደሚገባ ያሳስባል። ሙስሊም ሴቶች ፈጣሪያቸውን በመፍራትና ራሳቸውን በመሰብሰብ የሚለብሱትን ሂጃብና ኒቃብ “ለደህንነት ስጋት ነው” በማለት የሚቀርቡ ምክንያቶች ከጥፋቱ ሰበቡ የከፋና ኡማው ላይ ያልሆነ ስም የመለጠፍ ያህል ተፈጥሯዊ ስርዓትን የጣረ ድርጊት ነው። እርግጥ ነው፣ ለደህንነት የሚፈለግን የፊት ገጽታንና መታወቂያን የማረጋገጥ ጥንቃቄ ሂጃብ ፈፅሞ አያደናቅፍም፤ ሊያደናቅፍም አይችልም። ሂጃብ ለሴቶች ብቻ ሳይሆን ለወንዶችም ጭምር መገለጫ የሆነ የጋራ ክብራችን በመሆኑ፣ ይህ አይነቱ ትንኮሳና ድርብ ጥፋት በአስቸኳይ እንዲቆም እኛም የተሰጠንን ክብር ለማስጠበቅና ኃላፊነታችንን በሙሉ አቅም ለመወጣት የበኩላችንን አደራ ልንወጣ ይገባል።" ብለውም ማህበረሰቡን አስገንዝበዋል።
መሰል እንቅስቃሴዎች የሚበረታቱ እና ሌሎች መሳጂዶች ላይም በስፋት መቀጠል ያለባቸው እንቅስቃሴዎች ናቸው።
ጥያቄ አለን መልስ እንፈልጋለን!!!
@aaumsu
«ኒቃቧንም ትለብሳለች ትምህርቷንም ትማራለች!»
🌹 ኒቃብ ለባሽዋ እህቴ ...❗️
ኡስታዝ ጂብሪል አክመል
💥💥 Today is the day 💥💥
ዛሬ ከዚህ ድንቅ ኡስታዝ ጋር Live ቀጠሮ አለን አይቀርም‼️
9: 30 PM
@Qireat6k
🌟 አለመቸኮል ለዱዓ ተቀባይነት አንዱ መስፈርት ነው!
ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦
﴿يُسْتَجَابُ لِأَحَدِكُمْ مَا لَمْ يَعْجَلْ، يَقُولُ : دَعَوْتُ فَلَمْ يُسْتَجَبْ لِي﴾
“አንዳችሁ የምታደርጉት ዱዓችሁ ተቀባይነት ያገኛል እሳካልቸኮላችሁ ድረስ።
መቸኮል ማለት፦ ዱዓ አድርጌ ነበር ተቀባይነት አላገኘልኝም ማለቱ ነው።”
📚 ቡኻሪ ዘግበውታል: 6340
🎉ዛሬ ጁምዓ ነው በነቢዩ ﷺ ላይ
ሰለዋትን እናብዛ🎉✨✨
💎 { إِنَّ اللَّهَ وَمَلائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى
النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا
عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيمًا }
✨✨ ﷺ,ﷺ,ﷺ,ﷺ,ﷺ,ﷺ ✨✨
🌸የአሏህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፡-
" የውመል ጁሙአ ቀኑንም ማታውን እኔ ላይ ሰለዋት ማድረግን አብዙ፡ እኔ ላይ አንድን ሰለዋትን ያወረደ አሏህ በሱ ላይ አስር ሰለዋት
ያወርድለታል........
"أكثروا الصلاة علي يوم الجمعة وليلة الجمعة فمن صلى علي صلاة صلى الله عليه عشراً"
ሰለዋት ልብን ያረጋጋል፣
ሰለዋት ጭንቀትን ይቀንሳል፣
ሰለዋት ከአላህ ዘንድ በረካ እና ምህረትን ያመጣል፣
۩ ከጁምዓ ቀን ሱናዎች፦
➊ መታጠብ
➋ ሽቶ መቀባት(ለወንዶች)
➌ መፋቂያ(ሲዋክ) መጠቀም
➍ ቆንጆ ልብስ መልበስ
➎ ሱረቱል ካህፍ መቅራት
➏ በጊዜ መስጂድ መግባት
➐ ዱዓ እና ሰለዋት ማብዛት ﷺ
‣ በመጨረሻው ሰአት (ከአስር በኋላ ) ዱዓ ማድረግ- እስልምናን ለማስከበር ለሚታገሉ እህት/ወንድሞቻችን በዱዓ እናስታውሳቸው
🌟 መልካም ጁምአ🌟
@fivekjemaa
✨🎓የምስጋናና የመልካም ምኞት መግለጫ ከታናሾች ለታላላቆች!🎓✨
የጌታችን አላህ ቀን ደረሰና እነሆ ልባችን እየተሰበረም ቢሆን "Well Go!" ለማለት ተዘጋጀን...
እንደ አምስት ኪሎ የምናዘጋጀው ዓመታዊ የዳዕዋና ሽኝት ፕሮግራማችን ከፈተና ጭንቀት እንደተላቀቃችሁ በዕለተ ጁምዓ ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ.ል ይካሄዳል።
✨"ቅድመ ዝግጅታችሁ ምን ይመስላል?" ያላችሁ እንደሆነ ለተናፋቂው ቀናችን መዳረሻ የሚሆን አንድ አዲስ ነገር ይዘንላችሁ መጥተናል። በግቢ ቆይታችን ወቅት እስከሚመረቁበት ዕለት ድረስ አብረውን ለነበሩ፣ በዲንም በዱንያም እኛን በመቅረጽና በመገንባት ላይ አሻራቸውን ላሳረፉ ምርጥና እንቁ ወንድሞችና እህቶቻችን ያለንን ፍቅር፣ መልካም ምኞትና ዱዓ የምንገልጽበት እንዲሁም መውደዳችንን የምናንጸባርቅበት ልዩ ዕድል!
“አንድ ሰው ወንድሙን ከወደደ፣ እንደሚወደው ይንገረው።”
(አቡ ዳውድና ቲርሚዚ)
"እኔን አንጾኛል" ብላችሁ የምታስቡት እነዚህ ተመራቂዎች ላይ አስተውላችሁ ትምህርት የቀሰማችሁበት ልዩ ስነ-ምግባር፣ ተሞክሮ ወይም ደግሞ ከእነዚህ ወርቅ ልጆች የተቀበላችሁት "በህይወቴ ጠቅሞኛል" የምትሉት ወርቃማ ምክር ካለ፣ እንደዚሁም ደግሞ ለእነሱና ለወደፊት ህይወታቸው የምትመኙላቸውንና ዱዓችሁን ለማስተላለፍ ቦታችን እነሆ!
እንዲሁም ውድ ተመራቂዎች በግቢ ቆይታችሁ በዝቅታም በከፍታም አብረዋችሁ ለነበሩ ጓደኞቻችሁ፣ እንዲሁም በእናንተ ላይ መልካምን ለዋሉ ወንድም እህቶቻችሁ ያላችሁን ምስጋና ማድረስና ከተመራቂ እህት ወንድሞቻችሁ ጋር ያላችሁን የትዝታ ስንቅ ማካፈል ትችላላችሁ።
ትዝታችሁና ትዝታችን አሁን ላይ መደሰቻና ማስታወሻ ሆኖን፣ ለወደፊታችን ደግሞ የጉዟችን ስንቅ ይሆነናልና አጋጣሚውን ተጠቅመን የወንድማማችነት ድባቡን እናጠንክር! የምንወዳቸውንም በአማረና ልብን በሚያሞቅ መልኩ እንሰናበት!
ይህንን ዕድል በመጠቀም ትውስታ፣ መልዕክትና ምኞታችሁን በዚህ ቦት ላኩልን👇👇👇
@fivekjemaa_bot
💬 የላካችሁልንን መልዕክት አምስት ኪሎ ጀመዓ ገጻችን ላይ ለሁሉም የምናጋራ ይሆናል።
🌟
በዕለተ ሽኝታችን ላይ ከመገናኘታችን በፊት በልባችን ያለውን በጽሁፍ አስፍረን ሽኝቱን ይበልጥ እናስውበው‼️