5killo Jem'a official Channel
Открыть в Telegram
This is the official channel of AAiT jem'a where we provide info abt 👉Jem'a Tutors 👉Trainings and Da'ewa programs 👉Weekly lunches and halaqas(circles) 👉qira'ts (Qur'an and other Kitabs) 👉Weekly Q&A sessions Group: https://t.me/+cw97UaRUF1YzMTg0
Больше1 161
Подписчики
-124 часа
+17 дней
+530 день
Архив постов
አሰላሙዓለይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካትሁ
📢 በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ቻናል የሚካሄድ ታላቅና ልዩ የሁለት ቀናት የኦንላይን ስልጠና !
በሀገራችንም ሆነ በዩኒቨርስቲያችን አውድ ውስጥ በስፋት ከሚነሱና በሙስሊም ተማሪዎች ዘንድ ከፍተኛ ግራ መጋባትና ተፅዕኖ ከሚፈጥሩ አጀንዳዎች መካከል ሴኩላሪዝም በቀዳሚነት የሚጠቀስ ነው። ይህ አይዲዮሎጂ በበቂ ሁኔታ ግንዛቤ ያልተፈጠረበት እና የድንበር ወሰኑ ያልተለየ በመሆኑ ብዙ ጊዜ የሃይማኖት ነፃነትን ከማስከበር አልፎ ሙስሊም ተማሪዎች እምነታዊ መብቶቻቸውን በነፃነት እንዳይጠቀሙና በግቢ ሕይወታቸው ውስጥ አላስፈላጊ ጫናዎች እንዲደርሱባቸው ሲያደርግ ይስተዋላል።
ስለሆነም ተማሪዎች ስለ ሴኩላሪዝም ግልጽና መረጃን መሠረት ያደረገ እውቀት እንዲኖራቸው፣ በሕግና በተቋማዊ አውድ ውስጥ እንዴት እንደሚተገበር እንዲረዱ እንዲሁም መብትና ግዴታቸውን ለይተው በእምነታቸውና በአቋማቸው ላይ በጽናት እንዲቆሙ ለማስቻል የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት በመጪው ቅዳሜ እና እሁድ (ሐምሌ 25 እና 26) ልዩ ስልጠና አዘጋጅቶላችኋል!
📌 የመርሃ-ግብሩ ዝርዝር መረጃዎች፦
📝ርዕስ ፦ ሴኩላሪዝም — ትርጉሙ፣ በሀገራዊና በዩኒቨርስቲ አውድ ያለው ተፅዕኖ፣ እና የተማሪዎች መብትና ግዴታ
👤 አሰልጣኝ ፦ በሕግ ዘርፍ ሰፊ ልምድ ያላቸው የሕግ ባለሙያው ሙስጠፋ ሽፋ
🎙 የፕሮግራሙ አስተባባሪ ፦ ወንድማችን ሙሐመድ አሚን ካሳው (የኢትዮጵያ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ፕሬዝዳንት)
🗓 ዕለት ፦ መጪው ቅዳሜ እና እሁድ (ሐምሌ 25 እና 26)
⏰ ሰዓት ፦ በሀገር ውስጥ ሰዓት አቆጣጠር ከምሽቱ 3:00 ሰዓት ጀምሮ
📍ቦታ ፦ በዚሁ በ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ዋና ቴሌግራም ቻናል ላይ
ይህ ስልጠና እያንዳንዱ ተማሪ በግቢ ሕይወቱ የሚያጋጥሙትን አላስፈላጊ ጫናዎችና የሕግ/አስተሳሰብ ግራ መጋባቶች ለመቅረፍ እጅግ ወሳኝና አስፈላጊ ስልጠና ነው! ስለሆነም በርካታ ተማሪዎች የዚህ ትልቅ መርሃ-ግብር ተካፋይ እንዲሆኑና መብቶቻቸውን በግልጽ እንዲረዱ ይህንን ማስታወቂያ በቴሌግራም ስቶሪ ላይ በመልቀቅ፣ ለቅርብ ጓደኞቻችሁ እና በምትገኙባቸው የተለያዩ ግሩፕ እና ቻናሎች ሁሉ ሼር በማድረግ የበኩላችሁን እንድትወጡ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን!
ቅዳሜ ምሽት 3:00 ሰዓት ላይ በሕብረቱ ቻናል እንገናኝ!
@aaumsu
🛠️ Thinking of Choosing Electrical Engineering?
The Unfiltered Truth 🇪🇹💡
3 Ground-Level Realities
👉 It’s no longer just "wiring houses or fixing fuses": The era of treating Electrical Engineering as basic residential wiring in Addis is long over. The local market has matured. Modern EE in Ethiopia is heavily focused on power grid stability, embedded microcontrollers, high-frequency telecommunications, industrial PLC/SCADA automation, and renewable energy integration.
👉 The Mega-Grid & Power Export Boom: Ethiopia is positioning itself as the clean energy powerhouse of East Africa. With the Grand Ethiopian Renaissance Dam (GERD) boosting national generation capacity past 10,000 MW, engineers aren't just managing local lines; they are running high-voltage HVAC/HVDC transmission, smart grid load dispatching, and cross-border power trading with Kenya, Djibouti, and Sudan.
👉 The Telecom Duopoly & Hardware-Software Bridge: The aggressive rollout of 5G sites and optical fiber networks by Ethio Telecom and Safaricom Ethiopia has created demand for RF, optical, and network infrastructure engineers. Simultaneously, modern industrial parks require engineers who can bridge hardware with embedded code (C/C++, Microcontrollers, IoT) to program automated assembly lines.
Electrical and computer Engineers who have the duality of both software and firmware skills are highly demanded in the job market.
All of the above means the ceiling is incredibly high, but only if you treat circuit theory as deep mathematical science, and additionally have the willing to continuously teach yourself and cope up with the ever changing character of the field.
The Transition: You will move from basic freshman calculus and physics into intense vector calculus, Maxwell’s equations, Signals & Systems, and Power System Analysis. The real challenge is shifting from "plug-and-chug circuit formulas" to abstract frequency-domain thinking and hardware debugging.
Join our resource sharing group for Electrical department here:
https://t.me/+MvU0oK75kexiNDhk
✍Academic Sector
🌟 በምድር ላይ ለፍጡራን ጠቃሚ የሆነ አዝዕርት (ችግኝ) መተከል ታላቅ ምንዳ የሚያስገኝ ስራ ሲሆን፤ በጀነት ውስጥም በቀለለ መንገድ የራስህን አሻራ ማኖር ትችላለህ…
ከአብደላህ ቢን መስዑድ (ረዲየሏሁዓንሁ ) ተይዞ፡ ነቢዩ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦
﴿لَقِيتُ إبراهيمَ ليلةَ أُسْرِيَ بِي، فقال: يا مُحَمَّدُ، أَقْرِئْ أُمَّتَك مِنِّي السلامَ، وأَخْبِرْهم أنَّ الجنةَ طَيِّبَةُ التُّرْبَةِ، عَذْبَةُ الماءِ، وأَنَّها قِيعانٌ، وأَنَّ غِراسَها سبحانَ اللهِ، والحمدُ للهِ، ولا إله إلا اللهُ، واللهُ أكبرُ﴾
“ኢስራዓ ወልሚዕራጅ በተጎዝኩ ግዜ ኢብራሂምን (አለይሂሰላም ) አገኘሁት። እንዲህም አለኝ፦ ሙሐመድ ሆይ! ለሕዝቦችህ ከእኔ ሰላምታ አቅርብላቸው። ሰለ ጀነትም አፈሯ እጅግ መልካምና ለም የሆነች፣ ውሃዋ ጣፋጭ የሆነች፣ ሜዳማ (ባዶ መሬት) መሆኗን ተክሎቿም ሱብሃንአላህ፣ ወልሐምዱሊላህ፣ ወላኢላሃኢለላህ ወላሁ አክበር የሚሉት (የዚክር) ቃላቶች መሆኑን ንገራቸው።”
📚 ቲርሚዚ ሶሂህ ብለውታል፡ 3462
"ብዕራችሁ የሐቅ ድምፅ፡ ቃላትሁ የእውነት ጋሻ ይሁኑ!"
ቀደም ሲል ይፋ ባደረግነው የ"ሀሳን" ልዩ የስነ-ፅሁፍ ውድድር ክፍት ሆኖ የሚቆየው ለአንድ ሳምንት (ለ7 ቀናት) ብቻ መሆኑን ለውድ ተወዳዳሪዎች በሙሉ እናሳውቃለን። ጊዜው ሳያልቅ የብዕር አሻራችሁን ለማሳረፍ ፈጥናችሁ ተሳተፉ!
📌 የውድድሩ ርዕሶች፡ በመብትና ፍትህ ጥያቄዎች፣ በሙስሊሞች ላይ በሚደርሱ በደሎች፣ በሒጃብ ክብርና ፈተናዎች፣ እንዲሁም በእውነትና ማህበራዊ ትግል ዙሪያ።
📌 የፅሁፍ ዘርፍ፡ ግጥም ወይም ዝርው (ወግ፣ ልቦለድ፣ እውነተኛ ታሪክ)።
📌 ሽልማት፡ ከ 1ኛ እስከ 3ኛ ለሚወጡ ተወዳዳሪዎች ልዩ ሽልማት ተዘጋጅቷል! 🏆
እውነትን፣ ፅናትንና የሙስሊሙን ማህበረሰብ ድምፅ በብዕራችሁ ለማስተጋባት ቀሪዎቹን ቀናት ተጠቅማችሁ አሁኑኑ ስራዎትን ይላኩ።
📩 የምትልኩበት አድራሻ (Telegram Bot): @Niqab_issueBot
@aaumsu
ሀሳን ልዩ የስነ-ፅሁፍ ውድድር!
"ብዕርህ የሐቅ ድምፅ፡ ቃላትህ የእውነት ጋሻ ይሁኑ!"
ሀሳን ኢብኑ ሳቢት (ረዲየላሁ ዐንሁ) ስንኞቹን በአላህ መንገድ በመሰደር፣ በብዕሩና በጥበቡ ለእስልምናና ለእውነት ሲታገል የነበረ ታላቅና ጀግና ሶሃቢ ነው።
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት የዚሁን ታላቅ ሶሃቢ አሰረ-ፍኖት በመከተል፣ በስሙ የተሰየመ ልዩ የስነ-ፅሁፍ ውድድር ይፋ ማድረጉን በታላቅ ደስታ ያበስራል።
🎨 የውድድሩ ዓላማና ዋና ዋና ጭብጦች
በግጥምም ሆነ በዝርው (ወግ፣ ልቦለድ፣ እውነተኛ ታሪክ) የመፃፍ ክህሎትና የጥበብ ስጦታ ያላችሁ ተማሪዎች በሙሉ ብዕራችሁን በማንሳት የመብታችሁና የእውነታው ድምፅ ታሰሙ ዘንድ ጥሪ ቀርቦላችኋል።
የሚላኩት ፅሁፎች የሚከተሉትን አበይት ርዕሰ ጉዳዮች ማጠንጠኛ ያደረጉ መሆን አለባቸው፡
🗯ስለ መብት፣ እኩልነት እና የፍትህ ጥያቄዎች
🗯በሙስሊሞች ላይ የደረሱና የሚደርሱ መብት ገፈፋዎችና በደሎች
🗯ስለ ሒጃብ ክብር፣ መብት እና የሚያጋጥሙ ፈተናዎች
🗯ስለ እውነት፣ ፅናትና የማህበራዊ ትግል ጉዞ
🎊🏆 ከአንድ እስከ ሶስት ደረጃ የሚይዙ ተሸላሚ የሚሆኑ ይሆናል።
📩 አሻራችሁን ለማሳረፍና ለመሳተፍ
የጥበብ ውጤታችሁን እና ድምፃችሁን ለማድረስ የፍቅርና የእውነት አሻራችሁን አሁኑኑ ላኩልን!
የምትልኩበት አድራሻ (Telegram Bot): @Niqab_issueBot
በጥበብዎ አሻራዎን ያሳርፉ፤ የመብትና የእውነት ድምፅ ይሁኑ!
@aaumsu
🌟 ሱረቱል አል‐ሙልክን አዘውትሮ ማንበብ ያለው ትሩፋት!
ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦
﴿سورةُ تبارك هي المانعةُ من عذابِ القبرِ﴾
“ምዕራፍ አል‐ሙልክን መቅራት (ማንበብ) ከቀብር ቅጣት ይጠብቃል።”
📚 ሶሂህ አልጃሚዕ: 3643
5killo Jem'a official Channel:
🗣ታላቅ እድል ለእናንተ✨✨
ከእናንተው ወደ እናንተው ! !
ለኢማም አሕመድ ኢብን ኢብራሒም አልጋዚ ልጆች !!
የአፄ ልብነድንግል መንግስት የክርስትና ሀይማኖትን በግዳጅ ለመጫን ተደጋጋሚ ዘመቻዎችን አደረገ። በጀመረው ወራራም በመንገዱ የሚያገኛቸው ሙስሊሞች ላይ ተደጋጋሚ ግድያዎችን ይፈፅም ያዘ። የነበረው ሰራዊት ቁጥሩ ብዙ፤ ስንቁ የተሞላለት፤ መሳሪያም በደንቡን የታጠቀ ነበርና አስፈሪ ነበር። ሆኖም አላህ ባሮች ነበሩትና በዚያ አስፈሪ ሰዓት የአዳሉ ኢማም አሕመድ ኢብን ኢብራሒም ይህንን ጨቋኝ አገዛዝ ለመጋፈጥ ቆርጠው ተነሱ። 12 ሺህ ሆነው ከ212 ሺህ በላይ የሆነውን የልብነድንግል ጦርን አሸንፈውም የነበረውን ጭቆና አስወገዱ፤ ነፃነትንም አበሰሩ።
ጨቋኝን ጨቋኝ ወርሶት ክፈለ ዘመናት ካለፉ በኋላ፣ ዛሬ ደግሞ ከዘመናዊ እና ስልታዊ ጭቆና ጋር ተጋፈጥን። በራሳችን ተቋም ሃይማኖታዊ መብታችንን የሚገፍ መመሪያ ወጣ፤ ሰብዓዊ መብቶቻችንም በተደጋጋሚ ተጣሱ። ሆኖም የነፃነት አርበኝነት ይወረሳልና ስለ መብታችን ዓመቱን ሙሉ ስንጠይቅ እና ስንታገል ከረምን። ቅንጣት ሳናፈገፍግ፣ ለማስፈራሪያዎቻቸውም ሳንረታ ዓመቱ ተገባደደ።
🎬ይህ መድረክ የእናንተው ነው🎤
ይህ መድረክ በዓመቱ ውስጥ ያለፋችሁበትን የጽናት ጉዞ፣ የደረሰባችሁን የመብት ጥሰት፣ የማትረሱትን ገጠመኝ እና በሂደቱ ያበራታችሁን ልምድ ለወንድም እህቶቻችሁ ታጋሩ ዘንድ የተዘጋጀ ነው።
🔈ያለፋችሁበትን ፈተና ተናገሩ፡ ድምፅ መሆን ለተሳነው ድምፅ ሁኑ!
🔈ጽናታችሁን መስክሩ፡ ለቀጣዩ ትውልድ ጥንካሬን እና ብርሃንን አውርሱ!
📌አሁንም እንላለን :-"ፍትህ ቀባሪዎቿን ትቀብራለች!"
💡 ታሪካችሁን፣ ገጠመኛችሁን እና አስተያየታችሁን በውስጥ መስመራችን @Niqab_issueBot አጋሩን።
©aaumsu
@fivekjemaa
🗣ታላቅ እድል ለእናንተ✨✨
ከእናንተው ወደ እናንተው ! !
ለኢማም አሕመድ ኢብን ኢብራሒም አልጋዚ ልጆች !!
የአፄ ልብነድንግል መንግስት የክርስትና ሀይማኖትን በግዳጅ ለመጫን ተደጋጋሚ ዘመቻዎችን አደረገ። በጀመረው ወራራም በመንገዱ የሚያገኛቸው ሙስሊሞች ላይ ተደጋጋሚ ግድያዎችን ይፈፅም ያዘ። የነበረው ሰራዊት ቁጥሩ ብዙ፤ ስንቁ የተሞላለት፤ መሳሪያም በደንቡን የታጠቀ ነበርና አስፈሪ ነበር። ሆኖም አላህ ባሮች ነበሩትና በዚያ አስፈሪ ሰዓት የአዳሉ ኢማም አሕመድ ኢብን ኢብራሒም ይህንን ጨቋኝ አገዛዝ ለመጋፈጥ ቆርጠው ተነሱ። 12 ሺህ ሆነው ከ212 ሺህ በላይ የሆነውን የልብነድንግል ጦርን አሸንፈውም የነበረውን ጭቆና አስወገዱ፤ ነፃነትንም አበሰሩ።
ጨቋኝን ጨቋኝ ወርሶት ክፈለ ዘመናት ካለፉ በኋላ፣ ዛሬ ደግሞ ከዘመናዊ እና ስልታዊ ጭቆና ጋር ተጋፈጥን። በራሳችን ተቋም ሃይማኖታዊ መብታችንን የሚገፍ መመሪያ ወጣ፤ ሰብዓዊ መብቶቻችንም በተደጋጋሚ ተጣሱ። ሆኖም የነፃነት አርበኝነት ይወረሳልና ስለ መብታችን ዓመቱን ሙሉ ስንጠይቅ እና ስንታገል ከረምን። ቅንጣት ሳናፈገፍግ፣ ለማስፈራሪያዎቻቸውም ሳንረታ ዓመቱ ተገባደደ።
🎬ይህ መድረክ የእናንተው ነው🎤
ይህ መድረክ በዓመቱ ውስጥ ያለፋችሁበትን የጽናት ጉዞ፣ የደረሰባችሁን የመብት ጥሰት፣ የማትረሱትን ገጠመኝ እና በሂደቱ ያበራታችሁን ልምድ ለወንድም እህቶቻችሁ ታጋሩ ዘንድ የተዘጋጀ ነው።
🔈ያለፋችሁበትን ፈተና ተናገሩ፡ ድምፅ መሆን ለተሳነው ድምፅ ሁኑ!
🔈ጽናታችሁን መስክሩ፡ ለቀጣዩ ትውልድ ጥንካሬን እና ብርሃንን አውርሱ!
📌አሁንም እንላለን :-"ፍትህ ቀባሪዎቿን ትቀብራለች!"
💡 ታሪካችሁን፣ ገጠመኛችሁን እና አስተያየታችሁን በውስጥ መስመራችን @Niqab_issueBot አጋሩን።
@aaumsu
"ሴኩላሪዝም አልጠራልንም። ሴኩላሪዝም Atheism (ሀይማኖት የለሽነት) የሚመስላቸው አሉ። አንድ ተማሪ አልሐምዱሊላህ ሲል ሴኩላሪዝም የተጣሰ የሚመስላቸው አሉ። በምሳ ሰዓት አንድ ተማሪ ሶላት ልስገድ ሲል ልምን አትሰግድም ይባላል። ምን አገባው? ይህ እኮ ሰብዓዊ መብቴ ነው።" - አልዩ ሰዒድ (በፌደራል መጅሊስ የትምህርት ክፍል ዳይሬክተር)
ከበር አውልቀነው የምንገባው ሀይማኖት የለንም። ሴኩላሪዝም የትምህርት ስርዓቱን ከሐይማኖት ተፅዕኖ ነፃ ያወጣል እንጅ፤ በሴኩላሪዝም ስም እኛ ከሀይማኖት ነፃ እንድንሆን አንገደድም።
ለሁላችንም የሚሆን ቻለንጅ፦
መልዕክቱ ለሁሉም ይደርስ ዘንድ https://vt.tiktok.com/ZSXwfPJ2n/ በመግባት ኮፒሊንክ ሪፖስት አድርጉ። ይህ ለጥያቄ አለን ትውልድ ቀላሉ ሀላፊነት ነው።
ወደ ተግባር ! ! !
@aaumsu
"PVA የሚባል ትምህርት አለ። እዚያ ላይ እርቃን ሆኖ ስለሚሰራ ሮማንስ የሚተርክ ክፍል አለ። መሰሉ ድርጊት የማን ባህል ነው? የአማራ ባህል ነው? የኦሮሞ ባህል ነው? የየትኛው ኢትዮጵያዊ ባህልስ ነው? ይህ የመፅሐፍ ክፍል እንዲጠፋ ብንጠይቅም አልጠፋም። ደግሞኮ እነዚሁ እርቃንነትን መብት ያደረጉ ሰዎች ገላን መሸፈንን ወንጀል አድርገው ሙስሊም ተማሪዎችን ከትምህርት ሊያፈናቅሉ ይሞክራሉ። ኒቃብን መከልከል የአፋር ኢሹ አይደለም። አፋር በሴት ፈታሽ ፈትሾ ያስገባል። የአፋር ኢሹ ካልሆነ፤ የሶማሌ ኢሾ ካልሆነ፤ የኦሮምያ ኢሹ ካልሆነ፤ ለምንድን ነው ግለሰቦች ሲፈልጉ የሚያጦዙት?!" - አልዩ ሰዒድ (በፌደራል መጅሊስ የትምህርት ክፍል ዳይሬክተር)
መልዕክቱ ለሁሉም ይደርስ ዘንድ https://vt.tiktok.com/ZSXTSxwwk/ በመግባት ኮፒሊንክ ሪፖስት እናድርግ።
ወደ ተግባር!
ይህ ትንሹ ሀላፊነታችን ነው!!
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! !
@aaumsu
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረትን የYoutube እና Instagram ገፆች Follow ያላደረጋችሁ አሁኑ Follow አድርጉ። ለሌሎችም በማሰራጨት የሙስሊም ተማሪዎች ድምፅ የሆነውን ገፅ እናሳድግ።
ኢንስታግራም https://www.instagram.com/p/DbNlBxcjCRG/?igsh=aHlwN3B0azFva2E3 ነው።
የYoutube ደግሞ https://youtube.com/shorts/zyZxLAY3k1c?si=GyYdW3CzDke-QbI2 ነው። Subscribe ማድረግ እኖዳይዘነጋ።
ይህ ትንሹ ሀላፊነታችን ነው!
ወደ ተግባር!!
@aaumsu
🚨 ቀኑ ዛሬ ነው!
በየቦታውና በማኅበራዊ ሚዲያ በሚነሱ የሐሳብ ፍሰቶች ሳይነዱ ስለ «Feminism» በሚዛናዊው የእስልምና ዕይታ ላይ የተመሰረተ ጥልቅ ግንዛቤ የምንጨብጥበት የሁለት ቀናት ልዩ ስልጠና ዛሬ ምሽት ይጀምራል!
📝 ርዕስ፦ Feminism — ታሪካዊ አመጣጡ፣ የሚያነሳቸው ጥያቄዎች እና ሚዛናዊው የእስልምና ዕይታ
👤 አሰልጣኝ፦ ጋዜጠኛ አብዱረህማን አሚን
⏰ ሰዓት፦ ዛሬ ማታ 3:00 ሰዓት ጀምሮ
📍 ቦታ፦ በዚሁ በ6 ኪሎ ጀመዓ ዋና የ ቴሌግራም ቻናል
©AAU6kilojemea
@fivekjemaa
በፈረንሳይ ሀገር ሙስሊም ተማሪዎች ወደ ት/ቤት ሲገቡ ሒጃባቸውን ጥለው እንዲገቡ ይገደዳሉ። ልክ በአክሱም እንደተደረገው፤ በጉንችሬ እንደተደረገው፤ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሊደረግ መመሪያ እንደወጣለት ማለት ነው። የሀይማኖት ነፃነት መብት የት ነው? የመማር ነፃነት የት ነው? ሰብዓዊ መብት የት ነው? ዛሬ ኒቃብን ካስወለቁ ነገ ፀጉር ግለጡ ማለታቸው አይቀርም። ሆኖም ግን ፈፅሞ አይሆንም!!!
ቻሌንጅ ለሁላችን፦
መልዕክቱ ለሁሉም ይደርስ ዘንድ በቲክቶክ በመግባት ኮፒሊንክ ሪፖስት እናድርግ። ሊንኩ https://vt.tiktok.com/ZSXcA1HkJ/ ነው።
ይህ በዚህ መንገድ ትንሹ ሀላፊነታችን ነው !
ወደ ተግባር !!
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! !
@aaumsu
🎙ከሰለፎች አንደበት!
ኢማሙ ኢብኑልቀዪም (ረሂመሁላህ) እንዲህ ይላሉ፦
﴿خير أيام العبد على الإطلاق وأفضلها، يوم توبته إلى الله﴾
“ለአንድ ባሪያ ፍፁም ከሁሉ የተሻለውና ምርጥ ቀን የሚባለው፤ ወደ አላህ የተመለሰበት (ተውበት ያደረገበት) ቀን ነው።”
📚 ዛዱል‐መዓድ፡ 3/512
"የሀይማኖት ጉዳዮች በሀገራዊ ምክክሩ ላይ አጀንዳ ይሆን ዘንድ ሕዝበ ሙስሊሙ ታግሏል። ሙስሊም ተማሪዎችም ዘርፈብዙ የሆነ ንቅናቄ አድርገዋል። ሀገራዊ ምክክሩ እንደተቋጨ የሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥያቄዎች ዘላቂ፣ ፍትሐዊ እና ተፈፃሚ ምላሽ ሊያገኙ ይገባል።" - ሙሐመድአሚን ካሳው
ቻሌንጅ ለሁላችን፦
መልዕክቱ ለሁሉም ይደርስ ዘንድ በቲክቶክ በመግባት ኮፒሊንክ ሪፖስት እናድርግ። ሊንኩ https://vt.tiktok.com/ZSX7DFQ2R/ ነው።
ይህ በዚህ መንገድ ትንሹ ሀላፊነታችን ነው !
ወደ ተግባር !!
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! !
@aaumsu
ረሱል 🤎 እንዲህ ብለዋል፦
﴿مَنِ اغْتَسَلَ يَوْمَ الْجُمُعَةِ وَتَطَهَّرَ بِمَا اسْتَطَاعَ مِنْ طُهْرٍ، ثُمَّ ادَّهَنَ أَوْ مَسَّ مِنْ طِيبٍ، ثُمَّ رَاحَ فَلَمْ يُفَرِّقْ بَيْنَ اثْنَيْنِ، فَصَلَّى مَا كُتِبَ لَهُ، ثُمَّ إِذَا خَرَجَ الْإِمَامُ أَنْصَتَ غُفِرَ لَهُ مَا بَيْنَهُ وَبَيْنَ الْجُمُعَةِ الْأُخْرَى﴾
“በእለተ ጁምዓ ታጥቦ፣ ከመፀዳዳትም የቻለውንም ተፀዳድቶ፣ ከሚቀባባ ነገርም ተቀባብቶ፣ ቤቱ ውስጥ ከሚገኝ ሽቶ ተቀብቶ፣ ከዚያም ከቤቱ ወጥቶ በሁለት ሰዎች መካከል ሳይለያይ፣ ከዚያም የተፃፈለትን ከሰገደ፣ ከዚያም ኢማሙ በተናገረ ጊዜ ዝም ካለ፣ በዚያች ጁምዓ እና በቀጣዩዋ ጁምዓ መካከል ያለውን ወንጀል ይቅር ይባላል።”
📚ቡኻሪ ዘግበውታል፡ 910
"ፍትሕ ለሙስሊም ተማሪዎች፤ ፍትሕ ፍትሕን ለተራቡ ሁሉ!" - በሱሉልታ የኡመር መህዲ ተማሪዎች የቁርዓን ምርቃት ላይ የተላለፈ መልዕክት
የሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥያቄ ስለፍትሕ የሚቆም ሰው ሁሉ ጥያቄ ነው። ከመድረሳ ተማሪዎች ጀምሮ ሁሉም አካል ይመለከተዋል። ፍትሐዊ መልስ መጥቶ የሙስሊም ተማሪዎች ነፃነት ተከብሮ በእኩልነት መማር እስኪጀምሩ ድረስ መጠየቅ ግድ ነው።
መልዕክቱ ለሁሉም ይደርስ ዘንድ በቲክቶክ https://vt.tiktok.com/ZSXnsYgVr/ በመግባት ኮፒሊንክ ሪፖስት አድርጉ።
ወደ ተግባር!
ይህ ትንሹ ሀላፊነት ነው!!
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ !
@aaumsu
