5killo Jem'a official Channel
Ir al canal en Telegram
This is the official channel of AAiT jem'a where we provide info abt 👉Jem'a Tutors 👉Trainings and Da'ewa programs 👉Weekly lunches and halaqas(circles) 👉qira'ts (Qur'an and other Kitabs) 👉Weekly Q&A sessions Group: https://t.me/+cw97UaRUF1YzMTg0
Mostrar más1 162
Suscriptores
Sin datos24 horas
+37 días
+730 días
Archivo de publicaciones
ሀሳን ልዩ የስነ-ፅሁፍ ውድድር!
"ብዕርህ የሐቅ ድምፅ፡ ቃላትህ የእውነት ጋሻ ይሁኑ!"
ሀሳን ኢብኑ ሳቢት (ረዲየላሁ ዐንሁ) ስንኞቹን በአላህ መንገድ በመሰደር፣ በብዕሩና በጥበቡ ለእስልምናና ለእውነት ሲታገል የነበረ ታላቅና ጀግና ሶሃቢ ነው።
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት የዚሁን ታላቅ ሶሃቢ አሰረ-ፍኖት በመከተል፣ በስሙ የተሰየመ ልዩ የስነ-ፅሁፍ ውድድር ይፋ ማድረጉን በታላቅ ደስታ ያበስራል።
🎨 የውድድሩ ዓላማና ዋና ዋና ጭብጦች
በግጥምም ሆነ በዝርው (ወግ፣ ልቦለድ፣ እውነተኛ ታሪክ) የመፃፍ ክህሎትና የጥበብ ስጦታ ያላችሁ ተማሪዎች በሙሉ ብዕራችሁን በማንሳት የመብታችሁና የእውነታው ድምፅ ታሰሙ ዘንድ ጥሪ ቀርቦላችኋል።
የሚላኩት ፅሁፎች የሚከተሉትን አበይት ርዕሰ ጉዳዮች ማጠንጠኛ ያደረጉ መሆን አለባቸው፡
🗯ስለ መብት፣ እኩልነት እና የፍትህ ጥያቄዎች
🗯በሙስሊሞች ላይ የደረሱና የሚደርሱ መብት ገፈፋዎችና በደሎች
🗯ስለ ሒጃብ ክብር፣ መብት እና የሚያጋጥሙ ፈተናዎች
🗯ስለ እውነት፣ ፅናትና የማህበራዊ ትግል ጉዞ
🎊🏆 ከአንድ እስከ ሶስት ደረጃ የሚይዙ ተሸላሚ የሚሆኑ ይሆናል።
📩 አሻራችሁን ለማሳረፍና ለመሳተፍ
የጥበብ ውጤታችሁን እና ድምፃችሁን ለማድረስ የፍቅርና የእውነት አሻራችሁን አሁኑኑ ላኩልን!
የምትልኩበት አድራሻ (Telegram Bot): @Niqab_issueBot
በጥበብዎ አሻራዎን ያሳርፉ፤ የመብትና የእውነት ድምፅ ይሁኑ!
@aaumsu
🌟 ሱረቱል አል‐ሙልክን አዘውትሮ ማንበብ ያለው ትሩፋት!
ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦
﴿سورةُ تبارك هي المانعةُ من عذابِ القبرِ﴾
“ምዕራፍ አል‐ሙልክን መቅራት (ማንበብ) ከቀብር ቅጣት ይጠብቃል።”
📚 ሶሂህ አልጃሚዕ: 3643
5killo Jem'a official Channel:
🗣ታላቅ እድል ለእናንተ✨✨
ከእናንተው ወደ እናንተው ! !
ለኢማም አሕመድ ኢብን ኢብራሒም አልጋዚ ልጆች !!
የአፄ ልብነድንግል መንግስት የክርስትና ሀይማኖትን በግዳጅ ለመጫን ተደጋጋሚ ዘመቻዎችን አደረገ። በጀመረው ወራራም በመንገዱ የሚያገኛቸው ሙስሊሞች ላይ ተደጋጋሚ ግድያዎችን ይፈፅም ያዘ። የነበረው ሰራዊት ቁጥሩ ብዙ፤ ስንቁ የተሞላለት፤ መሳሪያም በደንቡን የታጠቀ ነበርና አስፈሪ ነበር። ሆኖም አላህ ባሮች ነበሩትና በዚያ አስፈሪ ሰዓት የአዳሉ ኢማም አሕመድ ኢብን ኢብራሒም ይህንን ጨቋኝ አገዛዝ ለመጋፈጥ ቆርጠው ተነሱ። 12 ሺህ ሆነው ከ212 ሺህ በላይ የሆነውን የልብነድንግል ጦርን አሸንፈውም የነበረውን ጭቆና አስወገዱ፤ ነፃነትንም አበሰሩ።
ጨቋኝን ጨቋኝ ወርሶት ክፈለ ዘመናት ካለፉ በኋላ፣ ዛሬ ደግሞ ከዘመናዊ እና ስልታዊ ጭቆና ጋር ተጋፈጥን። በራሳችን ተቋም ሃይማኖታዊ መብታችንን የሚገፍ መመሪያ ወጣ፤ ሰብዓዊ መብቶቻችንም በተደጋጋሚ ተጣሱ። ሆኖም የነፃነት አርበኝነት ይወረሳልና ስለ መብታችን ዓመቱን ሙሉ ስንጠይቅ እና ስንታገል ከረምን። ቅንጣት ሳናፈገፍግ፣ ለማስፈራሪያዎቻቸውም ሳንረታ ዓመቱ ተገባደደ።
🎬ይህ መድረክ የእናንተው ነው🎤
ይህ መድረክ በዓመቱ ውስጥ ያለፋችሁበትን የጽናት ጉዞ፣ የደረሰባችሁን የመብት ጥሰት፣ የማትረሱትን ገጠመኝ እና በሂደቱ ያበራታችሁን ልምድ ለወንድም እህቶቻችሁ ታጋሩ ዘንድ የተዘጋጀ ነው።
🔈ያለፋችሁበትን ፈተና ተናገሩ፡ ድምፅ መሆን ለተሳነው ድምፅ ሁኑ!
🔈ጽናታችሁን መስክሩ፡ ለቀጣዩ ትውልድ ጥንካሬን እና ብርሃንን አውርሱ!
📌አሁንም እንላለን :-"ፍትህ ቀባሪዎቿን ትቀብራለች!"
💡 ታሪካችሁን፣ ገጠመኛችሁን እና አስተያየታችሁን በውስጥ መስመራችን @Niqab_issueBot አጋሩን።
©aaumsu
@fivekjemaa
🗣ታላቅ እድል ለእናንተ✨✨
ከእናንተው ወደ እናንተው ! !
ለኢማም አሕመድ ኢብን ኢብራሒም አልጋዚ ልጆች !!
የአፄ ልብነድንግል መንግስት የክርስትና ሀይማኖትን በግዳጅ ለመጫን ተደጋጋሚ ዘመቻዎችን አደረገ። በጀመረው ወራራም በመንገዱ የሚያገኛቸው ሙስሊሞች ላይ ተደጋጋሚ ግድያዎችን ይፈፅም ያዘ። የነበረው ሰራዊት ቁጥሩ ብዙ፤ ስንቁ የተሞላለት፤ መሳሪያም በደንቡን የታጠቀ ነበርና አስፈሪ ነበር። ሆኖም አላህ ባሮች ነበሩትና በዚያ አስፈሪ ሰዓት የአዳሉ ኢማም አሕመድ ኢብን ኢብራሒም ይህንን ጨቋኝ አገዛዝ ለመጋፈጥ ቆርጠው ተነሱ። 12 ሺህ ሆነው ከ212 ሺህ በላይ የሆነውን የልብነድንግል ጦርን አሸንፈውም የነበረውን ጭቆና አስወገዱ፤ ነፃነትንም አበሰሩ።
ጨቋኝን ጨቋኝ ወርሶት ክፈለ ዘመናት ካለፉ በኋላ፣ ዛሬ ደግሞ ከዘመናዊ እና ስልታዊ ጭቆና ጋር ተጋፈጥን። በራሳችን ተቋም ሃይማኖታዊ መብታችንን የሚገፍ መመሪያ ወጣ፤ ሰብዓዊ መብቶቻችንም በተደጋጋሚ ተጣሱ። ሆኖም የነፃነት አርበኝነት ይወረሳልና ስለ መብታችን ዓመቱን ሙሉ ስንጠይቅ እና ስንታገል ከረምን። ቅንጣት ሳናፈገፍግ፣ ለማስፈራሪያዎቻቸውም ሳንረታ ዓመቱ ተገባደደ።
🎬ይህ መድረክ የእናንተው ነው🎤
ይህ መድረክ በዓመቱ ውስጥ ያለፋችሁበትን የጽናት ጉዞ፣ የደረሰባችሁን የመብት ጥሰት፣ የማትረሱትን ገጠመኝ እና በሂደቱ ያበራታችሁን ልምድ ለወንድም እህቶቻችሁ ታጋሩ ዘንድ የተዘጋጀ ነው።
🔈ያለፋችሁበትን ፈተና ተናገሩ፡ ድምፅ መሆን ለተሳነው ድምፅ ሁኑ!
🔈ጽናታችሁን መስክሩ፡ ለቀጣዩ ትውልድ ጥንካሬን እና ብርሃንን አውርሱ!
📌አሁንም እንላለን :-"ፍትህ ቀባሪዎቿን ትቀብራለች!"
💡 ታሪካችሁን፣ ገጠመኛችሁን እና አስተያየታችሁን በውስጥ መስመራችን @Niqab_issueBot አጋሩን።
@aaumsu
"ሴኩላሪዝም አልጠራልንም። ሴኩላሪዝም Atheism (ሀይማኖት የለሽነት) የሚመስላቸው አሉ። አንድ ተማሪ አልሐምዱሊላህ ሲል ሴኩላሪዝም የተጣሰ የሚመስላቸው አሉ። በምሳ ሰዓት አንድ ተማሪ ሶላት ልስገድ ሲል ልምን አትሰግድም ይባላል። ምን አገባው? ይህ እኮ ሰብዓዊ መብቴ ነው።" - አልዩ ሰዒድ (በፌደራል መጅሊስ የትምህርት ክፍል ዳይሬክተር)
ከበር አውልቀነው የምንገባው ሀይማኖት የለንም። ሴኩላሪዝም የትምህርት ስርዓቱን ከሐይማኖት ተፅዕኖ ነፃ ያወጣል እንጅ፤ በሴኩላሪዝም ስም እኛ ከሀይማኖት ነፃ እንድንሆን አንገደድም።
ለሁላችንም የሚሆን ቻለንጅ፦
መልዕክቱ ለሁሉም ይደርስ ዘንድ https://vt.tiktok.com/ZSXwfPJ2n/ በመግባት ኮፒሊንክ ሪፖስት አድርጉ። ይህ ለጥያቄ አለን ትውልድ ቀላሉ ሀላፊነት ነው።
ወደ ተግባር ! ! !
@aaumsu
"PVA የሚባል ትምህርት አለ። እዚያ ላይ እርቃን ሆኖ ስለሚሰራ ሮማንስ የሚተርክ ክፍል አለ። መሰሉ ድርጊት የማን ባህል ነው? የአማራ ባህል ነው? የኦሮሞ ባህል ነው? የየትኛው ኢትዮጵያዊ ባህልስ ነው? ይህ የመፅሐፍ ክፍል እንዲጠፋ ብንጠይቅም አልጠፋም። ደግሞኮ እነዚሁ እርቃንነትን መብት ያደረጉ ሰዎች ገላን መሸፈንን ወንጀል አድርገው ሙስሊም ተማሪዎችን ከትምህርት ሊያፈናቅሉ ይሞክራሉ። ኒቃብን መከልከል የአፋር ኢሹ አይደለም። አፋር በሴት ፈታሽ ፈትሾ ያስገባል። የአፋር ኢሹ ካልሆነ፤ የሶማሌ ኢሾ ካልሆነ፤ የኦሮምያ ኢሹ ካልሆነ፤ ለምንድን ነው ግለሰቦች ሲፈልጉ የሚያጦዙት?!" - አልዩ ሰዒድ (በፌደራል መጅሊስ የትምህርት ክፍል ዳይሬክተር)
መልዕክቱ ለሁሉም ይደርስ ዘንድ https://vt.tiktok.com/ZSXTSxwwk/ በመግባት ኮፒሊንክ ሪፖስት እናድርግ።
ወደ ተግባር!
ይህ ትንሹ ሀላፊነታችን ነው!!
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! !
@aaumsu
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረትን የYoutube እና Instagram ገፆች Follow ያላደረጋችሁ አሁኑ Follow አድርጉ። ለሌሎችም በማሰራጨት የሙስሊም ተማሪዎች ድምፅ የሆነውን ገፅ እናሳድግ።
ኢንስታግራም https://www.instagram.com/p/DbNlBxcjCRG/?igsh=aHlwN3B0azFva2E3 ነው።
የYoutube ደግሞ https://youtube.com/shorts/zyZxLAY3k1c?si=GyYdW3CzDke-QbI2 ነው። Subscribe ማድረግ እኖዳይዘነጋ።
ይህ ትንሹ ሀላፊነታችን ነው!
ወደ ተግባር!!
@aaumsu
🚨 ቀኑ ዛሬ ነው!
በየቦታውና በማኅበራዊ ሚዲያ በሚነሱ የሐሳብ ፍሰቶች ሳይነዱ ስለ «Feminism» በሚዛናዊው የእስልምና ዕይታ ላይ የተመሰረተ ጥልቅ ግንዛቤ የምንጨብጥበት የሁለት ቀናት ልዩ ስልጠና ዛሬ ምሽት ይጀምራል!
📝 ርዕስ፦ Feminism — ታሪካዊ አመጣጡ፣ የሚያነሳቸው ጥያቄዎች እና ሚዛናዊው የእስልምና ዕይታ
👤 አሰልጣኝ፦ ጋዜጠኛ አብዱረህማን አሚን
⏰ ሰዓት፦ ዛሬ ማታ 3:00 ሰዓት ጀምሮ
📍 ቦታ፦ በዚሁ በ6 ኪሎ ጀመዓ ዋና የ ቴሌግራም ቻናል
©AAU6kilojemea
@fivekjemaa
በፈረንሳይ ሀገር ሙስሊም ተማሪዎች ወደ ት/ቤት ሲገቡ ሒጃባቸውን ጥለው እንዲገቡ ይገደዳሉ። ልክ በአክሱም እንደተደረገው፤ በጉንችሬ እንደተደረገው፤ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሊደረግ መመሪያ እንደወጣለት ማለት ነው። የሀይማኖት ነፃነት መብት የት ነው? የመማር ነፃነት የት ነው? ሰብዓዊ መብት የት ነው? ዛሬ ኒቃብን ካስወለቁ ነገ ፀጉር ግለጡ ማለታቸው አይቀርም። ሆኖም ግን ፈፅሞ አይሆንም!!!
ቻሌንጅ ለሁላችን፦
መልዕክቱ ለሁሉም ይደርስ ዘንድ በቲክቶክ በመግባት ኮፒሊንክ ሪፖስት እናድርግ። ሊንኩ https://vt.tiktok.com/ZSXcA1HkJ/ ነው።
ይህ በዚህ መንገድ ትንሹ ሀላፊነታችን ነው !
ወደ ተግባር !!
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! !
@aaumsu
🎙ከሰለፎች አንደበት!
ኢማሙ ኢብኑልቀዪም (ረሂመሁላህ) እንዲህ ይላሉ፦
﴿خير أيام العبد على الإطلاق وأفضلها، يوم توبته إلى الله﴾
“ለአንድ ባሪያ ፍፁም ከሁሉ የተሻለውና ምርጥ ቀን የሚባለው፤ ወደ አላህ የተመለሰበት (ተውበት ያደረገበት) ቀን ነው።”
📚 ዛዱል‐መዓድ፡ 3/512
"የሀይማኖት ጉዳዮች በሀገራዊ ምክክሩ ላይ አጀንዳ ይሆን ዘንድ ሕዝበ ሙስሊሙ ታግሏል። ሙስሊም ተማሪዎችም ዘርፈብዙ የሆነ ንቅናቄ አድርገዋል። ሀገራዊ ምክክሩ እንደተቋጨ የሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥያቄዎች ዘላቂ፣ ፍትሐዊ እና ተፈፃሚ ምላሽ ሊያገኙ ይገባል።" - ሙሐመድአሚን ካሳው
ቻሌንጅ ለሁላችን፦
መልዕክቱ ለሁሉም ይደርስ ዘንድ በቲክቶክ በመግባት ኮፒሊንክ ሪፖስት እናድርግ። ሊንኩ https://vt.tiktok.com/ZSX7DFQ2R/ ነው።
ይህ በዚህ መንገድ ትንሹ ሀላፊነታችን ነው !
ወደ ተግባር !!
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! !
@aaumsu
ረሱል 🤎 እንዲህ ብለዋል፦
﴿مَنِ اغْتَسَلَ يَوْمَ الْجُمُعَةِ وَتَطَهَّرَ بِمَا اسْتَطَاعَ مِنْ طُهْرٍ، ثُمَّ ادَّهَنَ أَوْ مَسَّ مِنْ طِيبٍ، ثُمَّ رَاحَ فَلَمْ يُفَرِّقْ بَيْنَ اثْنَيْنِ، فَصَلَّى مَا كُتِبَ لَهُ، ثُمَّ إِذَا خَرَجَ الْإِمَامُ أَنْصَتَ غُفِرَ لَهُ مَا بَيْنَهُ وَبَيْنَ الْجُمُعَةِ الْأُخْرَى﴾
“በእለተ ጁምዓ ታጥቦ፣ ከመፀዳዳትም የቻለውንም ተፀዳድቶ፣ ከሚቀባባ ነገርም ተቀባብቶ፣ ቤቱ ውስጥ ከሚገኝ ሽቶ ተቀብቶ፣ ከዚያም ከቤቱ ወጥቶ በሁለት ሰዎች መካከል ሳይለያይ፣ ከዚያም የተፃፈለትን ከሰገደ፣ ከዚያም ኢማሙ በተናገረ ጊዜ ዝም ካለ፣ በዚያች ጁምዓ እና በቀጣዩዋ ጁምዓ መካከል ያለውን ወንጀል ይቅር ይባላል።”
📚ቡኻሪ ዘግበውታል፡ 910
"ፍትሕ ለሙስሊም ተማሪዎች፤ ፍትሕ ፍትሕን ለተራቡ ሁሉ!" - በሱሉልታ የኡመር መህዲ ተማሪዎች የቁርዓን ምርቃት ላይ የተላለፈ መልዕክት
የሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥያቄ ስለፍትሕ የሚቆም ሰው ሁሉ ጥያቄ ነው። ከመድረሳ ተማሪዎች ጀምሮ ሁሉም አካል ይመለከተዋል። ፍትሐዊ መልስ መጥቶ የሙስሊም ተማሪዎች ነፃነት ተከብሮ በእኩልነት መማር እስኪጀምሩ ድረስ መጠየቅ ግድ ነው።
መልዕክቱ ለሁሉም ይደርስ ዘንድ በቲክቶክ https://vt.tiktok.com/ZSXnsYgVr/ በመግባት ኮፒሊንክ ሪፖስት አድርጉ።
ወደ ተግባር!
ይህ ትንሹ ሀላፊነት ነው!!
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ !
@aaumsu
🛠️ Thinking of Choosing Chemical Engineering? The Unfiltered Truth 🇪🇹
💡 3 Ground-Level Realities
👉 It’s no longer just "working in a laboratory": The era of treating Chemical Engineering as purely bench chemistry in Addis is over. Modern ChemE in Ethiopia revolves around continuous mega-plant operations, heat exchanger networks, fluid flow simulation, and industrial process automation.
👉 The Import-Substitution & Fertilizer Boom: Ethiopia’s chemical industrialization is hyper-focused on raw resource processing. Massive industrial investments like the multi-billion-dollar Dangote Fertilizer complex in Gode and the high-automation Lemi National Cement plant are reshaping the sector. You are being trained to design mass-transfer systems that replace multi-million-dollar chemical imports with local limestone, natural gas, and agricultural inputs.
👉 The Energy & Natural Resource Transition: The local chemical landscape is shifting heavily toward domestic energy recovery and heavy process efficiency. As a chemical engineer here, you aren't just mixing batch chemicals; you are managing large-scale bio-processing, local agro-chemical plants, and optimizing waste-heat recovery systems in industrial corridors like Kilinto and Dire Dawa Free Trade Zone.
All of the above means the potential for impact is huge—but only if you view process scale-up as a discipline of precision, safety, and system-level thinking.
The Transition: You will move from basic freshman chemistry and calculus into intense thermodynamics, mass transfer, and transport phenomena. The real challenge is shifting from "mixing reagents in beaker experiments" to calculating mass balances across massive industrial heat exchangers and reactors. If you cannot spend six hours solving differential heat transfer equations or troubleshooting a fluid flow simulation without getting frustrated, this field will drain you quickly.
Join our resource sharing group for Chemical department here:
https://t.me/+QZE_9Wdk28Q1ZTJk
✍Academic Sector
አሰላሙዓለይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካትሁ
📢 በ6 ኪሎ ጀመዓ ዋና ቻናል የሚካሄድ ታላቅና ልዩ የሁለት ቀናት የኦንላይን ስልጠና !
በዘመናችን በፍጥነት እየተስፋፉ ያሉ የሐሳብ ፍሰቶች፣ የአስተሳሰብ አቅጣጫዎች እና ማኅበራዊ ግፊቶች በተለይ በዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ላይ ጥልቅ ተፅዕኖ እያሳደሩ ይገኛሉ። ዛሬ ተማሪዎች ከትምህርታቸው ሥነ-ምህዳር በተጨማሪ በማኅበራዊ ሚዲያ፣ በተለያዩ የውይይት መድረኮች እና በውጭ የሐሳብ ግፊቶች መካከል በብዙ አቅጣጫዎች ተጋጥመው ይገኛሉ። ይህም እምነታቸውን፣ አቋማቸውን እና የአኗኗር መርሃቸውን በሚመለከቱ ጉዳዮች ላይ ግልጽ አቋም እንዳይኖራቸው እና ለተለያዩ ግራ መጋባቶች እንዲዳረጉ ምክንያት ይሆናል። በተለይም በቅርብ ዓመታት በጀመዓችን ግሩፖች፣ በተለያዩ መድረኮች እና በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ በተደጋጋሚ እየተነሱ በሚገኙ ጉዳዮች መካከል የ ፌምኒዝም አጀንዳ በቀዳሚነት የሚጠቀስ ነው!
አብዛኛውን ጊዜ ፌምኒዝም በትክክል ሳይገለጽ ወይም ከእስልምና እይታ ጋር ያለው ግንኙነት በበቂ ሁኔታ ሳይታይ፤ በስሜት ወይም በተሳሳተ መረጃ ላይ ተመሥርቶ ውይይት ሲደረግ ይስተዋላል። ይህ ደግሞ ስለ ሴት መብት፣ ስለ ፍትሕ፣ ስለ ቤተሰብ አወቃቀር ፣ እስልምና ለሴቶች ስላለው ክብር እና እውነተኛ ዕይታ የተዛባ ግንዛቤ እንዲፈጠር አድርጓል።
ስለሆነም ተማሪዎች በቂ የመረጃ መሠረት ሳይኖራቸው ወደ አላስፈላጊ ክርክር ከመግባት እንዲቆጠቡና በእውቀት ላይ የተመሠረተ ሚዛናዊ አቋም እንዲኖራቸው ለማስቻል የ6 ኪሎ ጀመዓ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ሴክተር በመጪው ቅዳሜ እና እሁድ (ሐምሌ 18 እና 19) ልዩ ስልጠና አዘጋጅቶላችኋል!
📌 የመርሃ-ግብሩ ዝርዝር መረጃ፦
📝 ርዕስ ፦Feminism — ታሪካዊ አመጣጡ፣ የሚያነሳቸው ጥያቄዎች እና ሚዛናዊው የእስልምና ዕይታ
👤 አሰልጣኝ ፦ባለፈው ሳምንት በ«Critical Thinking» ርዕስ ዙሪያ ስልጠና የሰጠን በጋዜጠኝነትና በዘመናዊ አስተሳሰቦች (Ideologies) ዙሪያ ሰፊ ልምድ ያለው ወንድማችን ጋዜጠኛ አብዱረህማን አሚን
🗓 ዕለት ፦መጪው ቅዳሜ እና እሁድ (ሐምሌ 18 እና 19)
⏰ ሰዓት፦በሀገር ውስጥ ሰዓት አቆጣጠር ከምሽቱ 3:00 ሰዓት ጀምሮ
📍 ቦታ ፦በ6 ኪሎ ጀመዓ ዋና ቴሌግራም ቻናል ላይ ( @AAU6KiloJemea )
ይህ ስልጠና ሁሉም አካል አእምሮውን ከተዛቡ አመለካከቶች ለመጠበቅና በእውቀት ላይ የተመሰረተ አቋም ለመያዝ የግድ ሊወስደው የሚገባ እጅግ አስፈላጊና ወሳኝ ስልጠና ነው!
ስለሆነም በርካታ ተማሪዎች የዚህ ወርቃማ እድል ተካፋይ እንዲሆኑና ከግርግር የፀዳ እውነተኛ ግንዛቤ እንዲጨብጡ ይህንን ማስታወቂያ በቴሌግራም ስቶሪ ላይ በመለቀቅ፣ ለቅርብ ጓደኞቻችሁ እና በምትገኙባቸው የተለያዩ ግሩፕ ወይም ቻናል ሁሉ ሼር በማድረግ እንዲሁም ሌሎችም ሰዎች እንዲከታተሉ በመጋበዝ የበኩላችሁን እንድትወጡ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን!
🎙️ከሰለፎች አንደበት!
ኢማሙ ኢብኑልቀዪም (🤎) እንዲህ ይላሉ፦
﴿وغض البصر عن النساء يورث في قلبك القوة والشجاعة والفراسة ويورثك انشراح في الصدر﴾
“እይታን ከተከለከሉ ሴቶች መስበር በልብህ ውስጥ ጥንካሬን፣ ጀግንነትን እና ጥልቅ ማስተዋልን (የልብ ብልህነትን) ያሳድጋል። በደረትህም (በውስጣዊ ማንነትህ) ውስጥ የልብ ሰላምንና እፎይታን ያወርሳል።”
📚 ረውደቱል ሙሒቢን፡ 101
"በምርቃት ቀናቸው በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ከእስር ቤት እንዲውሉ የተደረጉ ሙስሊም ተማሪዎች ነበሩ። ምክንያታቸው ደግሞ የለበሳችሁት ሪቫን ላይ ጥቁር ነገር አለው፤ አረብኛ ፅሁፍ አለው፤ የዩኒቨርስቲው ሎጎ የለውም ምናምን የሚሉ ነበሩ። ይህንን ብለው ሙስሊም ተማሪዎችን በደስታ ቀናቸው ከእስር ቤት አዋሏቸው። ይህ ፍፁም ስህተት ነው። ፍትሕ ያስፈልጋል።"
በተማሪዎቹ ላይ የተፈፀመው ነገር መብታቸውን የጣሰ፤ የደስታ ቀናቸውን ያደፈረሰ ብሎም መጥፎ አርዓያነት ያሳረፈ ውንብድና ነበር። እስካሁን ድረስ በዚህ ዙሪያ ከዩኒቨርስቲው ምንም አይነት ማብራሪያ አልተሰጠም። ምንም ሆነ ምን ግን ፍትሕ እስኪመጣ፤ እስኪሰፈን መጠየቃችንን እንቀጥላለን።
መልዕክቱ ለሁሉም ይደርስ ዘንድ https://vt.tiktok.com/ZSXXrgMTD/ በመግባት ኮፒሊንክ ሪፖስት እናድርግ።
ወደ ተግባር!
ይህ በመንገዱ ውስጥ ትንሹ ሀላፊነታችን ነው!!
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! !
@aaumsu
