cookie

Мы используем файлы cookie для улучшения сервиса. Нажав кнопку «Принять все», вы соглашаетесь с использованием cookies.

avatar

Abu hatim Abduselam Aselefiy

ትክክለኛው እስላማዊ አስተምህሮ ከቁርአንና ከሐዲስ ከደጋግ ቀደምቶች አረዳድ ከታማኝ ዑለሞች ንግግር የሚሰራጭበት ቻናል ነው።

Больше
Рекламные посты
1 336
Подписчики
+1224 часа
+307 дней
+4630 дней

Загрузка данных...

Прирост подписчиков

Загрузка данных...

« وَاتَّقُوا فِتْنَةً لَّا تُصِيبَنَّ الَّذِينَ ظَلَمُوا مِنكُمْ خَاصَّةً ۖ وَاعْلَمُوا أَنَّ اللَّهَ شَدِيدُ الْعِقَابِ » " ከናንተም ውስጥ እነዚያን የበደሉትን ብቻ ለይታ የማትነካን ፈተና ተጠንቀቁ ፡፡ አላህም ቅጣቱ ብርቱ መኾኑን እወቁ ፡፡ " የአላህ መልእክተኛ የዘረኝነት አስከፊነትና የከረፋ ጥንብ መሆኑን እንዲሁም አንዱ ሙስሊም በሌላው ላይ ያለው ሐቅ ምን እንደሆነና መግደሉ ኩፍር መስደቡ ፊስቅ መሆኑን የተናገራባቸው ሐዲሶች አንድ መፅሀፍ ይወጣቸዋል ። ነገር ግን የሰው ልጅ ልቦና በወንጀል ከታወረ ማየትም መስማትም አይችልምና ከልቦና መታወር ጠብቀኝ ብሎ አላህን መለመን ያስፈልጋል ። አላህ አላዋቂዎች በሚሰሩት ግፍ ምክንያት ከሚመጣ መቅሰፍትና ፈተና ይጠብቀን ። የሰውም የአጋንንትም ሸይጣኖችን የስራቸውን ሰጥቶ የወንድሞቻችንን ደም ይጠብቅልን ። https://t.me/bahruteka
Показать все...
ባህሩ ተካ - Bahiru Teka

السلام عليكم ورحمة الله وبركاته قناة رسمية لمحاضرات ودروس الأستاذ بحرو تكا (أبو عبيدة) الدعوة السلفية በአላህ ፈቃድ በዚህ ቻናል የአማርኛ ትምህርቶችን እንዲሁም አጫጭር የአረብኛና የአማርኛ ፁሁፎችን እንለቃለን ከዚህ ቻናል ውጪ ከሌላ ቦታ ተወስደው ለሚለቀቁ ኦዲዮዎች እውቅና አልሰጥም

https://telegram.me/bahruteka

Фото недоступноПоказать в Telegram
👍 2
👉 የማንም ብሄር ሆኖ መፈጠር ወንጀል አይደለም ። ይድረስ በሳውዲና በየትኛውም የዐለማችን ክፍል ለምትኖሩ ኢትዮዽያዊያን ሙስሊሞች ። የትም ኑሩ የትም ተፈጠሩ የየትኛውም ብሄር ወይም ጎሳ አባል ሁኑ ይህ በማናችሁም ላይ ወንጀል ሊሆን አይገባም ። ምክንያቱም ማንም ከዚህ ብሄር ( ጎሳ ) መፈጠር እፈልጋለሁ ብሎ አላህ ዘንድ ማመልከቻ አስገብቶ የተፈጠረ የለም ። ለምን ኦሮሞ ሆንክ ለምን አማራ ሆንክ ብሎ ሰውን መግደል ፣ አካል ማጉደል ፣ ደም ማፍሰስ የተከበረውን የሰው ልጅ ከፈጠረው አምላክ ጋር መዋጋት ነው ። በየትኛውም መመዘኛ ተቀባይነት የሌለው ነብዩ ከመላካቸው በፊት የነበሩት የመሀይማን ህዝቦች ተግባር ነው ። እንደዚህ አይነቱ ተግባር በተለይ በሙስሊሞች ሲፈፀም በጣም ያሳዝናል ። በአላህና በመጨረሻ ቀን ያመነ ሙስሊም ፣ ነገ ራቁቱን አላህ ፊት የሚቆም መሆኑን ያመነ ሙስሊም ። እንዴት ወንድሙን ከዚህ ብሄር ነው የተፈጠርከው ስለዚህ ሞት ይገባሀል ብሎ ይገድላል ? ‼ አሳፋሪ ነው ። ኢስላም አላህ የሰውን ልጅ በብሄርና በጎሳ ከፋፍሎ የፈጠረው ሊተዋወቁበት እንጂ ሊፎካከሩበት ፣ እኔ እበልጥ እኔ እበልጥ ሊባባሉበት እንዳልሆነ በሑጅራት ምእራፍ 13ኛው አንቀፅ እንዲህ በማለት ይነግረናል : – « يَا أَيُّهَا النَّاسُ إِنَّا خَلَقْنَاكُم مِّن ذَكَرٍ وَأُنثَىٰ وَجَعَلْنَاكُمْ شُعُوبًا وَقَبَائِلَ لِتَعَارَفُوا ۚ إِنَّ أَكْرَمَكُمْ عِندَ اللَّهِ أَتْقَاكُمْ ۚ إِنَّ اللَّهَ عَلِيمٌ خَبِيرٌ » " እናንተ ሰዎች ሆይ! እኛ ከወንድና ከሴት ፈጠርናችሁ ፡፡ እንድትተዋወቁም ጎሳዎችና ነገዶች አደረግናችሁ ፡፡ አላህ ዘንድ በላጫችሁ በጣም አላህን ፈሪያችሁ ነው፡፡ አላህ ግልጽን ዐዋቂ ውስጥንም ዐዋቂ ነው ፡፡" በዚህ መለኮታዊ የአላህ ቃል አላህ የሰውን ልጅ ከወንድና ከሴት በጎሳና በነገድ ከፋፍሎ የፈጠረው ለመተዋወቅ እንደሆነና ከዚህ ውጪ ትርጉም የሌለው መሆኑን ነው ። በዚህ መለኮታዊ የአላህ ቃል የሚያምን ሙስሊም በምን መመዘኛ አንዱን ከዚህ ጎሳ መፈጠር አልነበረብህም ወይም ሆነህ በመፈጠርህ ወንጀለኛ ያደርግሀል ብሎ አባሮ አድኖ ይገድለዋል ? ‼ እስኪ መልሱን ይንገሩን ። ይህ ማለት ጦርነቱ ከአላህ ጋር ነው ማለት ነው ። እንዴት እገሌን አማራ ወይም ኦሮሞ አድርገህ ፈጠርክ ብሎ ጠርነት መክፈት ነው ። በጣም አሳፋሪ ተግባር መሆኑ ብቻ ሳይሆን በምድር ላይ ጥፋት እንዲሰፍን መቅሰፍት እንዲመጣ የሚያደርግ ነው ። የዚህ አይነቱን ተግባር የማያወግዝ ትውልድ መቆሚያ የሌለው በላእ ለመቀበል ራሱን ያዘጋጅ ። እንዲህ አይነቱን ድርጊት ማስቆም የማይችል መንግስት በመከራና ሰቆቃ የሚኖር ሀገርን ለመምራት ራሱን ያዘጋጅ ። አላህ የሰው ልጆች የሚሰሩት ሀጢያት በምድር ላይ ጥፋት እንዲንሰራፋ ምክንያት የሚሆን መሆኑን ሲነግረን በሩም ምእራፍ በ41 ኛው አንቀፅ እንዲህ ይለናል : – « ظَهَرَ الْفَسَادُ فِي الْبَرِّ وَالْبَحْرِ بِمَا كَسَبَتْ أَيْدِي النَّاسِ لِيُذِيقَهُم بَعْضَ الَّذِي عَمِلُوا لَعَلَّهُمْ يَرْجِعُونَ » " የሰዎች እጆች በሠሩት ኃጢኣት ምክንያት የዚያን የሠሩትን ከፊሉን ያቀምሳቸው ዘንድ መከራው በየብስና በባሕር ተገለጠ ፤ (ተሰራጨ) ፡፡ እነርሱ ሊመለሱ ይከጀላልና ፡፡ " በዚህ አንቀፅ አላህ እንደሚነግረን የሰው ልጆች በሚሰሩት ግፍ ምክንያት በምድርና በባህር ላይ መከራ እንደሚንሰራፋ ( አላህ መቅሰፍት የሚያመጣ ) መሆኑን የመቅሰፍቱ መምጣት ሰዎቹ ከግፋቸውና ከበደላቸው ይመለሱ ዘንድ ተፈልጎ መሆኑን ነው ። ይህ ማለት ሰዎች በሰው ሲመከሩ አሻፈረኝ ካሉ የሚመክራቸው መከራ መምጣቱን ነው ። ነገር ግን መከራም መጥቶ ላይመከሩ ይችላሉ ። እንከን የሌለው የኢስላም አስተምሮ አንድ ሰው ሌላውን ያለ ወንጀሉ በግፍ ከገደለ የሰውን ዘር በሙሉ እንደገደለ መሆኑን በተቃራኒው አንዲትን ነፍስ ከሞት ለመትትረፍ ምክንያት የሆነም የሰውን ዘር ባጠቃላይ ከሞት ለመትረፍ ሰበብ እነደሆነ ነው የሚነግረን ። ይህ የመጠቀ መርህ በማኢዳ ምእራፍ በ32 ኛው አንቀፅ አላህ እንዲህ ብሎ ይነግረናል : – « مِنْ أَجْلِ ذَٰلِكَ كَتَبْنَا عَلَىٰ بَنِي إِسْرَائِيلَ أَنَّهُ مَن قَتَلَ نَفْسًا بِغَيْرِ نَفْسٍ أَوْ فَسَادٍ فِي الْأَرْضِ فَكَأَنَّمَا قَتَلَ النَّاسَ جَمِيعًا وَمَنْ أَحْيَاهَا فَكَأَنَّمَا أَحْيَا النَّاسَ جَمِيعًا ۚ وَلَقَدْ جَاءَتْهُمْ رُسُلُنَا بِالْبَيِّنَاتِ ثُمَّ إِنَّ كَثِيرًا مِّنْهُم بَعْدَ ذَٰلِكَ فِي الْأَرْضِ لَمُسْرِفُونَ » " በዚህ ምክንያት በእስራኤል ልጆች ላይ እነሆ ያለ ነፍስ (መግደል) ወይም በምድር ላይ ያለማጥፋት (ካልሆነ በስተቀር) ነፍስን የገደለ ሰው ሰዎቹን ሁሉ እንደገደለ ነው ፤ ሕያው ያደረጋትም ሰው ሰዎቹን ሁሉ ሕያው እንዳደረገ ነው ማለትን ጻፍን ፡፡ መልክተኞቻችንም በግልጽ ተዓምራት በእርግጥ መጡዋቸው ፡፡ ከዚያም ከዚህ በኋላ ከእነሱ ብዙዎቹ በምድር ላይ ወሰንን አላፊዎች ናቸው ፡፡ " የእነዚህ ረቂቅ መርሆችና አስተምሮዎች ባለቤት የሆነ ሙስሊም ወንድሙን በግፍ እንዴት እንደ ከብት አስተኝቶ ያርዳል ?‼ ነው ወይስ ለሸይጣናዊ አመለካከት ዲኑን ሽጦ ከአላህ ጋር መገናኘት የሚባል ነገር የለም ብሎ በመጪው ዐለም ክዶ ነው ? ይከብዳል ።!!!!! እባካችሁ ሙስሊሞች ከእንቅልፋችሁ ንቁ አኼራን አስታውሱ ካልነበራችሁበት ያስገኛችሁን እሱ ፊት ራቁታችሁ የምትቆሙት አላህን ፍሩ ። ወደራሳችሁ ተመለሱ ሀገራችሁንና ህዝባችሁን ከመከራ አድኑ ። በሰው ልጆች ደምና መከራ ለሚከብሩ በሰው አምሳል ለተፈጠሩ ሰው በላ አውሬዮች ሸቀጥ አትሁኑ ። በጣም የሚያሳዝነውና የሚያሳፍረው በአሁኑ ጊዜ ቁርኣን በወረደበት ፣ ጅብሪል በተመላለሰበት ፣ ነብዩ አውስና ኸዝረጅን ከ50 አመት የእርስ በርስ የመሀይምነት እልቂት በኋላ በላ ኢላሃ ኢልለላህ ( በኢስላም) አንድ ባደረጉበት ሀገር ሳውዲ ላይ የዚህ አይነቱ አሳፋሪ ተግባር በሀገራችን ሙስሊሞች መካከል መፈፀሙ ነው ። ውድ በሳውዲ የምትኖሩ የሀገራች ሙስሊሞች ዛሬ ነገ ሳትሉ ካላችሁበት የዘረኝት ስካር ወጥታችሁ ወደ አላህ ተመልሳችሁ ተውበት አድርጉ ። ውድ የኦሮሞና አማራ መሻኢኽና ዑለሞች እንዲሁም ዱዓቶች አላህ የጣለባችሁን አደራ ከምን ጊዜውም በላይ የምትወጡበት ጊዜ አሁን ነውና በመልካም በማዘዝና ከመጥፎ በመከልከል ድርሻችሁን ተወጡ ካልሆነ የሚመጣውን ፊትና ለመቀበለደ ተዘጋጁ ። ‼ አላህ በምድር ላይ ጥፋት ተንሰራፍቶ ግፍ ሲበዛ ግፈኞቹን ብቻ ለይቶ የማይነካ ፈተና የሚመጣ መሆኑንና እንድንጠነቀቅ በአንፋል ምእራፍ በ25ኛው አንቀፅ እንዲህ ብሎ ይነግረናል : –
Показать все...
👍 1
ሰምንተዊ የቁሪአን ተፊስር ልጀምር ነዉ ገባ        ገባ                 በሉ https://t.me/abuhatimaselefiy
Показать все...
Abu hatim Abduselam Aselefiy

ትክክለኛው እስላማዊ አስተምህሮ ከቁርአንና ከሐዲስ ከደጋግ ቀደምቶች አረዳድ ከታማኝ ዑለሞች ንግግር የሚሰራጭበት ቻናል ነው።

👉 የሙሐረም ወርና ሙስሊሞች የሙሐረም ወር ከሂጅሪያ ወሮች የመጀመሪያውና አላህ ለይቶ ካላቃቸው አራቱ ወራቶች አንዱ ነው ። ይህ ወር የሂጅሪያ ወር መጀመሪያ ቢሆንም ሙስሊሞች የዘመን መለወጫ ብለው በዚህ ወር መግቢያ ላይ የተለየ የሚሰሩት ነገር የለም ። ይልቁንም ሙስሊሞቸው ህይወታቸው የሰከንዶች ሽርፍራፊ ጥርቅም መሆኑንና እየአንዳንዱ ሽርፍራፊ በተቀነሰ ቁጥር ከእድሜያቸው እየተቀነሰና ወደ ቀብር እየተጠጉ መሆናቸውን ነው የሚያውቁት ። በመሆኑም በየትኛውም ዘመን ፣ አመት ፣ ወር ፣ ሳምንት ፣ ሳአት ፣ ደቂቃና ሰከንድ ለሚቀጥለው ዐለም መዘጋጀት እንዳለባቸው ያውቃሉ ። ከዚህ ዝግጅታቸው አንዱ ምንዳና ቱሩፋት አለባቸው በተባሉ ቦታና ጊዜያቶች የታዘዙትን መልካም ስራዎች መስራት ነው ። በመሆኑም በሙሐረም ወር ውስጥ የታዘዙ የአምልኮ አይነቶችን ይፈፅማሉ ምንዳውንም ከጌታቸው ይጠብቃሉ ። የሙሐረም ወር ከአራቱ የተከበሩ ወራቶች ለመሆኑ በመልእክተኛው ሐዲስ የተረጋገጠ ሲሆን ከ12ቱ አራቱ የተከበሩ መሆናቸው ደግሞ አላህ በተከበረው ቃሉ በተውባ ምእራፍ 36ው አንቀፅ እንዲ ብሎ ይነግረናል : – « إِنَّ عِدَّةَ الشُّهُورِ عِندَ اللَّهِ اثْنَا عَشَرَ شَهْرًا فِي كِتَابِ اللَّهِ يَوْمَ خَلَقَ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضَ مِنْهَا أَرْبَعَةٌ حُرُمٌ ۚ ذَٰلِكَ الدِّينُ الْقَيِّمُ ۚ فَلَا تَظْلِمُوا فِيهِنَّ أَنفُسَكُمْ ۚ وَقَاتِلُوا الْمُشْرِكِينَ كَافَّةً كَمَا يُقَاتِلُونَكُمْ كَافَّةً ۚ وَاعْلَمُوا أَنَّ اللَّهَ مَعَ الْمُتَّقِينَ » " የወሮች ቁጥር አላህ ዘንድ በአላህ መጽሐፍ ውስጥ ሰማያትንና ምድርን በፈጠረበት ቀን ዐሥራ ሁለት ወር ነው ፡፡ ከእነሱ አራቱ የተከበሩ ናቸው ፡፡ ይህ ቀጥተኛው ሃይማኖት ነው ፡፡ በእነርሱ ውስጥም ነፍሶቻችሁን አትበድሉ ፡፡ አጋሪዎችንም በአንድ ላይ ኾነው እንደሚዋጉዋችሁ በአንድ ላይ ኾናችሁ ተጋደሉዋቸው ፡፡ አላህም ከሚፈሩት ጋር መኾኑን ዕወቁ ፡፡" የአላህ መልእክተኛ – ሶለላሁ ዓለይሂ ወሰለም – የተከበሩት ወራት የተኞቹ እንደሆኑ በሚከተለው በሐዲሳቸው ነገረውናል : – عن أَبي بَكْرَةَ رضي الله عنه عَنْ النَّبِيِّ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ أنه قَالَ :  " إنَّ الزَّمَانَ قَدْ اسْتَدَارَ كَهَيْئَتِهِ يَوْمَ خَلَقَ اللَّهُ السَّمَوَاتِ وَالأَرْضَ السَّنَةُ اثْنَا عَشَرَ شَهْرًا مِنْهَا أَرْبَعَةٌ حُرُمٌ ثَلاثٌ مُتَوَالِيَاتٌ ذُو الْقَعْدَةِ وَذُو الْحِجَّةِ وَالْمُحَرَّمُ وَرَجَبُ مُضَرَ الَّذِي بَيْنَ جُمَادَى وَشَعْبَانَ " متفق عليه አቡ በክረተ የተባለ ሶሐብይ እንዳወራው የአላህ መልእክተኛ እንዲህ ብለዋል ይላል : – " ዘመን አላህ ሰማይና ምድር ሲፈጥር ወደ ነበረበት ተመልሷል ። ( የሐጅ ወር አላህ በዙል ሒጃ አድርጎታል ። መሀይማኖች የቀየሩት ውድቅ ሆኖ ወደዛው ተመልሷልና ይህን ያዙ ) ። አመት አስራ ሁለት ወር ነው ። ከእነሱ ውስጥ አራቱ የተከበሩ ናቸው ። ሶስቱ ተከታታዮች ናቸው ። ዙል ቀዕዳ ፣ ዙል ሒጃ ፣ ሙሐረም , ረጀብ ደግሞ በጁማደ ሳኒና በሻዕባን መካከል ነው ። " ከእነዚህ ከአራቱ ደግሞ ሙሐረም ይበልጥ የተከበረ ወር መሆኑን ሲነግሩን የአላህ መልእክተኛ እንዲህ ይላሉ : – عن أبي ذر رضي الله عنه قال :  سألت النبي – صلى الله عليه وسلم – : أي الليل خير وأي الأشهر أفضل؟ فقال : " خير الليل جوفه وأفضل الأشهر شهر الله الذي تدعونه المحرم " አቡ ዘር የተባለ ሶሐብይ – ረዲየላሁ ዐንሁ – የአላህ መልእክተኛን የትኛው ለይል ይበልጣል ? የትኛውስ ወር በላጭ ነው ብዬ ጠየቋቸው ። እሳቸውም እንዲ አሉ : – " ከለሊቱ ውስጥ በላጩ ድቅድቁ ( ከመካከለኛው በኋላ) ያለው ነው ። ከወሮች ደግሞ እናንተ ሙሐረም ብላችሁ የምትጠሩት ነው ። " በዚህ ወር ውስጥ ተወዳጅ የሆው መልካም ስራ ደግሞ ፆም ነው ። ይህንንም መልእክተኛው እንዲህ በማለት ይነግሩናል : –  عن أبي هريرة أن النبي صلى الله عليه وسلم قال :  " أفضل الصيام بعد شهر رمضان شهر الله الذي تدعونه المحرم وأفضل الصلاة بعد الفريضة قيام الليل " . رواه مسلم አቡ ሁረይራ ባወሩትና ኢማሙ ሙስሊም በዘገቡት ሐዲስ ነብዩ እንዲህ ብለዋል : – " ከፆሞች ሁሉ በላጩ ከረመዳን ወር በኋላ ሙሐረም ብላችሁ የምትጠሩት ወር ( መፆም ነው) ከሶላት ሁሉ በላጩ ከፈርድ ሶላት በኋላ የለይል ሶላት ነው ። " የአላህ መልእክተኛ በሙሐረም ወር መፆም ( የቻሉትን ማለት ነው) ከረመዳን ወር ፆም ቀጥሎ የተወደደ መሆኑን እየነገሩን ነው ። በመሆኑም አንድ ሰው በሙሐረም ወር ውስጥ የቻለውን ያክል ቢፆም በጣም ተወዳጅ ነው ። እዚህ ጋር መታወቅ ያለበት ከረመዳን ውጪ ወሩን ሙሉ መፆም እንደማይቻል ነው ። በዚህ በሙሐረም ወር የዐስረኛውን ቀን መፆም ያለፈውን አመት ወንጀል የሚያስምር መሆኑን መልእክተኛው በሚቀጥለው ሐዲሳቸው ነግረውናል ። عن أبي قَتادة رضي الله تعالى عنه ، عن الرّسول - صلّى الله عليه وسلّم - قال : " صوم عاشوراء يكفِّر السّنة الماضية " رواه النسائي አቡ ቀታዳ የተባለ ሶሐብይ የአላህ መልእክተኛ እንዲህ ብለዋል ይላል : – " የዓሹራእ ቀንን መፆም ያለፈው አመት ወንጀል ያስምራል ። " ከእነዚህ መረጃዎች በመነሳት ሙስሊሞች በሙሐረም ወር ከፆም የበለጠ የተወደደ ስራ አለመኖሩን ያውቃሉ ። በቻሉት አቅም በፆም ወደ አላህ ይቃረባሉ ከዚህ ውጪ አላስፈላጊ አመለካከትና እምነት ከኢስላም አንፃር ቦታ የለውም ። አላህ ከተጠቃሚዮች ያድረገን ። https://t.me/bahruteka
Показать все...
ባህሩ ተካ - Bahiru Teka

السلام عليكم ورحمة الله وبركاته قناة رسمية لمحاضرات ودروس الأستاذ بحرو تكا (أبو عبيدة) الدعوة السلفية በአላህ ፈቃድ በዚህ ቻናል የአማርኛ ትምህርቶችን እንዲሁም አጫጭር የአረብኛና የአማርኛ ፁሁፎችን እንለቃለን ከዚህ ቻናል ውጪ ከሌላ ቦታ ተወስደው ለሚለቀቁ ኦዲዮዎች እውቅና አልሰጥም

https://telegram.me/bahruteka

የነብዩላህ ኢብራሂም ታሪክ ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ 📝 በኡስታዝ አቡ ዑበይዳህ ባህሩ ተካ በተከታታይ በቴሌግራም ቻናል ቀርቦ 💻 በወንድም አቡ ዒምራን ሙሐመድ መኮንን በሰኔ 2016 E.C በpdf መልኩ ለአንባቢያን ምቹ ሆኖ ቀረበ። 🏝 وَلَقَدْ أَرْسَلْنَا رُسُلًا مِّن قَبْلِكَ مِنْهُم مَّن قَصَصْنَا عَلَيْكَ وَمِنْهُم مَّن لَّمْ نَقْصُصْ عَلَيْكَ 🏝 ካንተ በፊትም መልክተኞችን በእርግጥ ልከናል፡፡ ከእነርሱ ባንተ ላይ የተረክንልህ አልለ፡፡ ከእነርሱም ባንተ ላይ ያልተረክነው አልለ፡፡ [ሱረቱ አል-ሙእሚን - 78] ✅ [የነብዩሊሂ ኢብራሂም ታሪክ ቁርኣን ሊይ ቱክረት ከተሰጣቸው የነብያት ታሪክ ውስጥ በግንባር ቀደምትነት ይመደባል። ታሪካቸው ቁርኣን ውስጥ በ17 ምእራፍ ወደ 69 ጊዜ ተጠቅሷል። ይህ የሚያሳየው ታሪካቸው ምን ያክል አስፈሊጊና ቁም ነገር አዘል መሆኑ ነው።] ▵▮▱▰▱▰▱▰▱▰▱▰▯▴ ⚙ 📝 أَبُـــو عِـمْــرَان ❨𝕒𝕓𝕦 𝕚𝕞𝕣𝕒𝕟❩ 🏝 ••⇣⇣.  🏖   ••⇣⇣  ╰𝐒𝐡𝐚𝐫𝐞.   ╰𝐒𝐡𝐚𝐫𝐞 🖥️ በ 𝐓𝐞𝐥𝐞𝐠𝐫𝐚𝐦~𝐂𝐡𝐚𝐧𝐧𝐞𝐥 🏝 ⇣⇣⇣🍭⇣⇣⇣📲 ⇣⇣⇣↙️ https://t.me/AbuImranAselefy/8873 https://t.me/AbuImranAselefy https://t.me/AbuImranAselefy ሀሳብ  ካለዎ  ⤵️⤵️⤵️⤵️ https://t.me/AbuImranAselefybot
Показать все...
የነብዩላህ ኢብራሒም ታሪክ.pdf3.43 MB
👍 2
ሰምንተዊ የቁሪአን ተፊስር ልጀምር ነዉ ገባ        ገባ                 በሉ https://t.me/abuhatimaselefiy
Показать все...
Abu hatim Abduselam Aselefiy

ትክክለኛው እስላማዊ አስተምህሮ ከቁርአንና ከሐዲስ ከደጋግ ቀደምቶች አረዳድ ከታማኝ ዑለሞች ንግግር የሚሰራጭበት ቻናል ነው።

👍 2
የጎንፎ ዳዕዋ ግብዢያ ለታ ርዕስ" ያአላህን ድንና የነብዩን መንገድ ጨምድደን እንያዝ ከተዳሰሱት ነጥቦች መካከል> አላህን በብቸኝነት ማምለክ ነጃ የመውጫ ጣፋጭና አዋጭ ነው ተውሂድ የነብያቶች ሁሉ ጥሪ ስለመሆኑ ከተለያዩ አንጃዎች ያስጠነቀቁበት ወሳኝ ምክር « መሰረታዊ፣አሳሳቢና ሁሌም ወቅታዊ  የሆነውን አሏህን ያዘዘውን በመታዘዝ እና የከለከለውን በመከልከል ተገቢውን ፍራቻ መፍራት በሚል መሰረታዊ እና ሁሌም በየትኛውም ሁኔታችን፣ቦታ፣ጊዜ  ልንዘነጋው የማይገባ ትልቅ ወስያ ዙሪያ የተሰጠ እጅግ ወሳኝ ምክር»በሚል 👉አሏህ ያዘዘውን በመታዘዝ እና የከለከለውን በመከልከል ተገቢውን ፍራቻ መፍራት 👉ነብያቶች ሳይቀሩ አሏህን እንዲፈሩ የታዘዙበት ስለመሆኑ 👉አሏህን መፍራት ና ውጤቱ ምን እንደሆነ 👉ሪዝቃችን በረካ ፣ሀገራችን ሰላም እንዲሆን ዋና ሰበቡ አላህን መፍራት ስለመሆኑ 👉አሏህን መፍራት ሙሉ ሰላም የሚገኝበት ስለመሆኑ 👉አሏህን በመፍራት ላይ ኢስቲቃማ ሊኖረን ይገባል 🎤 በሸይኽ ሙሐመድ ሃያት ከሃራ [ሃፊዘሁሏህ] 🕌መስጅደ ፉርቃን  ጎንፎ 🗓ሰኔ‐ 26‐ 10 - 2016E.c https://t.me/SheikMohmmedHyatHara
Показать все...
ሸይኽ ሙሀመድ ሀያት ጎንፎ.mp38.54 MB
አስሰላሙዓለይኩም ወራሕመቱላሂ ወበረካቱሁ! ውድ የአል-ኢስላሕ መድረሳ ሳምንታዊ የእሑድ ደርስ ተከታታዮች:- ዘወትር እሑድ በየሳምንቱ የሚሰጠው የኪታብ ቂርኣት ደርሳችን በሰዓቱ የሚቀጥል  ይሆናል። 1. አል አጅዊበቱል ሙፊዳህ   በኡስታዝ በሕሩ ተካ ሐፊዘሁሏህ 2. ሙቀዲመቱል ኣጁሩሚየቲ ፊ ነሕው በኡስታዝ ዐብዱሶመድ ሙሐመድ ሐፊዘሁሏህ 3. አልሐቁል አውከድ ዐላ ጀሚዒል ዒባድ በኡስታዝ ዐብዱልቃዲር ሐሰን ሐፊዘሁሏህ ✍ አል ኢስላሕ መድረሳ t.me/medresetulislah
Показать все...
مدرسة الإصلاح (አል ኢስላሕ መድረሳ)

ይህ ቻናል “❝ከፉሪ ሕይወት ፋና ወደ የስ ውሃ ፋብሪካ በሚወስደው መንገድ በተለምዶ ኑሪ ሜዳ ተብሎ የሚጠራው አካባቢ የሚገኘው የአል ኢስላሕ መድረሳ ኦፊሺያል የቴሌግራም ቻናል ነው።❞ በአላህ ፍቃድ በመድረሳው የሚሰጡና በተለያዩ የሰለፊያህ ዱዓቶች፣ ኡስታዞችና መሻኢኾች የሚተላለፉ መልዕክቶች (በድምፅም ይሁን በፅሑፍ) ይተላለፉበታል። ወዳጅ ዘመድዎን ይጋብዙ።

https://t.me/medresetulislah

👉 የሙሐረም ወርና ሙስሊሞች የሙሐረም ወር ከሂጅሪያ ወሮች የመጀመሪያውና አላህ ለይቶ ካላቃቸው አራቱ ወራቶች አንዱ ነው ። ይህ ወር የሂጅሪያ ወር መጀመሪያ ቢሆንም ሙስሊሞች የዘመን መለወጫ ብለው በዚህ ወር መግቢያ ላይ የተለየ የሚሰሩት ነገር የለም ። ይልቁንም ሙስሊሞቸው ህይወታቸው የሰከንዶች ሽርፍራፊ ጥርቅም መሆኑንና እየአንዳንዱ ሽርፍራፊ በተቀነሰ ቁጥር ከእድሜያቸው እየተቀነሰና ወደ ቀብር እየተጠጉ መሆናቸውን ነው የሚያውቁት ። በመሆኑም በየትኛውም ዘመን ፣ አመት ፣ ወር ፣ ሳምንት ፣ ሳአት ፣ ደቂቃና ሰከንድ ለሚቀጥለው ዐለም መዘጋጀት እንዳለባቸው ያውቃሉ ። ከዚህ ዝግጅታቸው አንዱ ምንዳና ቱሩፋት አለባቸው በተባሉ ቦታና ጊዜያቶች የታዘዙትን መልካም ስራዎች መስራት ነው ። በመሆኑም በሙሐረም ወር ውስጥ የታዘዙ የአምልኮ አይነቶችን ይፈፅማሉ ምንዳውንም ከጌታቸው ይጠብቃሉ ። የሙሐረም ወር ከአራቱ የተከበሩ ወራቶች ለመሆኑ በመልእክተኛው ሐዲስ የተረጋገጠ ሲሆን ከ12ቱ አራቱ የተከበሩ መሆናቸው ደግሞ አላህ በተከበረው ቃሉ በተውባ ምእራፍ 36ው አንቀፅ እንዲ ብሎ ይነግረናል : – « إِنَّ عِدَّةَ الشُّهُورِ عِندَ اللَّهِ اثْنَا عَشَرَ شَهْرًا فِي كِتَابِ اللَّهِ يَوْمَ خَلَقَ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضَ مِنْهَا أَرْبَعَةٌ حُرُمٌ ۚ ذَٰلِكَ الدِّينُ الْقَيِّمُ ۚ فَلَا تَظْلِمُوا فِيهِنَّ أَنفُسَكُمْ ۚ وَقَاتِلُوا الْمُشْرِكِينَ كَافَّةً كَمَا يُقَاتِلُونَكُمْ كَافَّةً ۚ وَاعْلَمُوا أَنَّ اللَّهَ مَعَ الْمُتَّقِينَ » " የወሮች ቁጥር አላህ ዘንድ በአላህ መጽሐፍ ውስጥ ሰማያትንና ምድርን በፈጠረበት ቀን ዐሥራ ሁለት ወር ነው ፡፡ ከእነሱ አራቱ የተከበሩ ናቸው ፡፡ ይህ ቀጥተኛው ሃይማኖት ነው ፡፡ በእነርሱ ውስጥም ነፍሶቻችሁን አትበድሉ ፡፡ አጋሪዎችንም በአንድ ላይ ኾነው እንደሚዋጉዋችሁ በአንድ ላይ ኾናችሁ ተጋደሉዋቸው ፡፡ አላህም ከሚፈሩት ጋር መኾኑን ዕወቁ ፡፡" የአላህ መልእክተኛ – ሶለላሁ ዓለይሂ ወሰለም – የተከበሩት ወራት የተኞቹ እንደሆኑ በሚከተለው በሐዲሳቸው ነገረውናል : – عن أَبي بَكْرَةَ رضي الله عنه عَنْ النَّبِيِّ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ أنه قَالَ :  " إنَّ الزَّمَانَ قَدْ اسْتَدَارَ كَهَيْئَتِهِ يَوْمَ خَلَقَ اللَّهُ السَّمَوَاتِ وَالأَرْضَ السَّنَةُ اثْنَا عَشَرَ شَهْرًا مِنْهَا أَرْبَعَةٌ حُرُمٌ ثَلاثٌ مُتَوَالِيَاتٌ ذُو الْقَعْدَةِ وَذُو الْحِجَّةِ وَالْمُحَرَّمُ وَرَجَبُ مُضَرَ الَّذِي بَيْنَ جُمَادَى وَشَعْبَانَ " متفق عليه አቡ በክረተ የተባለ ሶሐብይ እንዳወራው የአላህ መልእክተኛ እንዲህ ብለዋል ይላል : – " ዘመን አላህ ሰማይና ምድር ሲፈጥር ወደ ነበረበት ተመልሷል ። ( የሐጅ ወር አላህ በዙል ሒጃ አድርጎታል ። መሀይማኖች የቀየሩት ውድቅ ሆኖ ወደዛው ተመልሷልና ይህን ያዙ ) ። አመት አስራ ሁለት ወር ነው ። ከእነሱ ውስጥ አራቱ የተከበሩ ናቸው ። ሶስቱ ተከታታዮች ናቸው ። ዙል ቀዕዳ ፣ ዙል ሒጃ ፣ ሙሐረም , ረጀብ ደግሞ በጁማደ ሳኒና በሻዕባን መካከል ነው ። " ከእነዚህ ከአራቱ ደግሞ ሙሐረም ይበልጥ የተከበረ ወር መሆኑን ሲነግሩን የአላህ መልእክተኛ እንዲህ ይላሉ : – عن أبي ذر رضي الله عنه قال :  سألت النبي – صلى الله عليه وسلم – : أي الليل خير وأي الأشهر أفضل؟ فقال : " خير الليل جوفه وأفضل الأشهر شهر الله الذي تدعونه المحرم " አቡ ዘር የተባለ ሶሐብይ – ረዲየላሁ ዐንሁ – የአላህ መልእክተኛን የትኛው ለይል ይበልጣል ? የትኛውስ ወር በላጭ ነው ብዬ ጠየቋቸው ። እሳቸውም እንዲ አሉ : – " ከለሊቱ ውስጥ በላጩ ድቅድቁ ( ከመካከለኛው በኋላ) ያለው ነው ። ከወሮች ደግሞ እናንተ ሙሐረም ብላችሁ የምትጠሩት ነው ። " በዚህ ወር ውስጥ ተወዳጅ የሆው መልካም ስራ ደግሞ ፆም ነው ። ይህንንም መልእክተኛው እንዲህ በማለት ይነግሩናል : –  عن أبي هريرة أن النبي صلى الله عليه وسلم قال :  " أفضل الصيام بعد شهر رمضان شهر الله الذي تدعونه المحرم وأفضل الصلاة بعد الفريضة قيام الليل " . رواه مسلم አቡ ሁረይራ ባወሩትና ኢማሙ ሙስሊም በዘገቡት ሐዲስ ነብዩ እንዲህ ብለዋል : – " ከፆሞች ሁሉ በላጩ ከረመዳን ወር በኋላ ሙሐረም ብላችሁ የምትጠሩት ወር ( መፆም ነው) ከሶላት ሁሉ በላጩ ከፈርድ ሶላት በኋላ የለይል ሶላት ነው ። " የአላህ መልእክተኛ በሙሐረም ወር መፆም ( የቻሉትን ማለት ነው) ከረመዳን ወር ፆም ቀጥሎ የተወደደ መሆኑን እየነገሩን ነው ። በመሆኑም አንድ ሰው በሙሐረም ወር ውስጥ የቻለውን ያክል ቢፆም በጣም ተወዳጅ ነው ። እዚህ ጋር መታወቅ ያለበት ከረመዳን ውጪ ወሩን ሙሉ መፆም እንደማይቻል ነው ። በዚህ በሙሐረም ወር የዐስረኛውን ቀን መፆም ያለፈውን አመት ወንጀል የሚያስምር መሆኑን መልእክተኛው በሚቀጥለው ሐዲሳቸው ነግረውናል ። عن أبي قَتادة رضي الله تعالى عنه ، عن الرّسول - صلّى الله عليه وسلّم - قال : " صوم عاشوراء يكفِّر السّنة الماضية " رواه النسائي አቡ ቀታዳ የተባለ ሶሐብይ የአላህ መልእክተኛ እንዲህ ብለዋል ይላል : – " የዓሹራእ ቀንን መፆም ያለፈው አመት ወንጀል ያስምራል ። " ከእነዚህ መረጃዎች በመነሳት ሙስሊሞች በሙሐረም ወር ከፆም የበለጠ የተወደደ ስራ አለመኖሩን ያውቃሉ ። በቻሉት አቅም በፆም ወደ አላህ ይቃረባሉ ከዚህ ውጪ አላስፈላጊ አመለካከትና እምነት ከኢስላም አንፃር ቦታ የለውም ። አላህ ከተጠቃሚዮች ያድረገን ። https://t.me/bahruteka
Показать все...
ባህሩ ተካ - Bahiru Teka

السلام عليكم ورحمة الله وبركاته قناة رسمية لمحاضرات ودروس الأستاذ بحرو تكا (أبو عبيدة) الدعوة السلفية በአላህ ፈቃድ በዚህ ቻናል የአማርኛ ትምህርቶችን እንዲሁም አጫጭር የአረብኛና የአማርኛ ፁሁፎችን እንለቃለን ከዚህ ቻናል ውጪ ከሌላ ቦታ ተወስደው ለሚለቀቁ ኦዲዮዎች እውቅና አልሰጥም

https://telegram.me/bahruteka

👍 2
Выберите другой тариф

Ваш текущий тарифный план позволяет посмотреть аналитику только 5 каналов. Чтобы получить больше, выберите другой план.