1 148
Подписчики
-124 часа
-27 дней
-1830 день
Архив постов
1 148
https://vm.tiktok.com/ZMHvC2VcEdfpG-4ifEq/ This post is shared via TikTok Lite. Download TikTok Lite to enjoy more posts: https://www.tiktok.com/tiktoklite
1 148
13/02/2018 ዓ/ም
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የአዲስ አሰልጣኞች የ E-LMIS ምዝገባ በማድረግ ለሳይኮሜትር የሙያ ዝንባሌ ምዘና አደዳዲስ ሰልጣኞች ኖለሳይኮሜትር የሙያ ምዝገባ ተጠናክሮ ቀጥሏል።
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የአዳዲስ ሰልጣኞች ቅበላ በ11/02/2018 ዓ/ም የጀመረ ሲሆን ኮሌጅ በሚሰጣቸው በእስቴቲክስ ፣ በአውቶሞቲቭ ቴክኖሎጂ፣በአይሲቲ፣ በቴክስታይል ኤንድ ጋርመንት ፣ በሆቴል ሰርቪስ ኤንድ ቱሪዝም ፣ በኤሌክትሪካል ኤንድ ኤሌክትሮኒክስ ፣ በቢዝነስ ኤንድ ፋይናንስ ፣ በአርበን አግሪካልቸር ፣ በውድ ወርክ ኤንድ ሜታል ቴክኖሎጂ እና በኮንስትራክሽን ቴክኖሎጂ ምዝገባ ለመጀመር የ E-LMIS ምዝገባ በማድረግ ለሳይኮሜትር የሙያ ዝንባሌ ምዘና ሰልጣኞች እንዲወስድ እየሰራ ይገኛል ።ዠ
የምን ባለሙያ መሆኑ ይፈልጋሉ???
በኤስቴቲክስ🎥፣ በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ 🖥፣ የውበት 💄፣ የአውቶሞቲቭ 🚗፣ የፈርኒቸር 🪑፣ የሆቴልና ቱሪዝም 🏨፣ የኮንስትራክሽን 🏗፣ የፋሽን ዲዛይን 👗፣ በብረታ ብረት እና በእንጨት ስራ 🪵 ቢዝነስ እና ፋይናስ🗃፣ ወይስ ከተማ ግብርና 🌾🐏 ሌላ? 🔧
🛑 ፍላጎትዎን እውን ያደርጉ ብቁ ተወዳዳሪና ስራ ፈጣሪ ይሆኑ ዘንድ በአንጋፋው ተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ (TVET) እርስዎን ለመቀበል ሙሉ ዝግጅታችንን አጠናቀን እናንተን ክቡራን ሰልጣኞችን በመጠባበቅ ላይ ነን ። በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በመመዝገብ ፍላጎቶን እውን ማድረግ የሚያስችልዎትን ስልጠና ያግኙ ። ✨ ✨
ኮሌጃችን በሁለት ቀናት ማለትም በ12 እና 13/02/2018 ዓ.ም 300 ሰልጣኞችን E-LMIS ምዝገባ በማድረግ ለሳይኮሜትር የሙያ ዝንባሌ ምዘና እየተጠባበቁ ይገኛሉ!!!!እጀ-ወርቅ ባለሙያ ሆነው የነገ መዳረሻዎን እራስዎ ይወስኑ!🥇
ዘመን ተሻጋሪ!!
ከኮሚኒኬሽን በድን
1 148
የአርቡ መድረክ ሰአቱ ጠዋት 2:00 ንፋስልክ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ መሆኑን አውቃችሁ ቀድማችሁ ተሰባስባችሁ እንድትገኙ ፣
👉 ዲፓርትመንት ሄዶችና አስተባባሪዎችም ይገኛሉ ።
መልካም ቀን
1 148
የምን ባለሙያ መሆኑ ይፈልጋሉ?
የቴክኖሎጂ 🖥️፣ የውበት 💄፣ የአውቶሞቲቭ 🚗፣ የፈርኒቸር 🪑፣ የሆቴልና ቱሪዝም 🏨፣ የኮንስትራክሽን 🏗️፣ የፋሽን ዲዛይን 👗 ወይስ ሌላ? 🔧
ፍላጎትዎን እውን ያደርጉ ዘንድ የቴክኒክና ተቋሞቻችን (TVET) ሙሉ ዝግጅታቸውን አጠናቀው እርስዎን ለመቀበል በመጠባበቅ ላይ ናቸው። ✅
አቅራቢያዎ ወደሚገኝ ቴክኒክና ሙያ ተቋም በመሄድ ፍላጎቶን እውን ማድረግ የሚያስችልዎትን ስልጠና ያግኙ።✨
እጀ-ወርቅ ባለሙያ ሆነው የነገ መዳረሻዎን እራስዎ ይወስኑ! 🥇
' የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር'
1 148
Repost from ጎፋ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ Gofa Industrial College
የምን ባለሙያ መሆኑ ይፈልጋሉ?
የቴክኖሎጂ 🖥️፣ የውበት 💄፣ የአውቶሞቲቭ 🚗፣ የፈርኒቸር 🪑፣ የሆቴልና ቱሪዝም 🏨፣ የኮንስትራክሽን 🏗️፣ የፋሽን ዲዛይን 👗 ወይስ ሌላ? 🔧
ፍላጎትዎን እውን ያደርጉ ዘንድ የቴክኒክና ተቋሞቻችን (TVET) ሙሉ ዝግጅታቸውን አጠናቀው እርስዎን ለመቀበል በመጠባበቅ ላይ ናቸው። ✅
አቅራቢያዎ ወደሚገኝ ቴክኒክና ሙያ ተቋም በመሄድ ፍላጎቶን እውን ማድረግ የሚያስችልዎትን ስልጠና ያግኙ።✨
እጀ-ወርቅ ባለሙያ ሆነው የነገ መዳረሻዎን እራስዎ ይወስኑ! 🥇
' የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር'
1 148
11/02/2018 ዓ/ም
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለባለ ድርሻ አካላት የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርት አቀረበ ።
አንደኛው ከፖሊሲ አንፃር ከተቀመጠው የባለድርሻ አካላት ተቋማችን በISO2100l:2018EMS እውቅና ስላገኘ ከባለድርሻ አካላት ጋር የሚያስቀምጠው ጉዳይ ከባለድርሻ አካላት ጋር አብሮ የመስራት ፍላጎታቸውን ከኮሌጅ እቅድና ተግባር ጋር አብሮ አያይዞ መስራት በየእሩብ አመቱ እቅድ አፈፃፀም መገምገም ።የኮሌጅ ዲን አቶ አብድልበር መሀመድ ከባለድርሻ አካላት ጋር ረዘም ላለ ጊዜ እየሰራ የሚገኝ አንጋፋ የመቶ አመት እድሜ ያለው ኮሌጅ መሆኑን የገለፁ ሲሆን የኮሌጅ ሰልጣኞች በኢንድስትሪ ገብተው የሚሰሩ ስለሆነ እቅዳችን በማሳወቅ አብረን ተናበን የምንሰራበትን አውድ መፍጠር ተገቢ ስለሆነ ከወር በፊት እቅድ ላይ ወገናኘታቸውን አስታውሰው ዛሬ በሚቀርበውን እቅድ አፈፃፀም ላይ፣ኮሌጅ የነባር ሰልጣኞች ምዝገባ ጨርሶ አዲስ ሰልጣኞችን እየተቀበለ እንደሚገኝ አስረድተው ሰልጣኞች ስልጠና የሚወስድበትን እና የሰልጣኞች ቅበላን እንዲመለከቱና አስተያየት እንዲሰጡበት ጠይቀው በሚገኘው አስተያየት ላይ የኮሌጅ ማኔጅመንት ገምግሞ ምላሽ እንደሚሰጥበት አስገንዝበዋል ።በቀጣይም በግማሽ አመት የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ላይ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር መድረክ እንደሚፈጠር አስረድተዋል ። የኮሌጅ የአንደኛ ሩብ አመት እቅድ አፈፃፀም በንግስቲ ገ
/ሂወት ቀርቧል። በቀረበውም የእቅድ አፈፃፀም እሪፖርት ላይ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር የሚካሄድ የጋራ መድረክ፣ የቀዳማዊ ልጅነት ላይ መድረክ ፣ በኢንድስትረ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ፣ በአጭር የስልጠና አገልግሎት እና ሌሎች የተከናወኑ ተግባራ ቀርበዋል ባለድርሻ አካላትም በቀረበው የሩብ አመትየእቅድ አፈፃፀም እሪፖርት ላይ አስተያየት ሰተውበታል ።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://t.me/EntotoPtc1917
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
1 148
10/02/2018 ዓ/ም
የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የተቋም ልማት እና አስተዳደር ጉዳዩች የ2018 በጀት ዓመት የእውቀት ሽግግር ዕቅድ ቀረበ ።
በተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በወርቃማ ሰኞ መረሀ ግብር ላይ የተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የተቋም ልማት እና አስተዳደር ጉዳዩችየ2018 በጀት ዓመት የእውቀት ሽግግር ዕቅድ የቀረበ ሲሆን የአዲሰ አበባ ከተማ አስተዳደር ባወረደው ጨለማው ሰኞ (Black Monday) የሚሉትን እኛ ወርቃማው ሰኞ ‘’Golden Monday’’ በማለት ለተገልጋዮች ቅርብ ለመሆን እና አገልግሎታችንን ለማሻሻል እርስ በእርሳችን የምንመካከርበት፣ የምንማማርበት፣ ልምድ የምንለዋወጥበት እንዲሁም እንደ መሪ ታች ካሉ ሰራተኞቻችን ጋር ጭምር ማህበራዊ ህይወታችንን ከስራችን ጋር በማስተሳሰር ለመቀራረብ እና ሃሳብ ለመለዋወጥ በ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት ግቦችንና ዓላማዎችን እውን ማድረግ የሚያስችል አደረጃጀት ለመፍጠር እንዲመች የተቋም ልማትና እና አስተዳደር ጉዳዮች ዘርፍ ዕቅዱ ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡የእውቀት ሽግግር’’knowledge transfers’’ (KT) እቅድ በአንድ መስሪያ ቤት (በኮሌጅ) ውስጥ ወሳኝ መረጃዎችን፣ ክህሎቶችን እና እውቀትን ከአንድ ሰው ወይም ቡድን ወደ ሌላ ሰው ለመቅዳት እና ለማንቀሳቀስ የተዋቀረ ስልት ነው፣አጠቃላይ እቅድ ቁልፍ እውቀትን መለየት ፣ መመዝገብ ፣መስቀመጥ እና የግንኙነት ስርዓቶችን መዘርጋት ፣የማስተላለፊያ ሂደቱን መግለፅ ፣ ሚናዎችን መስጠት እና ለስኬት እና ለማመቻቸት ሂደቱን ለመገምገም፣ ለአዳዲስ ተቀጣሪዎች እና ሰራተኞች አስፈላጊ መረጃዎችን በመስጠት ወደ አዲስ ሚናዎች ለሚገቡ ሰራተኞች ቀለል ያለ የቦርድ ጉዞን ለመፍጠር እንዲሁም በኮሌጁ ውስጥ ስልታዊ እና ቀጣይነት ያለው የመረጃ ፍሰት እንዲኖር ያበረታታል።በአጠቃላይ ዝርዝር ዓላማዎች፣ተልዕኮ፣ ራዕይና እሴቶች፣ተልዕኮ፣ እሴቶች፣የሚከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት ፣ግቦችና ተግባራት ፣አፈጻጸም ክትትልና ግምገማ ሥርዓት በዝርዝር ቀርበዋል።በቀረበው የኮሌጁ የተቋም ልማት እና አስተዳደር ጉዳዩች የ2018 በጀት ዓመት የእውቀት ሽግግር ዕቅድ ላይ የኮሌጁ ዲን እና ምክትል ዲኖች ማብራሪያ ለኮሌጁ ማህበረሰብ ሰጥተዋል ።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://t.me/EntotoPtc1917
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
Уже доступно! Исследование Telegram 2025 — ключевые инсайты года 
