1 148
Подписчики
-124 часа
-27 дней
-1830 день
Архив постов
1 148
10/02/2018 ዓ/ም
የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የተቋም ልማት እና አስተዳደር ጉዳዩች የ2018 በጀት ዓመት የእውቀት ሽግግር ዕቅድ ቀረበ ።
በተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በወርቃማ ሰኞ መረሀ ግብር ላይ የተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የተቋም ልማት እና አስተዳደር ጉዳዩችየ2018 በጀት ዓመት የእውቀት ሽግግር ዕቅድ የቀረበ ሲሆን የአዲሰ አበባ ከተማ አስተዳደር ባወረደው ጨለማው ሰኞ (Black Monday) የሚሉትን እኛ ወርቃማው ሰኞ ‘’Golden Monday’’ በማለት ለተገልጋዮች ቅርብ ለመሆን እና አገልግሎታችንን ለማሻሻል እርስ በእርሳችን የምንመካከርበት፣ የምንማማርበት፣ ልምድ የምንለዋወጥበት እንዲሁም እንደ መሪ ታች ካሉ ሰራተኞቻችን ጋር ጭምር ማህበራዊ ህይወታችንን ከስራችን ጋር በማስተሳሰር ለመቀራረብ እና ሃሳብ ለመለዋወጥ በ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት ግቦችንና ዓላማዎችን እውን ማድረግ የሚያስችል አደረጃጀት ለመፍጠር እንዲመች የተቋም ልማትና እና አስተዳደር ጉዳዮች ዘርፍ ዕቅዱ ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡የእውቀት ሽግግር’’knowledge transfers’’ (KT) እቅድ በአንድ መስሪያ ቤት (በኮሌጅ) ውስጥ ወሳኝ መረጃዎችን፣ ክህሎቶችን እና እውቀትን ከአንድ ሰው ወይም ቡድን ወደ ሌላ ሰው ለመቅዳት እና ለማንቀሳቀስ የተዋቀረ ስልት ነው፣አጠቃላይ እቅድ ቁልፍ እውቀትን መለየት ፣ መመዝገብ ፣መስቀመጥ እና የግንኙነት ስርዓቶችን መዘርጋት ፣የማስተላለፊያ ሂደቱን መግለፅ ፣ ሚናዎችን መስጠት እና ለስኬት እና ለማመቻቸት ሂደቱን ለመገምገም፣ ለአዳዲስ ተቀጣሪዎች እና ሰራተኞች አስፈላጊ መረጃዎችን በመስጠት ወደ አዲስ ሚናዎች ለሚገቡ ሰራተኞች ቀለል ያለ የቦርድ ጉዞን ለመፍጠር እንዲሁም በኮሌጁ ውስጥ ስልታዊ እና ቀጣይነት ያለው የመረጃ ፍሰት እንዲኖር ያበረታታል።በአጠቃላይ ዝርዝር ዓላማዎች፣ተልዕኮ፣ ራዕይና እሴቶች፣ተልዕኮ፣ እሴቶች፣የሚከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት ፣ግቦችና ተግባራት ፣አፈጻጸም ክትትልና ግምገማ ሥርዓት በዝርዝር ቀርበዋል።በቀረበው የኮሌጁ የተቋም ልማት እና አስተዳደር ጉዳዩች የ2018 በጀት ዓመት የእውቀት ሽግግር ዕቅድ ላይ የኮሌጁ ዲን እና ምክትል ዲኖች ማብራሪያ ለኮሌጁ ማህበረሰብ ሰጥተዋል ።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://t.me/EntotoPtc1917
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
1 148
በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ከ4 መቶ 54 ሺህ 106 በላይ ዜጎችን ተቀብሎ ለማስተናገድ ዝግጅት ተደርጓል
ክቡር ተሻለ በሬቻ(ዶ/ር)
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ
🇪🇹 ጥቅምት 10/2018 ዓ.ም 🇪🇹
የ2018 የትምህርትና ስልጠና ዘመን የቴክኒክና ሙያ ስልጠና የመቁረጫ ነጥብ ዛሬ ይፋ ተደርጓል፡፡
የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ለዜጎች ተግባራዊ እውቀትና ክህሎትን በማስታጠቅ የሥራ ፈጠራ አቅምና ችግር ፈቺ አስተሳሰቦችን ያለውን ቁልፍ ሚና በመገንዘብ መንግስት ለዘርፉ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራበት ይገኛል፡፡
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ባለፉት ዓመታት ዘርፉ ለሀገራዊ የልማት ፍላጎት ምላሽ መስጠት እንዲችል የሥራ ገበያውን መሰረት ያደረገ የክህሎት ልማት አቅጣጫ ነድፎ በየዓመቱ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች በመደበኛና አጫጭር ስልጠና ተደራሽ እያደረገ ይገኛል፡፡
በዚህ መሠረት 2017 የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች ውጤትን፣ የሥራ ገበያው ፍላጎት እና የቴክኒክና ሙያ ተቋማት የቅበላ አቅምን ከግምት ውስጥ በማስገባት የ2018 የትምህርትና ስልጠና ዘመን የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት መቀበያ መቁረጫ ነጥብን ይፋ አድርጓል፡፡
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር፣ የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ተሻለ በሬቻ(ዶ/ር) የመቁረጫ ነጥቡን አስመልክቶ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ባለፉት ሦስት ዓመታት በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ ከ1,500 ባላይ የቴክኒክና ሙያ ተቋማትን በአካባቢያቸው ያለውን ተፈጥሯዊ ፀጋ መሰረት ባደረገ መልኩ እንዲደራጁና ስልጠና እንዲሰጡ መደረጉን ክቡር ሚኒስትር ድኤታው አስታውቀዋል፡፡
የተቋማቱን የቅበላ አቅም ለማሳደግ በሚያስችል መልኩ የውስጥና የዲጂታል መሰረተ ልማትን የማስፋፋት ሥራ ሲሠራ መቆየቱን የገለፁት ሚኒስትር ዴኤታው በ2017 ዓ.ም በመደበኛ ከ5መቶ ሺ በላይ፣ በአጫጭር ስልጠና ደግሞ ከ4ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ ሰልጣኞችን ተቀብሎ ማስተናገድ መቻሉን አስረድተዋል፡፡
ከዚህ በተጨማሪ ከ1መቶ ሺ በላይ የሚሆኑ በልምድ የሙያ ባለቤት የሆኑ ዜጎች ተመዝነው ዕውቅና ማግኘታቸውን ብሎም ከ5መቶ ሺ የሚልቁ ደግሞ ለውጭ ሀገር ሥራ ሥምሪት ብቁ የሚያደርጓቸውን ስልጠናዎች በቴክኒክና ሙያ ተቋማት መከታተላቸው ተገልጿል፡፡
በ2018 የትምህርትና ስልጠና ዘመን 12ኛ ክፍል ያጠናቀቁ ከ4መቶ 54ሺ1መቶ ስድስት የሚሆኑ ዜጎችን ተቀብሎ በመደበኛ ፕሮግራም ለማሰልጠን፣ 4ሚሊየን ለሚሆኑ ዜጎች አጫጭር ስልጠና በመስጠት ለሀገር ውስጥ የሥራ መስኮች ለማብቃት እንዲሁም ቁጥራቸው እስከ 8መቶ ሺ የሚሆኑ ዜጎችን ደግሞ በስልጠና አብቅቶ ለውጭ ሀገር የሥራ ገበያ ዝግጁ ለማድረግ የሚያስችል ዕቅድ መያዙንም አስታውቀዋል፡፡
1 148
ለትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ 2018 ዓ.ም የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ምዝገባ መጀመሩን በደስታ እንገልፃለን ከዛሬ ጀምሮ 10/01/2018 መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን በደስታ እንገልፃለን፡፡
1 148
ለትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ 2018 ዓ.ም የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ምዝገባ መጀመሩን በደስታ እንገልፃለን ከዛሬ ጀምሮ 10/01/2018 መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን በደስታ እንገልፃለን፡፡
1 148
ለትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ 2018 ዓ.ም የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ምዝገባ መጀመሩን በደስታ እንገልፃለን ከዛሬ ጀምሮ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን በደስታ እንገልፃለን፡፡
1 148
ለትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ 2018 ዓ.ም የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ምዝገባ መጀመሩን በደስታ እንገልፃለን ከዛሬ ጀምሮ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን በደስታ እንገልፃለን፡፡
1 148
የቴክኒክና ሙያ ተቋማት አመራርና አሰልጣኝ በዘርፉ እሳቤና ስትራቴጂ ዙሪያ የጠራ ግንዛቤ በመያዝ ክህሎት ያለው ዜጋ የመፍጠር ሂደቱን እንዲያፋጥን ተጠየቀ።
ጥቅምት 9/2018 ዓ.ም
የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ዘርፉን ሪፎርም ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር መጠነ ሰፊ ተግባራትን በማከናወን ላይ ይገኛል።
የዚሁ ተግባር አንዱ አካል የሆነው እና 310 የቴክኒክና ሙያ አመራሮችና፣የስልጠና ዘርፍ ተጠሪዎችና አስተባባሪዎች የተሳተፉበት የአቅም ግንባታ ስልጠና ላለፉት ሁለት ቀናት ሲካሄድ ቆይቶ በዛሬው ዕለት ፍፃሜውን አግኝቷል።
በስልጠናው የዘርፉ አዲሱ እሳቤን ጨምሮ የቴክኒክና ሙያ ስትራቴጂ፤በአስራ አንዱ ዘረመል እንዲሁም በአመራር ጥበብ ዙሪያ ገለፃና ማብራሪያ ተሰጥቷል።
ገለፃውን ተከትሎም በተካሄደው የቡድን ውይይት ዘርፉን ወደ ፊት ሊያራምዱ የሚችሉ ጠቃሚ ሀሳቦች ማሰባሰብ ተችሏል።
በማጠቃለያ መድረኩ የተገኙት በቢሮ ሀላፊ ደረጃ የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ የውጤት ተኮር ስልጠናና ተቋማት አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ ክብርት ወ/ሮ ዳግማዊት ግርማ ስልጠናው ብቃት ያለው አመራርና አሰልጣኝ በመፍጠር እና ፍላጎት መር የአሰለጣጠን ስርዓት በመተግበር የበቃ ሰልጣኝ ለመፍጠር ያስችላል ብለዋል።
ክብርት ወ/ሮ ዳግማዊት አያይዘውም ስልጠናው የዘርፉ አመራር፣ የስልጠና ዘርፍ ተጠሪዎችና አስተባባሪዎች በዘርፉ እሳቤና ስትራቴጂ ዙሪያ የጠራ እሳቤ እንዲይዝ በማድረግ ክህሎት ያለው ዜጋ ለመፍጠር የሚያስችል በመሆኑ አመራሩና አሰልጣኙ የበኩላቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል።
በህብረተሰቡ ዘንድ ለዘርፉ ያለውን ግንዛቤ ለማሳደግ በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸው የተገለፀ ሲሆን የ2018 የቴክኒክና ሙያ መግቢያ መቁረጫ ነጥብ ነጥብ መሰረት በብሎክ አደረጃጀት ሰልጣኞች ወደ ስልጠና እንዲቀላቀሉ እንደሚሰራ ተጠቁሟል።
በሌላ በኩል ከአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ጋር በመቀናጀት ተማሪዎች በቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጆች በደረጃ አንድና ሁለት የተግባር ስልጠና እንዲወስዱ ይደረጋል ተብሏል።
ይህም የቴክኒክና ሙያ ሰልጣኞችን እጥረት ከመቅረፍ ባሻገር ዜጎች የክህሎት ባለቤት እንዲሆኑ ያስችላል።
ዘርፉ ያለውን እምቅ አቅም ወደ ተግባር በመለወጥ የከተማችንን ብሎም የሀገራችንን ችግር መፍታት ይኖርብናል ሲሉም ኃላፊዋ አሳስበዋል።
በስልጠናው ተሳታፊዎች በበኩላቸው ስልጠናው በዘርፉ እሳቤ ዙሪያ ግልፅነትን በመፍጠር ለቀጣይ ተልዕኮ መነሳሳትን የፈጠረ ነው ሲሉ ተደምጠዋል።
ስልጠናው የዞኒንግና ዲፈረንሼሽን ትግበራው ተከትሎ በሚፈጠረው የአሰልጣኞች ድልድል መሰረት እንደሚቀጥል ይጠበቃል።
<<ከፍታን ማፅናት፤ ነገን ማላቅ>>
ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ
👉 Tiktok
https://www.tiktok.com/@bols20116?_t=ZM-8y9L28EOubG&_r=1
👉Facebook
https://www.facebook.com/addisababatvetbureau
👉Telegram
https://t.me/AABOLS
👉YouTube
https://youtube.com/channel/UCvdSuxRP-cMVC7-lSv2fxag?si=YiWZURWWlmGDBPjv
👉website
https://aabols.gov.et
👉ለቅሬታ፣ አስተያየትና ጥቆማ
https://complain.aabols.gov.et
Уже доступно! Исследование Telegram 2025 — ключевые инсайты года 
