ru
Feedback
Ethiopian Public Service University

Ethiopian Public Service University

Открыть в Telegram

ፐብሊክ አገልግሎት ልህቀት በተግባር ተኮር እውቀት

Больше

📈 Аналитический обзор Telegram-канала Ethiopian Public Service University

Канал Ethiopian Public Service University (@epsutelegram) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 12 737 подписчиков, занимая 15 736 место в категории Образование и 2 645 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 12 737 подписчиков.

Согласно последним данным от 13 июля, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 112, а за последние 24 часа — 2, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 34.81%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 15.93% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 4 434 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 2 029 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 30.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
ፐብሊክ አገልግሎት ልህቀት በተግባር ተኮር እውቀት

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 14 июля, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Образование.

12 737
Подписчики
+224 часа
+217 дней
+11230 день
Архив постов
photo content

photo content
+5

photo content
+9

በኢፐሰዩ በተካሄደው የአመራር ሽግሽግ መሰረት ርክክብ ሥነ- ስርዓት ተካሄደ የኢትዮጵ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የሥራ አመራር ቦርድ፣ ታህሳስ 24 ቀን 2018 ዓ/ም ባካሄደው ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባ ባሳለፈው ውሳኔ መሰረት፣ ከጥር 1 ቀን 2018 ዓም ጀምሮ በተፈጸመው የአመራር ሽግሽግ፣ ተሰናባቾቹ የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዘደንት፣ የምርምር እና ትብብር ምክትል ፕሬዘዳንት እና የአስተዳደር እና ልማት ምክትል ፕሬዘዳንት፣ በተጠባባቂነት ለየዘርፉ ከተመደቡት ምክትል ፕሬዘዳንቶች ጋር የስራ ርክክብ አደረጉ፡፡ በሽግሽጉ መሰረት ከአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝደንትነት ዶ/ር ለማ ጉዲሳ ተነስተው፣ በምትካቸው ዶ/ር አማኑኤል ኩሲያ ተመድበዋል፤ ከምርምርና ትብብር ምክትል ፕሬዘደንትነት ዶ/ር አለማዬሁ ደበበ ተነስተው፣ በምትካቸው ዶ/ር ምትኩ አዲሱ ተመድበዋል፤ እንዲሁም ከአስተዳደርና ልማት ምክትል ፕሬዘደንትነት ዶ/ር ታዴዎስ ሜንታ ተነስተው፣ በምትካቸው ዶ/ር ተሾመ ዱላ ተመድበዋል፡፡ በርክክቡ ሥነ- ስርዓቱ ላይ ተሰናባቾቹ ምክትል ፕሬዘደንቶች፣ የመውጫ ሪፖርት አዘጋጅተው ያስረከቡ ሲሆን፣ ሲመሩት ለቆዩት ዘርፍ የተሰጠው የመደበኛ እና የሪፎርም ስራ አፈጻጸም ያለበትን ደረጃ በዝርዝር አስረድተዋል፤ በመጨረሻም በየዘርፉ ያሉ ዲኖችን፣ ዳይሬክተሮችን፣ ስራ አስፈጻሚወችን እና የትምህርት ክፍል ኃላፊዎችን ከአዲሶቹ ምክትል ፕሬዘደንቶች ጋር አስተዋውቀው ስነስርአቱ ተጠናቋል፡፡ Visit our website: http://www.epsu.edu.et/ Follow our Facebook page: https://web.facebook.com/EPSUfb Follow our Telegram Channel: https://t.me/epsutelegram Follow us on LinkedIn: https://www.linkedin.com/.../ethiopian-public.../about/ Subscribe to our YouTube channel: https://www.youtube.com/@EPSUyt ፐብሊክ አገልግሎት ልህቀት በተግባር ተኮር እውቀት at EPSU PR call: 0945746405

photo content
+6

ኢፐሰዩ ለኢራስመስ + 2026 የፕሮፖዛል የምርምር ቡድን አባላት ኦሬንቴሽን ተሰጠ፤ በኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የአውሮፓ የትምህርት እና የባህል አስፈፃሚ ኤጀንሲ ኢራስመስ+ 2026 የፕሮፖዛል ጥሪ (Erasmus+ 2026 call for proposals) በሚል ባቀረበው የምርምር ፕሮፖዛል ላይ ለሚሳተፉ የምርምር ቡድን አባላት፣ ጥር 4 ቀን 2018 ዓ/ም በዩኒቨርሲቲው የሴኔት አዳራሽ ኦሬንቴሽን ተሰጠ፡፡ ለምርምር ቡድኑ አባላት ኦሬንቴሽን የሰጡት፣ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዘዳንት ንጉስ ታደሰ (ዶ/ር) ሲናገሩ፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚፈለገው የፕሮጀክት አጻጻፍ፣ በእኛ ከተለመደው የተለዬ ባለብዙ ዘርፍ (multidisciplinary) መሆን እንዳለበት መገንዘብ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸው፣ “አንድ ችግር በአንድ የሙያ መስክ እና በአንድ አካባቢ በሚገኝ ተቋም በሚካሄድ ጥናት እንደማይፈታ ስምምነት ላይ ተደርሷል፤ይህንን አስተሳሰብ ለምርምር ድጋፍ የሚያደርጉ ተቋማትም እንደ መስፈርት እየተጠቀሙበት ነው፤ ስለዚህ እኛም በትብብር የመስራትን ባህል ማዳበር ይኖርብናል፤ በቀጣይም የመምህራንን የምርምር ስራ ከአዲሱ አስተሳሰብ ጋር የሚያገናኝ ስልጠና እናዘጋጃለን፡፡” ብለዋል፡፡ በማስከተልም ፕሬዘዳንቱ፣ ዩኒቨርሲቲው የአጋርነት እና የትብብር ስራዎችን እራሱን አስችሎ የሚመራ ዳይሬክቶሬት አደራጅቶ ወደ ስራ መግባቱን አስታውሰው፣ “በትብብር እና አጋርነት ዘርፍ እራሳችንን ከፍ ለማድረግ የምንችለው፣ የተደራጀ የግራንት አስተዳደር ፕሮፋይል ሲኖረን ነው፤ ስለዚህ ይህ አዲሱ የአጋርነት እና ትብብር ዳይሬክቶሬት፣ የምርምር ስራዎችን አሰባስቦ ወደ ዳታ ቤዝ ማስገባት ይጠበቅበታል፡፡” ብለዋል፡፡ የፕሬዘዳንቱ ልዩ ረዳት አብርሃም ሀጎስ (ዶ/ር)፣ ዩኒቨርሲቲው አሁን ያለበት የሪፎርም ሁኔታ ባለመፍቀዱ፣ ለዚህ ፕሮፖዛል የተመራማሪዎች ምርጫ በፕሮፋይል ፍተሸ መካሄዱን፣ በቀጣይ ግን በውድድር መምረጥ የሚያስችል ስርዓት እንደሚዘረጋ ገልጸዋል፡፡ ቀጥለውም፣ “የአጋርነትና ትብብር ዳይሬክቶሬት ከተደራጀ ወዲህ አዲስ ባህል እየተፈጠረ መሆኑን መመልከት የሚያስችል ጅማሮ እየታየ ነው፤ የተጀመረው የሀገር ውስጥ እና የዓለም አቀፍ ጥናቶችን እያፈላለጉ ወደ ዩኒቨርሲቲው የማምጣት ስራ ተጠናክሮ መቀጠል ይኖርበታል፡፡” ብለዋል፡፡ የትብብርና አጋርነት ዳይሮክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት ደረጀ ተ/ማርያም (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ ዛሬ በዩኒቨርሲቲ ደረጃ ከኤራስመስ የቀረበው የሪሰርች ፕሮፖዛል የውድድር ጥሪ፣ ለምርምር እና ለአቅም ግንባታ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚደረግ ውድድር መሆኑን ገልጸው፣ “የኒቨርሲቲያችን እንደ ተቋም ከኤራስመስም ጋር የፕሮፖዛል ተሳትፎ ሲያደርግ የመጀመሪያው ነው፤ ከዚህ በኋላ ዳይሬክቶሬቱ የሀገር ውስጥ እና ዓለም አቀፍ ምርምሮችን እና ትብብሮችን እያፈላለገ ወደ ዩኒቨርሲቲው ማምጣት ዋነኛ ተግባሩ አድርጎ ይቀጥላል፡፡” ብለዋል፡፡ Visit our website: https://www.epsu.edu.et/ Follow our Facebook page: https://web.facebook.com/EPSUfb Follow our Telegram Channel: https://t.me/epsutelegram Follow us on LinkedIn: https://www.linkedin.com/.../ethiopian-public.../about/ Subscribe to our YouTube channel: https://www.youtube.com/@EPSUyt ፐብሊክ አገልግሎት ልህቀት በተግባር ተኮር እውቀት at EPSU PR call: 0945746405

Dear EPSU’s Ambassadors, Based on your valuable recommendations, we have created the official LinkedIn account for our univer
Dear EPSU’s Ambassadors, Based on your valuable recommendations, we have created the official LinkedIn account for our university. This account will be maintained actively, alongside our other social media platforms, to keep you informed about university updates and activities. We kindly invite you to follow our LinkedIn page to stay up-to-date with the latest news and announcements. To follow us, please click this link: https://www.linkedin.com/company/ethiopian-public-service-university-epsu/about/ Thank you once again for your insights and continued support.

photo content
+5

በኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በቀጠለው የቫሊዴሽን ወርክሾፕ የማኔጅመንት፣ የአመራር እና የአስተዳደር ኮሌጅ የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት ሪፖርቱን አስገመገመ፤ በኢፐሰዩ የማኔጅመንት፣ የአመራር እና የአስተዳደር ኮሌጅ College of Management, Leadership & Governance (CMLG) በተያዘለት መርሃ ግብር መሰረት ከ2018 ዓ.ም ጀምሮ ለዩኒቨርሲቲው በመጀመሪያ ዲግሪ እንዲሰጡ ከተመደቡለት የትምህርት ፕሮግራሞች መካከል በአራቱ ኮርሶች ላይ የሰበሰበውን የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት ሪፖርት፣ ጥር 1 ቀን 2018 በስልጠና ኢንስቲትዩት በተካሄደው Validation ወርክሾፕ ላይ አቅርቦ አስገመገመ፡፡ የዳሰሳ ጥናቱን ካካሄዱት ለየኮርሱ የተዋቀሩት የኮሚቴ አባላት ሲሆኑ፣ ለዳሰሳ ጥናት ሪፖርቱ ግብአት የሚሆን መረጃ ከአዲስ አበባ እና ከክልል መንግስታት ባለድርሻ አካላት እና ኬሌሎች ሴክተሮች በተሰበሰበ መሆኑ በሪፖርት አቅራቢዎቹ ተገልጿል፤ ሪፖርቱ ከመነሻው እስከ ጥናቱ ማጠቃለያ የነበረውን ሂደት ያካተተ ሲሆን፣ የህዝብ አስተዳደር እና አመራር ትምህርት ዳሰሳ ጥናት ሪፖርት በዶ/ር መልካሙ ሞሻጎ፣ የህዝብ ፖሊሲ ጥናት ትምህርት ዳሰሳ ጥናት ሪፖርት በዶ/ር ንጉሴ ዳባ፣ የማናጅመንት ትምህርት ዳሰሳ ጥናት ሪፖርት በዶ/ር ገብሬ ሶርሳ እና የልማት አስተዳደር ትምህርት ዳሰሳ ጥናት ሪፖርት በዶ/ር ታዬ ዓለሙ በኩል ቀርበው ውይይት ተካሂዶባቸዋል፡፡ በመጨረሻም ከተሰብሳቢዎቹ ለቀረቡት ሀሳብ እና አስተያየቶች በሪፖርት አቅራቢዎቹ እና በኮሚቴው አባላት ማብራሪያ የተሰጠ ሲሆን፣ ጥናቱ በተሰጡት ሃሳብ እና አስተያየቶች ዳብሮ፣ በኮሌጅ ደረጃ እንደሚጸድቅ እና ለዩኒቨርሲቲው ሴኔት እንደሚቀርብ ታውቋል፡፡ Visit our website: https://www.epsu.edu.et/ Follow our Facebook page: https://web.facebook.com/EPSUfb Follow our Telegram Channel: https://t.me/epsutelegram Subscribe to our YouTube channel: https://www.youtube.com/@EPSUyt ፐብሊክ አገልግሎት ልህቀት በተግባር ተኮር እውቀት at EPSU PR call: 0945746405

Visit our website: https://www.epsu.edu.et/ Follow our Facebook page: https://web.facebook.com/EPSUfb Follow our Telegram Cha
Visit our website: https://www.epsu.edu.et/ Follow our Facebook page: https://web.facebook.com/EPSUfb Follow our Telegram Channel: https://t.me/epsutelegram PR call: 0945746405

photo content

Ethiopia Public Service University, formerly known as Ethiopian Civil Service University, has played an important role in national economic development and in modernizing the public sector in Ethiopia. We are proud of the contributions we have made to our country so far, and we remain strongly committed to further modernization and digitalization of the public sector in the future. Through this communication, we would like to collect contact information of our university graduates who are serving in top leadership positions—such as regional sector office heads and above—at both federal and regional levels. We plan to feature their profiles on our website to show visitors how our university contributes to national development. Therefore, if you are a graduate of our university and currently serving in a senior leadership position, please send your full name, current position, and an official office photograph through my email: esheticho@gmail.com. Visit our website: https://www.epsu.edu.et/ Follow our Facebook page: https://web.facebook.com/EPSUfb Follow our Telegram Channel: https://t.me/epsutelegram PR call: 0945746405

photo content
+5

photo content
+9

photo content

የኢፐሰዩ የሪፎርም አደረጃጀት ግብረ-ኃይል የስራ ፍሰት ግምገማ የመጀመሪያ ሪፖርቱን ለዩኒቨርሲቲው የካውንስል አባላት አቀረበ፤ የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ፣ በአገር አቀፍ ደረጃ የመንግስትን አገልግሎት አሰጣጥ ለማዘመን የተጀመረውን የሪፎርም ስራ ተከትሎ፣ አደረጃጀቱን ለማስተካከል ያቋቋመው ግብረ-ኃይል፣ በነባሩ የስራ ፍሰት ላይ ያካሄደውን ዝርዝር የግምገማ ሪፖርት፣ ለዩኒቨርሲቲው ካውንስል አባላት ታህሳስ 28 ቀን 2018 ዓ/ም በህዳሴ አዳራሽ አቀረበ፡፡ ሪፖርቱ በአካዳሚክ እና በአስተዳደር የስራ ዘርፎች ውስጥ የሚገኙ ነባር የስራ ፍሰቶችን በጥልቀት የፈተሸ መሆኑ ከቀረበው ሪፖርት መረዳት ተችሏል፤ የካውንስሉ አባላት ለተሰራው ስራ ያላቸውን አድናቆት እየገለጹ፣ ቢጨመር እና ቢስተካከል መልካም ነው ያሉትን ገንቢ ሀሳብ እና አስተያየት ሰጥተዋል፤ በመቀጠልም የዩኒቨርሲቲው ፕሬዘዳንት ንጉስ ታደሰ (ዶ/ር) ግብረ- ኃይሉ ለሰራው አመርቂ ስራ ያላቸውን አድናቆት ገልጸው፣ “የዚህ ግብረ-ኃይል አባላት ከቤተሰባቸው ተለይተው እና በማይመች ሁኔታ እስከ ምሽት አራት ሰዐት ድረስ እየሰሩ ላመጡት አመርቂ ውጤት ምስጋና ይገባቸዋል፡፡” ብለዋል፡፡ አስከትለውም፣ የሪፎርም ዓላማ የተቋሙን ተልእኮ በውጤታማ መንገድ ማሳካት መሆኑን ገልጸው፣ “ውጤታማ ሪፎርም ለማካሄድ አሁን ላይ ያለንበትን ተጨባጭ ሁኔታ እና ነባሩን የስራ ፍሰት መፈተሸ አስፈላጊ ነው፤ ግብረ-ኃይሉ ዛሬ ያቀረበው ሪፖርት የስራውን ፍሰት በአግባቡ በመገንዘብ ችግሮቹን መለየቱን በግልጽ ያሳያል፤ ይህንን በአግባቡ ተገነዘብን ማለት በቀጣይ የምንሰራውን የሪፎርም ስራ ውጤታማ እንደሚያደርግልን መረዳት ይቻላል፡፡” በማለት ተናግረዋል፡፡ በመቀጠልም የግብረ-ኃይሉ አባላት ሪፖርታቸውን ሲያጠቃልሉ፣ ለዛሬው ስራ መሳካት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዘዳንት ዶ/ር ንጉስ ታደሰ ያደረጉት ያልተቋረጠ ድጋፍ እና ክትትል ትልቅ ድርሻ እንደነበረው በመግለጽ አመስግነዋቸዋል፡፡

photo content

መዋቅር.pdf3.39 MB

downloadfile.pdf3.66 KB

photo content
+1