fa
Feedback
Ethiopian Public Service University

Ethiopian Public Service University

رفتن به کانال در Telegram

ፐብሊክ አገልግሎት ልህቀት በተግባር ተኮር እውቀት

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام Ethiopian Public Service University

کانال Ethiopian Public Service University (@epsutelegram) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 12 732 مشترک است و جایگاه 15 748 را در دسته آموزش و رتبه 2 643 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 12 732 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 12 ژوئیه, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 112 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 6 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 34.77% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 16.09% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 4 428 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 2 049 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 27 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
ፐብሊክ አገልግሎት ልህቀት በተግባር ተኮር እውቀት

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 13 ژوئیه, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته آموزش تبدیل کرده‌اند.

12 732
مشترکین
+624 ساعت
+237 روز
+11230 روز
آرشیو پست ها
photo content
+9

በኢፐሰዩ በተካሄደው የአመራር ሽግሽግ መሰረት ርክክብ ሥነ- ስርዓት ተካሄደ የኢትዮጵ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የሥራ አመራር ቦርድ፣ ታህሳስ 24 ቀን 2018 ዓ/ም ባካሄደው ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባ ባሳለፈው ውሳኔ መሰረት፣ ከጥር 1 ቀን 2018 ዓም ጀምሮ በተፈጸመው የአመራር ሽግሽግ፣ ተሰናባቾቹ የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዘደንት፣ የምርምር እና ትብብር ምክትል ፕሬዘዳንት እና የአስተዳደር እና ልማት ምክትል ፕሬዘዳንት፣ በተጠባባቂነት ለየዘርፉ ከተመደቡት ምክትል ፕሬዘዳንቶች ጋር የስራ ርክክብ አደረጉ፡፡ በሽግሽጉ መሰረት ከአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝደንትነት ዶ/ር ለማ ጉዲሳ ተነስተው፣ በምትካቸው ዶ/ር አማኑኤል ኩሲያ ተመድበዋል፤ ከምርምርና ትብብር ምክትል ፕሬዘደንትነት ዶ/ር አለማዬሁ ደበበ ተነስተው፣ በምትካቸው ዶ/ር ምትኩ አዲሱ ተመድበዋል፤ እንዲሁም ከአስተዳደርና ልማት ምክትል ፕሬዘደንትነት ዶ/ር ታዴዎስ ሜንታ ተነስተው፣ በምትካቸው ዶ/ር ተሾመ ዱላ ተመድበዋል፡፡ በርክክቡ ሥነ- ስርዓቱ ላይ ተሰናባቾቹ ምክትል ፕሬዘደንቶች፣ የመውጫ ሪፖርት አዘጋጅተው ያስረከቡ ሲሆን፣ ሲመሩት ለቆዩት ዘርፍ የተሰጠው የመደበኛ እና የሪፎርም ስራ አፈጻጸም ያለበትን ደረጃ በዝርዝር አስረድተዋል፤ በመጨረሻም በየዘርፉ ያሉ ዲኖችን፣ ዳይሬክተሮችን፣ ስራ አስፈጻሚወችን እና የትምህርት ክፍል ኃላፊዎችን ከአዲሶቹ ምክትል ፕሬዘደንቶች ጋር አስተዋውቀው ስነስርአቱ ተጠናቋል፡፡ Visit our website: http://www.epsu.edu.et/ Follow our Facebook page: https://web.facebook.com/EPSUfb Follow our Telegram Channel: https://t.me/epsutelegram Follow us on LinkedIn: https://www.linkedin.com/.../ethiopian-public.../about/ Subscribe to our YouTube channel: https://www.youtube.com/@EPSUyt ፐብሊክ አገልግሎት ልህቀት በተግባር ተኮር እውቀት at EPSU PR call: 0945746405

ኢፐሰዩ ለኢራስመስ + 2026 የፕሮፖዛል የምርምር ቡድን አባላት ኦሬንቴሽን ተሰጠ፤ በኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የአውሮፓ የትምህርት እና የባህል አስፈፃሚ ኤጀንሲ ኢራስመስ+ 2026 የፕሮፖዛል ጥሪ (Erasmus+ 2026 call for proposals) በሚል ባቀረበው የምርምር ፕሮፖዛል ላይ ለሚሳተፉ የምርምር ቡድን አባላት፣ ጥር 4 ቀን 2018 ዓ/ም በዩኒቨርሲቲው የሴኔት አዳራሽ ኦሬንቴሽን ተሰጠ፡፡ ለምርምር ቡድኑ አባላት ኦሬንቴሽን የሰጡት፣ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዘዳንት ንጉስ ታደሰ (ዶ/ር) ሲናገሩ፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚፈለገው የፕሮጀክት አጻጻፍ፣ በእኛ ከተለመደው የተለዬ ባለብዙ ዘርፍ (multidisciplinary) መሆን እንዳለበት መገንዘብ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸው፣ “አንድ ችግር በአንድ የሙያ መስክ እና በአንድ አካባቢ በሚገኝ ተቋም በሚካሄድ ጥናት እንደማይፈታ ስምምነት ላይ ተደርሷል፤ይህንን አስተሳሰብ ለምርምር ድጋፍ የሚያደርጉ ተቋማትም እንደ መስፈርት እየተጠቀሙበት ነው፤ ስለዚህ እኛም በትብብር የመስራትን ባህል ማዳበር ይኖርብናል፤ በቀጣይም የመምህራንን የምርምር ስራ ከአዲሱ አስተሳሰብ ጋር የሚያገናኝ ስልጠና እናዘጋጃለን፡፡” ብለዋል፡፡ በማስከተልም ፕሬዘዳንቱ፣ ዩኒቨርሲቲው የአጋርነት እና የትብብር ስራዎችን እራሱን አስችሎ የሚመራ ዳይሬክቶሬት አደራጅቶ ወደ ስራ መግባቱን አስታውሰው፣ “በትብብር እና አጋርነት ዘርፍ እራሳችንን ከፍ ለማድረግ የምንችለው፣ የተደራጀ የግራንት አስተዳደር ፕሮፋይል ሲኖረን ነው፤ ስለዚህ ይህ አዲሱ የአጋርነት እና ትብብር ዳይሬክቶሬት፣ የምርምር ስራዎችን አሰባስቦ ወደ ዳታ ቤዝ ማስገባት ይጠበቅበታል፡፡” ብለዋል፡፡ የፕሬዘዳንቱ ልዩ ረዳት አብርሃም ሀጎስ (ዶ/ር)፣ ዩኒቨርሲቲው አሁን ያለበት የሪፎርም ሁኔታ ባለመፍቀዱ፣ ለዚህ ፕሮፖዛል የተመራማሪዎች ምርጫ በፕሮፋይል ፍተሸ መካሄዱን፣ በቀጣይ ግን በውድድር መምረጥ የሚያስችል ስርዓት እንደሚዘረጋ ገልጸዋል፡፡ ቀጥለውም፣ “የአጋርነትና ትብብር ዳይሬክቶሬት ከተደራጀ ወዲህ አዲስ ባህል እየተፈጠረ መሆኑን መመልከት የሚያስችል ጅማሮ እየታየ ነው፤ የተጀመረው የሀገር ውስጥ እና የዓለም አቀፍ ጥናቶችን እያፈላለጉ ወደ ዩኒቨርሲቲው የማምጣት ስራ ተጠናክሮ መቀጠል ይኖርበታል፡፡” ብለዋል፡፡ የትብብርና አጋርነት ዳይሮክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት ደረጀ ተ/ማርያም (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ ዛሬ በዩኒቨርሲቲ ደረጃ ከኤራስመስ የቀረበው የሪሰርች ፕሮፖዛል የውድድር ጥሪ፣ ለምርምር እና ለአቅም ግንባታ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚደረግ ውድድር መሆኑን ገልጸው፣ “የኒቨርሲቲያችን እንደ ተቋም ከኤራስመስም ጋር የፕሮፖዛል ተሳትፎ ሲያደርግ የመጀመሪያው ነው፤ ከዚህ በኋላ ዳይሬክቶሬቱ የሀገር ውስጥ እና ዓለም አቀፍ ምርምሮችን እና ትብብሮችን እያፈላለገ ወደ ዩኒቨርሲቲው ማምጣት ዋነኛ ተግባሩ አድርጎ ይቀጥላል፡፡” ብለዋል፡፡ Visit our website: https://www.epsu.edu.et/ Follow our Facebook page: https://web.facebook.com/EPSUfb Follow our Telegram Channel: https://t.me/epsutelegram Follow us on LinkedIn: https://www.linkedin.com/.../ethiopian-public.../about/ Subscribe to our YouTube channel: https://www.youtube.com/@EPSUyt ፐብሊክ አገልግሎት ልህቀት በተግባር ተኮር እውቀት at EPSU PR call: 0945746405

Dear EPSU’s Ambassadors, Based on your valuable recommendations, we have created the official LinkedIn account for our univer
Dear EPSU’s Ambassadors, Based on your valuable recommendations, we have created the official LinkedIn account for our university. This account will be maintained actively, alongside our other social media platforms, to keep you informed about university updates and activities. We kindly invite you to follow our LinkedIn page to stay up-to-date with the latest news and announcements. To follow us, please click this link: https://www.linkedin.com/company/ethiopian-public-service-university-epsu/about/ Thank you once again for your insights and continued support.

photo content
+5

በኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በቀጠለው የቫሊዴሽን ወርክሾፕ የማኔጅመንት፣ የአመራር እና የአስተዳደር ኮሌጅ የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት ሪፖርቱን አስገመገመ፤ በኢፐሰዩ የማኔጅመንት፣ የአመራር እና የአስተዳደር ኮሌጅ College of Management, Leadership & Governance (CMLG) በተያዘለት መርሃ ግብር መሰረት ከ2018 ዓ.ም ጀምሮ ለዩኒቨርሲቲው በመጀመሪያ ዲግሪ እንዲሰጡ ከተመደቡለት የትምህርት ፕሮግራሞች መካከል በአራቱ ኮርሶች ላይ የሰበሰበውን የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት ሪፖርት፣ ጥር 1 ቀን 2018 በስልጠና ኢንስቲትዩት በተካሄደው Validation ወርክሾፕ ላይ አቅርቦ አስገመገመ፡፡ የዳሰሳ ጥናቱን ካካሄዱት ለየኮርሱ የተዋቀሩት የኮሚቴ አባላት ሲሆኑ፣ ለዳሰሳ ጥናት ሪፖርቱ ግብአት የሚሆን መረጃ ከአዲስ አበባ እና ከክልል መንግስታት ባለድርሻ አካላት እና ኬሌሎች ሴክተሮች በተሰበሰበ መሆኑ በሪፖርት አቅራቢዎቹ ተገልጿል፤ ሪፖርቱ ከመነሻው እስከ ጥናቱ ማጠቃለያ የነበረውን ሂደት ያካተተ ሲሆን፣ የህዝብ አስተዳደር እና አመራር ትምህርት ዳሰሳ ጥናት ሪፖርት በዶ/ር መልካሙ ሞሻጎ፣ የህዝብ ፖሊሲ ጥናት ትምህርት ዳሰሳ ጥናት ሪፖርት በዶ/ር ንጉሴ ዳባ፣ የማናጅመንት ትምህርት ዳሰሳ ጥናት ሪፖርት በዶ/ር ገብሬ ሶርሳ እና የልማት አስተዳደር ትምህርት ዳሰሳ ጥናት ሪፖርት በዶ/ር ታዬ ዓለሙ በኩል ቀርበው ውይይት ተካሂዶባቸዋል፡፡ በመጨረሻም ከተሰብሳቢዎቹ ለቀረቡት ሀሳብ እና አስተያየቶች በሪፖርት አቅራቢዎቹ እና በኮሚቴው አባላት ማብራሪያ የተሰጠ ሲሆን፣ ጥናቱ በተሰጡት ሃሳብ እና አስተያየቶች ዳብሮ፣ በኮሌጅ ደረጃ እንደሚጸድቅ እና ለዩኒቨርሲቲው ሴኔት እንደሚቀርብ ታውቋል፡፡ Visit our website: https://www.epsu.edu.et/ Follow our Facebook page: https://web.facebook.com/EPSUfb Follow our Telegram Channel: https://t.me/epsutelegram Subscribe to our YouTube channel: https://www.youtube.com/@EPSUyt ፐብሊክ አገልግሎት ልህቀት በተግባር ተኮር እውቀት at EPSU PR call: 0945746405

Visit our website: https://www.epsu.edu.et/ Follow our Facebook page: https://web.facebook.com/EPSUfb Follow our Telegram Cha
Visit our website: https://www.epsu.edu.et/ Follow our Facebook page: https://web.facebook.com/EPSUfb Follow our Telegram Channel: https://t.me/epsutelegram PR call: 0945746405

Ethiopia Public Service University, formerly known as Ethiopian Civil Service University, has played an important role in national economic development and in modernizing the public sector in Ethiopia. We are proud of the contributions we have made to our country so far, and we remain strongly committed to further modernization and digitalization of the public sector in the future. Through this communication, we would like to collect contact information of our university graduates who are serving in top leadership positions—such as regional sector office heads and above—at both federal and regional levels. We plan to feature their profiles on our website to show visitors how our university contributes to national development. Therefore, if you are a graduate of our university and currently serving in a senior leadership position, please send your full name, current position, and an official office photograph through my email: esheticho@gmail.com. Visit our website: https://www.epsu.edu.et/ Follow our Facebook page: https://web.facebook.com/EPSUfb Follow our Telegram Channel: https://t.me/epsutelegram PR call: 0945746405

photo content
+5

የኢፐሰዩ የሪፎርም አደረጃጀት ግብረ-ኃይል የስራ ፍሰት ግምገማ የመጀመሪያ ሪፖርቱን ለዩኒቨርሲቲው የካውንስል አባላት አቀረበ፤ የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ፣ በአገር አቀፍ ደረጃ የመንግስትን አገልግሎት አሰጣጥ ለማዘመን የተጀመረውን የሪፎርም ስራ ተከትሎ፣ አደረጃጀቱን ለማስተካከል ያቋቋመው ግብረ-ኃይል፣ በነባሩ የስራ ፍሰት ላይ ያካሄደውን ዝርዝር የግምገማ ሪፖርት፣ ለዩኒቨርሲቲው ካውንስል አባላት ታህሳስ 28 ቀን 2018 ዓ/ም በህዳሴ አዳራሽ አቀረበ፡፡ ሪፖርቱ በአካዳሚክ እና በአስተዳደር የስራ ዘርፎች ውስጥ የሚገኙ ነባር የስራ ፍሰቶችን በጥልቀት የፈተሸ መሆኑ ከቀረበው ሪፖርት መረዳት ተችሏል፤ የካውንስሉ አባላት ለተሰራው ስራ ያላቸውን አድናቆት እየገለጹ፣ ቢጨመር እና ቢስተካከል መልካም ነው ያሉትን ገንቢ ሀሳብ እና አስተያየት ሰጥተዋል፤ በመቀጠልም የዩኒቨርሲቲው ፕሬዘዳንት ንጉስ ታደሰ (ዶ/ር) ግብረ- ኃይሉ ለሰራው አመርቂ ስራ ያላቸውን አድናቆት ገልጸው፣ “የዚህ ግብረ-ኃይል አባላት ከቤተሰባቸው ተለይተው እና በማይመች ሁኔታ እስከ ምሽት አራት ሰዐት ድረስ እየሰሩ ላመጡት አመርቂ ውጤት ምስጋና ይገባቸዋል፡፡” ብለዋል፡፡ አስከትለውም፣ የሪፎርም ዓላማ የተቋሙን ተልእኮ በውጤታማ መንገድ ማሳካት መሆኑን ገልጸው፣ “ውጤታማ ሪፎርም ለማካሄድ አሁን ላይ ያለንበትን ተጨባጭ ሁኔታ እና ነባሩን የስራ ፍሰት መፈተሸ አስፈላጊ ነው፤ ግብረ-ኃይሉ ዛሬ ያቀረበው ሪፖርት የስራውን ፍሰት በአግባቡ በመገንዘብ ችግሮቹን መለየቱን በግልጽ ያሳያል፤ ይህንን በአግባቡ ተገነዘብን ማለት በቀጣይ የምንሰራውን የሪፎርም ስራ ውጤታማ እንደሚያደርግልን መረዳት ይቻላል፡፡” በማለት ተናግረዋል፡፡ በመቀጠልም የግብረ-ኃይሉ አባላት ሪፖርታቸውን ሲያጠቃልሉ፣ ለዛሬው ስራ መሳካት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዘዳንት ዶ/ር ንጉስ ታደሰ ያደረጉት ያልተቋረጠ ድጋፍ እና ክትትል ትልቅ ድርሻ እንደነበረው በመግለጽ አመስግነዋቸዋል፡፡

መዋቅር.pdf3.39 MB

downloadfile.pdf3.66 KB

photo content
+1

Dear Public Policy, Development Policy, Social Policy, and Policy Analysis Graduates of EPSU, We have been informed that some regional Civil Service Commissions may not have included your program in the eligible job categories, which could limit your ability to apply your knowledge in practice. After communicating with the Department of Public Policy Studies at our university, we confirmed that the university requested the Federal Civil Service Commission to include these programs in the eligible job categories. In the letter dated May 21, 2016 (Ethiopian Calendar), the Commission approved this request and sent the letters to all sector ministries. If your regional Civil Service Commission has not yet updated the eligible job categories to include your program, please contact the responsible officer using the attached official letter from the Federal Civil Service Commission. You can also access a scanned copy of the letter here for reference: https://drive.google.com/.../17UnoS8vhNkchNVXMPEW.../view... If you need help, please do not hesitate to contact PR at 0945746405 Visit our website: https://www.epsu.edu.et/user Follow our Facebook page: https://web.facebook.com/EPSUfb Follow our Telegram Channel: https://t.me/epsutelegram PR call: 0945746405