ru
Feedback
Joseph Math Tutor

Joseph Math Tutor

Открыть в Telegram

Hello, welcome to Joseph Math Tutor channel! https://youtu.be/D8K0MVqynVA?si=y_uFeHG7awC1oX9Y Subscribe our youtube channel On tiktok : josephmathtutor Owner: Yosef Adefris @yosef_2580

Больше
1 857
Подписчики
Нет данных24 часа
+57 дней
+2130 день
Архив постов
ማስታወቂያ በሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎች ለመማር ለተመዘገባችሁ ተማሪዎች በሙሉ፣ በ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እና በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ገብታችሁ በአፕላይድ ሳይንስና በኢንጂነሪንግ የትምህርት ዘርፎች ለመማር ለተመዘገባችሁ ተማሪዎች የመግቢያ ፈተና የሚሰጠዉ ማክሰኞ መስከረም 20/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡00 ሰዓት ጀምሮ መሆኑን እንገልጻለን፡፡ ማሳሰቢያ፡- ተፈታኞች ለፈተናው መመዝገባችሁን የሚገልፅ ከሲስተም ላይ በማወረድ ፕሪንት አድርጋችሁ መያዝ ያስፈልጋል፡፡ ተፈታኞች ማንነታችሁን የሚገልጽ መታወቂያና የአድሚሽን ካርዳችሁን በመያዝ በምዝገባ ወቅት በመረጣችሁት የፈተና ማዕከል ከተጠቀሰው ሰዓት ቀደም ብላችሁ መገኘት አለባችው፡፡ ተፈታኞች ሞባይል ስልክ እና ስማርት ሰዓት ይዞ ወደ ፈተና ማዕከል መምጣት የተከለከለ ነው፡፡ የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እና የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ @Joseph_maths_tutorial

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን ። መልካም የደመራ በዓል ❤️
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን ። መልካም የደመራ በዓል ❤️

This video is the best👌😘 Specially for fresh students Join us @astujmt2018

#ASTU ለምትገቡ ተማሪዎች የተከፈተ አዲስ ግሩፕ በግሩፑ ውስጥ ✅ ስለ ግቢው አጠቃላይ ሁኔታ ✅ የሁሉንም Freshman course Material ✅ በ Joseph Math Tutorial የሚሰጡ Tu
#ASTU ለምትገቡ ተማሪዎች የተከፈተ አዲስ ግሩፕ በግሩፑ ውስጥ ✅ ስለ ግቢው አጠቃላይ ሁኔታ ✅ የሁሉንም Freshman course Material ✅ በ Joseph Math Tutorial የሚሰጡ Tutorial sessionoch ✅ ያላችሁን ጥያቄ የምትጠይቁበት ነው። #Share it for your partners

#Registration የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎች የ2018 ዓ.ም መግቢያ ፈተና የምዝገባ ጥሪ የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እና የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ለአገራችን ሁለንተናዊ ዕድገት መሳካት በሳይንስና ቴክኖሎጂ የሰለጠነ የሰው ሀይል ፍላጎትን ለማሟላት የበኩላቸዉን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ በመንግስት ልዩ ተልዕኮ ተሰጥቷቸው  የተደራጁ ሲሆን በዘርፉ ብቃት ያላቸውን ሙያተኞችን በማፍራት ላይ ይገኛሉ፡፡ በመሆኑም በ2018 ዓ.ም. በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እና አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ገብተው በአፕላይድ ተፈጥሮ ሳይንስና በኢንጂነሪንግ የትምህርት ዘርፎች ትምህርታቸውን መከታተል ለሚፈልጉ በ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና ወስደው ለዩኒቨርሲቲ መግቢያ የተወሰነውን 50% እና ከዚያ በላይ ውጤት ያስመዘገቡ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎችን ተጨማሪ የመግቢያ ፈተና በበይነ-መረብ (online) በመስጠት የዩኒቨርሲቲዎቹን መስፈርት የሚያሟሉ ተማሪዎችን ተቀብለን በቅድመ-ምረቃ ፕሮግራም ለማስተማር እንፈልጋለን፡፡ በየዩኒቨርሲቲዎቹ የሚሰጡ ትምህርቶችን ዝርዝር ከታች ተያይዟል፡፡ የምዝገባ ጊዜ፡- • ከመስከረም 13 እስከ መስከረም 18 ቀን 2018 ዓ.ም ምዝገባው የሚጠናቀቀው፡- • መስከረም 18 ቀን 2018 ዓ.ም  ከሌሊቱ 6 ሰዓት ይሆናል፡፡ የምዝገባ ቦታ፡ • የምዝገባ መስፈርቱን የሚያሟሉ አመልካቾች በማንኛውም ስፍራ በኢንተርኔት (online) በ  https://stuexam.astu.edu.et/ ሊንክ በመጠቀም መመዝገብ ይችላሉ፡፡ • ፈተናው የሚሰጥበት ቀን፡ በድረ-ገጻችን የምዝገባው ቀን ካበቃ በኋላ እናሳውቃለን። ፈተናው የሚሰጥበት ቦታ፡- • በምዝገባ ወቅት በመረጡት ዩኒቨርሲቲ (የፈተና ጣቢያ) በአካል በመቅረብ ይሆናል፡፡ ማሳሰቢያ፡- • አመልካቾች የሀገር አቀፍ ፈተና አድሚሽን ቁጥራቸውንና ሌሎች መረጃዎችን በትክክል መሙላታቸውን ማረጋገጥ አለባቸው ፡፡ • የፈተና ጣቢያዎቹ ያላቸው የመፈተኛ ቦታ ውስን በመሆኑ ይህንኑ አውቃችሁ ቅድሚያ እንድትመዘገቡ እናሳስባለን፡፡ • በቂ አመላካቾች የሌሉባቻው የፈተና ጣቢያዎች በቅርበት ወደሚገኙ የፈተና ጣቢያዎች ሊታጠፉ እንደሚችሉ እናሳውቃለን፡፡ • ለምዝገባና ለፈተና ምንም አይነት ክፍያ አይጠየቅም፣ • ከሚመዘገቡት አመልካቾች ውስጥ ለፈተና የሚቀርቡት ስም ዝርዝራቸው እና የፈተና ጣቢያዎች በሚከተሉት ድረ-ገፆች፡-  www.astu.edu.et: www.aastu.edu.et እንደአስፈላጊነቱም በe-mail የሚገለፅ ይሆናል፡፡ • አመልካቾች ከወዲሁ ፈተናው በሚሰጥባቸው የትምህርት ዓይነቶች፣ ማለትም (ከ9ኛ እስከ 12ኛ ክፍል) ባዮሎጂ፣ ኬሚስትሪ፣ ፊዚክስ፣ ሂሳብና እንግሊዝኛ እንዲዘጋጁ ይመከራል፡፡ • ፈተና የሚሰጠው በበይነ-መረብ (online) ስለሆነ አመልካቾች በፈተና ጊዜ ሊያጋጥም የሚችል ግራ መጋባትን ለማስቀረት በምዝገባ ጊዜ ከመመዝገቢያ ፎርማቱ ጋር ተያይዞ የቀረበውን የሙከራ ፈተና እንዲለማመዱ ይመከራል፡፡ • አመልካቾች ለፈተና ሲቀርቡ የ2017 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ውጤት፣ የሀገር አቀፍ ፈተና አድሚሽን ካርድ (ወይም መታወቂያ) እና የምዝገባ ማረጋገጫ ኮፒ መያዝ ይጠበቅባቸዋል፡፡ • የመግቢያ ፈተናውን የሚያልፉ አመልካቾች በትምህርት ሚኒስቴር በኩል በሚደረገው የዩኒቨርሲቲ ምደባ ውስጥ አይካተቱም፡፡ • በውጤታቸው የተመረጡ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ ምደባ ከላይ በተጠቀሱት ድረ-ገፆች ይገለፃል፡፡ • በመስፈርቱ መሰረት ያልተመረጡ አመልካቾች ከዚህ በፊት እንደሚደረገው በትምህርት ሚኒስቴር በኩል በሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች የሚመደቡ ይሆናል፡፡ • በፈተናው ዕለት ማንኛውንም የሞባይል ስልኮችንና ስማርት ሰዓቶችን ይዞ ወደ ፈተና ጣቢያ መግባት የተከለከለ ነው፡፡ • በፈተና ወቅት ያልተገባ ተግባር መፈፀም በጥብቅ የተከለከለ ነው፡፡ ለተጨማሪ ማብራሪያ ከዚህ በታች የተጠቀሱትን ድረ-ገፆች መጎብኘት ይቻላል፡፡ www.astu.edu.et;   www.aastu.edu.et የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እና የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ፡፡

#AASTU/ASTU AASTU/ASTU መግባት ለምትፈልጉ ተማሪዎች በሙሉ የምዝገባ ጊዜ፦ ➫ ከመስከረም 13 እስከ መስከረም 18 ቀን 2018 ዓ.ም ምዝገባው የሚጠናቀቀው፡- ➫ መስከረም 18 ቀን 201
+1
#AASTU/ASTU AASTU/ASTU መግባት ለምትፈልጉ ተማሪዎች በሙሉ የምዝገባ ጊዜ፦ ➫ ከመስከረም 13 እስከ መስከረም 18 ቀን 2018 ዓ.ም ምዝገባው የሚጠናቀቀው፡- ➫ መስከረም 18 ቀን 2018 ዓ.ም ከሌሊቱ 6 ሰዓት ይሆናል፡፡ መመዝገቢያ Link ➫ https://stuexam.astu.edu.et/ በዚህ Link በመጠቀም እና አቀራራቢያችሁ ያለውን መፈተኛ University በመምረጥ መመዝገብ ትችላላቹ። @Joseph_maths_tutorial

#Registration 👉 በ2017 ዓ.ም ኢንተራንስ አልፋችሁ ASTUን መቀላቀል ፈልጋችሁ የመግቢያ ፈተናውን የምትጠባበቁ በርካታ ተማሪዎች “ምዝገባ ተጀምሯል እንዴ? ፣ መቼ ነው የምንመዘገበው? ፣ መቼ ነው ግቢ የምንገባው?” እያላችሁ እየጠየቃችሁን ነው። 👉 የመመዝገቢያ ሊንክ እስከአሁን አልተለቀቀም ፤ ስለዚህ ምዝገባም አልተጀመረም። ሊንኩ ሲለቀቅ ምዝገባውም አብሮ ይጀምራል። ምዝገባው ከፊታችን ባሉት ጥቂት ቀናት ይጀምራል ብለን ተስፋ እናደርጋለን። ግቢ የምትገቡት ደግሞ ዩኒቨርስቲው ባሳወቀው ቀን ነው። የመግቢያ ፈተናውን ተፈትናችሁ ውጤት ከወጣ በኋላ ፈተናውን አልፋችሁ ASTU ለተመደባችሁ ተማሪዎች ወደግቢ የምትገቡበትን ቀን ዩኒቨርስቲው ይፋ ያደርጋል። እኛም እናሳውቃችኋለን! እስከዚያው ድረስ ለፈተናው እየተዘጋጃችሁ በትዕግሥት ጠብቁ!

ASTU የምትገቡ ተማሪዎች ግቢ ከገባችሁ በኋላ የሁሉንም Course Material የምታገኙበት ቻናል👇👇👇 https://t.me/josephmathtutor

Life savior of ASTU's students😊

የመጀመሪያ ሴሚስተር ኮርሶች (For both pre-engineering and pre-science 1. Applied Mathematics I 2. General Physics 3. General Chemistry 4. Logic and Critical Thinking 5. Civics and Ethics 6. Communicative English I 7. Introduction to programming - Python 8. HPE Logic and Critical Thinking እና Civics and Ethicsኮርሶች ተማሪዎች የሚበዙ ከሆነ በተራበተራ ይሰጣሉ። የመጀመሪያ ሴሚስቴር ላይ logic የወሰደ ሁለተኛው ላይ Civics ይወስዳል ... vice versa. ይ ቀ ጥ ላ ል . . .

#ASTU #ለምትገቡ #ተማሪዎች 📚 አንድ surprise አለ Engineering ለምትገቡ የአምስት ዓመቱን ትምህርት በአራት አመት የመማር ዕድል ሊያጋጥማቹህ ይችላል ግን በጣም ትልቅ ጥረት ያስፈልጋል (ፈተና አለው)  ለApplied science ተማሪዎችም የአራት ዓመቱን ትምህርት በሶስት ዓመት ማጠናቀቅ የሚችሉበት መንገድ በተመሳሳይ መልኩ ማለትም በቅድመ ፈተና ተፈትነው በማለፍ ብቻ ✅Fast track✅ pre  Engineering ሳይማሩ መመረቅ ይችላል።         ፈተናው ምን ምን ይይዛል❓  ፈተናው 3 ብቻ ነው።      Mathematics      Chemistry      Physics ፈተናው ይከብዳል? አዎ በጣም ይከብዳል የማይካድ ሐቅ ነው እስከዛሬ ከተፈተኑት ያለፉት 10 አይሆኑም🤭      Mathematics ላይ የሚመጡ   1. Limit & Continuity   2. Integration (ለዚያውም ገገማው part)😂   3. Epsilon-delta definition of limit (በተአምር የማይቀር)   4. Differentiation of different functions     12 ብትማሩም ባትማሩም ይመጣል አየት አየት አርጉ ከአሁኑ ባለፈው በለቀኩላችሁ መጽሐፍ (Begashaw I)    Chemistry & physics የተማራችሁት ነው 11 እና 12          

📢 ASTU ( Adama Science and Technology University ) 📚 አዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ከአዲስአበባ በ 100km ርቀት የሚገኝ ሲሆን ኢትዮጵያ ካሏት ሁለት የሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲዎች ውስጥ አንዱ ነው። 📚 የScience እና Technology  ዩኒቨርሲቲ እንደመሆኑ የሚሰጣቸው Departmentoch ውስን ናቸው ማለትም Engineering እና Applied Science ፊልዶች ብቻ ናቸው ። 🔎 በ Engineering ስር 3 Collgeoችን  1-College of Electrical 2-College of Mechanical 3-College of Civil and Architecture 📚 በእነዚህ Collegoች ስርም ፦ 1. College of Electrical computing ስር 📌-Software engineering 📌-Computer science and engineering(CSE) 📌 -Power and Control 📌 -Communication and Electronics 2.በCollege of Mechanical chemical and material ስር 📌 - Mechanical engineering 📌 -Chemical engineering 📌 -Material Science and Engineering 3.በCollege of Civil and Architecture ስር 📌 -Civil engineering 📌 -Architectural engineering 📌 -Water engineering      📚 በApplied Science ውስጥ ፦ 📌 -Applied Mathematics 📌 -Applied Chemistry 📌 -Applied Physics 📌 -Applied Geology 📌 -Industrial chemistry 📌 - Pharmacy 📚 ወደ ዩኒቨርስቲው ለመቀላቀል ፈተና ያለው ሲሆን የሚቀበላቸው ተማሪዎች ውስን ናቸው ተማሪ የምንቀበለው በ Laboratoryኣችን ልክ ነው ብለው ስለሚያምኑ ! በጠቅላላ ግቢው ውስጥ ከ Fresh እስከ Masters 7000 ተማሪዎች 2000 ሰራተኞች ይገኛሉ ። 📚 ተማሪዎች ትንሽ ከመሆናቸው አንፃር ምግብ ከየትኛውም ግቢ የተሻለ ነው ።  📚 library 1-Central Library 2-Applied Library 3-Liberal arts library 4-Post graduate library 5-Females library 📚 እንዲሁም በየdepartmentቶች  የየራሳቸው library ያላቸው ሲሆን የሴቶቹ ለብቻቸው የሚጠቀሙበትም አላቸው ።ሌላው ነገር libraryዎቹ በውስጣቸው በጣም ፈጣን WiFi እና Computer አላቸው ። ግቢው ለሚጠቀምበት በጣም ብዙ laboratoryዎች አሉ ። 📚 ግቢው ውስጥ Anfi የሚባል ቦታ አለ እዛ ላይ በ cinema standard led screen አለ እንዲሁም ሶስት ቦታዎች ላይ አነስተኛ screenoch አሉ ። ለሴቶች ትንሽ ሻል ያለ አገልግሎት ይሰጣል በዶርሚተሪ በlibraryም በብዙ ነገር ይጠቀማሉ ! 📚የራሱ ውሀ ማጣሪያ ያለው ሲሆን ፤ ብዙም የውሀ ችግር የለም መብራት አይጠፋም ከጠፋም በ 5 ደቂቃ ውስጥ የሚነሳ automatic generator አለ ። Dormitory አሪፍ  የሚባል ነው ።  የግቢ መግቢያ ሰዓት 3:00 ከሌሎች የተሻለ ነው ። ሌላው በፍፁም ሰው የማይተናኮሉ ለማዳ ለመባል የሚቀርቡ ጅቦች አሉ ፤ 🔎 በጣም ጠቃሚ ነገር 🔎 📌 ከሌሎች ዩኒቨርስቲዎች በተለየ ነው ት/ት የሚሰጠው ለምሳሌ Comon course የሚባል ነገር የለም engineering የሚገባ ቀጥታ pre engineering ይማራል  Appliedም እንደዛው ነው ። Gpa ከ 3.5 በላይ ካለ እና ሌላ ፊልድ ደርቦ መመረቅ ለሚፈልግም dual degree ይሰጣል ሁለት degree ማለት ነው ። 

ASTU ስትገቡ የEntrance ውጤት ምንም Matter አያደርግም! ፈተናውን ተፈትናችሁ ስታልፉ join ታደርጉና Pre Engineering እና Pre science ተብሎ ይከፈላል ከዚያ መርጣችሁ ትገቡና 1 ዓመት ትማሩና ከዚያ Pre science ከሆናችሁ ወደ ዲፓርትመንት ካልሆነ Engineering ከሆናችሁ ካሉት 3 Collegoch መርጣችሁ ትገባላችሁ ከዚያ ከ3 ሴሚስተር በኃላ ነው ወደ ዲፓርትመንት የምትገቡት።

#MoE በ2017 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስደው የዩኒቨርስቲ መግቢያ ውጤት ያመጡና ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች በወጪ መጋራት (ስኮላ
#MoE በ2017 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስደው የዩኒቨርስቲ መግቢያ ውጤት ያመጡና ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች በወጪ መጋራት (ስኮላርሽፕ) ለመማር ፍላጎት ያላቸው ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ እና የትምህርት መስክ ምርጫቸውን በየትምህርት ቤታቸው በተወከሉ መምህራን በኩል እስከ መስከረም 14/2018 ዓ.ም ድረስ ማስተካከል እንደሚችሉ ትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል። የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ከ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ጀምሮ በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ተማሪዎችን ስሚቀበል ምርጫቸው ውስጥ ማካተት የሚችሉ መሆኑን አሳውቋቃ። አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ እና አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎች ምርጫ ውስጥ የማይካተቱ መሆኑን አስገንዝቧል። #MoE

photo content

Just for fun...😜😂😁

+5
Mathematics  #AASTU_and_ASTU 👉 Entrance Exam 👇 Join Us👇 || @Joseph_maths_tutorial