cookie

Мы используем файлы cookie для улучшения сервиса. Нажав кнопку «Принять все», вы соглашаетесь с использованием cookies.

avatar

The Christian News

ይህ The Christian News ነዉ። ከመላዉ አለም ተዓማኒነት ያላቸዉ የክርስትያን ዜናዎች ይቀርቡበታል ከወደዱት ይቀላቀሉት። @TCNEW

Больше
Рекламные посты
4 936
Подписчики
+924 часа
+127 дней
+8130 дней
Время активного постинга

Загрузка данных...

Find out who reads your channel

This graph will show you who besides your subscribers reads your channel and learn about other sources of traffic.
Views Sources
Анализ публикаций
ПостыПросмотры
Поделились
Динамика просмотров
01
ተወዳጁ ዘማሪ አዉታሩ ከበደ ቁጥር 7ቱን የዝማሬ አልበም ሊለቅ ነዉ። "ከ9 አመታት በኋላ የ7 ቁጥር አልበሜ በመንፈስ ተጠምቆ ለቅዱሳን በረከት ላልዳኑ የኢየሱሰን አዳኝነት ለማብሰር ተጠናቋል" ሲል ዘማሪዉ ገልጿል። የምትፅልዩልኝ,በነገር ሁሉ ከጎኔ ያላችሁ እግዚአብሔር ይባርካችሁ። በሁላችሁ እጅ ላይ በቅርቡ የሚደርስበትን ቀን አሳውቃለው የዘማሪዉ መልዕክት ነዉ።
7480Loading...
02
የዝሙት ሕይወቴን ማንም አያወቅም ነበር ሰዎች መማር ካለባቸው ከእኔ ይማሩ #ድንቅ #ምስክርነት ከዚህ ልምምድ መውጣት ሲያቅተኝ ከጌታ ቤት ባክ አደረኩኝ https://youtu.be/ugkLCiXAYII
1 35311Loading...
03
#ይፈቱ በኤርትራ ከ 20 አመታት በላይ የታሰሩ የፕሮቴስታንት እምነት ፓስተሮች እንዲፈቱ አሜሪካ ጠየቀች። የአሜሪካው ዓለማቀፍ የኃይማኖት ነጻነት ኮሚሽን፣ የፕሬዝዳንት ጆ ባይደን አስተዳደር በኤርትራ ላለው የኃይማኖት ነጻነት ጥሰት ትልቅ ትኩረት እንዲሰጥ መጠየቁ ዳጉ ጆርናል ከዘገባዎች ተመልክቷል። ኮሚሽኑ፣ ፓስተር ኃይሌ ናይዝጊ እና ፓስተር ክፍሉ ገብረመስቀል የተባሉ የፕሮቴስታንት ኃይማኖት ሰባኪዎች ከታሠሩ ከ20 ዓመታት በላይ አስቆጥረዋል ሲል ለአብነት ጠቅሷል። #ኤርትራ ፣ ከኃይማኖት ነጻነት ጋር በተያያዘ 5 መቶ ያህል ሰዎችን ክስ ሳይመሠረትባቸው እንዳሠረች ኮሚሽኑ አመልክቷል። የኤርትራ መንግሥት ባለፈው ዓመት ከኃይማኖት ጋር በተያያዘ የታሠሩ ዘጠኝ እስረኞችን #ብቻ መፍታቱን ያስታወሰው ኮሚሽኑ፣ ጅምሩ #ግን ሳይቀጥል ቀርቷል በማለት ወቅሷል። ሲል ዋዜማ ሬድዬ ዘግቧል። ዜናውን ከወደዱት Like ማንኛውም አስተያየት እና ጥያቄ ካሎት Comment በፍጥነት ለወዳጆ ለማካፈል #share ያድረጉ
1 7293Loading...
04
#መቀሌ #ታላቁ ተልዕኮ ኢትዮጵያ 10 ቢሮውን በትግራይ መቀሌ ከፈተ። ግሬት ኮሚሽን ከ1972 ዓ.ም. ጀምሮ #በኢትዮጵያ የወንጌል ስራን ሲሰራ ቆይቷል። በአሁኑ ወቅት በአዳማ፣ ባህርዳር፣ ሃረር፣ ሃዋሳ፣ ጅማ፣ ነቀምቴ፣ አርባ ምንጭ፣ ሆሳዕና እና አምቦ የአካባቢ ቢሮዎችን አቋቁሞ በየአካባቢው ከሚገኙ ሚኒስትሪዎችና አብያተ ክርስቲያናት ጋር ወንጌልን እየሰራ ይገኛል። ግሬት ኮሚሽን #ኢትዮጵያ ሚኒስትሪ፣ የጂሰስ ፊልምን በ74 የሃገር ውስጥ ቋንቋዎች በማስተርጎምና በ10 ሃገራት ውስጥ ኢንዲጂተስ በተሰኘ የቴክኖሎጂ ማህበረሰብን በመፍጠር በኢትዮጵያና ከኢትዮጵያ ውጪም ወንጌልን እየሰራ ይገኛል። ከጦርነት መልስ የወንጌል ስርጭት ማዕከል በትግራይ የተከፈተውን ይሄንን ቢሮ ያስተባበረው ወንድም #ካሳሁን_ሰዒድ ሲሆን በመድረኩ እውቅና ተሰጥቶታል። ወንድም ካሳሁን መቀሌ እና መላውን ትግራይ ላለፉት 10 ዓመታት በወንጌል ለመድረስ ሲያገለግል ቆይቷል። ምንጭ፣ GCMEthiopia ዜናውን ከወደዱት Like ማንኛውም አስተያየት እና ጥያቄ ካሎት Comment በፍጥነት ለወዳጆ ለማካፈል #share ያድረጉ
1 6472Loading...
05
የሃይማኖት ተቋማት የፋይናንስ ኦዲት ሪፖርታቸውን ለመንግሥት እንዲያቀርቡ የሚደነግግ ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጀ ማንኛውም የሃይማኖት ተቋም የፋይናንስ ኦዲት ሪፖርቱን ለሰላም ሚኒስቴር ማቅረብ እንደሚኖርበት፣ ከውጭ አገር የሚመጣ የገንዘብ ዕርዳታ በሕግ ሥልጣን ለተሰጠው አካል ማሳወቅ እንደሚኖርበት የሚደነግግ ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጀ፡፡ " የሃይማኖት ጉዳዮች አዋጅ " የተሰኘው ረቂቅ አዋጅ፣ የሃይማኖት ተቋማቱ ተቀባይነት ያለው የሒሳብ አያያዝና የኦዲት ሥርዓት መዘርጋት እንደሚኖርባቸው፣ የኦዲት ሪፖርታቸውንም ለሰላም ሚኒስቴር ማቀረብ እንዳለባቸው የሚደነግግ መሆኑን ሪፖርተር ጋዜጣ አስነብቧል። የሃይማኖት ተቋማቱ የሚጠቀሙት የሒሳብ አያያዝ ሥርዓት የገቢ፣ የወጪና አጠቃላይ የንብረት ዝርዝር የያዘ መሆን እንደሚኖርበትና የገቢ አሰባሰብና የወጪ አስተዳደር በሕጋዊ መንገድ ማከናወን እንዳለባቸውም ይገልጻል። አንድ የሃይማኖት ተቋም በራሱ የገቢ ማስገኛ ሥራዎችን በሚያከናውንበት ጊዜ፣ ለዚሁ ሥራ የተለየ የባንክ ሒሳብ መክፈትና የተለየ መዝገብ መያዝ እንዳለበትም ተደንግጓል፡፡ በተጨማሪም ማንኛውም የሃይማኖት ተቋም ከውጭ አገር የሚላክለትን የገንዘብ ዕርዳታ፣ ስጦታ ወይም ሌሎች የገንዘብ ድጋፎችን በሕግ ሥልጣን ለተሰጠው አካል ማሳወቅ ይኖርበታል ተብሏል። በተጨማሪም የለጋሹን ድርጅት ወይም ግለሰብ ስምና አድራሻ፣ የተለገሰው የገንዘብ፣ ስጦታ ዓይነትና መጠን፣ እንዲሁም ስጦታው ወይም ድጋፉ የተሰጠበት ልዩ ዓላማ የሃይማኖት ተቋማቱ ጨምርው ማሳወቅ እንዳለባቸው ተገልጿል፡፡
1 3923Loading...
06
"#የአፍሪካ #መንፈሳዊ ቀን" በአፍሪካ ሕብረት ተካሄደ። በInter religious Association for Peace And Development (IAPD Africa) አዘጋጅነት "Educating the African person to be Spiritually fit in the 21st Century" በሚል መሪ ቃል ኢትዮጵያን ጨምሮ ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት የመጡ መሪዎች በተገኙበት በአፍሪካ ሕብረት ተከናውኗል። የሃይማኖት ተቋማት እና መሪዎች በሰላም እና በልማት ስራዎች ላይ በቅንጅት ለአፍሪካ መስራት እንደሚገባቸው በመድረኩ ተጠቅሷል። በመድረኩ የInter religious Association for Peace And Development (IAPD Africa) የአፍሪካ ሊቀመንበር ዶ/ር ኡዙዊን ጨምሮ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ክ እና የእስልምና እምነት በሀገራችን የትምህርት ስረዓት ያበረከቱትን አስተዋጽዖ በተመለከተ የተለያዩ ጽሑፎች ቀርበዋል። በጉባኤው በቅርብ ጊዜ የምስረታ 50ኛ ዓመት ክብረ በዓላቸውን ያከበሩት አንጋፋዎቹ የመሰረተ ክርስቶስ ቤ/ክ (ቢጫ ኳይር) ዝማሬ አቅርበዋል።
1 3102Loading...
07
#ቤተ #በአዲስ አበባ በሆሳዕና ለረጅም አመት እያገለገለች የምትገኘዉ ቤተምህረት #አሁን ደግሞ በአዲስ አበባ የቤተ ክርስቲያን ተከላና- የመክፈቻ ፕሮግራም ከግንቦት 21-25 / ከእሮብ እስከ ቅዳሜ ከ 10:00 ጀምሮ እሁድ ጠዋት ይከናወናል። #አድራሻ ፦ ከቡልጋሪያ #ወደ ቄራ ሲወርዱ ስካኒያ አካባቢ የቤተ ምህረት ማስታወቂያ ባለበት 100 ሜትር ገባ ብሎ ያገኙናል። #ቤተ ምህረት እንገናኝ 🙏🙏
1 9732Loading...
08
#የአርሰናል ደጋፊዎች በቤተክርስቲያን ምስጋና አቀረቡ። በኬንያ የሚገኙ የአርሰናል ደጋፊዎች ከድል በኋላ በቤተክርስቲያን ዉስጥ ምስጋና አቀረቡ በኬንያ ርዕሰ መዲና ናይሮቢ የሚገኙት የአርሰናል ደጋፊዎች ቅዳሜ እለት ባደረጉት የፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ቡድናቸው ክሪስታል ፓላስን 5 ለ 0 በመርታቱ አድናቆትን ከማትረፍ ባለፈ በአንድ አጥቢያ ቤተክርስትያን በመሰባሰብ ምስጋና አቅርበዋል፡፡ ደጋፊዎቹ የመድፈኞቹን ማሊያ ለብሰው በእሁድ ጠዋት አገልግሎት ላይ ቡድናቸው ላሳየው አስደናቂ ብቃት በደስታ ውዳሴ እና ምስጋና አቅርበዋል።በመጪው የውድድር ዘመን ለአርሰናል ቀጣይ ስኬት ተስፋ በማድረግ ጸሎት አቅርበዋል። ከታዳሚዎቹ መካከል ጋዜጠኛ ኬኔዲ ሙሪቲ በፀሎት ስነ ስርዓቱ ላይ የተነሱትን ፎቶዎች በማህበራዊ ሚዲያ ማጋራቱን ዳጉ ጆርናል ተመልክቷል።የሰሜን ለንደኑ አርሰናል አንድ ጨዋታ ከሚቀረው ማንቸስተር ሲቲ እኩል እና ከሊቨርፑል በአምስት ነጥብ ዝቅ ብሎ ተቀምጧል። ፎቶዎቹ በማህበራዊ ድረ-ገጾች ላይ የተለያዩ አስተያየቶችን የፈጠሩ ሲሆን አንዳንዶቹ በደጋፊዎች ላይ አፌዜዋለሁ፡፡
2 12212Loading...
09
ራስን ማጥፋት የስኮትላንድ አብያተ ክርስቲያናት መሪዎች፣ Assisted Suicide #ወይም በእገዛ ራስን ማጥፋትን እየተቃወሙ ይገኛሉ። ይሄንን ያውቁ ነበረ። በአለማችን 15 ሃገራት በሃኪም የታገዘ ራስን ማጥፋት ይፈቅዳሉ። በሃኪም የታገዘ ራስን ማጥፋት ማለት፣ #አንድ #ሰው ራሱን ሲያጠፋ በሃኪም እገዛ ህጋዊ በሆነ መንገድ የህይወት ጉዞውን ማብቃት ማለት ነው። የስኮትላንድ አብያተ ክርስቲያናት ይሄንኑ ድርጊት በሃገሪቱ ህጋዊ እንዲሆን መጠየቁን ተከትሎ ነው ድምጻቸውን ያሰሙት። ለ129 የምክር ቤት አባላት በተላከው ደብዳቤ መሰረት፣ በአንድ የምክር ቤቱ አባል የቀረበውን ይሄንኑ አጸያፊ ተግባር ህጋዊ እንዳይደረግ ጠይቀዋል። በደብዳቤያቸው፣ ይሄ ህግ የሰው ልጅን ሞራላዊነት አሽቀንጥሮ መጣል ነው፣ እንደ ሃገር አለን የምንለውን የሰው ልጆች ዋጋ የሚያሳጣን ነው ብለዋል። ህጉ የሚጸድቅ ከሆነ ስኮትላንድ ስነምግባር የሌለባት፣ ምክር ቤታችንም ለሰው ልጆች ዋጋ የሌለው አዳራሽ መሆኑ ነው ሲሉ አሳስበዋል። በእገዛ ራስን ማጥፋት ማለት የሰው ልጅ ህይወት ዋጋ የሌለው መሆኑን ማሳያ ነው። ዘፍጥረት ላይ #እግዚአብሔር በአምሳያው የሰውን ልጆች መፍጠሩ፣ ሁሉም የሰው #ልጆች በእግዚአብሔር እንደሚወደድ ማሳያ ነው። ስለዚህ የሰው ልጅ ህይወት ዋጋ አለው ብለዋል። ይሄንን ደብዳቤ የላኩት ቄስ አንድሪው ዶውኒ እና ቄስ ቦብ አክሮይድ የዩናይትድ ፍሪ ቸርች ኦፍ ስኮትላንድ አገልጋዮች ናቸው። ሃገራችን ስኮትላንድ ሰዎች ራሳቸውን ማጥፋት የማያስቡባት መሆን አለባት ብለዋል። ምናልባት በመሰል ስሜት ውስጥ የሚኖሩ ሰዎችን ማህበረሰባችን ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ፍቅርና እንክብካቤ ማሳየት አለበት ብለዋል። ስኮትላንድ የ1517ቱ ተሃድሶ እንቅስቃሴ እንዲስፋፋ ያገዙት ጆን ኖክስ ትውልድ ሃገር መሆኗ ይታወሳል።
2 9419Loading...
10
የአፍሪካ ወንጌላዊያን ማህበር በአዲስ አበባ ስብሰባውን አካሄደ። ማህበሩ ባካሄደው ስብሰባው የአፍሪካ አብያተ ክርስቲያናት ላይ ተጽኖ የሚያደርሱ ጉዳዮች በስፋት ተዳሰዋል። በስብሰባው ከአፍሪካ ህብረት ቢሮ፣ የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት ሕብረት፣ ከመንግስት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። ማህበሩ በአፍሪካ የሚገኙ ከ250 ሚሊዮን በላይ አባላት ያሉት ወንጌላዊያን አብያተ ክርስቲያናትን ያቀፈ ነው። በስብሰባው የአፍሪካ ህብረት በ2063 ሊያሳካ ካቀዳቸው ግቦች መካከል ጤናማ ዜጋ መፍጠር እና ተሸጋጋሪ ኢኮኖሚ ግንባታን እውን ማድረግን እንደሚያግዝ በመድረኩ ተነስቷል። አፍሪካን የበለጸገችና ሰላማዊ ለማድረግ እንደሚሰራም የአፍሪካ ወንጌላዊያን ማህበር ገልጿል።
2 4261Loading...
11
#እንኳን #ደስ አለህ #ወጣቱ ወንድማገኝ የመላዉ አፍሪካ አብያተክርስቲያናት ጉባኤ የጠቅላላ ኮሚቴ አባል በመሆን ተመርጧል። የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነየሱስ የልጆች እና ወጣቶች አገልግሎት መምሪያ ዳይሬክተር ወንድማገኝ ኡዴሳ ናይጄሪያ አቡጃ እየተካሄደ በሚገኘዉ በ12ኛው የመላ አፍሪካ አብያተ ክርስቲያናት ጉባኤ ወጣቶችን በመወከል የጠቅላላ ኮሚቴ አባል በመሆን ተመርጧል:: The Christian News - የክርስቲያን ዜና የተሰማንን ደስታ እየገለፅን #መልካም የአገልግሎት #ጊዜ እንዲሆንልህ እንመኛለን። Wondmagegn Udessa Bidire 🙏🙏🙏
2 1651Loading...
12
#ኑ አብረን እናመስንግን #እግዚአብሔር ድል ሰጥቶናልና #50 የድል ዓመታት የመሠረተ ክርስቶስ #ቤተክርስቲያን የመዘምራን ቡድን "ቢጫ ለባሾቹ" የምስረታ 50ኛ ዓመት ክብረ በዓል በድምቀት እያከበሩ ነው። በምስራቅ መሰረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን እየተከናወነ በሚገኘው የምስጋና ፕሮግራም የአብያተ ክርስቲያናት መሪዎች ፤ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በርካታ ምዕመናን በተገኙበት በድምቀት እየተከናወነ ይገኛል። የመዘምራን ኳየሩ ዝማሬዎቹን ለእግዚአብሔር ክብር ፤ ለህዝቡም በረከት እንዲያቀርብ ከተመሠረተበት ከ1966ዓ.ም ጀምሮ በሀገሪቱ ውስጥ በአዲስ አበባና ከአዲስ አበባ ውጭ ባሉ የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን አጥቢያዎች ፤ በባህር ማዶ በየኢትዮጵያውያን ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት አጥቢያዎች ሲያገለግሉ እንደቆዩ መድርረኩ ተጠቅሷል። The Christian News - የክርስቲያን ዜና ለዘጋባ በስፍራው በመገኘት እየተከታተለን ሲሆን ተጨማሪ ዝርዝር መረጃ ይዘንላችሁ የምንመለስ ይሆናል።
2 9055Loading...
13
"... ማን ያውራ ? የነበረ ...." የባሊ አቦው ልጅ የሐረር መምህራን ማሰልጠኛ ተማሪው የመጀመሪያ የጰንጠቆስጠ ቤተ ክርስቲያን አጀማመር በኢትዮጵያ ከፍተኛ አስተዋጽዖ ያበረከቱ የሙሉ ወንጌል ቤተክርስቲያን ምስረታ ውስጥ የነበሩ ባህር ተሻግረው ቤተክርስቲያን በመትከል እና የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ላይ በትጋት የሰሩ የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ከ60 ዓመት በላይ በማገልገል ባለውለታ የሆኑት ፓስተር ዶክተር ዘለቀ አለሙ ወደ አገለገሉት ጌታ ሄደዋል። በትዳር ከ46 ዓመታት በላይ ተሻግረዋል በምዕራቡ አለም ያላቸው ቆይታ አጠናቀው ወደ ሀገራቸው ሊገዙ እየተሰናዱ እና "ግሬስ" በተሰኘ ሴንተር የሰው ልጆች በሙሉ በክርስቶስ የተደረገልን ምንድነው የሚለውን እንዲረዱ ለመስራት እና ለመስበክ እና ደቀ መዛሙርት ለማፍራት እቅድ እንደነበራቸው በአንድው ወቅት The Christian News - የክርስቲያን ዜና ጋር #የክርስቲያን እንግዳ ሆነው ድንቅ ቆይታ ባደረግንበት ጊዜ አጫውተውን ነበር። "... ማን ያውራ ? የነበረ ..." እንዲሉ የኢትዮጵያ ጰንጠቆስጤአዊ እንቅስቃሴ አጀማመር መተረክ ከሚችሉት ጥቂት ሰዎች መካከል አንዱ መጋቢ ዘለቀ አለሙ (ዶ/ር) ነው። "ሕይወቴ እና ጰንጠቆስጤአዊ እንቅስቃሴ አጀማመር በኢትዮጵያ" በሚለው መጽሐፋቸው ላይ ቀድመው አስተያየት ከሰጡ ሰዎች መካከል መጋቢ በቀለ ወልደ ኪዳን አስተያየታቸው ሰጥተዋ ነበር። በቻናላችን ከ2ዓመት በፊት ያደረግንላቸውን ቃለ መጠይቅ ሊንኩን በመጫን እንድትመለከቱ ግንዣችን ነው። https://youtu.be/1FHp-jLOZJI?si=Fn1MqoGRvgaFq30H
2 1340Loading...
14
#ታላቁ #የወንጌል #አርበኛ #ወደ #ጌታ ተሰበሰቡ መጋቢ ሰለሞን ጂኖሎ የሻሸመኔ አጥቢያ የሕይወት ብርሃን ቤተክርስቲያን መሪ መጋቢ ወደ አገለገሉት ጌታ ሄደዋል። በወንጌል ላልተደረሱ አካባቢዎች ወንጌል የማድረስ ሸክም ሲሰሩ ቆይተዋል። በእንዲህ ሁኔታ በመሰጠት የሚያገለግሉ አባት ማጣት እጅግ ልብን የሚሰብር ዜና ቢሆንም ወዳገለገለው ጌታ ተሰብስቦአልና እንጽናናለን። መጋቢ ሰለሞም የኢትዮጵያ የሕይወት ብርሃን ቤተክርስቲያን ዋና ጸሐፊ በመሆንም ቤተክርስቲያንን አገልግለዋል። ጌታ ለመላው ቤተሰቡና ለወዳጅ ዘመዶቹ መጽናናትን እንዲሰጥ እንመኛለን።
1 8722Loading...
15
የቤተክርስቲያን ምክር አልሰማ ብላችሁ የባንክ ደብተር ይዛችሁ ወደ ሐሰተኞች የምትነጉዱ #ሥራ_ፈቶች ሆይ “በጸሎት ሒሳብ ላይ የሚጨመር ቁጥር የለም” ብሏችኃል አቶ አቤ ሳኖ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት (ዋልታ ቲቪ) ያለ ሥራ የሚገኝ በረከት የለም::ያለ አንተ ሥራ የሚገኘው ደህንነት ወይም በክርስቶስ የሚገኝ የዘላለም ሕይወት ብቻ ነው::
2 8096Loading...
16
#ጅማ ክርስቲያን በጅማ ዩኒቨርሲቲ ቴክኖ ካምፓስ የቀድሞ የ#ክርስቲያን ተማሪዎች ሕብረት (ኪቶ ፋሚሉ) አባል የነበሩ ተማሪዎች መልካም ግንኙነት ሊያስቀጥል የሚችል ክርስቲያን ኔትወርኪንግ ኢቨንት ተካሄደ። #ይህ ለሁለተኛ #ጊዜ የተዘጋጀው ፕሮግራም በዋናነት ከዩኒቨርስቲ ተመርቀው ወጥተው በተለያዩ የግል የስራ ዘርፎች የተሰማሩ ተማሪዎችን ግንኙነት ማስቀጠል #እና የተሰማሩበትን የቢዝነስ ዘርፍ አስተዋውቀው #መልካም ግንኙነት እንዲፈጠር ታስቦ የተዘጋጀ እንደሆነ የፕሮግራሙ አስተባባሪ ወንድም አቤኔዜር ማቴዎስ ለክርስቲያን ዜና ተናግሯል። አቤኒዘር አክሎ ተማሪዎች ከዩኒቨርሲቲ ከተመረቁ በኋላ አብዛኛውን ጊዜ ግንኙነቱ ሲቀጥል አይታይም ይህን ክፍተት ለመቀነስ ያሰበ መልካም ግንኙነት እንደሆነ ተናግሯል። ይህ ሕብረት በቀጣይ ከጅማ ዩኒቨርሲቲ ውጪ የሚገኙ ሕብረትን ለማሳደግ እንደሚሰሩ ወጣት አቤኔዜር አክሎ ለክርስቲያን ዜና ተናግሯል። ክርስቲያን #ዜና ያናገራቸው በፕሮግራሙ #ላይ የሚሰሩትን የተለያዩ ስራዎችን ይዘው የቀረቡ የቀድሞ ተማሪዎች ይህ የህብረት ፕሮግራም ከሌሎች ጋር የመተዋወቅን እና የቢዝነስ ስራ በጋራ ለማሳደግ ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው ነግረውናል። The Christian News - የክርስቲያን ዜና በስፍራው ተገኝተን ዘገባውን አዘጋጀን ተጨማሪ ዝርዝር መረጃ በክርስቲያን ዜና የዮቲዩብ ቻናል ይዘን እንመለሳለን።
2 3950Loading...
17
የወልቂጤ #ከተማ ወንጌላውያን አማኞች የትንሳኤ በአልን በህብረት አደባባይ ላይ አከበሩ። ምዕመኑ በአብሮነት ለሰላምና ለአንድነት መስራት ይጠበቅበታልም ተብሏል። የወልቂጤ ከተማ ወንጌላዉያን አብያተ ክርስቲያናት ህብረት ሰብሳቢ መጋቤ ብርሃኑ አቅነዳ የበአሉ አከባበርን አስመልክተው እንዳሉት የእምነቱ ተከታዮች በአንድነት እንዲያከብሩ መንግስት ማመቻቸቱ የሚያስደስትና እምነቱም ምእመን በጋራ እንዲያከብር የሚያዝ ነው ብለዋል። #ህብረቱ በበአል ወቅትም ይሁን ከበአል ውጪ የተቸገሩ ወገኖችን ማገዝ ልምዱ ነው ያሉት መጋቤ ብርሃኑ የትንሳኤ በአል አክባሪዎች ይህን ማጠናከር አለባቸው ብለዋል። የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ እንዳለ ስጦታው በዚህ ወቅት እንዳሉት ትንሳኤ ለህዝበ ክርስቲያኑ ታላቅ በአል ነው ብለዋል። በዋናነት እምነቱ በሚያዘው መሰረት አብሮነትን በማጠናከር ለተቸገሩ ወገኖችን ከመርዳት ባለፈ እርስ በርስ ከሚሸረሽሩ ተግባሮች ከመታቀብ ባለፈ የ #ሰላም መጠበቅ በሚያጸና መልኩ ሊሆን እንደሚገባም ገልፀዋል። የጉራጌ ዞን #ዋና አስተዳዳሪ ተወካይና የዞኑ ብልጽግና ፓርቲ ምክትል ኃላፊ #አቶ አለማየሁ ገብረመስቀል ፈጣሪ ሁሉን በእኩል የሚያይና በእኩል የሚዳኝ መሆኑን ተናግረዋል። የትንሳኤ በአል የደስታ በአል ነው ያሉት አቶ አለማየሁ የይሁዳ ፀፀት ቢዘጋም እርስ በርስ ዛሬም በሀገራችን አንዳንዶች በሰው #ደም የመነገድ ተግባር የሚፈፅሙ አሉ ብለው #ይህም ወንጀል መሆኑን መረዳትና ለሰላም መስራት ከምእመኑ ይጠበቃል ነው ያሉት። በአል አከባበሩ ላይ የተገኙት አካላትም በአሉን በአደባባይ በህብረት በማክበራቸው ደስተኛ መሆናቸውን ተናግረው ላመቻቹ አካላትም ምስጋና አቅርበዋል። በአሉ ሲከበር የተቸገሩትን በመርዳት መሆን እንዳለበትም ገልፀዋል።
2 7355Loading...
18
የትንሳዔ በዓልን የድሬዳዋ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ህብረት በድሬዳዋ ዓለም ዓቀፍ ስታዲየም በተለያየ የአምልኮ ስርዓት አከበሩ። በዛሬው የትንሳዔ በአል በድሬዳዋ ዓለም ዓቀፍ ስታዲየም ሲከበር የድሬዳዋ አስተዳደር #ከንቲባ ክቡር ከዲር ጁሀርን ጨምሮ የአስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች፣ በርካታ የወንጌላዉያን ዕምነት ተከታዮችና የሀይማኖት አባቶች ተገኝተዋል። በድሬዳዋ ዓለም አቀፍ ስታዲየም የድሬዳዋ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ህብረት በተዘጋጀው የትንሳኤ በዓል አከባበር ላይ የክብር እንግዳ የነበሩት የአስተዳደሩ ከንቲባ ክቡር ከድር ጁሀር በዓሉን ስናከብር ትላንት የነበሩ ዛሬ ያልነበሩ ወገኖቻችን ቤተ ዘመዶችን ከጎናቸው በመቆምና የተቸገሩትን ደግሞ በመደገፍ መሆን እንዳለበት አስገንዝበው ለመላው ክርስትና ዕምነት ተከታዮች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። በፕሮግራሙ #ላይ የድሬዳዋ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ህብረት ዋና ሰብሳቢ መጋቢ ሚኪያስ ታዬ የዛሬው የትንሳዔ በዓል አከባበር ዝግጅት መሳካት የድሬዳዋ አስተዳደር ላደገላቸዉ ትብብር ላቅ ያለ ምስጋናቸውን አቀርበዋል። የድሬዳዋ ሀይማኖት ተቋማት ጉባዔ ምክትል ሰብሳቢ ሊቀ ብርሀናት ቀለመ ወርቅ ቢምረው በዛሬው የትንሳኤ በዓል ዲያቢሎስ የታሠረበት፣ ሀጢያት የተሻረበት እንዲሁም ብዙዎች ነጻ የወጡበት በመሆኑ ልዩ ያደርገዋል ብለዋል። የዛሬው #የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት ህብረት የትንሣኤ በዓል ዝግጅት ለስኬት እንዲበቃ አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላትም የዕውቅና ምስክር ወረቀት ተበርክቷል። ጁሌት ተድላ ለድሬ ቲቪ እንደዘገበዉ ካሜራ:- ምንተስኖት ደረጀ https://youtu.be/tOWD7qwfcDo
2 1561Loading...
19
ተለቀቀ !!! #እኔ አገልጋይ ነኝ እያየሽ ግቢበት ነው ያልኳት ያልተሰሙ #አስገራሚ እና #አዝናኝ የተወዳጁ አገልጋይ #ዘማሪ እንዳለ ወ/ጊዮርጊስ እና ቤተሰቡ የበዓል ቆይታ https://youtu.be/tOWD7qwfcDo
2 4303Loading...
20
#ክህደት ፍቅርን አያጠፋም #የተከፈለው መሰዋዕትነት ለሌሎች ምህረት እንድናደርግ ነው የፓስተር ጻዲቁ አብዶ #ድንቅ መልዕክት #እንኳን አደረሳችሁ!! #live https://youtu.be/9juBNcr_16I
2 2372Loading...
21
♦️ በቅርብ ቀን♦️ "የአማኝ ህይወት" በሚል ርእሰ የተፃፈ ድንቅ መፅሐፍ ወጣት አገልጋይ ካሌብ ይዞልን እየመጣ ሲሆን በቅርብ #ቀን በታላቅ ድምቀት ይመረቃል።
3 0761Loading...
22
በ18 አመቴ ሀኪም ትሞታለህ እንጅ አትተርፍም ከሆስፒታል ውጣ አለኝ። #እኔ ደግሞ #ዛሬ በ78 ዓመቴ ኢየሱስ ያድናል እላለሁ! ዶ/ር ቤተ መንግስቱ ስንመለከታቸዉ እረጋ ያሉ በአገልግሎት ከኬኒያ እስከ አሜሪካ ከአሜሪካ እስከ ኢትዮጵያ የጉባኤ እግዚአብሔር ቤተክርስቲያን ምስረታ ቀዳሚ የነበሩ። ዶ / ር ቤተ መንግስቱ በአሁኑ ሰዓት በተልይ "አፍሪካ ተነሺ" በሚል አለም አቀፋዊ ጉባኤ የምትታወቀዉን የቤዛ ኢንተርናሽናል ቤተክርስቲያን እየመሩ ይገኛሉ።
2 8275Loading...
Фото недоступноПоказать в Telegram
ተወዳጁ ዘማሪ አዉታሩ ከበደ ቁጥር 7ቱን የዝማሬ አልበም ሊለቅ ነዉ። "ከ9 አመታት በኋላ የ7 ቁጥር አልበሜ በመንፈስ ተጠምቆ ለቅዱሳን በረከት ላልዳኑ የኢየሱሰን አዳኝነት ለማብሰር ተጠናቋል" ሲል ዘማሪዉ ገልጿል። የምትፅልዩልኝ,በነገር ሁሉ ከጎኔ ያላችሁ እግዚአብሔር ይባርካችሁ። በሁላችሁ እጅ ላይ በቅርቡ የሚደርስበትን ቀን አሳውቃለው የዘማሪዉ መልዕክት ነዉ።
Показать все...
👍 26 7🥰 1👏 1
የዝሙት ሕይወቴን ማንም አያወቅም ነበር ሰዎች መማር ካለባቸው ከእኔ ይማሩ #ድንቅ #ምስክርነት ከዚህ ልምምድ መውጣት ሲያቅተኝ ከጌታ ቤት ባክ አደረኩኝ https://youtu.be/ugkLCiXAYII
Показать все...

👍 14 2🔥 1🕊 1😭 1
Фото недоступноПоказать в Telegram
#ይፈቱ በኤርትራ ከ 20 አመታት በላይ የታሰሩ የፕሮቴስታንት እምነት ፓስተሮች እንዲፈቱ አሜሪካ ጠየቀች። የአሜሪካው ዓለማቀፍ የኃይማኖት ነጻነት ኮሚሽን፣ የፕሬዝዳንት ጆ ባይደን አስተዳደር በኤርትራ ላለው የኃይማኖት ነጻነት ጥሰት ትልቅ ትኩረት እንዲሰጥ መጠየቁ ዳጉ ጆርናል ከዘገባዎች ተመልክቷል። ኮሚሽኑ፣ ፓስተር ኃይሌ ናይዝጊ እና ፓስተር ክፍሉ ገብረመስቀል የተባሉ የፕሮቴስታንት ኃይማኖት ሰባኪዎች ከታሠሩ ከ20 ዓመታት በላይ አስቆጥረዋል ሲል ለአብነት ጠቅሷል። #ኤርትራ ፣ ከኃይማኖት ነጻነት ጋር በተያያዘ 5 መቶ ያህል ሰዎችን ክስ ሳይመሠረትባቸው እንዳሠረች ኮሚሽኑ አመልክቷል። የኤርትራ መንግሥት ባለፈው ዓመት ከኃይማኖት ጋር በተያያዘ የታሠሩ ዘጠኝ እስረኞችን #ብቻ መፍታቱን ያስታወሰው ኮሚሽኑ፣ ጅምሩ #ግን ሳይቀጥል ቀርቷል በማለት ወቅሷል። ሲል ዋዜማ ሬድዬ ዘግቧል። ዜናውን ከወደዱት Like ማንኛውም አስተያየት እና ጥያቄ ካሎት Comment በፍጥነት ለወዳጆ ለማካፈል #share ያድረጉ
Показать все...
👍 45 13🔥 1😭 1
Фото недоступноПоказать в Telegram
#መቀሌ #ታላቁ ተልዕኮ ኢትዮጵያ 10 ቢሮውን በትግራይ መቀሌ ከፈተ። ግሬት ኮሚሽን ከ1972 ዓ.ም. ጀምሮ #በኢትዮጵያ የወንጌል ስራን ሲሰራ ቆይቷል። በአሁኑ ወቅት በአዳማ፣ ባህርዳር፣ ሃረር፣ ሃዋሳ፣ ጅማ፣ ነቀምቴ፣ አርባ ምንጭ፣ ሆሳዕና እና አምቦ የአካባቢ ቢሮዎችን አቋቁሞ በየአካባቢው ከሚገኙ ሚኒስትሪዎችና አብያተ ክርስቲያናት ጋር ወንጌልን እየሰራ ይገኛል። ግሬት ኮሚሽን #ኢትዮጵያ ሚኒስትሪ፣ የጂሰስ ፊልምን በ74 የሃገር ውስጥ ቋንቋዎች በማስተርጎምና በ10 ሃገራት ውስጥ ኢንዲጂተስ በተሰኘ የቴክኖሎጂ ማህበረሰብን በመፍጠር በኢትዮጵያና ከኢትዮጵያ ውጪም ወንጌልን እየሰራ ይገኛል። ከጦርነት መልስ የወንጌል ስርጭት ማዕከል በትግራይ የተከፈተውን ይሄንን ቢሮ ያስተባበረው ወንድም #ካሳሁን_ሰዒድ ሲሆን በመድረኩ እውቅና ተሰጥቶታል። ወንድም ካሳሁን መቀሌ እና መላውን ትግራይ ላለፉት 10 ዓመታት በወንጌል ለመድረስ ሲያገለግል ቆይቷል። ምንጭ፣ GCMEthiopia ዜናውን ከወደዱት Like ማንኛውም አስተያየት እና ጥያቄ ካሎት Comment በፍጥነት ለወዳጆ ለማካፈል #share ያድረጉ
Показать все...
24👍 16🔥 1👏 1
Фото недоступноПоказать в Telegram
የሃይማኖት ተቋማት የፋይናንስ ኦዲት ሪፖርታቸውን ለመንግሥት እንዲያቀርቡ የሚደነግግ ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጀ ማንኛውም የሃይማኖት ተቋም የፋይናንስ ኦዲት ሪፖርቱን ለሰላም ሚኒስቴር ማቅረብ እንደሚኖርበት፣ ከውጭ አገር የሚመጣ የገንዘብ ዕርዳታ በሕግ ሥልጣን ለተሰጠው አካል ማሳወቅ እንደሚኖርበት የሚደነግግ ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጀ፡፡ " የሃይማኖት ጉዳዮች አዋጅ " የተሰኘው ረቂቅ አዋጅ፣ የሃይማኖት ተቋማቱ ተቀባይነት ያለው የሒሳብ አያያዝና የኦዲት ሥርዓት መዘርጋት እንደሚኖርባቸው፣ የኦዲት ሪፖርታቸውንም ለሰላም ሚኒስቴር ማቀረብ እንዳለባቸው የሚደነግግ መሆኑን ሪፖርተር ጋዜጣ አስነብቧል። የሃይማኖት ተቋማቱ የሚጠቀሙት የሒሳብ አያያዝ ሥርዓት የገቢ፣ የወጪና አጠቃላይ የንብረት ዝርዝር የያዘ መሆን እንደሚኖርበትና የገቢ አሰባሰብና የወጪ አስተዳደር በሕጋዊ መንገድ ማከናወን እንዳለባቸውም ይገልጻል። አንድ የሃይማኖት ተቋም በራሱ የገቢ ማስገኛ ሥራዎችን በሚያከናውንበት ጊዜ፣ ለዚሁ ሥራ የተለየ የባንክ ሒሳብ መክፈትና የተለየ መዝገብ መያዝ እንዳለበትም ተደንግጓል፡፡ በተጨማሪም ማንኛውም የሃይማኖት ተቋም ከውጭ አገር የሚላክለትን የገንዘብ ዕርዳታ፣ ስጦታ ወይም ሌሎች የገንዘብ ድጋፎችን በሕግ ሥልጣን ለተሰጠው አካል ማሳወቅ ይኖርበታል ተብሏል። በተጨማሪም የለጋሹን ድርጅት ወይም ግለሰብ ስምና አድራሻ፣ የተለገሰው የገንዘብ፣ ስጦታ ዓይነትና መጠን፣ እንዲሁም ስጦታው ወይም ድጋፉ የተሰጠበት ልዩ ዓላማ የሃይማኖት ተቋማቱ ጨምርው ማሳወቅ እንዳለባቸው ተገልጿል፡፡
Показать все...
👍 17 5🔥 2👌 1
Фото недоступноПоказать в Telegram
"#የአፍሪካ #መንፈሳዊ ቀን" በአፍሪካ ሕብረት ተካሄደ። በInter religious Association for Peace And Development (IAPD Africa) አዘጋጅነት "Educating the African person to be Spiritually fit in the 21st Century" በሚል መሪ ቃል ኢትዮጵያን ጨምሮ ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት የመጡ መሪዎች በተገኙበት በአፍሪካ ሕብረት ተከናውኗል። የሃይማኖት ተቋማት እና መሪዎች በሰላም እና በልማት ስራዎች ላይ በቅንጅት ለአፍሪካ መስራት እንደሚገባቸው በመድረኩ ተጠቅሷል። በመድረኩ የInter religious Association for Peace And Development (IAPD Africa) የአፍሪካ ሊቀመንበር ዶ/ር ኡዙዊን ጨምሮ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ክ እና የእስልምና እምነት በሀገራችን የትምህርት ስረዓት ያበረከቱትን አስተዋጽዖ በተመለከተ የተለያዩ ጽሑፎች ቀርበዋል። በጉባኤው በቅርብ ጊዜ የምስረታ 50ኛ ዓመት ክብረ በዓላቸውን ያከበሩት አንጋፋዎቹ የመሰረተ ክርስቶስ ቤ/ክ (ቢጫ ኳይር) ዝማሬ አቅርበዋል።
Показать все...
5👍 2🔥 1👏 1
Фото недоступноПоказать в Telegram
#ቤተ #በአዲስ አበባ በሆሳዕና ለረጅም አመት እያገለገለች የምትገኘዉ ቤተምህረት #አሁን ደግሞ በአዲስ አበባ የቤተ ክርስቲያን ተከላና- የመክፈቻ ፕሮግራም ከግንቦት 21-25 / ከእሮብ እስከ ቅዳሜ ከ 10:00 ጀምሮ እሁድ ጠዋት ይከናወናል። #አድራሻ ፦ ከቡልጋሪያ #ወደ ቄራ ሲወርዱ ስካኒያ አካባቢ የቤተ ምህረት ማስታወቂያ ባለበት 100 ሜትር ገባ ብሎ ያገኙናል። #ቤተ ምህረት እንገናኝ 🙏🙏
Показать все...
👍 20 11🔥 2👏 1🕊 1
#የአርሰናል ደጋፊዎች በቤተክርስቲያን ምስጋና አቀረቡ። በኬንያ የሚገኙ የአርሰናል ደጋፊዎች ከድል በኋላ በቤተክርስቲያን ዉስጥ ምስጋና አቀረቡ በኬንያ ርዕሰ መዲና ናይሮቢ የሚገኙት የአርሰናል ደጋፊዎች ቅዳሜ እለት ባደረጉት የፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ቡድናቸው ክሪስታል ፓላስን 5 ለ 0 በመርታቱ አድናቆትን ከማትረፍ ባለፈ በአንድ አጥቢያ ቤተክርስትያን በመሰባሰብ ምስጋና አቅርበዋል፡፡ ደጋፊዎቹ የመድፈኞቹን ማሊያ ለብሰው በእሁድ ጠዋት አገልግሎት ላይ ቡድናቸው ላሳየው አስደናቂ ብቃት በደስታ ውዳሴ እና ምስጋና አቅርበዋል።በመጪው የውድድር ዘመን ለአርሰናል ቀጣይ ስኬት ተስፋ በማድረግ ጸሎት አቅርበዋል። ከታዳሚዎቹ መካከል ጋዜጠኛ ኬኔዲ ሙሪቲ በፀሎት ስነ ስርዓቱ ላይ የተነሱትን ፎቶዎች በማህበራዊ ሚዲያ ማጋራቱን ዳጉ ጆርናል ተመልክቷል።የሰሜን ለንደኑ አርሰናል አንድ ጨዋታ ከሚቀረው ማንቸስተር ሲቲ እኩል እና ከሊቨርፑል በአምስት ነጥብ ዝቅ ብሎ ተቀምጧል። ፎቶዎቹ በማህበራዊ ድረ-ገጾች ላይ የተለያዩ አስተያየቶችን የፈጠሩ ሲሆን አንዳንዶቹ በደጋፊዎች ላይ አፌዜዋለሁ፡፡
Показать все...
😭 12👍 5 4🙏 1🕊 1
Фото недоступноПоказать в Telegram
ራስን ማጥፋት የስኮትላንድ አብያተ ክርስቲያናት መሪዎች፣ Assisted Suicide #ወይም በእገዛ ራስን ማጥፋትን እየተቃወሙ ይገኛሉ። ይሄንን ያውቁ ነበረ። በአለማችን 15 ሃገራት በሃኪም የታገዘ ራስን ማጥፋት ይፈቅዳሉ። በሃኪም የታገዘ ራስን ማጥፋት ማለት፣ #አንድ #ሰው ራሱን ሲያጠፋ በሃኪም እገዛ ህጋዊ በሆነ መንገድ የህይወት ጉዞውን ማብቃት ማለት ነው። የስኮትላንድ አብያተ ክርስቲያናት ይሄንኑ ድርጊት በሃገሪቱ ህጋዊ እንዲሆን መጠየቁን ተከትሎ ነው ድምጻቸውን ያሰሙት። ለ129 የምክር ቤት አባላት በተላከው ደብዳቤ መሰረት፣ በአንድ የምክር ቤቱ አባል የቀረበውን ይሄንኑ አጸያፊ ተግባር ህጋዊ እንዳይደረግ ጠይቀዋል። በደብዳቤያቸው፣ ይሄ ህግ የሰው ልጅን ሞራላዊነት አሽቀንጥሮ መጣል ነው፣ እንደ ሃገር አለን የምንለውን የሰው ልጆች ዋጋ የሚያሳጣን ነው ብለዋል። ህጉ የሚጸድቅ ከሆነ ስኮትላንድ ስነምግባር የሌለባት፣ ምክር ቤታችንም ለሰው ልጆች ዋጋ የሌለው አዳራሽ መሆኑ ነው ሲሉ አሳስበዋል። በእገዛ ራስን ማጥፋት ማለት የሰው ልጅ ህይወት ዋጋ የሌለው መሆኑን ማሳያ ነው። ዘፍጥረት ላይ #እግዚአብሔር በአምሳያው የሰውን ልጆች መፍጠሩ፣ ሁሉም የሰው #ልጆች በእግዚአብሔር እንደሚወደድ ማሳያ ነው። ስለዚህ የሰው ልጅ ህይወት ዋጋ አለው ብለዋል። ይሄንን ደብዳቤ የላኩት ቄስ አንድሪው ዶውኒ እና ቄስ ቦብ አክሮይድ የዩናይትድ ፍሪ ቸርች ኦፍ ስኮትላንድ አገልጋዮች ናቸው። ሃገራችን ስኮትላንድ ሰዎች ራሳቸውን ማጥፋት የማያስቡባት መሆን አለባት ብለዋል። ምናልባት በመሰል ስሜት ውስጥ የሚኖሩ ሰዎችን ማህበረሰባችን ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ፍቅርና እንክብካቤ ማሳየት አለበት ብለዋል። ስኮትላንድ የ1517ቱ ተሃድሶ እንቅስቃሴ እንዲስፋፋ ያገዙት ጆን ኖክስ ትውልድ ሃገር መሆኗ ይታወሳል።
Показать все...
👍 12🕊 2🔥 1😭 1
Фото недоступноПоказать в Telegram
የአፍሪካ ወንጌላዊያን ማህበር በአዲስ አበባ ስብሰባውን አካሄደ። ማህበሩ ባካሄደው ስብሰባው የአፍሪካ አብያተ ክርስቲያናት ላይ ተጽኖ የሚያደርሱ ጉዳዮች በስፋት ተዳሰዋል። በስብሰባው ከአፍሪካ ህብረት ቢሮ፣ የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት ሕብረት፣ ከመንግስት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። ማህበሩ በአፍሪካ የሚገኙ ከ250 ሚሊዮን በላይ አባላት ያሉት ወንጌላዊያን አብያተ ክርስቲያናትን ያቀፈ ነው። በስብሰባው የአፍሪካ ህብረት በ2063 ሊያሳካ ካቀዳቸው ግቦች መካከል ጤናማ ዜጋ መፍጠር እና ተሸጋጋሪ ኢኮኖሚ ግንባታን እውን ማድረግን እንደሚያግዝ በመድረኩ ተነስቷል። አፍሪካን የበለጸገችና ሰላማዊ ለማድረግ እንደሚሰራም የአፍሪካ ወንጌላዊያን ማህበር ገልጿል።
Показать все...
👍 13 5🔥 1🥰 1