cookie

Мы используем файлы cookie для улучшения сервиса. Нажав кнопку «Принять все», вы соглашаетесь с использованием cookies.

avatar

Blüë_Story

It's Hot channel Join u will love it

Больше
Страна не указанаЯзык не указанКатегория не указана
Рекламные посты
180
Подписчики
Нет данных24 часа
Нет данных7 дней
Нет данных30 дней

Загрузка данных...

Прирост подписчиков

Загрузка данных...

00:48
Видео недоступноПоказать в Telegram
1.35 MB
Показать все...
መላ መላ.mp33.44 MB
Фото недоступноПоказать в Telegram
#ገብርኤል_አባቴ😔🙏 የልቤን አንተ ታውቃለህና🥺 ከፊትህ ቆሜ የተማፀንኩህን አደራ😥💔💔 19
Показать все...
Repost from #Official-Kiya
00:17
Видео недоступноПоказать в Telegram
5.95 KB
Le reku
Показать все...
Фото недоступноПоказать в Telegram
7❤
Показать все...
Repost from N/a
ስህተትን የመደጋገም አጉል ተጽእኖ (“ራስን ማሸነፍ” ከተሰኘው የዶ/ር ኢዮብ ማሞ መጽሐፍ የተወሰደ) “ስህተት የሚሰራ ሰው፣ ሰው ይባላል፣ ስህተትን የሚደጋግም ግን ሞኝ ይባላል” የሚለውን አባባል ከዚህ በፊት እንደሰማኸው እገምታለሁ፡፡ አንድን ስህተት ከሰራ በኋላ አመዛዝኖና ሁኔታውን ፈትኖ በሚታረም ሰውና ያንኑ ስህተት በሚደጋግም ሰው መካከል ደግሞ ትልቅ ልዩነት አለ፡፡ ስህተትን የሚደጋግም ሰው ከዚያው ጋር ራሱን ለብዙ መዘዞች ያጋልጣል፡፡ ይህንን እውነታ ግን ሁሉም ሰው አይቀበለውም፡፡ አንዳንድ ሰዎች ስህተት እንዲሰሩ ምክንያት የሆነባቸውን ሰውና ሁኔታ ስለወቀሱ ወይም ስላሳበቡ ከመዘዝ የሚያመልጡ ይመስላቸዋል፡፡ አንድን መርዝ እንድንጠጣ አንድ ሰው ስላታለለንና ያንንም ሰው ስለወቀስነው ከመርዙ ሰበብ እንደማናመልጥ ሁሉ ከማንኛውም ተደጋጋሚ ስህተት አጉል ውጤትም ሰዎችን ስለወቀስን ሊቀርልን አይችልም፡፡ የማይድን ቁስል ተመሳሳይ ስህተትን መስራት ማለት ከተመሳሳይ ችግር ጋር መኖር ማለት ነው፡፡ ተመሳሳይ ችግር የሚያመጣብን መዘዝ ተመሳሳይ ቦታ ላይ የማቁሰል ሁኔታ ነው፡፡ ከዚህ በፊት ያንኑ ስህተት ሰርተን ከደረሰብን ሁኔታ በሚገባ ሳናገግም ያንኑ ስህተት በመድገም ተመሳሳይ ጉዳት ሲደርስብን ዝለት ይከተላል፡፡ በእንደዚህ ሁኔታ ለረጅም ጊዜ የሚከርም ሰው የኋላ ኃላ መዘዙን ማየት ይጀምራል፡፡ ሕይወት ከአንዱ ቁስል ወደ ሌላኛው ቁስል በመሸጋገር ለማገገም የምንመኝባት መስክ መሆን የለባትም፡፡ በምትኩ፣ ከስህተት በመማርና ስህተቱን ባለመድገም ከአንዱ ድል ወደ ሌላኛው ድል በመሸጋገር ለተሻለ ነገር የምንሰራባት መስክ ልትሆን ይገባል፡፡ የራስ-በራስ ንቀት አንድ ሰው የመጨረሻ ዝቅተኛ ደረጃ ወረደ የሚባለው በራሱ ላይ ያለው ግምት በጣም ሲወርድና ራሱን መናቅ ሲጀምር ነው፡፡ ይህ ሁኔታ ከሚከሰትባቸው ምክንያቶች አንዱ ደግሞ አንድን ስህተት ማረም እንዳለበት እያወቀ፣ ደግሞ ደጋግሞ በዚያው ስህተት የመገኘት ሁኔታ ነው፡፡ በስህተትና በጸጸት ዑደት (አዙሪት) ውስጥ የሚኖር ሰው ቀስ በቀስ ራሱን እንደ ሰነፍ፣ መሻሻል እንደማይችልና ሌሎች ሰዎች ማድረግ የቻሉትን ቀላል ነገር እሱ ግን እንዳቃተው ማሰብ ይጀምራል፡፡ ይህ ራስን የመናቅ ሁኔታ ለወደፊቱ የሚኖረውንም የመሻሻል ፍላጎት ስለሚነካበት ወደሌላ የግድ-የለሽነት ስህተት ይመራዋል፡፡ “የእድል ሰለባ” አመለካከት በዙሪያህ የሚገኙ ሰዎች ስህተታቸውን በማረምና ራሳቸውን በማሻሻል በሚያስገርም ፍጥነት ሲያልፉ እያየህ ራስህን ስትመለከተው ደግሞ ባለህበት እንደረገጥክ ሲሰማህ በአመለካከትህ ላይ ትልቅ ተጽእኖ ማስከተሉ አይቀርም፡፡ ለጥሩ ነገር እንዳልታደልክና ምንም ያህል ብትጣጣር የአንተ እድል አሁን ያለህበት ሁኔታ እንደሆነ ከማሰብ ውጪ ምንም ምርጫ እንዳይኖርህ ትገፋፋለህ፡፡ “ፈጣሪ ጨከነብኝ”፣ “ማንም ሰው ለእኔ ግድ የለውም”፣ “እድለ-ቢስ ነኝ” እና የመሳሰሉት አመለካከቶችና አባባሎች እንዲሁ አይመጡም፡፡ አእምሮን ተጠቅሞ በማሰብ፣ የተግባርንና የውጤትን ግንኙነት መገንዘብ ካልቻልክ ሁኔታዎችን ከእድል ሰለባነት ጋር ማገናኘትህ አይቀርም፡፡ Join: @Human_Intelligence Join: @Human_Intelligence
Показать все...
📚መልካምነት #መልካም ሰው ነህ የምትባለው አመለ-ሸጋ ስትሆን ሳይሆን መልካም የሚያሰኝህ ስብዕና ሲኖርህ ብቻ ነው። ምክንያቱም መልካምነት ፀባይ አይደለምና። #አንድ ሰው መልካም እንዲሆን መቀየር ያለበት ባሕርይውን አይደለም ሰውዬው እራሱ እንጂ! ሰውዬው መልካም ከመሆኑ በፊት "ክፉ" ነበር! ክፉነት ደግሞ ባህርዩ ሳይሆን ማንነቱ ነበር። ስለዚህ "ክፉው" ሰውዬ መሞት፣ ማለፍና መወገድ አለበት! ከዚያ መልካም የሆነው ይፈጠራል። #መልካምነት ክረምት ጊዜ በጣም እንደሚያስፈልግህ በጋ ላይ ግን ብዙም እንደማትፈልገው ካቦርትህ እየለበስክ የምታወልቀው ውጫዊ ልብስ ሳይሆን ከስብዕና ጋር የተቆራኘ ማንነት ነው። # መድረክ አዘጋጅተህ "መልካምነት ለራስ ነው!" እያልክ ትርዕይት የምታሳይበት የተውኔት ስጦታም አይደለም ማንነት እንጂ። አንተ መልካም ከሆንክ ሰው አየህ አላየህም መልካም ነህ! መልካምን ማድረግ ሞራልህ ሲመጣ የምታደርገው ሳይሆን የየዕለት ተግባርህ ነው #ዲያብሎስ ክፉ ነው! የክፋት ሁሉ አለቃና መሪም ነው። እርሱ "ክፉ" ሲባል ክፋት ባህርዩ ብቻ አይደለም ማንነቱም እንጂ። ስሙም በቅዱሱ መጽሐፍ በተደጋጋሚ "ክፉ" ተብሎ ተጠርቷል። ሰይጣን የክፋት በጀት እጥረት አጋጥሞት አያውቅም ክፋት የሆነ መጋዘኑ ውስጥ አከማችቶት የሚያኖረው ንብረቱ ሳይሆን ማንነቱ ነውና። #እግዚአብሔር ደግሞ ፍጹም መልካም ነው። እርሱ መልካም ብቻ ሳይሆን የመልካምነት ሁሉ መገኛ ምንጭ ነው። መልካም የሚያደርግልንም እርሱ መልካም እንደሆነ እንድናውቅ እንጂ ሰፖራይዚ ሊያደርገን አይደለም። #መልካም አደረገልኝ" የሚሉ እርሱ "መልካም ሆነልኝ" ወደ ማለት መረዳታቸው ከፍ እንዲል ይፈልጋል፤ እርሱ መልካም አድራጊ ብቻ ሳይሆን ፍጹም መልካም ነውና። #መልካምነት ጊዜ እየተጠበቀ የሚደረግ ተግባር ሳይሆን የሚኖር ሕይወትና ማንነት እንደሆነ እናስተውል። መልካም የሆኑ ሰዎች መልካም የሆኑ ተግባራትን ይከውኑ ይሆናል፤ ነገር ግን መልካም ተግባራትን በመከወን መልካምነት አይመጣም። መልካም መሆን መልካምን ከማድረግ ይቀድማልና! #እወዳችኋለሁ 🙏
Показать все...
ታዋቂዋ የአለም ሀብታም ዲዛይነር እና ፀሀፊ ክሪስዳ ሮዲሪጌዝ በካንሰር በሽታ ከመሞቷ በፊት ማስታወሻዋ ላይ እንዲህ ብላ ፅፋ ነበር ! 1 _ በዓለም ላይ አሉ ከሚባሉ ውድ መኪናዎች ውስጥ አንዱ በኔ ገራጂ የተቀመጠ ነው ። አሁን ግን በዊልቸር ነው የምንቀሳቀሰው ! 2 _ቤት ውስጥ በምርጥ ዲዛይነሮች የተሰሩ ውድ የሆኑ የሚያምሩ ልብሶች እና ጫማዎች አሉኝ ! አሁን ግን ከሆስፒታል በተሰጠኝ ስስ ጨርቅ ነው ገላዬን የሸፈንኩት ! 3 _ ባንክ አካውንቴ ላይ ከበቂ በላይ ገንዘብ አለኝ ግን እሱን አሁን ልጠቀምበት አልችልም ! 4 _ ቤቴ ፓላስ የሚባል አይነት ነው ግን እኔ አሁን ሆስፒታል ውስጥ በምትገኝ ትንሽዬ አልጋ ላይ ነው የተኛሁት ! 5 _ ካንዱ ባለ አምስት ኮኮብ ሆቴል እንዳሻኝ ወደ አንዱ ባለ አምስት ኮከብ ሆቴል እንሸራሸር የነበርኩ ሴትዮ አሁን እዛው ሆስፒታል ውስጥ ካንዱ የላቦራቶሪ ክፍል ወደ ሌላኛው ላቦራቶሪ ክፍል መመላለስ ግዴታዬ ነው ! 6 _ በየቀኑ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ፈርሚልን ብለው እንዳላስጨነቁኝ አሁን ግን የሚያክመኝ ዶክተር እንኳን አንድም ቀን ፊርማዬን ጠይቆኝ አያውቅም ! 7 _ ፀጉሬን የማስውብበት ውድ የተባሉ ሰባት አይነት አልማዞች እና ወርቆች ነበሩኝ አሁን ግን ይህንን ማድረግ አልችልም ምክንያቱም ፀጉር የለኝም ! 8 _ በግል አውሮፕላኔ አለም ላይ የፈለኩበት ቦታ ብቻዬን መሄድ እችል ነበረ አሁን ግን ለመናፈስ ስፈልግ እንኳን የግድ የሁለት ሰዎች እርዳታ ያስፈልገኛል 9 _ በቀን በቀን ብፌ በሚባል አይነት የተመረጡ ምግቦችን እመገብ ነበር አሁን ግን በቀን ሁለት ፍሬ ታብሌት እና ትንሽ ጠብታ ጨው ነው ማታ የምወስደው ነው ምግቤ ! ይሄ ሁሉ ሀብት እና ድሎት ግን እኔን ከበሽታዬ ሊያድነኝ አልቻለም እውነተኛ ህይወት ማለት ከፈጣሪ ጋር መኖር ፣ ለትዕዛዛቱም መገዛት ነው ። ጆይን ሼር @lehulumbufe
Показать все...
Фото недоступноПоказать в Telegram
Выберите другой тариф

Ваш текущий тарифный план позволяет посмотреть аналитику только 5 каналов. Чтобы получить больше, выберите другой план.