ru
Feedback
Gamo zone RMNCH-N team

Gamo zone RMNCH-N team

Открыть в Telegram

This channel is used to exchange new initiatives, ideas and updates within Gamo zone for sustainable, reliable and timely interaction among zone, woreda and PHCU staffs to strengthening routine immunization.

Больше
411
Подписчики
Нет данных24 часа
-27 дней
Нет данных30 день
Архив постов
እጅግ አስቾካይ በተደጋጋሚ የ 4ኛ ሩብ አመት የትራንስፎርሜሽን አጀንዳዎች Data elemenet ወደ DHIS2 እንዲገባ ብናሳስብም መረጃዎቹ እየገቡ ባለመሆኑ ከፍተኛ ችግር ሆነው ቀጥለዋል፡፡ በመሆኑ
+2
እጅግ አስቾካይ በተደጋጋሚ የ 4ኛ ሩብ አመት የትራንስፎርሜሽን አጀንዳዎች Data elemenet ወደ DHIS2 እንዲገባ ብናሳስብም መረጃዎቹ እየገቡ ባለመሆኑ ከፍተኛ ችግር ሆነው ቀጥለዋል፡፡ በመሆኑም በየደረጃው የምትገኙ ጉዳዩ የሚመለከታችሁ አካላት ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ሪፖርቱን አስገብታችሁ ለዞኑ እንድታሳውቁ እያሣሠበን የጽ/ቤት ኃላፊዎች ጉዳይኑ ተከታትላችሁ ሪፖርት እንድታደረጉ አጥብቀን እንገልጻለን፡፡ ግልባጭ ለአቶ ሴይፉ ዋናቃ ለወ/ሮ ባንጌ ባንጃ

photo content
+3

በዞኑ ከ 186 ሚሊዮን ብር በላይ ከማህበረሰብ አቀፍ ጤና መደህን አባላት መሰብሰብ መቻሉ ተነገረ ‎ ‎አርባ ምንጭ፡- ሰኔ 30/2018 ዓ.ም ( የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ) ‎ ‎የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ የ2018 በጀት ዓመት የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አመታዊ ማጠቃለያ የአፈጻጸም ግምገማ በበይነ-መረብ በመታገዝ ከባላድርሻ አካላት ጋር ማካሄዱ ታውቋል፡፡ ‎ ‎መምሪያው ባሣለፍነው በጀት ዓመት ውስጥ 195,471 የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አባላትን ያፈራ ሲሆን ከአባላት መዋጮ በአጠቃላይ ብር 186,398,747 መሠብሠብ መቻሉ በሪፖርት ተመላክቷል፡፡ ‎ ‎በቀጣይ ጊዚያት የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን ሒሳብ ኦዲት ማካሄድ፣ የአባላትን መረጃ በዲጂታል ሲስትተም በኮምፒውተር መዝግቦ መያዝ እንዲሁም የአባለትን መዋጮ ገንዘብን ወደ ዞናል ቋት የማስገባት ስራ ትኩረት ሊቸረው ይገባል ተብሏል፡፡ ‎ ‎በመጨረሻም በስብሰባው የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ሴይፉ ዋናቃ፣ የመምሪያው ም/ ኃላፊ ወ/ሮ ባንጌ ባንጃ፣ የመምሪያው ከፍተኛ ባለሙያዎች እንዲሁም የወረዳ እና የተማ አስተዳደር የጤና አመራር እና ባለሙያዎች ተሣትፈውበታል፡፡

Good

ok

photo content

photo content

photo content

photo content

photo content

#የስራ ማስታወቂያ
#የስራ ማስታወቂያ

Day four Mirab abaya HPV Report-1-4.xlsx0.12 KB

Thanks .

+1
1_ታላሚ_በሽታዎችና_ክትባቶቻቸዉ_edited.pptx7.90 MB

1_ታላሚ_በሽታዎችና_ክትባቶቻቸዉ_edited.pptx7.90 MB

photo content
+9

የማህጸን በር ካንሰርን ለመከላከል የህብረተሰቡ ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑ ተነገረ፤ ‎ ‎አርባ ምንጭ፡ ሰኔ 23/2018 ዓ.ም (የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ) ‎ ‎በዞኑ የማህፅን በር ካንሰር እያስከተለ የሚገኝውን ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም ስነ-ልቦናዊ ጫናን መግታት ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫ የውይይት መድረክ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመካሄድ ላይ ይገኛል። ‎ ‎የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ሴይፉ ዋናቃ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉ ሲሆን ኃላፊው በመክፈቻ ንግግራቸው የማህፀን በር ጫፍ ካንሰር ሂውማን ፓፒሎማ (HPV) በተሰኘ ቫይረስ የሚመጣ የካንሰር አይነት መሆኑን ያነሱት የመምሪያው ኃላፊ ክትባት ያለውና በቅድመ ካንሰር ደረጃ ላይ ስገኝ ቀላል ህክምና ያለው መሆኑንገልፀዋል። ‎ ‎ቫይረሱ ከሰው ወደ ሰው የሚተላለፍ እና ሁሉንም የኅብረተሰብ ክፍል የሚያጠቃ ሲሆን ካንሰሩ የሚከሰተው በቫይረሱ ከተያዙ ከረጅም ዓመታት በኋላ ነው ሲሉ አብራርተው  በሽታው በዓለም አቀፍ ደረጃ በሴቶች ላይ ከሚከሰቱ የካንሰር ዓይነቶች ከጡት ካንሰር ቀጥሎ በሁለተኛ ደረጃ ላይ እንደሚገኝም በንግግራቸው አክለዋል። ‎ ‎ለበሽታው መንስዔ ናቸው ተብለው ከተቀመጡት ምክንያቶች ውስጥ በለጋ ዕድሜ የግብረ ስጋ ግንኙነት መጀመር፣ ከብዙ ወንዶች ጋር የግብረ ስጋ ግንኙነት መፈጸም፣ በአባላዘር በሽታ መጠቃት፣ HIV/AIDS ጨምሮ የሰውነት በሽታ መከላከል አቅም መዳከም እና ሌሎች ተዛማጅ በሽታዎች ይጠቀሳሉ። ‎ ‎በበሽታው የተያዙ ሴቶች ደግሞ ያልተለመደ ከማህፀን የደም መፍሰስ፣ የምግብ ፍላጎት መቀነስ እና ክብደት መቀነስ፣ ያልተለመደ መጥፎ ጠረን ያለው ፈሳሽ መኖር፣ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ሲደርስ ደግሞ የእግር ማበጥ፣ የኩላሊት በሽታ እንዲሁም ሽንት ላይ ደም መቀላቀል የመሳሰሉ ምልክቶችን ያሳያሉ። ‎ ‎በሽታውን አንድ ለአንድ በመወሰን፣ በለጋ ዕድሜ ከግብረ ስጋ ግንኙነት በመታቀብ፣ መደበኛ የማኅጸን ምርመራ እና ክትባት በመከተብ መከላከል ይቻላል ሲሉ አቶ ሴይፉ አብራርተዋል። ‎ ‎በዞኑ የማህፀን ጫፍ ቅድመ ካንሰር ልየታ እና ህክምና በሰለጠኑ ባለሙያዎች እየተሰጠ መሆኑን ተናግረዋል። እድሜያቸው ከ30 አመት በላይ የሆኑ ሴቶች ምርመራውን እና ህክምናውን በነፃ በጤና ተቋማት ማግኘት እንደሚችሉ ጥሪ አስተላልፈዋል። ‎ ‎እየተካሄደ ባለው የባለድርሻ አካለት የውይይት መድረክ (Advocacy workshop) ላይ ከወረዳ ጤና ጽ/ቤት ተወካዮች፣ የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት ተወካዮች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የሃገር ሽማግሌዎች፣ ወጣቶች፣ የሆስፒታል ባለሙያዎች እንዲሁም የዞኑ ጤና መምሪያ ማናጅመንት አባላትና ከፍተኛ ባለሙያዎች ተገኝተውበታል።

Day three Mirab abaya HPV Report-3.xlsx0.12 KB

Day_3_HPV_Report_chencha_zuriya_woredaForm_sene_2018_EFY_Copy.xlsx0.11 KB

Day_2_HPV_Report_chencha_zuriya_woredaForm_sene_2018_EFY_Copy.xlsx0.11 KB