የሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ መዝሙሮች
Открыть в Telegram
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን ሥርዓት እና ደንብን የጠበቁ ዝማኔዎች እና መንፈሳዊ ትምህርቶች የሚተላለፉበት መንፈሳዊ ቻናል ነው
Больше4 690
Подписчики
+224 часа
-127 дней
-3230 день
Архив постов
Repost from N/a
📢በአዳማ ለምትገኙ ለጻድቁ ወዳጆች እና ለኦርቶዶክሳውያን ወጣቶች !
👉ወደ እግዚአብሔር መንግስት የምታገባ የመንግስተ ሰማያት ወንጌል እነሆ ተባላችኋል።
ሰኔ 24 በዕለተ ዕረቡ እና ሰኔ 25 በዕለተ ሐሙስ በዳግማዊው ደብረ ሊባኖስ በአዳማ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተክርስቲያን አውደ ምሕረት ወንጌል እንደ ወንዝ ዥረት ይፈሳል አንደበት ሁሉ ለምስጋና ይከፈታል።
የጭንቃችን ደራሽ የሕይወታችን አምላጅ ጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖትን ጧፍ እያበራን እናስባቸዋለን በብዙ በረከት በምልጃቸው እንባረከለን።
👉መቅረት አይደለም ማረፈድ ያስቆጫል።
ዕረቡ እና ሐሙስ ከ10:-30 እስከ1:-30 መልእክቱን ሼር በማድረግ ለሁሉም ኦርቶዶክሳውያን እናድርስ !
አምላክ ለጉባኤው በሰላም ያደርሰን ዘንድ ሁላችን ስለ
ሁሉንም የሚዲያ አማራጮቻችንን ሰብስክራይብ ፎሎ በማድረግ ለመንፈሳዊ እና ፈጣን መረጃ ቤተሰብ ይሁኑ! ለወዳጅዎም ያጋሩ
የዩቱብ ገጻችንን ለማግኘት👇https://www.youtube.com/@MediaZdebreAmin
የቲክቶክ ገጻችንን ለማግኘት👇https://www.tiktok.com/@mediazdebreamin?_r=1&_t=ZS-97ZErsj8fMC
የፌስቡክ ገጻችንን ለማግኘት👇https://www.facebook.com/share/1CqPayGume/
የቴሌግራም ገጻችንን ለማግኘት👇https://t.me/mediazdebreamin
Repost from N/a
የቲክቶክ አካውንታችንን አቅም እንዲኖረው ሪፖስት ኮፒሊንክ በማድረግ ለሁሉም አዲደርስ አድርጉልን
https://vt.tiktok.com/ZSCyXxj81/
ሁሉንም የሚዲያ አማራጮቻችንን ሰብስክራይብ ፎሎ በማድረግ ለመንፈሳዊ እና ፈጣን መረጃ ቤተሰብ ይሁኑ! ለወዳጅዎም ያጋሩ
የዩቱብ ገጻችንን ለማግኘት👇https://www.youtube.com/@MediaZdebreAmin
የቲክቶክ ገጻችንን ለማግኘት👇https://www.tiktok.com/@mediazdebreamin?_r=1&_t=ZS-97ZErsj8fMC
የፌስቡክ ገጻችንን ለማግኘት👇https://www.facebook.com/share/1CqPayGume/
የቴሌግራም ገጻችንን ለማግኘት👇https://t.me/mediazdebreamin
Repost from N/a
+4
በአስደናቂ ፍጥነት አየተገነባ ያለውን የአዳማ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ሕንጻ ቤተክርስቲያን የደረሰበትን ለመመልከት ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን ቪዲዮዎን ሪፖስት ሼር ኮፒሊንክ በማድረግ ለሁሉም እንዲደርስ አቅም ስጡት!
https://vt.tiktok.com/ZSCUHooqg/
Repost from 🕊¹²[ የዲያቆን ጐሥዓ ቶላ ትምህርቶች ፔጅ ]¹²🕊
+1
⏳ለዘንድሮ ለ12ተኛ ክፍል Entrance ተፈታኞች ብቻ!!!⏳
🗯ዘንድሮ በኮምፒውተር መፈተን አስፈርቷችኋል? የፈተናን ወጥመድ እንዴት አልፋችሁ መስራት እንደሚገባችሁ ዛሬ ማታ 2:30 ላይ ጠብቁ። የምንመለከታቸው ሐሳቦች፦
1ኛ፦የኦንላይን ፈተና የሰዓት አጠቃቀም ስልት!
2ኛ፦የንባብ ስልት ለኦንላይን ፈተና!
3ኛ፦የአሳሳች አማራጮች!
4ኛ፦የማግለል ጥበብ!
5ኛ፦የቁልፍ ቃላት አደን!
👉ይህ የ12 ዓመት ልፋታችሁን ወደ ስኬት የምትቀይሩበት የጥበብ ቁልፍ ነው።⏰የቀጠሮ ሰዓት፦ ዛሬ ማታ exactly 2:30 ላይ! 📍የሚለቀቅበት ቻናል፦ @Be_Gosa1224 ፦ @Be_Gosa1224 ፦ @Be_Gosa1224 👉አሁኑኑ ለጓደኞቻችሁ Share አድርጉና ማታ 2:30 ላይ ስልካችሁ ላይ “Notification” አብርታችሁ ጠብቁ! 👁🗨⚡️ 👉 http://t.me/Be_Gosa1224 👉 http://t.me/Be_Gosa1224 👉 http://t.me/Be_Gosa1224
Repost from 🕊¹²[ የዲያቆን ጐሥዓ ቶላ ትምህርቶች ፔጅ ]¹²🕊
⏳ሰው ከመሆንህ በፊት መምህር አትሁን!!!⏳
✍️ጸሐፊ፦ዲያቆን ጐሥዓ ቶላ!!!
🗯ይህ ቃል የሰው ልጅን የዕውቀት፣ የስልጣንና የመንፈሳዊ መሪነት ተዋረድ በጥልቀት የሚገስጽ፣ በተለይም በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሊቃውንታዊ ሥርዓት ውስጥ እጅግ ትልቅ ቦታ የሚሰጠው የስነ-ምግባር ማኅተም ነው። ሰው ከመሆንህ በፊት መምህር አትሁን ማለት ዕውቀትን ከማስተማርህ በፊት ሰብአዊነትን፣ ትሕትናንና የራስን ማንነት ማወቅ ይቀድማል ማለት ነው። በዚህ እጅግ ወቅታዊና ሥነ-ምግባራዊ በሆነው፣ የዕውቀት መቅደስ ከመረገጡ በፊት የሕይወትና የባሕርይ መታረም እንደሚቀድም በሚያሳስበው ሰው ከመሆንህ በፊት መምህር አትሁን የሚለው ቃል መሠረታዊ ነገር ነው።
🗯ሐዋርያው ቅዱስ ያዕቆብ "ወንድሞቼ ሆይ፥ ከእናንተ ብዙዎቹ አስተማሪዎች አይሁኑ፥ የባሰውን ፍርድ እንድንቀበል ታውቃላችሁና" (ያዕ፦3፥1)እንዳለ፣ መምህርነት ክብር ሳይሆን ከባድ መንፈሳዊ ፍርድና ኃላፊነት ያለበት ስፍራ ነው። መጀመሪያ በትሕትና፣ በታማኝነትና በሰው አክባሪነት "ሰው" ሳትሆንና በፈሪሃ እግዚአብሔር ሳትጸና ወደ መምህርነት መንበር ከተጠጋህ፣ ያ የወጣህበት ማዕረግ ራሱ ለውድቀትህና ለፍርድህ ምክንያት ይሆናል። መምህር ከመሆንህ በፊት እንደ ተማሪ ሆነህ ራስህን መርምር።
🗯በአንደበት መምህር መሆን እጅግ ቀላል ነው፤ መጻሕፍትን ገልጦ ማንበብና ቃላትን ማስተናገድ ማንኛውም ሰው ሊያደርገው ይችላል። ነገር ግን ያ የተናገርከው ቃል በአንተ ሕይወት ውስጥ "ሥጋ" ካልለበሰና ካልተኖረ፣ ትምህርትህ ድምፅ አውጪ እንደሚያናውጠው ናስ እንጂ የሰዎችን ልብ የሚቀይር መንፈሳዊ ኃይል አይኖረውም። መጻሕፍትን መሸምደድ፣ ቃላትን ማስተካከልና በጥልቀት መናገር መምህር አያደርግም። ሰው መሆን ማለት የተማሩትን መኖር መቻል ነው። ራስህን ሳታስተምርና ሳታርም ሌላውን ልገስጽ ማለት፣ የገዛ ቁስልህን ሳታክም ሐኪም ነኝ ብሎ ከመንቀሳቀስ የማይሻል እውርነት ነው።
🗯እውቀት ያለ ግብረ-ገብነት ሰይፍ የያዘ እብድ ማለት ነው። አንድ ሰው በጥበቡና በእውቀቱ የረቀቀ ቢሆንም፣ በሰብአዊነቱ ግን ሰዎችን የሚንቅ፣ በትዕቢት ያበጠ ይቅርታን የማያውቅና ፍቅር የሌለው ከሆነ፣ እርሱ ገና ሰው መሆን አልጀመረም። ራስን ሳይገነቡና ዐሰብአዊነትን ሳይላበስ መምህር ለመሆን መሮጥ፣ በደረቅ አሸዋ ላይ ትልቅ ሕንጻ የመሥራት ያህል አደገኛ ነው። መጀመሪያ ሰብአዊነት በውስጥህ ካልበቀለ፣ የምታስተምረው እውቀት ሰዎችን የሚፈውስ ሳይሆን የሚጎዳና የሚመርዝ ይሆናል። የቤተ ክርስቲያን መሠረቷ መጀመሪያ ግብረ-ገብነትን፣ ከዚያም እውቀትን ማልበስ ነው።
🗯በመጻሕፍት ገጾች ላይ ያሉ ቃላትን መድረክ ላይ መጮኽ መምህርነት አይደለም፤ ያማ በቀቀንም የሚደግመው የድምፅ ምላሽ ነው። እውነተኛ መምህርነት በአንደበቱ ሳይሆን በሥነ-ምግባሩ፣ በጸሎቱና በኑሮው የሚሰብከው ሰውነት ነው። አንተ ሳትለወጥ ሌላውን ልለውጥ ማለት ጨለማ ሆኖ ሳለ ብርሃንን ልስጥ እንደማለት ነው። ስለዚህ መጀመሪያ በፈሪሃ እግዚአብሔር የተገራ፣ ሰብአዊነት የተሞላበት "ሰው" ሁን፤ ያኔ ሳታስተምር ሕይወትህ ራሱ ሺህ ሰዎችን ወደ ቀናው መንገድ የሚመራ ታላቅ ወንጌል ይሆናል።
🗯የቤተ ክርስቲያን ሊቃውንትና ቅዱሳን አባቶች መጀመሪያ ራሳቸውን ለክርስቶስ አስገዝተው "ሰው" ሆኑ፤ ከዚያ በኋላ ግን ሳይናገሩ ሕይወታቸው ራሱ ታላቅ መምህር ሆነ። መምህርነት በወንበርና በማዕረግ የሚገኝ ሥልጣን ሳይሆን፣ በሕይወት ተገኝቶ የሚገለጥ የባሕርይ ፍሬ ነው። ራስህን መለወጥ ሳያቅትህ ሌላውን ለመለወጥ መነሳት፣ የዕውር መሪ መሆን ነው። ለዚህ ነው "ሰው መሆን ይቀድማል" የሚባለው።
🗯ሰው ከመሆን በፊት መምህር ለመሆን መጓጓትና መሮጥ፣ የትዕቢትና የራስ ወዳድነት መገለጫ ከመሆኑም በላይ የምትቀመጥበትን ወንበር የትዕቢት መንበር ያደርገዋል። በትዕቢት የቆመ መምህር ደግሞ የወደቀውን ሊያነሳ አይችልም፣ ምክንያቱም ራሱ ገና አልቆመምና። የቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት ግን ዕድሜ ልካቸውን ተምረው፣ አሁንም እንደ ትንሹ ሕፃን በትሕትና "ሰው ለመሆን" ይጥራሉ። መጀመሪያ ሰውን ማክበር፣ ማዳመጥና ማገዝ የምትችልበት ሰብአዊ ልብ ይኑርህ፤ ያኔ የእግዚአብሔር ጸጋ በላጭ እውቀትንና መንፈሳዊ መሪነትን ጨምሮ ይሰጥሃል።
🗯ሰው ከመሆንህ በፊት መምህር አትሁን የሚለው ቃል በዚህ ዘመን ላሉት አንዳንድ ኖላውያንና መምህራን የተሰጠ ታላቅ መንፈሳዊ ደወልና የሥልጣንና የማዕረግ ሽሚያ የሚገስጽ ሰማያዊ መስተዋት ነው። እውነተኛው መምህርነት ሰዎችን ለመግዛት ወንበር ላይ መቀመጥ ሳይሆን፣ ልክ እንደ ጌታችን ዝቅ ብሎ የሰዎችን እግር ማጠብና ማገልገል ነው። ይህንን የፍቅርና የትሕትና መንፈሳዊ ጠባይ በውስጥህ ሳታሳድግ መምህር ልትሆን አትመኝ።
🗯ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ሠላሳ ዘመን ሙሉ በዝምታ "ሰው ሆኖ" ኖረ እንጂ ወዲያው ማስተማር አልጀመረም። ይህ የሚያሳየው የሕይወት መታረም ከንግግር እንደሚቀድም ነው። እውቀትህና ንግግርህ ሰዎችን ከመማረኩ በፊት፣ ሰብአዊነትህና ክርስቲያናዊ ምግባርህ የሰዎችን ልብ ሊያሳርፍ ይገባል። መጀመሪያ ራስህን በእግዚአብሔር ቃል ቀርጸህ "ሰው" አድርገህ ስማው፤ ያኔ የምታስተምረው እያንዳንዱ ቃል በሰዎች ሕይወት ላይ የብርሃንና የሕይወት ፍሬ ያፈራል። ምላስን ቀድሞ ከማስኬድ ልብን ቀድሞ ማጽዳት እንደሚገባ ይነግረናል። ስለዚህ እውቀትህን በቃላት ከመመጻደቅህ በፊት፣ ሰብአዊነትህንና ክርስቲያናዊ ፍቅርህን በተግባር አሳይ። መጀመሪያ በትሕትና መሬት ላይ ቁም፤ ያኔ ለሰማያዊው ክብር ትበቃለህ። ይቆየን!!!
✍️ ጸሐፊ፦ዲያቆን ጐሥዓ ቶላ!!!
✨ ናዝሬት (አዳማ)፡ ኢትዮጵያ
✨ ሰኔ፦ 22, 2018 ዓ.ም
✨ ጠዋት ከረፋዱ 4፥23 ላይ ተለጠፈ!!!
http://t.me/Be_Gosa1224
http://t.me/Be_Gosa1224
http://t.me/Be_Gosa1224
©🕊¹²[ የዲያቆን ጐሥዓ ቶላ ትምህርቶች ፔጅ]¹²🕊
Repost from N/a
+2
በዛሬው ዕለት ሰኔ 21 2018 ዓ/ም የአዳማ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ-ክርስቲያን ሚዲያ የሆነው ሚዲያ ዘደብረ አሚን(MEDIA ZDEBRE AMIN) በደብራችን አስተዳዳሪ መልአከ ምህረት ቆሞስ አባ ፀሐይ ስመኝ ተባርኮ በይፋ ስራ ጀመረ
ሁሉንም የሚዲያ አማራጮቻችንን ሰብስክራይብ ፎሎ በማድረግ ለመንፈሳዊ እና ፈጣን መረጃ ቤተሰብ ይሁኑ! ለወዳጅዎም ያጋሩ
የዩቱብ ገጻችንን ለማግኘት👇https://www.youtube.com/@MediaZdebreAmin
የቲክቶክ ገጻችንን ለማግኘት👇https://www.tiktok.com/@mediazdebreamin?_r=1&_t=ZS-97ZErsj8fMC
የፌስቡክ ገጻችንን ለማግኘት👇https://www.facebook.com/share/1CqPayGume/
የቴሌግራም ገጻችንን ለማግኘት👇https://t.me/mediazdebreamin
⏳ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ታመሰግንሻለች!!!⏳
✍️ጸሐፊ፦ዲያቆን ጐሥዓ ቶላ!!!
🗯ክርስቶስ በጎኑ ፈሳሽ ያጠመቃትና በገዛ ደሙ ያነጻት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን፤ ወደ ዙፋኑ ስትመለከት ሙሽራዋን ታያለች፣ ወደ ድንግል ማርያም ስትመለከት ደግሞ እናቷን ታያለች። ሙሽራዋ የለበሰው የሥጋ ልብስ የተገኘው ከእናቷ ማኅፀን በመሆኑ፣ ቤተ ክርስቲያን እመቤታችንን የምታመሰግናት በባዕድ አንደበት ሳይሆን፣ በገዛ ልጇ የፍቅር ቃል ነው! ማስተዋል ለተሰጠው ምስጢር እውነታው ይህ ነው። ቤተ ክርስቲያን ለድንግል ማርያም የምታቀርበው ውዳሴ፣ መቅደስ ለመቅደስ የምታደርገው መንፈሳዊ ሰላምታ፣ እናም ትቢያ መለኮትን በወለደች እናት ፊት እጁን በአፉ ላይ ጭኖ በፍርሃትና በሐሤት የሚቆምበት ፍጹም ዕፁብ ድንቅ የምስጢር ጫፍ ነው!.........ሙሉውን ለማንበብ ይጫኑ
Repost from N/a
ይህ ገጽ የአዳማ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ-ክርስቲያን ሚዲያ ነው።
ሁሉንም የሚዲያ አማራጮቻችንን ሰብስክራይብ ፎሎ በማድረግ ለመንፈሳዊ እና ፈጣን መረጃ ቤተሰብ ይሁኑ! ለወዳጅዎም ያጋሩ
የዩቱብ ገጻችንን ለማግኘት👇https://www.youtube.com/@MediaZdebreAmin
የቲክቶክ ገጻችንን ለማግኘት👇https://www.tiktok.com/@mediazdebreamin?_r=1&_t=ZS-97ZErsj8fMC
የፌስቡክ ገጻችንን ለማግኘት👇https://www.facebook.com/share/1CqPayGume/
የቴሌግራም ገጻችንን ለማግኘት👇https://t.me/mediazdebreamin
Repost from 🕊¹²[ የዲያቆን ጐሥዓ ቶላ ትምህርቶች ፔጅ ]¹²🕊
⏳የፈጸምነው የመሰለን ያልፈጸምነው ጉዳይ አለን!!!!⏳
✍️ጸሐፊ፦ዲያቆን ጐሥዓ ቶላ!!!
🗯ወዳጆቼ! ሕይወት ማለት የጀመርነውን የምንጨርስባት መድረክ ሳትሆን፣ የጨረስነው የመሰለንን ነገር ገና እንዳልጀመርነው የምንረዳባት የመንፈሳዊ ብስለት ትምህርት ቤት ናት። ዕውቀት ጨረስን ስንል ድንቁርናችን ይጀምራል፤ ጽድቅን ፈጸምን ስንል ውድቀታችን ይፋጠናል፤ ፍቅርን አወቅን ስንል ራስ ወዳድነታችን ይገለጣል። ስለዚህ ኦክርስቲያናዊ ማስተዋል ማለት ሁልጊዜም ራስን "በመጀመሪያው ምዕራፍ" ላይ አቁሞ፣ በትሕትና ወደ ፊት መዘርጋትና "አምላኬ ሆይ ዛሬስ እውነተኛውን ክርስትና እንድጀምር እርዳኝ" ብሎ መጸለይ ነው።
🗯ይገርማችኋል ብዙዎቻችን ዕድሜያችንን ሙሉ በቤተ ክርስቲያን የኖርን፣ ጾም የጾምን፣ ጸሎት የጸለይንና ክርስትናን ፈጽመን የጨረስን ይመስለናል። ዓለምን የገዛን ሀብትና ዕውቀትን ያከማቸን፣ ስኬትንም ጨብጠን ሕይወትን የኖርናት ይመስለናል። ነገር ግን ነፍስ ከሥጋዋ ተለይታ በእግዚአብሔር ፊት ስትቆም ምድራዊው ስኬት ሁሉ ፈርሶ "ለካስ እውነተኛውንና ዘላለማዊውን ሕይወት ገና አልጀመርኩትም ነበር" በማለት ትገነዘባለች። የፈጸምነው የመሰለን ምድራዊ ኑሮ ቅዠት ሲሆን፣ ያልጀመርነው የመሰለን ሰማያዊ ሕይወት ግን እውነተኛው ማንነታችን ነው።
🗯ሰዎች መጻሕፍትን ስላነበቡ፣ ዶግማና ቀኖናን ስላጠኑ ብቻ እግዚአብሔርን በሚገባ ያወቁትና የደረሱበት ይመስላቸዋል። ነገር ግን እግዚአብሔርን ማወቅ ማለት የሚጨርስ የንባብ ምዕራፍ ሳይሆን፣ ፍጡር ዘልቆ የማይጨርሰው መለኮታዊ ውቅያኖስ ነው። እግዚአብሔርን አውቄዋለሁ ማለት አለማወቅን መጀመር ነው፤ ወድጄዋለሁ ማለትም የፍቅሩን ጥልቀት ገና አለመቅመስ ነው። ያወቅነው የመሰለን መለኮታዊ ጥበብ፣ ገና በፊደል መቆጠሪያው ላይ ያለን ሕፃናት መሆናችንን የምንረዳበት ስውር መስታወት ነው።
🗯ዕድሜያችንን ሙሉ ከንፈራችንን አዝለን የጸለይን፣ ዘወትርም ቅዱስ ቁርባንን የተቀበልን ስለሚመስለን ጸሎትንና ቅድስናን ፈጽመን የጨረስን ይመስለናል። ነገር ግን ልባችን ከምድራዊ ሐሳብ ፍጹም ተለይቶ፣ አዕምሯችንም በመለኮታዊ ፍቅር ተሰርቆ እግዚአብሔርን ብቻ የሚያይበትን እውነተኛውን "የልብ ጸሎት" ገና አልጀመርነውም። በየእሑዱ የምንቀበለው ሥጋውና ደሙ፣ እኛን ወደ ክርስቶስ ባሕርይ ለመለወጥ የመጣ ሰማያዊ እሳት ነው፤ እሳቱን ግን ተቀብለነው እንጂ ገና አልተቃጠልንበትም። የፈጸምነው የመሰለን አምልኮ፣ ገና ወደ ውስጠኛው መቅደስ ለመግባት የበረንዳውን በር መቆርቆር ነው።
🗯በሕይወታችን ማዕበል ሳይነሳ ማዕበሉም መጥቶ በሰላም ሲያልፍ "እግዚአብሔርን አምኜዋለሁ፤ እምነቴንም ፈጽሜያለሁ" ብለን እናስባለን። ነገር ግን እውነተኛ እምነት ገና ያልጀመርነው ምስጢር መሆኑ የሚታወቀው ነገሮች ሁሉ ተዘባርቀው፣ የሚታይ ተስፋ ሁሉ ጠፍቶ፣ እግዚአብሔር ራሱ ፊቱን የሰወረ ሲመስል ነው። በዚያ የጨለማ ምዕራፍ ውስጥ ስንወድቅና ስንናወጥ፣ ለካስ እምነታችን በራሳችን መረጋጋትና በምቾታችን ላይ የተመሠረተ እንደነበር እንረዳለን። የፈጸምነው የመሰለን እምነት፣ ገና ወደ እውነተኛው የእምነት ፈተና ሳንገባ የኖረ የቃላት ድርድር ብቻ ነው።
🗯ከዓለማዊ ኃጢአትና ከክፉ ተግባር ስለራቅን ብቻ ዓለምን የናቅንና ራሳችንን የካድን ይመስለናል። ነገር ግን እውነተኛ ክርስትና ራስን መካድ ማለት ከኃጢአት መራቅ ብቻ ሳይሆን፣ "እኔ" የሚለውን ትዕቢተኛ ማንነታችንን ሰብረን ክርስቶስ በውስጣችን እንዲነግሥ መፍቀድ መሆኑን ያውቃል። ስማችን፣ ክብራችንና መብታችን ሲነካ በቁጣ የምንናወጥ ከሆነ፣ ለካስ ራስን የመካድንና መስቀልን የመሸከምን መንገድ ገና መጀመርያውንም እንዳልጀመርነው ማሳያ ነው። ፈጽመን የጣልናት የመሰለን ዓለም፣ ዛሬም በልባችን ስውር ክፍል ውስጥ በክብር ተቀምጣለች።
🗯ለበደሉን ሰዎች ምላሽ ባለመስጠታችን ወይም ዝም በማለታችን ብቻ ይቅርታን ፈጽመን የጨረስን ይመስለናል። ነገር ግን እውነተኛው ክርስቲያናዊ ይቅርታ ማለት በደልን መርሳት ብቻ ሳይሆን፣ ያንን የበደለህን ሰው ልክ እንደ ራስህ አድርገህ መውደድና ስሙን በጸሎትህ መጥራት መሆኑን ያውቃል። በደሉን ባናነሳውም እንኳን፣ ስሙ ሲነሳ ልባችን ቅር የሚለውና ስኬቱን ስንሰማ ውስጣችን የማይደሰት ከሆነ፣ ለካስ ይቅር የማለትን አምላካዊ ጸጋ ገና መጀመርያውንም እንዳልጀመርነው ማሳያ ነው። የጨረስነው የመሰለን ይቅርታ፣ በልባችን የቆለፍንበት ስውር የበቀል ክፍል ሆኖ ሊገኝ ይችላል።
🗯ታላቁ የገዳም አባት ቅዱስ አርሳንዮስ ዕድሜ ልኩን በጋለ ዕንባና በተጋድሎ የኖረ፣ በዓለም ጥበብም የነገሥታት መምህር የነበረ አባት ነው፤ ነገር ግን ሊያርፍ ሲል "አምላኬ ሆይ! በፊተህ ምንም በጎ ነገር አላደረግኩም፤ ነገር ግን ካንተ ፊት መጀመሪያውን እንድጀምር ማስተዋሉን ስጠኝ" ብሎ አልቅሷል። ቅዱሳን በደረሱበት የቅድስና ማማ ላይ ሆነው "ገና አልጀመርንም" የሚሉት በትሕትና ብቻ ሳይሆን፣ የእግዚአብሔር የቅድስናው ታላቅነት በሄዱ ቁጥር እየራቀና እየሰፋ የሚሄድ ሰማያዊ ምስጢር መሆኑን ስለሚያውቁ ነው። እኛ ግን ጥቂት ጾመንና ጸልየን የደረስን የሚመስለን፣ የነፍሳችንን ዕውርነትና ድንቁርና ገና ስላልተረዳን ነው።
🗯ወዳጆቼ! እውነተኛው ክርስትና በየማለዳው ሲነሳ "አምላኬ ሆይ! እስካሁን ምንም መልካም ነገር አላደረግኩምና ዛሬ በጎ ነገርን ለመሥራት መጀመሪያውን ስጠኝ" እያለ ይጸልያል። ክርስትና ፍጻሜ የሌለው፣ በየቀኑ አዲስ የሚሆን የቅድስና ጉዞ ነው፤ በመሆኑም ፈጽሜዋለሁ የምንለው የትሕትናና የንስሐ ሕይወት ገና ያልጀመርነው ትልቁ ምስጢራችን ነው። ሰነፍ አዕምሮ "ሁሉን ፈጽሜያለሁ" ብሎ በትዕቢት ይተኛል፤ ቅዱሳን አባቶች ግን በዕድሜያቸው ፍጻሜ ላይ እንኳን "ገና አልጀመርኩም" ብለው በንስሐ ይተጋሉ።
🗯ወዳጄ! በሕይወትህ ሁሉን ያደረግህ ቢመስልህም፣ ወደ ልብህ ተመልሰህ ስትመረምር ክርስቶስን የመምሰልን፣ ፍጹም ይቅር የማለትንና የፍቅርን መንገድ ገና መጀመርያውንም እንዳልጀመርከው ታስተውላለህ። ይህንን ማወቅ ራሱ የክርስቲያናዊ ሕይወት ታላቁ ብስራትና የቅድስና መጀመሪያ ነው። ክርስቲያናዊ ሕይወት ያለው ሰው በሕይወቱ የመጨረሻ ሰዓት ላይ እንኳን "እኔ ተጓዥ ነኝ፤ ገና መንገድ አልጀመርኩም" የሚል ፍጹም የትሕትና ማኅተም አለው።
🗯ወዳጄ! ክርስቶስ በመስቀል ላይ "ተፈጸመ" (ያለው የእኛን የመዳን ምስጢርና የዲያብሎስን ሽንፈት ነው፤ ለእኛ ግን ያ ፍጻሜ አዲስ ሕይወት የምንጀምርበት መጀመሪያችን ነው። ስለዚህ "ሁሉን አድርጌያለሁ፣ ሁሉን ፈጽሜያለሁ" ከሚል የሰይጣን የዕረፍት ትዕቢት ወጥተን፣ ዘወትር "አምላኬ ሆይ! ዛሬስ ባሪያህ እውነተኛውን ፍቅርና ቅድስና መኖር እንድጀምር በቸርነትህ ርዳኝ" በማለት በትሕትና ወደ ፊቱ መቅረብ ይገባናል። ወዳጄ የክርስቲያን ታላቅነቱ "መፈጸሙ" ላይ ሳይሆን፣ በየቀኑ በአዲስ ንስሐ ሕይወቱን "መጀመሩ" ላይ ነው። አይመስልህም!??? ይቆየን!!!
✍️ ጸሐፊ፦ዲያቆን ጐሥዓ ቶላ!!!
✨ ናዝሬት (አዳማ)፡ ኢትዮጵያ
✨ ሰኔ፦20, 2018 ዓ.ም
✨ በዕለተ ቀዳሚት ሰንበት (ቅዳሜ) ማለዳ ላይ ተጻፈ!!!
http://t.me/Be_Gosa1224
http://t.me/Be_Gosa1224
http://t.me/Be_Gosa1224
©🕊¹²[ የዲያቆን ጐሥዓ ቶላ ትምህርቶች ፔጅ]¹²🕊
Repost from 🕊¹²[ የዲያቆን ጐሥዓ ቶላ ትምህርቶች ፔጅ ]¹²🕊
⏳ኪዳነ ምሕረት ምስጢረኛዬ!!!!⏳
✍️ጸሐፊ፦ዲያቆን ጐሥዓ ቶላ!!!
🍀እግዚአብሔር ለእናቱ የሰጣት የቅዱስ ኪዳን መሐላ የኃጢአተኞች መሸሸጊያ የዕሩቃን ልብስ፣ የቤት አልባዎች መጠለያ ነው። የኪዳነ ምሕረት ኪዳን በሰማይና በምድር የጸና የእግዚአብሔር መሐላ ነው። እርሷ የፈረሰውን የምታድስ፣ የራቀውን የምታቀርብ የሰላም እናት ናት።
🍀የኪዳነ ምሕረት ስም በተጠራበት ቦታ ሁሉ ሐዘን ይሰደዳል፣ ጭንቀትም ቦታ አይኖረውም። እርሷ መጽናኛችን የሆነችው መከራን ስለምታርቅልን ብቻ ሳይሆን፣ በመከራችን መካከል ሆነን መታገሥ የምንችልበትን ሰማያዊ ጸጋ ከልጇ ዘንድ ስለምታማልድልን ነው። ስለዚህ ኪዳነምሕረትን "ምስጢረኛዬ" የሚላት አዕምሮ፣ በማዕበል መካከል ሆኖ ፍጹም ሰላም ያለውና የማይናወጥ እውነተኛ ክርስቲያን ነው።
🍀ቤታችን ስትሰራ መች ትዘገይና እሷ! ፈጥኖ ደራሽ እኮ ናት። ምድራዊ ሕንጻን ብቻ ሳይሆን፣ በኃጢአትና በሐዘን የፈረሰውን የውስጥ ማንነታችንን በጸጋዋ እንደገና እንደምትሠራው ማመን ነው። ቤት ሲፈርስ ሰሪው ድንጋይና አሸዋ ይፈልጋል፤ የሰው የውስጥ ማንነት በሐዘንና በኃጢአት ሲፈርስ ግን ኪዳነ ምሕረት በጸሎትና በምሕረት ኪዳን ትሠራዋለች። ለዚህ ነው ዘማሪው "አትዘገይም ስትሠሪልኝ ቤቴን" የሚላት። ይህ ቃል የእናታዊ ፍጥነቷ መግለጫ ነው።
🍀ሰዎች ወደ እኛ የሚመጡት ችግራችንን አይተውና ጠይቀውን ነው፤ ኪዳነ ምሕረት ግን የልባችንን ስብራትና በስውር የምናፈስሰውን ዕንባ አይታ ሳይጠይቋት ፈጥና የምትደርስ ድንቅ እናት ናት። በቃና ዘገሊላ የወይን ጠጅ ባለቀባቸው ጊዜ "የወይን ጠጅ እኮ የላቸውም" ብላ ሳይጠይቋት እንደደረሰችላቸውና የጎደለውን እንደሞላች፣ ዛሬም በሕይወታችን ሰላምና ደስታ ሲያልቅብን ፈጥና የምትደርስ፣ የጎደለውን የምትሞላ የቤት ጠባቂያችን ናት። እርሷ የእግዚአብሔር የቸርነቱ ማኅተም ናት።
🍀ሰዎች የውስጣቸውን ምስጢር ለሰው ተናግረው በተከዱና በታመሙ ጊዜ፣ ኦርቶዶክሳዊ አዕምሮ ግን አማላጇን ኪዳነ ምሕረትን ያያል። ለሰው የተናገሩት ምስጢር ሐሜት ሆኖ ይወጣል፤ ለኪዳነ ምሕረት የነገሩት ምስጢር ግን ምሕረት ሆኖ ይወርዳል። የሰው ጆሮ ይሰለቻል፣ የሰው ልብ ይጨክናል፤ የኪዳነ ምሕረት እናታዊ ልብ ግን ዘወትር ክፍት ነው። በሰው ፊት አልቅሶ ከመዋረድ፣ በኪዳነ ምሕረት ፊት አልቅሶ መጽናናት የኦርቶዶክሳዊት ነፍስ ታላቅ ምስጢር ነው። ዓለም ዕንባችንን አይታ ስትፈርጅብን ወይም ስትንቀን፣ ኪዳነ ምሕረት ግን በቅድስት እቅፍዋ አቅፋ ዕንባችንን ወደ ደስታ ትለውጠዋለች።
🍀አልቅሶ መቅለል የሚቻለው፣ ልብን የሚረዳ ስውር አድማጭ ሲገኝ ብቻ ነው፤ እርሷ ደግሞ የነፍሳችን የማይከዳት ብቸኛ ምስጢረኛ ናት። በዕንባችን ውስጥ ሆነን "ምሥጢረኛዬ ነሽ" ስንላትት እርሷም ስውር ስቃያችንን በቸርነቷ ትሸፍነዋለች። የቱንም ያህል በኃጢአት ብንቆሽሽ፣ በሐዘንም ብንሰበር "እናቴ" ብለን ስንጠራት ምስጢራችንን በቸርነቷ ሸፍና፣ በልጇ ደም እንድንታጠብ በንስሐ ወደ መቅደሱ ትመራናለች።
🍀ኪዳነ ምሕረት ማለት የሕመምተኞች ሐኪም፣ የባዕዳን መጠጊያ፣ በጨለማ ውስጥ ላሉት ደግሞ የማይጠፋ የብርሃን ፋኖስ ናት። በኪዳነ ምሕረት ፊት የሚፈስ የዕንባ ጠብታ በከንቱ አይጠፋም፤ እርሷ የሐዘንተኞችን ዕንባ በወርቅ ጽዋ የምትሰበስብ፣ በልጇ ፊትም የምታቀርብ እውነተኛ እናት ናትና። ዓለም ጥላን ስትሄድ፣ የምስጢር ጓደኛ የተባለው ሁሉ ሲከዳን፣ የማይከዳ እናታዊ ልብ ይዛ ከጎናችን የምትቆመው ኪዳነ ምሕረት ናት። ዓለም ስብራታችንን ዐይታ ስትተወን፣ ኪዳነ ምሕረት ግን "ልጄ ሆይ ማርልኝ" በማለት በኪዳኗ ትታደገነች።
🍀በምድር ላይ ማዕበል ሲበዛና የሰው ቃል ሁሉ ባዶ ሆኖ ሲቀር፣ የኪዳነ ምሕረት ስም የነፍስ ማረፊያ ወደብ ይሆናል። እርሷን "ምስጢረኛዬ" ብሎ የጠራት ሰው፣ ከሰማይ በታች ያለውን መከራ ረክሶ ከሰማይ በላይ ያለውን መለኮታዊ ሰላም ይለማመዳል። ልጇ ክርስቶስ ስለ እናቱ ፍቅር ሲል የነፍሳችንን ስብራት ይጠግናል፤ አምላክን የወለደች እናት ለምታለቅስ ነፍስ ሁልጊዜም ቅርብ ናት። አልቅሰን የምንቀለው በፊቷ ስንቆም ብቻ ነው፤ ምክንያቱም ልጇን የታቀፉት እናታዊ እጆቿ ዛሬም የእኛን ስብራት ለማቀፍ የተዘረጉ ናቸውና። በእርሷ ፊት የሚፈስ የዕንባ ጠብታ፣ ነገ በሰማያዊው ኢየሩሳሌም የማይጠወልግ የደስታ አክሊል ሆኖ ይመለሳል።
🍀ወዳጆቼ ሆይ! በሕይወታችሁ ጨለማ ውስጥ ሆናችሁ "መጽናኛዬ" ስትሏት፣ እርሷም በምሕረት ቀሚሷ ትሸፍናችኋለች። ለሰው የተናገሩት ሐሜት በሆነበት ዓለም፣ ለእርሷ የነገሩት ምስጢር ግን ምሕረት ሆኖ ይወርዳል። እርሷ የነፍሳችን የማይከዳት ታማኝ ባልንጀራችን ናትና። ይቆየን!!!
✍️ ጸሐፊ፦ዲያቆን ጐሥዓ ቶላ!!!
✨ ናዝሬት (አዳማ)፡ ኢትዮጵያ
✨ ሰኔ 16, 2018 ዓ.ም
http://t.me/Be_Gosa1224
http://t.me/Be_Gosa1224
http://t.me/Be_Gosa1224
✅❤️የተወለዱበትን ወር በመምረጥ የሚደርሶትን መንፈሳዊ ቻናል በመቀላቀል ዕውቀቶችን ያግኙ
መልካም ዕድል!!!
𝚆𝚊𝚟𝚎 👉 @Beni_tes
https://t.me/addlist/U85kg1EyDQg3YzNk
https://t.me/addlist/U85kg1EyDQg3YzNk
https://t.me/addlist/U85kg1EyDQg3YzNk
Repost from 🕊¹²[ የዲያቆን ጐሥዓ ቶላ ትምህርቶች ፔጅ ]¹²🕊
🚩ሰንበት ክርስቲያን ቅድስት (እሑድ) እና እኛ ክርስቲያኖች!!!🚩
✍️በዲያቆን ጐሥዓ ቶላ!!!
🍀ሰንበተ ክርስቲያን (እሑድ) በሰው ልጅ የዘመን ታሪክ ውስጥ ምድራዊ የሥራ መጀመሪያ ቀን ብቻ ሳትሆን፣ የዓለም መድኃኒት የሆነው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሞትንና የሲኦልን የብረት መዝጊያ ሰብሮ፣ የመቃብሩን ማኅተም ሳይለውጥ በታላቅ መለኮታዊ ኃይልና ሥልጣን ከሙታን ተለይቶ የተነሳባት ፍጹም የብርሃን ማኅተም ናት። እኛ ክርስቲያኖች ይህችን ቅድስት ዕለት በደስታ ስናስብ ተራ ማኅበራዊ ዕረፍትን ብቻ ሳይሆን፣ አምላክ ለሰው ልጅ የሰጠውን የዘላለም ነፃነትና የሕይወት መታደስ የምናይበትን፣ የጨለማው ሥልጣን የተሸነፈበትንና ወደ ሰማያዊው የብርሃን ምንጭ የምንቀርብበትን ምስጢራዊ ጥልቀት የሚያሳይ ሰማያዊ መግለጫ ነው። ይህ ሥርዓት በሰው ዓይን ፊት ከተለመደው የምድር ለቅሶና ፍርሃት ተለይቶ በደስታ የመቆም ሥርዓት ቢመስልም፣ በውስጡ ግን ሕይወት በክርስቶስ ትንሣኤ እውነተኛ ክብርና ዘላለማዊነት እንዳገኘች ሁሉ ፍጻሜዋም በቅድስና ተከብሮ ወደ ሰማያዊው ዙፋን ፊት መቅረብ እንዳለበት የሚያስረዳ ጽኑ ዓለት ነው። ስለዚህ በሰንበተ ክርስቲያንና በሰው ልጅ የዳግም ልደት ሕይወት መካከል ያለውን ያንን ጥልቅ ግንኙነት የሚረዳና የነፍስን ቅድስና ወደ ዘላለማዊ በረከት የሚለውጥ ሰማያዊ አባት ብቻ መሆኑን ማስተዋል እውነተኛ መለኮታዊ እውቀት ነው።
✍️"በሳምንቱም በመጀመሪያው ቀን ማርያም መግደላዊትና ሌላዋ ማርያም መቃብሩን ሊያዩ መጡ። እነሆም፥ የጌታ መልአክ ከሰማይ ስለ ወረደ ታላቅ የምድር መንቀጥቀጥ ሆነ፤ መጥቶም ድንጋዩን አንከባሎ በእርሱ ላይ ተቀመጠ። እርሱ ግን ከሙታን ተነሥቷል።" እንዲል። 📚ማቴ፦28፥1-2🍀በሐዲስ ኪዳን ታሪክ ውስጥ መድኃኒታችን ክርስቶስ በገባው መለኮታዊ የተስፋ ቃል መሠረት፣ በዓለ ሃምሳ በተፈጸመበት በዕለተ እሑድ መንፈስ ቅዱስ በነደደ እሳት አምሳል በቅዱሳን ሐዋርያት ላይ የወረደበትና የክርስቶስ አካል የሆንችው ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በምድር ላይ የተመሠረተችበት ታላቅ ምስጢር ነው። ሰንበተ ክርስቲያንን ማክበር ማለት ተራ በዓልን ጠብቆ መብላትና መጠጣት ሳይሆን፣ ያንን በዕለቱ በጽዮን ማኅደር የተሰጠውን ሰማያዊ የመንፈስ ቅዱስ በረከት ለመቀበል፣ የልብን ቃጠሎ በጸጋ ለማቀዝቀዝ፣ ለዓለማዊ ፈተና ለተጋለጠው ወንድምና እኅት የነፍስን ቅድስና ለማብሰር የሚደረግ ታላቅ ፍቅር ነው። ይህ የሰንበትን ክብር የመጠበቅና የነፍስን ጽዋ በቅዱስ ቃል ማደስ ምስጢር፣ በቅዱሳን አባቶች ሕይወት ውስጥ ከሚታየው የእምነት ታማኝነት ጋር የሚመሳሰል በመሆኑ፣ በምድር ማዕበል ውስጥ የሚሰቃይ ሰው ሁልጊዜ መለኮታዊ መጽናናት ያስፈልገዋል። ሕጉ ምንም ያህል ቢከብድና የሥጋ ምኞት የሰዎችን አንደበት ቢያፍነውም፣ ያንን በሰንበት የተሰጠውን በረከት የሚቆጥርና ወደ ሕይወት ክብር የሚለውጥ መለኮታዊ ጌታ ከጎን እንዳለ ማሰብ ለነፍስ ታላቅ ዕረፍት ነው።
✍️"በዓለ ሃምሳ የተባለውም ቀን በደረሰ ጊዜ፥ ሁላቸው በአንድ ልብ ሆነው በአንድ ስፍራ ነበሩ። እንደ ሚነካካ ጽኑ ነፋስም ከሰማይ ድምፅ መጣ፥ ተቀምጠው የነበሩበትንም ቤት ሁሉ ሞላው። እንደ እሳትም የተከፈሉ ልሳኖች ታዩአቸው።" እንዲል። 📚ሐዋ፦2፥1-3🍀በቤተ ክርስቲያን ቀኖናና በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ሥርዓት መሠረት፣ ሰንበተ ክርስቲያን በሐዲስ ኪዳን ፍጹም የሆነ መለኮታዊ ትርጉም ያገኘችው፣ የዓለም ምእመናን ሁሉ በአንድነት ተሰብስበው የጌታን ሥጋና ደም ለመቀበልና የክርስቶስን ሞትና ትንሣኤ በቅዱስ መሠዊያ ላይ ለማብሰር የተመረጠች ዕለት በመሆኗ ነው። እኛ ክርስቲያኖች ይህችን ዕለት ስናስብ፣ ሐዋርያት በየሳምንቱ በመጀመሪያው ቀን እየተሰበሰቡ መለኮታዊውን ምሥጢር ያከናውኑ እንደነበረ፣ ምጽዋትን ያከማቹ እንደነበረና የክርስቲያናዊ አንድነትን መሠረት ለመመስከር የተሰጠች ታላቅ የዕረፍት መገኛ መሆኗን ነው። ያ በመሠዊያው ፊት ማረፍ ሰውን ለማጥፋት ሳይሆን፣ የኃጢአትን ምድራዊ ሥልጣን ሰብሮ ለማስወገድ፣ የትንሣኤውን ተስፋ በብርሃን ልብስ ለመግለጥና ከአምላክ ዘንድ እውነተኛ የምሕረት ቃልን ለመቀበል የሚደረግ መንፈሳዊ ትግል በመሆኑ የክብር መነሻ ነው። ስለዚህ በቅዱስ ቍርባንና በሰንበተ ክርስቲያን መካከል ያለውን ያንን የዕረፍት ምስጢር ተረድቶ፣ ከመረገም በመራቅና በታላቅ አክብሮት በቅዱስ ሥርዓት መመላለስ እውነተኛ የክርስትና ምግባርና የጽድቅ ፍሬ ነው።
✍️"ከሰባት ቀንም በኋላ በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን እንጀራ ለመቁረስ ተሰብስበን ሳለን፥ ጳውሎስ በማግሥቱ ሊሄድ ስላሰበ ይናገራቸው ነበር፥ እስከ እኩለ ሌሊትም ድረስ ነገሩን አረዘመው። እኛም ተሰብስበን በነበርንበት በሰገነት ብዙ መብራት ነበረ።" እንዲል። 📚ሐዋ፦20፥7-8🍀በሐዲስ ኪዳን ፍጻሜ በቅዱስ ዮሐንስ ራእይ መጽሐፍ ላይ እንደተጻፈው፣ ፍቅር የነበረው ደቀመዝሙር ዮሐንስ በፍጥሞ ደሴት በስደትና በመከራ ውስጥ ሳለ፣ በዕለተ እሑድ (በጌታ ቀን) በመንፈስ ሆኖ የሰማያትን መከፈትና የአዲሱን ዓለም ምስጢር ያየበት ታላቅ ዕለት ነው። እኛ ክርስቲያኖች ሰንበተ ክርስቲያንን ዛሬ በምድር ላይ ስንጠብቃት፣ ይህንን የማይታለፈውንና የማይሻረውን የሰማይ መከፈት እያሰብን፣ ነፍሳችን ከምድራዊው ጥማትና ስቃይ ወጥታ ወደማያልቀው የመለኮት ምስጋና እንድትደርስ ራሷን የምታለማምድበት ታላቅ መንፈሳዊ ትርጉም አለው። ሰንበት ነፍስን የምታነጻ እንደሆነች ሁሉ፣ ያ የቅድስና አምልኮ ደግሞ የውስጥን ማስተዋልና እምነት የሚመሰክር ታላቅ የመንፈስ ቅዱስ ማኅተም በመሆኑ በሰማይም በምድርም ዘንድ ታላቅ የክብር አክሊልን ያጎናጽፋል። ወዳጄ! በምድር ሕይወትህ ላይ የምታከብራትን ሰንበት፣ የሰማያዊው ሕይወትህ መተኪያና የውስጥ ማንነትህ መባያ አድርገህ በቅድስናና በንጽሕና ልታስባት ይገባል።
✍️"በጌታ ቀን በመንፈስ ነበርሁ፥ በስተ ኃላዬም እንደ መለከት ድምፅ ታላቅ ድምፅ ሰማሁ፥ የሚታየውንም በመጽሐፍ ጽፈህ ወደ ሰባቱ አብያተ ክርስቲያናት ስደድ አለኝ። ዘወርም አልሁ የሰው ልጅ የሚመስለውን አየሁት።" እንዲል። 📚ራእይ፦1፥10-12✍️ ጸሐፊ፦ዲያቆን ጐሥዓ ቶላ!!! ✨ ሰኔ 07, 2018 ዓ.ም ✨ ናዝሬት (አዳማ)፡ ኢትዮጵያ ✨ በዕለተ ሰንበት (እሑድ) የተጻፈ!!!
✅❤️የተወለዱበትን ወር በመምረጥ የሚደርሶትን መንፈሳዊ ቻናል በመቀላቀል ዕውቀቶችን ያግኙ
መልካም ዕድል!!!
𝚆𝚊𝚟𝚎 👉 @Beni_tes
https://t.me/addlist/U85kg1EyDQg3YzNk
https://t.me/addlist/U85kg1EyDQg3YzNk
https://t.me/addlist/U85kg1EyDQg3YzNk
Repost from 🕊¹²[ የዲያቆን ጐሥዓ ቶላ ትምህርቶች ፔጅ ]¹²🕊
🚩ፈተና እና ጽናት!!!🚩
🍀ብዙዎች ፈተና ሲመጣ እግዚአብሔር የተዋቸው ወይም የረሳቸው ይመስላቸዋል። እውነታው ግን ፈተና የእግዚአብሔር መረጣ ምልክት ነው። ታላቁ የሃይማኖት አባት ኢዮብን አስብ፤ እርሱ ከፈተናው በፊት ጻድቅ ነበረ፣ ከፈተናው በኋላ ግን ክብሩ እጥፍ ሆኖ ተጨመረ። ፈተና ወደ ላቀ መንፈሳዊ ማዕረግና ክብር መሻገሪያ ድልድይ ነው።
🍀በፈተና ውስጥ ጽናት አስፈላጊ ነው። ጽናት ማለት ዝም ብሎ በግዴታ መከራን መቀበል ማለት አይደለም። ጽናት ማለት በመከራው መካከል ሆነው እግዚአብሔርን አለማማረር፣ ነገሮች ሁሉ በጨለማ በተዋጡበት ጊዜ እንኳን የብርሃኑን መምጣት በተስፋ መጠበቅ፣ እና በክፉ ፈንታ ክፉ አለማድረግ ነው። በፈታኞቻችን ላይ ቁጣን ሳይሆን ምሕረትን ማሳየት መቻል እውነተኛው የጽናት መሠረት ነው።
🍀ይሄንን የመጣብንን ፈተናን የምናሸንፍባቸው መንፈሳዊ መሣሪያዎች አሉ። ከእነዚህም ውስጥ መሠረቶቹ፧
➥ጸሎት፦በፈተና ማዕበል ውስጥ ስንናወጥ ልባችንን ሳይናወጥ የሚያጸና፣ ከፈጣሪ ጋር የሚያገናኝ ታላቅ መልሕቅ ነው።
➥የእግዚአብሔር ቃል፦ በዙሪያችን ጨለማ ሲነግሥና ግራ ሲገባን፣ የትኛውን መንገድ መምረጥ እንዳለብን የሚያሳየን እውነተኛ መብራት ነው።
➥ፍጹም እምነት፦ እግዚአብሔር ታማኝ እንደሆነና ከአቅማችን በላይ እንድንፈተን እንደማይፈቅድልን፣ ከፈተናውም ጋር መውጫውን እንደሚያዘጋጅልን በልብ ማመን ነው።
🍀ወዳጄ! ሁሌም ቢሆን ከፈተና ጀርባ በረከት አለ። መርከበኛ የሚመሰገነው ባሕሩ ፀጥ ባለበት ጊዜ ሳይሆን ማዕበሉን አሸንፎ ወደ ወደቡ ሲደርስ ነው። አንተም በሕይወትህ የሚገጥሙህን ማዕበሎች በጽናት ስትጋፈጣቸው፣ መንፈሳዊ ጡንቻህ ይጠነክራል። ፈተናዎች ሥጋህን ቢያደክሙትም፣ ነፍስህን ግን ያጠሯታል፣ ያለመልሟታል።
↪️ስለዚህ ወዳጄ፤ ፈተና ሲገጥምህ አትደንግጥ፣ አትሸበርም። ይልቁኑ "ይህም ያልፋል፣ ከዚህ በኋላ ግን የጽናት አክሊል አለ" ብለህ ልብህን አበርታ። አንደበታችን ለአማማረር ሳይሆን ለማመስገን፣ ልባችን ለጥርጣሬ ሳይሆን ለጽናት የተፈጠረ ነውና።
✍️ዲያቆን ጐሥዓ ቶላ!!!
http://t.me/Be_Gosa1224
http://t.me/Be_Gosa1224
http://t.me/Be_Gosa1224
Repost from 🕊¹²[ የዲያቆን ጐሥዓ ቶላ ትምህርቶች ፔጅ ]¹²🕊
🚩ቤተ ክርስቲያን ዕለተ ዓርብ ላይ ናት!!!🚩
✍️[ በዲያቆን ጐሥዓ ቶላ ]
🗯ዕለተ ዓርብ የፍጥረት ሁሉ ጌታ በዕንጨት መስቀል ላይ ተሰቅሎ፣ ዓለምን ከጨለማ ግዛት ወደ ብርሃን ማዕረግ ያሻገረባት የታላቅ መስዋዕትነት ዕለት ናት። በዚያች አስፈሪና አስጨናቂ ሰዓት፣ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ሳለ፣ የአንዱ ወታደር ጦር ቅዱስ ጎኑን በወጋው ጊዜ፥ ከጎኑ "ደምና ውሃ" ፈሰሰ። ያ ከጎኑ የፈሰሰው ሕያው ፈሳሽ ተራ ነገር አልነበረም፤ እርሱማ እውነተኛይቱ ሙሽራው ቅድስት ቤተ ክርስቲያን የተወለደችበት መለኮታዊ ማኅፀን ነበር። ልክ የመጀመሪያው አዳም ተኝቶ ሳለ ከጎኑ ሔዋን እንደተገኘች ሁሉ፣ ሁለተኛው አዳም ክርስቶስም በመስቀል ላይ አንቀላፍቶ ሳለ ከጎኑ የጥምቀት ውሃና የቅዱስ ቁርባን ደም ፈስሶ ቤተ ክርስቲያንን ወለዳት። እርሷ በቀራንዮ ኮረብታ ላይ፣ በክርስቶስ ክቡር ደም የተዋጀች፣ በዕንባና በስቃይ መካከል የተመሠረተች የሰማዕታትና የቅዱሳን እናት ናት።
🗯ዛሬ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እና ምዕመናን እየኖሩት ያለው እውነተኛ ሕማምና ሰማዕትነት ነው። ሰዓቱ የጨለመበት፣ ግፈኞች የበረቱበት፣ የታረዱ ቅዱሳን ደም የምድርን ፊት ያጠለቀበት፣ ይህ ዘመን የቀራንዮው ስቅለት ዳግም በምድር ላይ የሚታይበት "የቤተ ክርስቲያን ዕለተ ዓርብ" ነው። ነገር ግን ዛሬ ይህቺ በቀራንዮ የተወለደችው የክርስቶስ ሙሽራ፥ ዛሬም ማቅ ለብሳ በቀራንዮ ጎዳና ላይ ትገኛለች፤ ጌታዋ የለበሰውን የመከራ ግምጃ ለብሳ በግፍ አደባባይ ላይ ቆማለች።
🗯በዕለተ ዓርብ ግፈኞች አይሁድ የክርስቶስን ልብስ ገፈው፣ ተካፈሉበት፣ ዕጣ ተጣጣሉበት፤ እርሱንም ዕራቁቱን አቆሙት። ዛሬም ታቦታቱ ከመንበረ ክብራቸው ተፈንግለው በምድረ በዳ ሲንከራተቱ፣ መቅደሶቿ በእሳት ነበልባል ተለኩሰው አመድ ሲሆኑ፣ የቅዱሳን ሥዕላትና ንዋያተ ቅድሳት ሲፈርሱ ማየት የክርስቶስን አካል ዳግመኛ እንደ መግፈፍና እንደ ማራቆት ነው። ቤተ ክርስቲያን የክርስቶስ አካል ናትና መቅደሷ ሲፈርስ ዛሬም አካሏ እየቆሰለ፣ ልብሷ እየተቀደደ ነው።
🗯የአይሁድ ወታደሮች በዕለተ ዓርብ የክርስቶስን ጀርባ በብረት ጅራፍ ሸነቆጡት። ዛሬ ያ ጅራፍ በምዕመናን ላይ እየዞረ ነው። በየመንገዱና በየቀያቸው በግፍ የሚታረዱ፣ የሚሰቀሉና የሚቃጠሉ ክርስቲያኖች ሥጋ የዕለተ ዓርቡ የክርስቶስ ሥጋ ስብራት ማሳያ ነው። እያንዳንዱ የሰማዕት ዕንባ እና የደምና ውሃ መፍሰስ ከቀራንዮ የምንጭ ውሃ ጋር አንድ ሆኖ ይፈሳል።
🗯ጌታችን የከበደውን መስቀል በትከሻው ላይ ተሸክሞ ወደ ቀራንዮ ኮረብታ ሲወጣ፣ መንገዱ በደም፣ በዕንባና በግርፋት የተሞላ ነበር። ዛሬ ንብረታቸውን ጥለው፣ ሃይማኖታቸውን ባለመካዳቸው ብቻ ከቀያቸው ተፈናቅለው በምድረ በዳ የሚንከራተቱ፣ ስደትን የጀመሩ ክርስቲያኖች ያንን የቀራንዮን የደም ጎዳና በባዶ እግራቸው እየረገጡት ነው። ዛሬ አማንያን የሚቀበሉት ግፍ የዕለተ ዓርቡ የጅራፍ ስቃይና የግርፋት ነበልባል ትውስታ ነው።
🗯በቀራንዮ ስር ዓለም ሁሉ ይሳለቅ፣ ሮማውያንና አይሁድ በድል ስሜት በፌዝና በደስታ ይጩኹ ነበር፤ መስቀሉ ስር ግን ቅድስት ድንግል ማርያምና ወዳጁ ቅዱስ ዮሐንስ ብቻቸውን በሐዘን ተሰብረው፣ በዝምታና በታላቅ ሐዘን ዕንባ ያፈሱ ነበር። ዛሬም የቤተ ክርስቲያን ልጆች በግፍ ሲታረዱና ሲሰደዱ ዓለም ፊቷን አዙራ በዝምታ ስትመለከት ወይም በክፋት ስትሳለቅ፣ ያ በመስቀል ስር የነበረው የብቻኝነትና የሐዘን ጽዋ ዛሬም በቤተ ክርስቲያን እጅ ላይ ይገኛል። የዛሬዋ ቤተ ክርስቲያን እንደ ማርያም አልቅሳ ዕንባዋን ወደ ውስጥ እያጠበች ትገኛለች።
🗯ክርስቶስ በመስቀል ላይ ሆኖ በዘጠኝ ሰዓት "አምላኬ አምላኬ ለምን ተውኸኝ?" (ኤሎሄ ኤሎሄ ላማ ሰበቅታኒ) ብሎ በታላቅ ድምፅ ጮኸ። ይህ ጩኸት የአብ መራቅ ሳይሆን የሰዋዊ ፍጥረት መከራ ጥልቀት የተገለጠበት ነበር። ዛሬም ክርስቲያኖች በየበረሃውና በየአውራ ጎዳናው በግፍ ሲታረዱና የነፍስ ጩኸታቸውን ወደ ሰማይ ሲያረጉ፣ ያ የቀራንዮው የጌታ ጩኸት በልጆቹ አንደበት ዳግመኛ እያስተጋባ ነው።
🗯ወዳጄ ሆይ! አስታውስ ከሰዓታት በኋላ ዕለተ እሑድ አለ! አዎ! አሁን ያለንበት ሰዓት ስድስት ሰዓት ነው፣ ምድር የጨለመችበት፣ ጨለማው በብርሃን ላይ የሰለጠነ የመሰለበት፣ ግፈኞች በዙፋን ላይ የሳቁበት ሰዓት ነው። አሁን ያለንበት ሰዓት ዘጠኝ ሰዓት ነው፣ "ኤሎሄ" ተብሎ የሚጮኽበት የጭንቅ ሰዓት ነው። ነገር ግን የዕለተ ዓርብ የመጨረሻው መቃብር አይደለም! ከዓርብ ጀርባ የማይቀረውና የማይታገደው የእሑድ ጥዋት የትንሣኤ ብርሃን አለ። የፈረሱት መቅደሶች በክብር ይሰራሉ! የተሰደዱት ታቦታት በዝማሬና በዕልልታ ወደ መንበራቸው ይመለሳሉ! በግፍ የፈሰሰው የሰማዕታት ደም ለቤተ ክርስቲያን የድል አክሊል ሆኖ ይበራል!
🗯አንቺ በደምና በውሃ የተወለድሽ፣ ዛሬም በግፈኞች ሰይፍና እሳት እየደማሽ ያለሽ የክርስቶስ እውነተኛይቱ ሙሽራ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሆይ! ፈተናሽ የበረታ፣ መከራሽ የቀራንዮን ያህል የከበደ ቢሆንም በፍጹም አትፍሪ! ክርስቶስ በዕለተ እሑድ ሞትን ድል አድርጎ እንደተነሳ፣ ታቦታቱ ከመንበራቸው ቢወጡም በክብር ይመለሳሉ፤ የፈረሱት መቅደሶችሽ በሰማዕታት ደም ታድሰው ይገነባሉ፤ የተሰደዱት ልጆችሽ በድል አክሊል ይመለሳሉ። በቀራንዮ የፈሰሰው የክርስቶስ ደም የማይጠፋ የዘላለም ሕይወትሽ መሠረት ስለሆነ፣ መከራ ያደማሻል እንጂ አያጠፋሽም!
"በዚችም ዓለት ላይ ቤተ ክርስቲያኔን እሠራታለሁ፥ የገሃነም ደጆችም አይችሏትም።" 📚 ማቴ ፲፮፥፲፰✍️ጸሐፊ፦ዲያቆን ጐሥዓ ቶላ!!! http://t.me/Be_Gosa1224 http://t.me/Be_Gosa1224 http://t.me/Be_Gosa1224
✅❤️የተወለዱበትን ወር በመምረጥ የሚደርሶትን መንፈሳዊ ቻናል በመቀላቀል ዕውቀቶችን ያግኙ
መልካም ዕድል!!!
𝚆𝚊𝚟𝚎 👉 @Beni_tes
https://t.me/addlist/U85kg1EyDQg3YzNk
https://t.me/addlist/U85kg1EyDQg3YzNk
https://t.me/addlist/U85kg1EyDQg3YzNk
Repost from 🕊¹²[ የዲያቆን ጐሥዓ ቶላ ትምህርቶች ፔጅ ]¹²🕊
🚩አርሲ ደም እየተፋች እኛ ግን ኮንሰርት እናዘጋጃለን!!!🚩
✍️ይድረስ አራዳ ነኝ ለሚለው ለዘመኑ ወጣት ከዲያቆን ጐሥዓ ቶላ!!!!
👉አርሲ ዛሬ የደም ወንዝ ሆናለች፤ አፈሯ የንጹሐንን ደም ጠጥታ የጠገበች፤ ሰማይዋ የጭንቀት ጩኸትን ሰብስባ የደፈነች። በየዕለቱ የሰው ልጅ በየመንገዱ፣ በየቤቱ፣ በየጫካው እንደ አውሬ እየታደነ ይታረዳል፤ ነገር ግን በዚሁ መሃል፣ የደም ጠረን በሚያጠግበው አየር ላይ፣ የሙዚቃና የዳንስ ድምፅ ይሰማል። ይሄ ነው ታላቁ መቅሰፍት!🔥ወዳጄ ሆይ፣ በአንገትህ ላይ ያሰርከው ያ ማኅተብ የክርስቶስን ስቅለት የሚያስታውስ እንጂ የክብር ሰንሰለት ብቻ አይደለም። ዛሬ በአንገትህ ማኅተብ ተቸንክሮ እያለ፣ ወንድምህ ደም እየተፋ፣ እናትህ በጎራዴ ስትገደል አንተ ግን በኮንሰርት መድረክ ላይ ትዘፍናለህን? ይህ እኮ ከይሁዳ መሳም የከፋ ነው። ታቦት ከመንበሩ ወጥቶ ወደ ስደት ሲሄድ፣ አባቶችህ በልቅሶ አይናቸው ሲጠፋ፣ አንተ የሙዚቃ ዜማ ታስተጋባለህን? የክርስቶስ ማኅተብ በደረትህ ላይ እያለ፣ የሰማዕታት ደም በምድር ላይ እየፈሰሰ፣ አንተ የምድራዊ ደስታ ምርኮኛ ሆነሃል። ይህ የልቦና ክህደት መሆኑን አላስተዋልክምን? 🔥በአርሲ ምድር ቤተ ክርስቲያን ተቃጥላለች፤ ታቦተ ጽዮን ተሸክመው የሚሰደዱት የእምነት አባቶች እግር በለቅሶ አፈር ረጥቧል። ቤተ ክርስቲያን ስትቃጠል፣ የእግዚአብሔር ማደሪያ ስትፈርስ፣ የቅዱሳን አጥንት በየሜዳው ሲበተን የሚደንስ ሰው፣ ከገዳዮች ጋር ይቆጠራል! የሚለውን ቃል ረስተኸው ነውን? አንተ ግን የባዶነትን ትርኢት ትሠራለህን? የቅዱስ ታቦት ስደት አይታይህምን? የቤተ ክርስቲያን አመድ አይሸትህምን? መቅደሱ ሲደፈር፣ ምድሪቱ የምትቀበለው የክርስቲያን ሬሳ እያለ፣ አንተ በድምፅ ማጉያ የምታስተጋባው ድምፅ፣ የሟቾችን ደም በቁስላቸው ላይ የሚረጭ መርዝ መሆኑን አታውቅምን? 🔥የሰው ልጅ “አትግደሉን!” ብሎ መጮኽ መብቱ ነው፤ ነገር ግን ይህንን መብት እንደ ፖለቲካ አጀንዳ መቁጠር የፍትሕ ሞት ነው። በአርሲ ምድር፣ ንጹሐን ሕፃናት በጭካኔ ሲታረዱ፣ እናቶች በጎራዴ ሲቆረጡ፣ ይህን ድምፅ የሚሰማው ያጣው ሕዝብ እያለ፣ ኮንሰርት ማዘጋጀት የደም መጋራት አይሆንምን? ይህ ጥፋት አይደለምን? አትግደሉን ማለት ፖለቲካ ሳይሆን፣ የሰው ልጅ ትንፋሽ ነው። ይህን ትንፋሽ መከልከል፣ የገዳዮቹን እጅ እንደ ማበርታት እንደሚቆጠር አታውቅምን? ዝምታችሁ የደም መዳረሻ መሆኑን አላስተዋላችሁምን? 🔥መጽሐፍ ቅዱስ በኤርምያስ 8፡22 ላይ “በጊልዓድ ዘንድ መድኃኒት የለምን?” ይላል። የሕዝቤ ደም በከንቱ ሲፈስ፣ የፍትሕ ድምፅ በየመድረኩ መስተጋባት ሲገባው፣ ዝምታን መምረጥ የገዳዩን ሰይፍ መሳል አይሆንምን? የፍትሕ መጥፋት የሃይማኖት ተቋማትን በሞራል ይገላል። አባቶች ሆይ፣ መንጋችሁ እንደ በግ ለታረደው ሲሰጥ፣ እናንተ የዝምታን መጋረጃ መቼ ነው የምትገፉት? አርሲ ዛሬ የሬሳ መቁጠሪያ ሆናለች። በየዕለቱ የክርስቲያኖች ደም እንደ ዝናብ ይረግፋል። በምድር ላይ ያለውን አፈር፣ የንጹሐን ደም ተቀብሎት እንደ ጭቃ ተለቅልቋል። ይህንን እያዩ፣ ይህን እያወቁ፣ ልብ ያለው ሰው እንዴት ድግስ ይደግሳል? እንዴትስ ይጨፍራል? የሰማዕታት ደም እየጮኸ፣ የሕፃናት ደም በምድር ላይ እየተንተከተከ፣ መኖር እየፈለጉ በጭካኔ የሞቱትን ወገኖች የዘነጋ፣ የሰውነት ጠባይ አጥቷል። ይህ መቅሰፍት በላያችሁ ላይ እንደሚወርድ አላስተዋላችሁምን? 🔥ሕፃናት በአርሲ ምድር መጫወት፣ መማር፣ ማደግ ሲገባቸው፣ የጎራዴ ሹልነትንና የጥይት ድምፅን እየለመዱ ነው። አቤቱ፣ ጌታ ሆይ! እነዚህ ንጹሐን ምን በደሉ? እያደጉ ያሉት በደም ማዕበል ውስጥ ነው። ወጣቱ ግን ለዚህ ሁሉ ኀዘን መፍትሔ ከመፈለግ ይልቅ፣ በኮንሰርት አደንዛዥ ዕፅ ይደሰታል። ይህ ትውልድ፣ የገዛ ወገኑን ደም ረግጦ የደስታ መድረክ መገንባቱ፣ ከወደቀው የሰው ዘር ሁሉ የባሰ ነው። ነቢዩ "የዓይኔ እንባ እንደ ምንጭ ይፍሰስ” ብሎ ሲጮኽ፣ የሕዝቡን መከራ አይቶ ነበር። ዛሬ በአርሲ የሚታየው መከራ፣ ከኤርምያስ ሰቆቃ በላይ ነው። ሟቾች የቀብር ስነ-ስርዓት የላቸውም፤ የሟቾች ቤተሰቦች የልቅሶ ቦታ የላቸውም፤ ምክንያቱም የሚገደሉበት እና የሚሰደዱበት ነው። ይህ መከራ የፍትሕን ዙፋን ያናውጣል። ፍትሕ የጠፋበት ምድር፣ የገዳዮች መፈንጫ ትሆናለች። 🔥ወዳጄ ሆይ፣ በአንተ እጅ የያዝከው ማይክሮፎን፣ በወንድምህ ደም የተበከለ መሆኑን አስተውል። ስትዘፍን፣ የሟቾችን ደም እያስለቀስክ መሆኑን አስብ፣ ስትጨፍር፣ የሰማዕታትን አጥንት እያስደነገጥክ መሆኑን ተረዳ፣ ይህ የሞራል ውድቀት መሆኑን እወቅ። የክርስቲያንነትህ ማኅተብ በደረትህ ላይ እያለ፣ የሰይጣንን ድግስ መደገስ፣ ከገዳዩ ጋር መተባበር መሆኑን ተረዳ። ተመለስ! ከደም ማጥ ተመለስ! የሟቾች ደም ይጮኻል፣ የሕፃናት ጩኸት አየር ላይ ሰፍሯል፤ አንተ ግን ደንታ ቢስ አትሁን የዕለተ አርብን የክርስቶስን ስቃይ አስብ! 🙏ወዳጄ! የሰው ልጅ ልብ እንደ መቅደስ ነው፤ በውስጡ መኖር ያለበት የጸሎትና የፍትሕ ጩኸት ነው። ነገር ግን፣ የደም መሬት በአርሲ እየተዘረጋ፣ በሬሳ ላይ ኮንሰርት የሚያዘጋጅ ትውልድ፣ የእግዚአብሔርን ቁጣ በገዛ እጁ እየጠራ ነው። “ደም የፈሰሰበት ምድር በጸሎት እንጂ በሙዚቃ አትታደስም!” የፍትሕና የሰላም ባለቤት የሆነው አምላክ፣ የንጹሐንን ደም መቼም አይረሳም። የሰማዕታት ደም፣ የምድር መሠረት እየተንቀጠቀጠ የሚጠይቀው ፍትሕ ነው። እስክትመለሱ፣ እስክትጮኹ፣ እስክትከሱ ድረስ፣ ምድር ሰላም አታገኝም። መድረኩን ለሰማዕታት ደም ክብር ስጡ፣ የልቅሶና የጸሎት ቤት መሆኗን አስታውሱ፤ አለያማ፣ የደም ጩኸቱ በእናንተ ላይ ይበረታል። ➥ብርሃነ ዓለም ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ "የቀረውንም ነገር ሳልቆጥር፥ ዕለት ዕለት የሚከብድብኝ (የሚያሳስበኝ) የአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ አሳብ (ጉዳይ) ነው" ይላል። (2ኛ፦ቆሮ.11፥28) እኛስ? መልሱን ለእናንተ ትቻለው።
👉ዛሬም፣ ነገም ፍትሕን ለተነፈገች ቤተ ክርስቲያን ፍትሕ!http://t.me/Be_Gosa1224 http://t.me/Be_Gosa1224 http://t.me/Be_Gosa1224 ➥[ግንቦት 29/ 09/2018 ዓ.ም] ➥[ዕለተ ቅዳሜ] ➥[ጠዋት 3:15 ተለጠፈ።]
Уже доступно! Исследование Telegram 2025 — ключевые инсайты года 
