1 744
Подписчики
+224 часа
+37 дней
-130 день
Архив постов
በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በ2014 ዓ.ም ለሚከናወኑ ተግባራት/እቅድ ቅንጅታዊ አሰራር ማስፈንና በየተቋማቱ የሚገኙ የሰዉ ኃይልና የቴክኖሎጂ አቅሞችን በጋር መጠቀም ስለሚቻልበት፤ ስለቴ/ሙ/ት/ስ ፣ ስለፈጠራ ስራዎች ፣ ስለቴክኖሎጂ ሽግግርና ስለSTEM እውቀቶች በተግባር ለመፈጸም የሚያስችል ግንዛቤ ማስጨበጥና ምቹ ሁኔታ መፍጠር ስሚቻልበት ከትምህርት ቤቶች ዋና ር/መ/ር ፣ ም/ር/መ/ራን እና አስተባባሪዎች ጋር ስልጠናዊ መድረክ በማዘጋጀት ውይይት አደረገ፡፡ በዚህ መሰረት የ18 ትምህርት ቤት ተወካዮች ተሳታፊ ሆነዋል፤ በመድረኩም አዲሱ የቴ/ሙ/ት/ስ ፖሊሲና ስትራቴጅ ገለጻ የሳቴምሒ ፕሮግራም ድጋፍ የአሰጣጥ ስልትና ጠቀሜታን በማስገንዘብ የ2014 በጀት ዓመት የሳ/ቴ/ም/ሒ ረቂቅ የስምምነት ሰነድ የጋራ እቅድ ገለጻ በማድረግና በማወያየት ስምምነቱን የማጽደቅ ስነ ስርዓት ማካሄድ ተችላል።
"ምቹ የስራ አካባቢን መፍጠር"
በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በ2014 ዓ.ም በጀት አመት የዝግጁነት ምዕራፍ በዕቅድ ተይዞ እየተሰራበት የሚገኘው የስራ አካባቢን ምቹነት የማሻሻል ስራ የቴክኒክና ሞያ እና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ ሀላፊዎችን እንዲሁም የአቻ ኮሌጅ አመራሮችን ማስጎብኘት ተችሏል በጉብኝቱም ላይ የኮሌጁ ዲን ይህ ጅምር ስራ ሰፍቶና ዳብሮ በቀጣይ የኮሌጁን አገልግሎት ለማሻሻል ከሚሰሩ ስራዎች ጋር ጎንለጎን በሁሉም የስራ አካባቢዎች የሚቀጥል እንደሆነ ተናግረዋል።
ጥቅምት 27/2014 ዓ.ም
"የምስጋናና የእውቅና ፕሮግራም"
በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የ2013 ዓ.ም በጀት አመት የምስጋናና እውቅና ፕሮግራም አጠቃላይ የኮሌጁ አሠልጣኝ መምህራንና አስተዳደር ሰራተኞች በተገኙበት በደማቅ ሁኔታ ተካሄደ። በፕሮግራሙም ላይ የቴክኒክና ሞያ እና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ በተለያየ ደረጃ ያሉ ሀላፊዎች የተገኙ ሲሆን ለፈጻሚዎች፣ ክፍሎች እና የስራ ሂደቶች ላስመዘገቡት የተሻለ የስራ አፈጻጸም እና ላበረከቱት አስተዋጽኦ እውቅናና ምስጋና ተበርክቶላቸዋል።
ጥቅምት 27/2014 ዓ.ም
ለኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለመደበኛ ነባር የምሽት ሰልጣኝ ተማሪዎች የተላለፈ ጥሪ።
በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሰራተኞች የ2014 ዓ.ም እቅድ ላይ ተወያዩ።
………………………………………………
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አመራሮች የ2013ዓ.ም አፈፃፀም ሪፖርት እና 2014ዓ.ም እቅድን አስመልክቶ አጠቃላይ የተቋሙን ሰራተኛ ያሳተፈና ሰፋ ያለ መድረክ በማዘጋጀት እንዲወያዩበት አድርገዋል።
በመድረኩ በቀዳሚነት ለተሳታፊዎች የቀረበው የ2013ዓ.ም አፈፃፀም ሲሆን በዚህም የተቋሙ የስራ ሂደቶች በቅደም ተከተል የአፈፃፀም ሪፖርታቸውን ያቀረቡበት ነበር። በመቀጠልም የ2014 ዓ.ም የተቋሙ ዕቅድ በኮሌጁ ዲን እና ምክትል ዲኖች ለተሳታፊዎች የቀረበበት ነበር።
በመጨረሻም ተሳታፊዎች በቀረቡላቸው የአፈፃፀም ሪፖርቶች እና ቀጣይ ሊተገበር በታቀደው ዕቅድ ላይ እንደ ክፍተት ያዩትንና ቢሻሻሉ ያሏቸውን ገምቢ ሀሳቦችን ለቤቱ በማቅረብ በቀጣይ የታቀደው እቅድ መሬት ወርዶ ግቡን እንዲመታ የበኩላቸውን እንደሚወጡ የገለፁበት መድረክ ሆኖ አልፏል።
በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በ2013 በጀት ዓመት የስራ አፈጻጸም ግምገማና የ2014 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ ውይይት አደረገ
በ2013 በጀት ዓመት የስራ አፈጻጸም ግምገማና የ2014 በጀት ዓመት ዕቅድ ዘግጅት ግምገማ ላይ የኮሌጁ ፑል አመራር አባላት የተሳተፉ ሲሆን የተጠናቀቀው በጀት አመት ዕቅድ አፈጻጸምና የ2014 በጀት ዓመት የውጤት ተኮር እና የቴክኖሎጂ ሽግግርና የኢንደስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት አብይ የስራ ሂደቶች ዕቅድ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል፡፡
በውይይት መድረኩ የተገኙት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ በ2013 በጀት ዓመት ስለነበረው የስራ አፈጻጸም ለተሳታፊዎችምስጋናቸውን አቅርበው በ2013 በጀት ዓመት የነበሩ ክፍተቶችን በመለየትና ያጋጠሙ ችግሮችን አጥርቶ በማውጣት ላለንበት የ2014 በጀት ዓመት ችግሮቹን አስወግደንክፍተቶቻችንን በመሙላት በተለይም በKPI (key Performance Indicator ) ላይ በተመላከተው ልክ ውጤትን መሰረት በማድረግ ዕቅዱ መፈጸም እንዳለበት አስገንዝበዋል፡፡
ነጩ ፖሰታ ለነጩ ቤተመንግስት መርሃ-ግብር በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ!
አሸባሪውና የእናት ጡት ነካሹ የህወሀት ጁንታ ቡድን ሀገራችን ኢትዮጵያ ላይ እያደረሰ ያለውን ሰብአዊና ቁሳዊ ውድመት ብሎም የውሸት ፕሮፖጋንዳ የአሜሪካ መንግስትናመላው አለማቀፍ ማህበረሰብ የሽብርተኛውን ቡድን ሴራ ይረዱት ዘንድ የኮሌጁን አመራር ፑል በማስተባበር ስለ አሸባሪው የህወሀት ሴራ ደብዳቤ ላይ በመፈረምና በፖሰታ በማድረግ በዛሬው ዕለት የኮሌጁ ዲን እና ም/ዲኖች በተገኙበት በይፋ ተጀምሯል፡፡
በቀሩት ጥቂት ቀናትም ኮሌጁ መሰል የተለያዩ መርሃ-ግብሮች በማዘጋጀት አጠቃላይ የኮሌጁን ማህበረሰብ ተሳታፊ እንዲሆን በማድረግ ለዚህ ሀገራዊ ጉዳይ ተገቢውን ምላሽ እንደሚሰጥ የኮሌጁ ዲን ገልጸዋል፡፡
ኢትዮጵያዊነት ሁሌም ያሸንፋል!
Уже доступно! Исследование Telegram 2025 — ключевые инсайты года 
