1 743
Подписчики
+224 часа
+37 дней
-130 день
Архив постов
Repost from Ministry of Labor and Skills - Ethiopia
+2
የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ተቋማት መግቢያ የመቁረጫ ነጥብ ይፋ ሆነ
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የ2017 ዓ.ም የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ተቋማት የመግቢያ መቁረጫ ነጥብ በዛሬው እለት ይፋ አድርጓል፡፡
በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ(ደ/ር) የመቁረጫ ነጥቡን አስመልክተው ጋዜጣዊ መግለጻ ሰጥተዋል፡፡
ዶ/ር ተሻለ በመግለጫቸው የሥራ ገበያውን ፍላጎት መሰረት በማድረግ ወደ ቴክኒክና ሙያ ተቋማት መግቢያ ነጥብ እንደሚዘጋጅ ገልጸው በዚህ ዓመትም የ12 ክፍል የማጠቃለያ ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል 526,683 የሚሆኑት ከደረጃ 1 እስከ 5 በመደበኛ ስልጠና ለመሰልጠን ተቋማቱን ይቀላቀላሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ገልጸዋል፡፡
ገበያ ተኮር በሆኑ በአጫጭር ስልጠናዎች ደግሞ ከ3 ሚሊየን በላይ የሚሆኑ ዜጎች በተቋማቱ ስልጠና ለመስጠት ታቅዶ ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል ብለዋል፡፡
ሰልጣኞች በተቋማቱ በቂ ክህሎት ታጥቀው እንዲወጡ በክረምቱ የአሰልጣኞች የአቅም ግንበናታ ስልጠና፣ የማሽነሪዎች ጥገና እና አስፈላጊ የማሰልጠኛ ግብዓቶችን የማሟላት ሥራ ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል፡፡
በሀገሪቱ የሚገኙ የመንግስት እና የግል ማሰልጠኛ ተቋማት ይህንን የመቁረጫ ነጥብ መነሻ አድርገው ሰልጣኞችን መቀበል ይጀምራሉ ብለዋል፡፡
ለማህበራዊ ሳይንስ እና ለተፈጥሮ ሳይንስ የተቀመጡ የመቁረጫ ነጥቦች ዝርዝር ከታች ይመልከቱ
ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር መረጃ ፡
ጥቅምት 11፤ 2017
በድረገጽ፡- http://mols.gov.et/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/MolsFDRE
ቴሌግራም፦ https://t.me/fdre_mols
"የዘንድሮውን የምረቃ ሥነ-ሥርዓት ለየት ከሚያደርጉት አንዱና ዋነኛው ኮሌጃችን በምስራቅ ኢትዮጵያ የመንግስት ተቋም ሆኖ የአለም አቀፍ የጥራት ደረጃ የሆነውን የISO 9001 2015 QUALITY MANAGEMENT SYSTEM እውቅና ያገኘ የመጀመርያው የመንግስት ተቋም በሆነ ማግስት መደርጉ ልዩ ያደርገዋል"
የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ
በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ ስር የሚገኙት የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ እና የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በተለያየ የትምህርትና ስልጠና መስክ ያሰለጠኗቸውን ሰልጣኝ ተማሪዎች በጋራ በደማቁ አስመረቁ።
የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ክቡር ከድር ጁሀር በምረቃ መርኃግብሩ ላይ ተገኝተው ለተመራቂ ሰልጣኝ ተማሪዎች የእንኳን ደስ አላችሁ መልክት ያስተላለፉ ሲሆን ክቡር ከንቲባ በመልዕክታቸው ተመራቂዎች የነገው ህይወታቸውን ለመቀየር መጪው ዘመን ፉክክርና ተወዳዳሪነት የበዛበት በመሆኑ እራሳቸውን በክህሎት፣ በዕውቀትና በቴክኖሎጂ በቴክኒክና ሙያ አብቅተው በተለይ በድሬዳዋ አስተዳደር የተፈጠሩ ዕድሎችን በመጠቀም ለአገሪቷ መጻኢ ሁለንተናዊ ብልጽግና የበኩላቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል፡፡
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው ለተመራቂዎች ባስተላለፉት መልዕክት በ2016 ዓ.ም ስልጠናቸውን ያጠናቀቁ 447 ሴት 234 ወንድ በአጠቃላይ 681 ሰልጣኞች ተመራቂ መሆናቸውን ገልጸው መጪው ጊዜ በርካታ የሰለጠነ የሰው ሀይል የሚፈልግ በመሆኑ ለሀገር ዕድገትና ብልጽግና ተመራቂዎች የሚኖራቸው ሚና የላቀ እንደሚሆንና በተለይ በሥራ ዕድል ፈጠራው አቅጣጫ አቅም እንዲፈጥሩ ቢሮው እንደሚያግዝ ተናግረዋል፡፡
የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ በበኩላቸው ለመጀመሪያ ጊዜ በአዲሱ የትምህርትና ስልጠና ካሪኩለም ሰልጥናችሁ የተመረቃችሁ ከፊታቸው ብዙ ዕድሎች እንደሚጠብቋቸው አስታውሰው በተጨማሪም ኮሌጃችን ብቁና ተወዳዳሪ ዜጎችን ለማፍራት በሚያደርገው ጥረት በርካታ የሪፎርም ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ በመጥቀስ የዘንድሮን የምረቃ ሥነ-ሥርዓት ለየት ከሚያደርጉት መካከል ኮሌጃችን በምስራቅ ኢትዮጵያ የመንግስት ተቋም ሆኖ የመጀመርያው የአለም አቀፍ የጥራት ደረጃ የሆነውን የISO 9001 2015 QUALITY MANAGEMENT SYSTEM እውቅና ያገኘ ተቋም በሆነ ማግስት መደርጉ ልዩ ያደርገዋል ያሉ ሲሆን የዘንድሮ ተመራቂዎችን ጨምሮ ከኮሌጁ በሚሰጣቸው ሰርትፊኬት ላይ የአለም አቀፍ የጥራት ደረጃ ምልክት የሆነው የISO BRAND የሚካተት መሆኑን በማብሰር ይህም ሰልጣኝ ተማሪዎች በሄዱበት ሁሉ ተመራጭ የሚያደርጋቸው አጋጣሚ መሆኑን በመግለፅ ለተመራቂዎች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡
በምረቃ ስነስርዓቱም ላይ የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ክቡር ከድር ጁሀር፣ የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ክብርት ፈቲህያ አደን፣ የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ክቡር ሮቤል ጌታቸው፣ የሥራና ክህሎት ቢሮ ም/ኃላፊ ክብርት ፈጡም ሙስጠፋ፣ የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ሳሊም ኡስማን፣ የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ታደለ አሰፋን ጨምሮ ሌሎች አመራሮችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡
በአጠቃላይ በዛሬው ዕለት የተመረቁ ሰልጣኝ ተማሪዎች የዘንድሮ ምረቃ ስነስርዓት ልዩ የሚያደርገው ጉዳይ በዘርፍ አዲሱ ፖሊሲ መሰረት ስልጠናቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ሰልጣኝ ተማሪዎች የተመረቁበት ሲሆን ከፍተኛ አካዳሚክ ውጤት ያላቸው ሰልጣኝ ተማሪዎች ተሸላሚም ሆነዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ህዝብ ግንኙነት
ጥቅምት 9/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በተለያዩ የሞያ መስኮች ያሰለጠናቸውን ሰልጣኝ ተማሪዎች በነገው ዕለት ቅዳሜ ጥቅምት 9/2017 ዓ.ም በኮንጎ ሜዳ ወጣትቶች አካዳሚ አዳራሽ በደማቅ ሁኔታ የሚያስመርቅ መሆኑን እየገለፅን ኮሌጁ ለተመራቂ ሰልጣኝ ተማሪዎችና ቤተሰቦች እንኳን ደስ አላችሁ ማለት ይወዳል::
🏆እንኳን ደስ አላችሁ እንኳን ደስ አለን🏆
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በISO 9001 2015 QUALITY MANAGEMENT SYSTEM የአሰራር ስርዓቱን ለማሻሻልና እውቅና ለማግኘት ባለፉት ጊዜያት እንደ ተቋም የተለያዩ ስራዎችን እየሰራ እንደነበር የሚታወቅ ሲሆን ላለፉት 10ቀናት ከኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት በተመደበ የኦዲት ባለሙያ የEXTERNAL OR CERTIFICATION AUDIT ሲካሄድ ቆይቶ በዛሬው ዕለትም በተደረገው የCLOSING MEETING ኮሌጃችን የISO 9001 2015 ሰርተፊኬት እውቅና ለማግኘት ብቁ መሆኑንና RECOMMEND መደረጉን በኦዲተሩ በኩል ተረጋግጧል::
ይህ ስኬት በሁሉም የጋራ ጥረትና ድካም የተገኘ በመሆኑ የኮሌጃችን ማህበረሰብ በሙሉ በድጋሚ እንኳን ደስ አለን::🔥🔥🏆🏆🏆
"ሰንደቅ ዓላማችን ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ከፍታ!" በሚል መሪ ቃል የሰንደቅ ዓላማ ቀን ተከበረ፡፡
በዚህም 17ኛውን የብሔራዊ የሰንደቅ አላማ ቀን በዓል የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ እንዲሁም የኮሌጅ አመራሮችና ሰራተኞች ቃለ-መሃላ በመግባት አክብረዋል፡፡
በበዓሉ ማጠናቀቂያ በአንድነት ለሰንደቅ ዓላማ ክብር በሰጠና የብሔራዊ አንድነታችን መገለጫ እንዲሁም የሉአላዊነታችንና የኢትዮጵያ ከፍታ ምልክት መሆኑን በሚያሳይ በኢትዮጵያ ህዝብ መዝሙር የታጀበ የባንዲራ መስቀል ስነ-ሥርዓት ተካሂዷል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ጥቅምት 4/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Abiy Ahmed Ali 🇪🇹
ትናንት አልቋል። ዛሬም እየተገባደደ ነው። ነገ ግን ገና አልተነካም። ነገን ለመጠቀም ታድያ ዛሬ መሥራት አለብን።
ሕዳሴ ግድብ፤ የገበታ ለሀገርና የገበታ ለትውልድ ፕሮጀክቶች፤ መንገዶችና ግድቦች፤ የተቋም ግንባታ ሥራዎች፤ አረንጓዴ ዐሻራና ኢትዮጵያ ታምርት፤ የኮሪደር ልማትና የሌማት ትሩፋት ፤ ዲጂታል ኢትዮጵያ እና የትምህርት ቤት ምገባ፤ ሀገራዊ ምክክርና የሽግግር ፍትሕ፤ ሌሎችም.. ነገን የተሻለ ለማድረግ የምንሠራቸው ናቸው።
የነገው ትውልድ እጅግ የተሻለች ኢትዮጵያን እንደሚረከብ ርግጠኞች ነን። ለነገ ዛሬ እየሠራን ነውና።
Kaleessi dhumeera. Har'is xumuramaa jira. Bor garuu ammayyuu hin tuqamne. Boritti fayyadamuuf garuu har'a hojjechuu qabna.
Hidhi Haaromsaa, piroojektoonni Maaddiin Biyyaafiifi Maaddiin Dhalootaaf, daandiiwwaniifi hidhawwan, hojiileen ijaarsa dhaabbilee, Ashaaraa Magariisaafi Itoophiyaan Haa Hoomishtu, Misoomni Kooriidariifi Maaddii Guutuun, Itoophiyaa Dijitaalofteefi sooruun manneen barnootaa, Mariin Biyyaalessaafi Haqni Cehumsaa, kanbiroonis... bor kan wayyu akka ta'uuf hojiilee hojjennudha.
Dhaloonni borii Itoophiyaa baay'ee wayyitu akka dhaalu kan mirkanaa'edha. Boriif har'a waan hojjetaa jirruuf.
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የህብር ቀንን ምክንያት በማድረግ ዝቅተኛ ግቢ ለሚያገኙ የተቋሙ ሰራተኞች ድጋፍ አደረገ::
በዛሬው እለት ጳጉሜ 4 "ሕብራችን ለሰላማችን" በሚል መሪቃል እየተከበረ ሚገኘውን "የሕብር ቀን" ምክንያት በማድረግ ኮሌጁ ባዘጋጀው የማዕድ ማጋራት መርሃ-ግብር 50 ለሚሆኑና በዝቅተኛ ገቢ ለሚተዳደሩ ሰራተኞች አዲስ ዓመትን የሚያሳልፋበት የማዕድ ማጋራት መርሃግብር ተከናውኗል::
በመርሃ-ግብሩ ላይ በመገኘት ለሰራተኞቹ ለ2017 ዘመን መለወጫ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ያስተላለፉት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ አክለውም ተቋም ሲባል ዋና መገለጫው በውስጡ የሚሰሩትን ሰራተኞች መሆናቸውን ገልፀው ተቋማት ሰው ሰው የሚሸቱና የሰውን ችግር የሚረዱ መሆን እዳለባቸው አቅጣጫ የተቀመጠ መሆኑ በመግለፅ ኮሌጁም በቀጣይ መሰል በዓላት ሲመጡ ብቻ ሳይሆን ሰራተኛውን በዘላቂነት ለመደገፍ የተለያዩ ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝና በቀጥይ የተሻለ ነገር እንደሚኖር በመጠቆም በዕለቱ የዘጋጀውን ማዕድ ከማኔጅመንቱ ጋር በመሆን ለሰራተኞቹ አስረክበዋል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፓሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን
ጳግሜ 4/2016 ዓ.ም
Уже доступно! Исследование Telegram 2025 — ключевые инсайты года 
