ru
Feedback
Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

Открыть в Telegram
1 743
Подписчики
+224 часа
+37 дней
-730 день
Архив постов
photo content

photo content
+9

photo content
+9

#የቴክኒክና_ሙያ_ሳምንት        የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ  ከታህሳስ 18/2015 ዓ.ም ጀምሮ ለአንድ ሳምንት የሚቆየውን የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና የንቅናቄ ሣምንት በዛሬው እለት በደማቅ ሁኔታ አስጀምሯል።         ለአንድ ሳምንት በሚቆየው በዚህ የንቅናቄ መርሀ ግብር ላይ በኮሌጃችን የቴክኖሎጂ ፈጠራ አውደ ርዕይ እና የፓናል ውይይት የሚካሄድም ይሆናል።        እርሶም ለአንድ ሳምንት በሚቆየው የቴክኖሎጂ አውደ ርዕይ  ላይ ተገኝተው  በመጎብኘት ስለ ቴክኒክና ሙያ ዘርፍ የተሻለ ግንዛቤ እንዲጨብጡ ተጋብዘዋል። የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ታህሳስ 18/2015 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+4

photo content
+9

#የምስጋና_እና_የዕውቅና_ፕሮግራም። ………………………………………………………………     የኢትዮ-ጣሊያን ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከህዳር 19-25/03/2015 ዓ.ም ድረስ በሀገር አቀፍ ደረጃ በተዘጋጀው 9ኛው የዓለም አቀፍ የኢንተርፕሩነርሺፕ ሳምንት መድረክ ላይ የድሬዳዋ አስተዳደርን ወክለው የተሳተፉትና በኢትዮ-ጣሊያን ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የተሰሩት የዳቦ ማምረቻ ማሽኖች(ሙሉ ፓኬጅ)  በቴክኖሎጂ ሽግግር ዘርፍ ተወዳድረው አንደኛ ደረጃን ይዘው በማጠናቀቃቸው እንዲሁም የድሬዳዋ አስተዳደር እና የኮሌጁን በትልቅ ደረጃ ያስጠሩ በመሆኑ ቴክኖሎጂዎች ላይ ለተሳተፉትን የኮሌጁን አሰልጣኝ መምህራን የምስጋና እና ዕውቅና ፕሮግራም በዛሬው እለት ተደርጎላቸዋል።         በእውቅና መድረኩም ላይ የኮሌጁ ዲኖች የእንኳን ደስ አለን ንግግር ያደረጉ ሲሆን በመቀጠልም  የቴክኒክና ሙያ ኤጀንሲ ሀላፊ የሆኑት ወይዘሮ ፈጡም ሙስጠፋ ለቴክኖሎጂው ባለቤቶች የእንኳን ደስ አላችሁ መልክታቸውን በማስተላለፍ የተዘጋጀውን የምስጋና ምስክር ወረቀት ከሰጡ በኋላ ለዕለቱ የተዘጋጀውን ኬክ በጋራ ቆርሰዋል። ታህሳስ 06/2015 የኢትዮ-ጣሊያን ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ኮምንኬሽን

photo content
+3

የኢትዮ-ጣሊያን ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አግልግሎት ትግበራ በአካል በመገኘት ድጋፍ ለሚያደርግላቸውን ኢንተርፕራይዞች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሂዷል።      በመድረኩም ተሳታፊ ከነበሩ ኢንተርፕራይዞች በርከት ያሉ ሀሳቦች የተነሱ ሲሆን በቀጣይም የኢንደስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ድጋፉን በተቀላጠፈ ሁኔታና በሚፈለገው ደረጃ ተግባራዊ ለማድረግ የሚያችል ሰፋ ያለ ውይይትም ተደርጎበታል። ህዳር 28/2015 የኢትዮ-ጣሊያን ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ኮምንኬሽን

photo content
+1

photo content
+9

photo content
+9

#ፅዱና_ውብ_የስራ_አካባቢን_መፍጠር          የኢትዮ- ጣሊያን ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሰራተኞች ኮሌጁን ፅዱና ውብ ለማድረግ ባለመውና በየወቅቱ በሚደረገውን የፅዳት ፕሮግራም ላይ የተሳተፉ ሲሆን በቀጣይም የፅዳት ዘመቻው በየወቅቱ  የሚቀጥል ይሆናል። ህዳር 27/2015 የኢትዮ-ጣሊያን ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ኮምንኬሽን

photo content
+7

#እንኳን_ደስ_አለን🏆 የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የድሬዳዋ አስተዳደርን በመወከል የተሳተፈበትን የቴክኖሎጂ ፈጠራ ውድድር አንደኛ በመውጣት በአሸናፊነት አጠናቋል። ……………………………………………………………… ለአንድ ሳምንት በተለያዩ ሥነ-ሥርዓቶች ሲካሄድ የቆየው #9ኛው_አለም_አቀፍ_የኢንተርፕረነርሺፕ_ሳምንት_በኢትዮጵያ በዛሬው እለት ፍፃሜውን ያገኘ ሲሆን በሳምንቱ የተለያየ የፈጠራ ሀሳብ ባላቸውና ከተለያዩ አካባቢዎች በተገኙ ቴክኖሎጂ ፈጣሪዎች መካከል በተደረገ ውድድር የድሬዳዋ አስተዳደርን በመወከል የተሳተፈውና በስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ስር የሚገኘው #የኢትዮ_ጣሊያን_ፖሊ_ቴክኒክ_ኮሌጅ በሀገር አቀፍ ደረጃ የተደረገውን ውድድር አንደኛ በመውጣት ውድድሩን በአሸናፊነት አጠናቆ በድል ተመልሷል። በውድድሩ አሸናፊ ለሆኑትና ቴክኖሎጂ ላይ ለተሳተፉ መምህራን 2መቶ ስልሳ ሺህ ብር ሽልማት የተበረከተላቸው ሲሆን እንኳን ደስ አላችሁ እንኳን ደስ አለን እያልን… በዚህ ስራ ውጤት ላስመዘገቡ የኮሌጁ አሰልጣኝ መምህር ዘሪሁን ነጋሽ፣ሲሳይ ምንዳ፣አበበ ተረፈ፣ስንታየው ቀጭኔ፣ጎሳዬ አዳነ ፣ ብሩክ አንለይ እና ለአስተባበራችሁ ድጋፍ ላረጋችሁ ሁሉ ኮሌጁን ለዚህ ውጤት ስላበቃችሁ በኮሌጁ ስም እናመሰግናለን።