ru
Feedback
Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

Открыть в Telegram
1 743
Подписчики
+224 часа
+37 дней
-730 день
Архив постов
ADRA ኢትዮጵያ(ድሬዳዋ) ከፕሮጀክቱ ጅማሮ እስከ አሁን የተጏዘበትን ውጤታማ የአፈፃፀም ልምድ በተለያዩ ክልሎች ፕሮጀክቱን ለሚያስተገብሩ አስተባባሪዎች የልምድ ልውውጥ መድረክ አካሄደ:: ADRA ኢትዮጵያ ፕሮጀክት ከኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ጋር በመተባበር ባለፉት አመታት በ Solar PV Installation Maintenance ስልጠና 120 ወጣቶችን አሰልጥኖ ወደ ስራ እንዲገቡ ከማድረግ አኳያ ኘሮጀክቱ ከሚተገበርባቸው ከያትኛውም አካባቢዎች የተሻለ ውጤታማ አፈፃፀም የተመዘገበበት እንደሆነም ተገልፇል:: በዛሬው እለት ከADRA ኢትዮጵያ(ድሬዳዋ) ጋር ልምድ ልውውጥ ለማድረግ ከተለያዩ የአገሪቱ ክፍል የመጡት የፕሮጀክቱ ቅርንጫፎች(ከአርባምንጭ፣ ከአፋር፣ ከወልቂጤ) የተገኙ ሲሆን ፕሮጀክቱ ከኮሌጁ ጋር በመተባበር ያከናወናቸውን ዘርፈ ብዙ ተግባራት ተዘዋውረው ተመልክተዋል:: የልምድ ልውውጡ ዋና አላማ በADRA ኢትዮጵያ በምስራቁ ክፍል ድሬዳዋ ላይ በፕሮጀክቱ አፈፃፀም የተፈጠረውን ትልቅ አቅምና ልምድ ወደተቀሩት አካባቢዎችም ማስተላለፍ እንዲቻል የመማማሪያ ሁኔታን ለመፍጠር ያለመ መሆኑም በመድረኩ ተገልፇል:: የADRA ፕሮጀክት ከኮሌጁ ጋር በመተባበር ከጅምሩ አንስቶ የመጣበትን መንገድና የተሰሩ ውጤታማ ተግባራትን በዝርዝር የሚያመላክት ገለፃ በፕሮጀክቱ አስተባባሪ አቶ ሀብታሙ በየነ አማካኝነት ለመድረኩ ተሳታፊዎች የቀረበ ሲሆን ለልምድ ልውውጡ በኮሌጁ የተገኙ ተሳታፊዎችም በየአካባቢያቸው ያከናወኗቸውንና ተመኩሮ ሊሆኑ የሚችሉ ተግባራትን እቅርበው የምክክር መድረክም ተካሂዷል:: የADRA ፕሮጀክት በአስተዳደሩ የሚገኙ ወጣቶችን ተጠቃሚ ማድረግ የቻለ ትግበራ ማከናወኑ የተገለፀ ሲሆን ለዚህም ኮሌጁን ጨምሮ በአስተዳደሩ በተለያየ ደረጃ የሚገኙ ባለድርሻ አካላት ጉዳዩን በባለቤትነት በመያዝ ተገቢውን ድጋፍ በማድረጋቸው ጭምር የተመዘገበ ውጤት መሆኑም በመድረኩ ተገልፇል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ሐምሌ 11/2017 ዓ.ም

photo content
+9

photo content
+9

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በEASE ፕሮጀክት አማካኝነት ኢንድርስትሪው ላይ ለሚገኙ ባለሙያዎች ሲሰጥ የነበረው የክህሎት ስልጠና ተጠቀቀ:: በኮሌጁ ለ15 ቀናት ኢንዱስትሪዎች ላይ በተለየው የክህሎት ክፍተት መሰረት ሲሰጥ የቆየው ስልጠና መጠናቀቁን ተከትሎ የኮሌጁ ማኔጅመንት አባላት በተገኙበት የስልጠናው አጠቃላይ ሂደት የሚያመላክት የሪፖርት መድረክ ተካሂዷል:: በEASE ፕሮጀክቱ አማካኝነት ከዚህ ቀደም በኮሌጁ ከተለመደው የክህሎት ክፍተት ስልጠና አሰጣት በተለየ ሁኔታ የክህሎት ስልጠናው ውጤታማ እንዲሆን በማቀድ ኢንዱስትሪዎች ላይ የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት ተደርጎ ወደ ትግበራ መገባቱን ያስታወሰሱት የኮሌጁ የቴ/ሽ/ኢ/ኤ አገልግሎት ዋና ስራ ሂደት ም/ዲን አቶ ተሾመ ሸዋዬ ሲሆኑ አክለውም በተለየው ፍላጎት መሰረትም በመጀመሪያ ዙር ትግበራ በሁለት አምራች ኢንዱስትሪዎች ላይ ለሚገኙ ባለሙያዎች በተመረጡ የሙያ ዘርፎች የክህሎት ስልጠናው መስጠት መቻሉንም ገልፀዋል:: የክህሎት ስልጠናውን በማሰልጠንም ሆነ በማስተባበር የተሳፉትን አካላት ማመስገን ያስፈልጋል ያሉት የፕሮጀክቱ አስተባባሪ ኢንጂነር ፋሲል ማዘንጊያ ሲሆኑ አክለውም ይህ ስልጠና ኮሌጁ በፕሮጀክቱ አማካኝነት ኢንዱስትሪዎች ላይ ከሚሰራቸው ተግባራት መካከል አንዱ መሆኑን ገልፀው የክህሎት ስልጠናው እንደ ጅማሮ ጥሩ አፈፃፀም ያገኘንበትና በቀጣይ በሌሎች የሙያ ዘርፎች ኢንዱስትሪዎች ላይ ለምንሰጠው የክህሎት ስልጠና ምርጥ ተሞክሮ የተገኘበትም ነበር ብለዋል:: የክህሎት ስልጠናው ከጅምሩ እስከ ፍፃሜው የነበረውን አጠቃላይ ሂደት ዝርዝር ሪፖርት የኢንዱርስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ክፍል ተጠሪ በሆኑት አቶ አቤል ዘገየ አማኝነት ለመድረኩ የቀረበ ሲሆን በቀረበው ሪፖርትም የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት ከማካሄድ ጀምሮ የማሰልጠኛ ሞጁል በማዘጋጀት ከኢንዱስትሪዎች ለተወጣጡ ሰራተኞች በኮሌጁ ወርክሾፖች የክህሎት ስልጠናው መሰጠቱ የተገለፀ ሲሆን እንዲሁም በስልጠናው ሂደት የተገኙ መልካም አጋጣሚዎችና የተሰተዋሉ ክፍተቶችም በሪፖርቱ ተካተው ቀርበዋል:: የክህሎት ስልጠናው በአስተዳደሩ በሚገኙ የConel Industrial P.l.c እና የFerida Plastic Recycling በተሰኙ አምራች ድኢንዱስትሪዎች ውስጥ ለሚገኙ 58 ባለሙያዎች በHydraulics,Pneumatic በmachining እና በWelding የሙያ መስኮች የክህሎት ስልጠና የተሰጣቸው ሲሆን በተጨማሪም በLeadership እንዲሁም በOccupational Safety and Health (OSH) ስልጠናዎችን በመስጠት ባለሙያዎቹን ማብቃት መቻሉም ተገልፇል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ሐምሌ 10/2017 ዓ.ም

የውጭ ሃገር የሥራ ዕድል... በሥራና ክህሎት ሚንስቴር የውጪ ሃገር ሥራ ስምሪት በሰለጠነ እና በከፊል የሰለጠነ የሰው ሃይል የዜጎችን መብት፣ ደህንነት እና ጥቅም አስጠብቆ በማሰማራት ትልቅ ስኬት መመዝገቡ ይታወቃል። አሁንም ህጋዊ የውጪ ሃገር ሥራ ስምሪት በሰለጠነ የሰው ሃይል በተለያዩ የሞያ ዘርፎች በቁጥር ከፍተኛ የሆነ የሰው ሃይል ይፈለጋል። በመሆኑም ከዚህ በታች በተዘረዘሩት የሞያ ዘርፎች መሰማራት የምትፈልጉ በሙሉ ከታች በተቀመጠው ሊንክ በመግባት ፎርሙን ሞልታችሁ የእድሉ ተጠቃሚ እንድትሆኑ ስንል እናሳውቃለን። Driving & Transportation 1. Light Vehicle Driver 2. Heavy Vehicle Driver (e.g., Grader Operator) 3. House Driver 4. Trolley Operator Security & Safety 5. Security Guard 6. CCTV Surveillance Operator 7. Office Security Personnel 8. Plumber 9. Electrician 10. HVAC Technician 11. AC Technician 12. Pumper Domestic & Facility Services 13. Housekeeper 14. House Maid 15. House Cleaner 16. Housekeeping Supervisor 17. Houseman 18. Caretaker 19. Steward 20. Laundry Attendant 21. Bellman Hospitality & Food Services 22. Receptionist 23. Waiter/Waitress 24. Barista 25. Sous Chef 26. Pastry Chef / Dessert Chef 27. Garde Manger Chef 28. Arabica Cuisine Chef 29. Kitchen Assistant 30. Private Cook 31. Room Attendant 32. Hotel Assistant Manager Healthcare & Caregiving 33. Nurse 34. Junior Nurse 35. Home Care Nurse 36. Private Nurse 37. Junior Midwife / Clinical Nurse 38. Elderly Care Assistant 39. Live-in Support Assistant 40. Neonatal Intensive Care Unit (NICU) Nurse 41. Junior Physiotherapist Childcare Services 42. Babysitter 43. Childcare Worker Beauty & Salon Services 44. Hairdresser 45. Hairstylist 46. Beauty Therapist 47. Salon Manager 48. Nail Technician 49. Nail Art Instructor 50. Massage Therapist 51. Makeup Artist Agriculture & Farming 52. Indoor Farmer 53. General Farm Worker Administrative & Marketing 54. Junior Administrative Assistant 55. Junior Marketing Assistant 56. Junior Account Manager 57. Sales Representative 58. Purchaser Skilled Labor 59. Construction Worker 60. Laborer 61. Tailor 62. Storekeeper 63. Supervisor Retail & Customer Services 64. Cashier 65. Promoter https://forms.gle/TF5BcYBtrhwkyjR59 መልካም ዕድል! የሥራ ባለቤት እርስዎ ነዎት!

photo content
+9

photo content
+9

በኮሌጁ ባለፉት ሳምንታት በትምህርትና ስልጠና ክፍሎች ላይ ሲካሄድ የቆየው ምልከታ ተጠናቀቀ:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ማኔጅመንት በኮሌጁ የሚገኙ የትምህርትና ስልጠና ክፍሎች ላይ የአፈፃፀም ትግበራን በተመለከተ ሲያካሂድ የቆየውን የግምገማ መድረክ በዛሬው እለት አጠናቋል:: በምልከታ መርሃ-ግብሩ መሰረት የተቀሩ ዲፓርትመንቶችን (ማኑፋክቸሪንግ ፣ኮንስትራክሽን፣ድራፍቲንግና ሰርቬይ እንዲሁም የሆቴልና ቱሪዝም) ዲፓርትመንቶችን የአፈፃፀም ሪፖርት የተመለከተ ሲሆን በዚህም የትምህርትና ስልጠና ክፍሎቹ በ2017 ዓ.ም የትምህርትና ስልጠና ዘመን ከተቀመጠው ግብ አንፃር ያከናወኗቸውን ዝርዝር ተግባራት መመልከትም ተችሏል:: የኮሌጁ ማኔጅመንት ከትምህርትና ስልጠና ክፍሎች በተጨማሪም የኮሌጁን የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን እና ቴክኖሎጂ ሽግግር ስራ ሂደትን አመታዊ ሪፖርት ተገኝቶ የተመለከተ ሲሆን በዚህም በበጀት አመቱ የተሰሩ ችግር ፈቺ ቴክኖሎጂዎች እንዲሁም በኢንተርፕራይዞችና ኢንዱስትሪዎች ላይ የተከናወኑ ውጤታማ ተግባራትን ተመልክተዋል:: ምልከታ በተካሄደባቸው ክፍሎች የቀረቡት የአፈፃፀም ሪፖርቶችን መነሻ በማድረግም በማኔጅመንት አባላት ግብረ መልሶች የተሰጡ ሲሆን በተጨማሪም በኮሌጁ ዲን የቀጣይ የስራ አቅጣጫ ለትምህርትና ስልጠና ክፍሎቹ በመስጠት የምልከታ መድረኩ ተጠናቋል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ሐምሌ 4/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

የኮሌጁ ማኔጅመንት በትምህርትና ስልጠና ክፍሎችና ስራ ሂደቶች ላይ እያካሄደ የሚገኘው የምልከታ መድረክ መካሄዱን ቀጥሏል:: ሰኔ 14/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ማኔጅመንት በኮሌጁ የሚገኙ የትምህርትና ስልጠና ክፍሎች የስልጠና አሰጣጥ ትግበራን በተመለከተ እያካሄደ የሚገኘው የግምገማ መድረክ በዚህ ሳምንትም ቀጥሎ ተካሂዷል:: የምልከታ ቡድኑ በተዘጋጀው መርሃ-ግብር መሰረት በዚህ ሳምንት የኤሌክትሪካል/ኤሌክትሮኒክስ ዲፓርትመንት እና የቢዝነስ ዲፓርትመትን የተመለከተ ሲሆን በዚህም የትምህርትና ስልጠና ክፍሎቹ በ2017 ዓ.ም የስልጠና ዘመን ከተቀመጠው ግብ አንፃር ያከናወኗቸውን ዝርዝር ተግባራት መመልከትም ተችሏል:: የቀረቡት የአፈፃፀም ሪፖርቶችን መነሻ በማድረግም በምልከታ ቡድኑ ሀሳብ አስተያየት የተሰጠባቸው ሲሆን ጥሩ አፈፃፀም በታየባቸው ጉዳዮች ላይ አውቅናን በመስጠት እንዲሁም ዝቅተኛ እፈፃፀም በተስተዋለባቸው ጉዳዮች ላይም ዲፓርትመንቶቹ በቀጣይ ትኩረት ሰጠተው እንዲሰሩ ግብረ-መልስ ተስጥቷል:: በትምህርትና ስልጠና ክፍሎች የሚካሄደው ይህ የግምገማ መድረክ በቀጣይም በተቀረሩት ዲፓርትመንቶች ላይ በተቀመጠው መርሃ-ግብር መሰረት የሚቀጥልም ይሆናል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ

በኮሌጁ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር አገልግሎት ዋና ስራ ሂደት የበጀት አመቱን የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርት መድረክ ማካሄድ ጀመረ:: ሰኔ 20/2017ዓ.ም ድሬዳዋ በእለቱ በነበረው መርሀ-ግብር በዋና ስራ ሂደቱ የሚገኙ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ድጋፍ የወረዳ ተጠሪዎች እና በሂደቱ የጥናት፣ቴክኖሎጂ ሽግግር ስር የሚገኙ ባለሙያዎችን የአፈፃፀም ሪፖርት መመልከት ተችሏል:: በመድረኩም በ2017 በጀት ዓመት በዋና ስራ ሂደቱ ይከናወናሉ ተብለው በእቅድ ከተያዙ ተግባራት አንፃር የተሰሩ ስራዎች አፈፃፀምን የተመለከት ሪፖርት በተጠሪዎች ቀርቧል:: በሪፖርት መድረኩ በዋናነት በኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት በአራቱ የድጋፍ ማዕቀፎች ላይ የተከናወኑ ተግባራትን፣ ቴክኖሎጂንዎችን ከማሸጋገር አንፃር የተሰሩ ስራዎችን እንዲሁም በጥናትና ምርምር የተገኙ ውጤቶችን ጨምሮ በኮሌጁ የሚሰጡ ተጨማሪ ተልዕኮዎችን ከመፈፀም አኳያ የተከናወኑ ተገባራትን በዝርዝር የሚዳስስ ሪፖርትም ቀርቦበታል:: በቀረቡት ሪፖርቶች መነሻነትም በመድረኩ ሰፊ ውይይት የተካሄደበት ሲሆን የታዩ ጠንካራ ጎኖችን በይበልጥ አጠናክሮ ለማስቀጠል እንዲሁም ክፍተት በተስተዋለባቸው ጉዳዮች ላይም በቀጣይ በትኩረት መስራት እንደሚገባም ተገልፇል:: የሪፖርት መድረኩ በቀጣይ ቀናትም ቀጥሎ የሚካሄድ ሲሆን ተጨማሪ የተሰሩ ስራዎችን ጨምሮ የዋና ሂደቱን አጠቃላይ አፈፃፀም የሚመለከት ይሆናል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ

photo content
+9

የበጀት ኢኮኖሚ ንግድና ኢንደስትሪ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የአፈፃፀም ግምገማና የመስክ ምልከታ አካሄደ:: ቋሚ ኮሚቴው የፕሮጀክቶች አፈፃፀም በተመለከተ የኢትዮ ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የአዳራሽ እድሳት ምን ደረጃ ላይ እንደሚገኝና ከቴክኖሎጂ ሽግግር እንዲሁም ከስራ እድል ፈጠራ ጋር የተሰሩ ስራዎችን ቋሚ ኮሚቴው በምልከታው አካቷል። የኢትዮ ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የአዳራሽ እድሳ ፊዚካል አፈፃፀሙ 87በመቶ የደረሰ ሲሆን የወንበር ገጠማና የማጠናቀቂያ ስራዎች የሚቀሩት መሆኑን ኮሚቴዉ ተመልክቷል። በተጨማሪም የዶሮ ማቀነባበሪያ ፣ የንብ ቀፎ ÷ የኮሪደር ልማትን ታሳቢ ያደረገ የመንገድ ላይ መቀመጫዎች በኮንቴነር ተለዋጭ የሚሆን ሱቅ በኮሌጁ የተሰሩ ስራዎችን ቋሚ ኮሚቴዉ በመዘዋወር ምልከታ አድርጓል ። በተለያዩ የስራ ዘርፍ ላይ ካሉ የኮሌጁ አመራሮች ጋር በተደረገው ውይይት ኮሌጁ ከአገልግሎት አሰጣጥ አንፃር አለም አቀፍ የጥራት ደረጃ እዉቅና የተሰጠዉና በክህሎት ዉድድር በአይሲቲ ዘርፍ አንደኛ በመዉጣት ያጠናቀቀ ፣ የተማረ በክህሎት የላቀ ዜጋን ለማፍራት በርካታ ስራዎችን እየሰራ መሆኑ ተገልጿል። በተጨማሪም ኮሌጁ የሴቶችን፣ ህፃናትንና አካል ጉዳተኞችን ማዕከል ያደረገ የመማር ማስተማር ሂደት ቀርፆ እየሰራ እንደሚገኝ ለቋሚ ኮሚቴው ገለፃ አድርገዋል ። የድሬደዋ አስተዳደር ምክር ቤት የበጀት ኢኮኖሚ ንግድና ኢንደስትሪ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴም ኮሌጁ ከጊዜ ወደ ጊዜ እራሱን እያሳደገ መሆኑ ገልፀዉ በቀጣይ ዉስጠ ገቢን የማሳድግ ስራ ትኩረት ተሰጥቶበት መሰራት እንዳለበት ጠቁመዋል። ከአምራች ኢንዱስትሪዎች ጋር ኮሌጁ ቅንጅታዊ አሰራር በማጠናከር በሀገር ዉስጥ ተኪ ምርት የማምረት እና የገጠሩንም የማህበረሰብ ክፍል አካታች የሆኑ ስራዎች መሰራት እንዳለባቸው ቋሚ ኮሚቴው አፅኖት ሰጥቶቷል ። የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት

photo content
+9

photo content
+9

በትምህርትና ስልጠና ክፍሎች ላይ በኮሌጁ ማኔጅመንት አባላት እየተካሄደ የሚገኘው የምልከታ መድረክ በተጠናከረ መልኩ በመካሄድ ላይ ይገኛል:: ሰኔ 14/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ማኔጅመንት በኮሌጁ የሚገኙ የትምህርትና ስልጠና ክፍሎች የስልጠና አሰጣጥ ትግበራን በተመለከተ እያካሄደ የሚገኘው የግምገማ መድረክ በዚህ ሳምንትም ቀጥሎ ተካሂዷል:: የለምልከታ ቡድኑ በተዘጋጀው መርሃ-ግብር መሰረት በዚህ ሳምንት የኤሌክትሪካል/ኤሌክትሮኒክስ ዲፓርትመንት እና የቢዝነስ ዲፓርትመትን የተመለከተ ሲሆን በዚህም የትምህርትና ስልጠና ክፍሎቹ በ2017 ዓ.ም የስልጠና ዘመን ከተቀመጠው ግብ አንፃር ያከናወኗቸውን ዝርዝር ተግባራት መመልከትም ተችሏል:: የቀረቡት የአፈፃፀም ሪፖርቶችን መነሻ በማድረግም በምልከታ ቡድኑ ሀሳብ አስተያየት የተሰጠባቸው ሲሆን ጥሩ አፈፃፀም በታየባቸው ጉዳዮች ላይ አውቅናን በመስጠት እንዲሁም ዝቅተኛ እፈፃፀም በተስተዋለባቸው ጉዳዮች ላይም ዲፓርትመንቶቹ በቀጣይ ትኩረት ሰጠተው እንዲሰሩ ግብረ-መልስ ተስጥቷል:: በትምህርትና ስልጠና ክፍሎች የሚካሄደው ይህ የግምገማ መድረክ በቀጣይም በተቀረሩት ዲፓርትመንቶች ላይ በተቀመጠው መርሃ-ግብር መሰረት የሚቀጥልም ይሆናል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ

photo content
+5

photo content
+9