fa
Feedback
Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

رفتن به کانال در Telegram
1 740
مشترکین
+124 ساعت
+37 روز
-530 روز
آرشیو پست ها
በኮሌጁ ባለፉት ሳምንታት በትምህርትና ስልጠና ክፍሎች ላይ ሲካሄድ የቆየው ምልከታ ተጠናቀቀ:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ማኔጅመንት በኮሌጁ የሚገኙ የትምህርትና ስልጠና ክፍሎች ላይ የአፈፃፀም ትግበራን በተመለከተ ሲያካሂድ የቆየውን የግምገማ መድረክ በዛሬው እለት አጠናቋል:: በምልከታ መርሃ-ግብሩ መሰረት የተቀሩ ዲፓርትመንቶችን (ማኑፋክቸሪንግ ፣ኮንስትራክሽን፣ድራፍቲንግና ሰርቬይ እንዲሁም የሆቴልና ቱሪዝም) ዲፓርትመንቶችን የአፈፃፀም ሪፖርት የተመለከተ ሲሆን በዚህም የትምህርትና ስልጠና ክፍሎቹ በ2017 ዓ.ም የትምህርትና ስልጠና ዘመን ከተቀመጠው ግብ አንፃር ያከናወኗቸውን ዝርዝር ተግባራት መመልከትም ተችሏል:: የኮሌጁ ማኔጅመንት ከትምህርትና ስልጠና ክፍሎች በተጨማሪም የኮሌጁን የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን እና ቴክኖሎጂ ሽግግር ስራ ሂደትን አመታዊ ሪፖርት ተገኝቶ የተመለከተ ሲሆን በዚህም በበጀት አመቱ የተሰሩ ችግር ፈቺ ቴክኖሎጂዎች እንዲሁም በኢንተርፕራይዞችና ኢንዱስትሪዎች ላይ የተከናወኑ ውጤታማ ተግባራትን ተመልክተዋል:: ምልከታ በተካሄደባቸው ክፍሎች የቀረቡት የአፈፃፀም ሪፖርቶችን መነሻ በማድረግም በማኔጅመንት አባላት ግብረ መልሶች የተሰጡ ሲሆን በተጨማሪም በኮሌጁ ዲን የቀጣይ የስራ አቅጣጫ ለትምህርትና ስልጠና ክፍሎቹ በመስጠት የምልከታ መድረኩ ተጠናቋል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ሐምሌ 4/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

የኮሌጁ ማኔጅመንት በትምህርትና ስልጠና ክፍሎችና ስራ ሂደቶች ላይ እያካሄደ የሚገኘው የምልከታ መድረክ መካሄዱን ቀጥሏል:: ሰኔ 14/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ማኔጅመንት በኮሌጁ የሚገኙ የትምህርትና ስልጠና ክፍሎች የስልጠና አሰጣጥ ትግበራን በተመለከተ እያካሄደ የሚገኘው የግምገማ መድረክ በዚህ ሳምንትም ቀጥሎ ተካሂዷል:: የምልከታ ቡድኑ በተዘጋጀው መርሃ-ግብር መሰረት በዚህ ሳምንት የኤሌክትሪካል/ኤሌክትሮኒክስ ዲፓርትመንት እና የቢዝነስ ዲፓርትመትን የተመለከተ ሲሆን በዚህም የትምህርትና ስልጠና ክፍሎቹ በ2017 ዓ.ም የስልጠና ዘመን ከተቀመጠው ግብ አንፃር ያከናወኗቸውን ዝርዝር ተግባራት መመልከትም ተችሏል:: የቀረቡት የአፈፃፀም ሪፖርቶችን መነሻ በማድረግም በምልከታ ቡድኑ ሀሳብ አስተያየት የተሰጠባቸው ሲሆን ጥሩ አፈፃፀም በታየባቸው ጉዳዮች ላይ አውቅናን በመስጠት እንዲሁም ዝቅተኛ እፈፃፀም በተስተዋለባቸው ጉዳዮች ላይም ዲፓርትመንቶቹ በቀጣይ ትኩረት ሰጠተው እንዲሰሩ ግብረ-መልስ ተስጥቷል:: በትምህርትና ስልጠና ክፍሎች የሚካሄደው ይህ የግምገማ መድረክ በቀጣይም በተቀረሩት ዲፓርትመንቶች ላይ በተቀመጠው መርሃ-ግብር መሰረት የሚቀጥልም ይሆናል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ

በኮሌጁ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር አገልግሎት ዋና ስራ ሂደት የበጀት አመቱን የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርት መድረክ ማካሄድ ጀመረ:: ሰኔ 20/2017ዓ.ም ድሬዳዋ በእለቱ በነበረው መርሀ-ግብር በዋና ስራ ሂደቱ የሚገኙ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ድጋፍ የወረዳ ተጠሪዎች እና በሂደቱ የጥናት፣ቴክኖሎጂ ሽግግር ስር የሚገኙ ባለሙያዎችን የአፈፃፀም ሪፖርት መመልከት ተችሏል:: በመድረኩም በ2017 በጀት ዓመት በዋና ስራ ሂደቱ ይከናወናሉ ተብለው በእቅድ ከተያዙ ተግባራት አንፃር የተሰሩ ስራዎች አፈፃፀምን የተመለከት ሪፖርት በተጠሪዎች ቀርቧል:: በሪፖርት መድረኩ በዋናነት በኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት በአራቱ የድጋፍ ማዕቀፎች ላይ የተከናወኑ ተግባራትን፣ ቴክኖሎጂንዎችን ከማሸጋገር አንፃር የተሰሩ ስራዎችን እንዲሁም በጥናትና ምርምር የተገኙ ውጤቶችን ጨምሮ በኮሌጁ የሚሰጡ ተጨማሪ ተልዕኮዎችን ከመፈፀም አኳያ የተከናወኑ ተገባራትን በዝርዝር የሚዳስስ ሪፖርትም ቀርቦበታል:: በቀረቡት ሪፖርቶች መነሻነትም በመድረኩ ሰፊ ውይይት የተካሄደበት ሲሆን የታዩ ጠንካራ ጎኖችን በይበልጥ አጠናክሮ ለማስቀጠል እንዲሁም ክፍተት በተስተዋለባቸው ጉዳዮች ላይም በቀጣይ በትኩረት መስራት እንደሚገባም ተገልፇል:: የሪፖርት መድረኩ በቀጣይ ቀናትም ቀጥሎ የሚካሄድ ሲሆን ተጨማሪ የተሰሩ ስራዎችን ጨምሮ የዋና ሂደቱን አጠቃላይ አፈፃፀም የሚመለከት ይሆናል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ

የበጀት ኢኮኖሚ ንግድና ኢንደስትሪ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የአፈፃፀም ግምገማና የመስክ ምልከታ አካሄደ:: ቋሚ ኮሚቴው የፕሮጀክቶች አፈፃፀም በተመለከተ የኢትዮ ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የአዳራሽ እድሳት ምን ደረጃ ላይ እንደሚገኝና ከቴክኖሎጂ ሽግግር እንዲሁም ከስራ እድል ፈጠራ ጋር የተሰሩ ስራዎችን ቋሚ ኮሚቴው በምልከታው አካቷል። የኢትዮ ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የአዳራሽ እድሳ ፊዚካል አፈፃፀሙ 87በመቶ የደረሰ ሲሆን የወንበር ገጠማና የማጠናቀቂያ ስራዎች የሚቀሩት መሆኑን ኮሚቴዉ ተመልክቷል። በተጨማሪም የዶሮ ማቀነባበሪያ ፣ የንብ ቀፎ ÷ የኮሪደር ልማትን ታሳቢ ያደረገ የመንገድ ላይ መቀመጫዎች በኮንቴነር ተለዋጭ የሚሆን ሱቅ በኮሌጁ የተሰሩ ስራዎችን ቋሚ ኮሚቴዉ በመዘዋወር ምልከታ አድርጓል ። በተለያዩ የስራ ዘርፍ ላይ ካሉ የኮሌጁ አመራሮች ጋር በተደረገው ውይይት ኮሌጁ ከአገልግሎት አሰጣጥ አንፃር አለም አቀፍ የጥራት ደረጃ እዉቅና የተሰጠዉና በክህሎት ዉድድር በአይሲቲ ዘርፍ አንደኛ በመዉጣት ያጠናቀቀ ፣ የተማረ በክህሎት የላቀ ዜጋን ለማፍራት በርካታ ስራዎችን እየሰራ መሆኑ ተገልጿል። በተጨማሪም ኮሌጁ የሴቶችን፣ ህፃናትንና አካል ጉዳተኞችን ማዕከል ያደረገ የመማር ማስተማር ሂደት ቀርፆ እየሰራ እንደሚገኝ ለቋሚ ኮሚቴው ገለፃ አድርገዋል ። የድሬደዋ አስተዳደር ምክር ቤት የበጀት ኢኮኖሚ ንግድና ኢንደስትሪ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴም ኮሌጁ ከጊዜ ወደ ጊዜ እራሱን እያሳደገ መሆኑ ገልፀዉ በቀጣይ ዉስጠ ገቢን የማሳድግ ስራ ትኩረት ተሰጥቶበት መሰራት እንዳለበት ጠቁመዋል። ከአምራች ኢንዱስትሪዎች ጋር ኮሌጁ ቅንጅታዊ አሰራር በማጠናከር በሀገር ዉስጥ ተኪ ምርት የማምረት እና የገጠሩንም የማህበረሰብ ክፍል አካታች የሆኑ ስራዎች መሰራት እንዳለባቸው ቋሚ ኮሚቴው አፅኖት ሰጥቶቷል ። የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት

በትምህርትና ስልጠና ክፍሎች ላይ በኮሌጁ ማኔጅመንት አባላት እየተካሄደ የሚገኘው የምልከታ መድረክ በተጠናከረ መልኩ በመካሄድ ላይ ይገኛል:: ሰኔ 14/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ማኔጅመንት በኮሌጁ የሚገኙ የትምህርትና ስልጠና ክፍሎች የስልጠና አሰጣጥ ትግበራን በተመለከተ እያካሄደ የሚገኘው የግምገማ መድረክ በዚህ ሳምንትም ቀጥሎ ተካሂዷል:: የለምልከታ ቡድኑ በተዘጋጀው መርሃ-ግብር መሰረት በዚህ ሳምንት የኤሌክትሪካል/ኤሌክትሮኒክስ ዲፓርትመንት እና የቢዝነስ ዲፓርትመትን የተመለከተ ሲሆን በዚህም የትምህርትና ስልጠና ክፍሎቹ በ2017 ዓ.ም የስልጠና ዘመን ከተቀመጠው ግብ አንፃር ያከናወኗቸውን ዝርዝር ተግባራት መመልከትም ተችሏል:: የቀረቡት የአፈፃፀም ሪፖርቶችን መነሻ በማድረግም በምልከታ ቡድኑ ሀሳብ አስተያየት የተሰጠባቸው ሲሆን ጥሩ አፈፃፀም በታየባቸው ጉዳዮች ላይ አውቅናን በመስጠት እንዲሁም ዝቅተኛ እፈፃፀም በተስተዋለባቸው ጉዳዮች ላይም ዲፓርትመንቶቹ በቀጣይ ትኩረት ሰጠተው እንዲሰሩ ግብረ-መልስ ተስጥቷል:: በትምህርትና ስልጠና ክፍሎች የሚካሄደው ይህ የግምገማ መድረክ በቀጣይም በተቀረሩት ዲፓርትመንቶች ላይ በተቀመጠው መርሃ-ግብር መሰረት የሚቀጥልም ይሆናል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ

በኮሌጁ የትምህርትና ስልጠና ክፍሎች ላይ የስልጠና አሰጣጥ ትግበራ ላይ የምልከታ መድረክ መካሄድ ጀመረ:: ሰኔ 9/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ማኔጅመት በኮሌጅ የሚገኙ የትምህርትና ስልጠና ክፍሎች የስልጠና አሰጣጥ ትግበራን በተመለከተ የግምገማ መድረክ እያካሄደ ይገኛል:: ለግምገማ መድረኩ በተዘጋጀው መርሃ-ግብር መሰረት የአውቶሞቲቭ እና የአይ.ሲ.ቲ ዲፓርትመንቶች በ2017 ዓ.ም ያከናወኗቸውን ዝርዝር ተግባራት የማኔጅመንትና አካዳሚክ ኮምሽን አባላት በተገኙበት ያቀረቡ ሲሆን በቀረበው ሪፖርት መሰረትም ሰፊ ውይይቶች ተካሂደው ግብረ-መልስ ተሰጥቶባቸዋል:: የግምገማ መድረኩ ዋና አላማ በበጀት አመቱ በትምህርትና ስልጠና ክፍሎች በተሻለ ደረጃ የተከናወኑ አፈፃፀሞችን ይበልጥ ተጠናክረው እዲቀጥሉ ለማስቻል እንዲሁም እንደ ክፍተት በተለዩ ችግሮች ላይ በቀጣይ ትኩረት ሰጥተው እንዲሰሩ ለማስቻልም እንደሆነ ተገልፇል:: በትምህርትና ስልጠና ክፍሎች የሚካሄደው ይህ የግምገማ መድረክ በቀጣይም በተቀረሩት ዲፓርትመንቶችም ላይ በተቀመጠው መርሃ-ግብር መሰረት የሚቀጥልም ይሆናል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ

እንኳን አደረሳችሁ!! ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1446 ኛው የኢድ አል-አድሃ(አረፋ) በዓል አደረሳችሁ እያልኩ በዓሉ የሰላም፣የጤና፣የመተሳሰብ ይሆንላችሁ ዘንድ መልካም ምኞ
+1
እንኳን አደረሳችሁ!! ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1446 ኛው የኢድ አል-አድሃ(አረፋ) በዓል አደረሳችሁ እያልኩ በዓሉ የሰላም፣የጤና፣የመተሳሰብ ይሆንላችሁ ዘንድ መልካም ምኞቴን እገልፃለው:: አቶ ታደለ አሰፋ የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዲን  #ኢድ_ሙባረክ!!

በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ተሻለ በሬቻ የተመራ ልዑክ በዛሬው እለት ኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ድጋፋዊ የስራ ጉብኝት አካሄደ፡፡ ግንቦት 28/2017 ዓ.ም በሚኒስትር ዴኤታው የተመራው ልዑካን ቡድን በኮሌጁ ሲደርስ በኮሌጁ ዲኖች የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባበል የተደረገለት ሲሆን ቡድኑ በነበረው ቆይታም በበጀት አመቱ በኮሌጁ የተሰሩ ዋና ዋና ትግባራትን እንዲሁም በተቋሙ እየተከናወኑ የሚገኙ ዘርፈ ብዙ የለውጥ ስራዎችንም ተመልክተዋል:: በበጀት አመቱ በኮሌጁ የተከናወኑ አጠቃላይ ተግባራትን ዝርዝር ሪፖርት በኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ አማካኝነት ለልዑካን ቡድኑ የቀረበ ሲሆን በሪፖርቱም ኮሌጁ በትምህርትና ስልጠና አሰጣጥ፣በቴክኖሎጂ ፈጠራዎች፣በስራ ዕድል ፈጠራዎች፣ በእንተርፕራይዞች ድጋፍ ጨምሮ ከአዲሱ የቴክኒክና ሙያ እሳቤ አኳያ የተከናወኑ ተግባራት በዝርዝር ተብራርተዋል:: በመስክ ምልከታው ልኡክ ቡድኑን የመሩት ሚንስትር ዴኤታው ከሱፐርቪዥኑ በኃላ በሰጡት አስተያየት በተቋሙ በነበራቸው ምልከታ የተሻለ የሚባል አፈፃፀምና የስራ እንቅስቃሴ መመልከታቸውን ገልፀው በቀጣይም ከአዲሱ የቴክኒክና ሙያ እሳቤ አንፃር በኮሌጁ የተጀመሩ ተግባራትን ከዳር ለማድረስ በትኩረት መስራት ይጠበቃልም ብለዋል:: በእለቱ በኮሌጁ የተካሄደው ድጋፋዊ ሱፕርቪዥን ምልከታም በሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ተሻለ በሬቻ የቀጣይ የስራ አቅጣጫ ለተቋሙ በመስጠት ተጠናቋል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ

Repost from N/a
photo content
+9

Repost from N/a
photo content
+9