1 739
Подписчики
-124 часа
+17 дней
-730 день
Архив постов
አድራ ኢትዮጵያ በሶላር ፒቪ የመንገድ መብራት ዝርጋታ እና ጥገና የእሴት ሰንሰለት ዙሪያ ተዘጋጅቶ በቀረበ ሰነድ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አካሄደ::
አድራ ኢትዮጵያ ከአድራ ጀርመኒ ጋር በመተባበር በጀርመን መንግስት ድጋፍ ለሶላር ፒቪ ዝርጋታ እና ጥገና የሚሆን የማሰልጠኛ ወርክሾፕ በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በማዘጋጀት ስልጠና እየሰጠ እንደሚገኝ የሚታወቅ ሲሆን በዘርፉ ያሉትን ማነቆዎች ለመቀነስ እና አዲሱን የGreen TVET Approach ለማሳወቅ ከፍተኛ ስራ እየሰራም ይገኛል።
በዚህም መሰረት ከድሬደዋ TVET ኤጀንሲ ቢሮ ጋር በመተባበር በተሰራው የሶላር ፒቪ የመንገድ መብራት ዝርጋታ እና ጥገና የእሴት ሰንሰለት በድሬደዋ ከተማ (Value Chain Analysis On Solar PV Street Light Installation & Maintenance in DD city)በሚል ርዕስ ተዘጋጅቶ በቀረበው ሰነድ ላይ ዘርፉን የሚያነቃቃ ጠቃሚ እና ሰፊ ውይይት ከባለድርሻ አካላት ጋር በማድረግ ዘርፉ ላይ ያሉትን ክፍተቶች ወደ መልካም አጋጣሚ በመቀየር ለሰልጣኞች ሰፊ የስራ እድል መፍጠር የሚያስችል ሁኔታ መፍጠር እንደሚቻልም በመድረኩ ተመላክቷል።
በዚህም ትልቁን ድርሻ ከሚወስደው የድሬደዋ መንገዶች ባለስልጣን ጋር አብሮ ለመስራት የሚያስችል ሁኔታዋችም መፈጠራቸው የተገለፀ ሲሆን በቀጣይም ስራውን በማስፋትና ወደ ገጠሩ አካባቢ በመውረድ ገጠሩን አካታች የሆነ የእሴት ሰንሰለት በመስራት አብሮ ችግሩን መቅረፍ የሚያስችል ሁኔታ እንዲፈጠርም አቅጣጫ ተይዟል።
ኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን
ታህሳስ 22/2016 ዓ.ም
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የቴክኖሎጂ ሽግግር እና ኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ስራ ሂደት በዳይመንድ ሚስማር ፋብሪካ የመስክ ምልከታ አካሄደ::
በፋብሪካው በነበረው ጉብኝት በቅድሚያ ከድርጅቱ ሀላፊና ባለቤቶች ጋር በስራ ላይ ስለሚገጥሟቸው ችግሮች እንዲሁም ከተቋሙ በሚደረግላቸው የድጋፍ አይነቶች ዙሪያ ውይይቶች የተደረጉ ሲሆን የሚስማር ማምረቻ ወርክ ሾፖችንም ተዘዋውረው ተመልክተዋል::
በምልከታው ወቅትም ድርጅቱ በማሽን ጥገና ወቅት የመለዋወጫ እጥረት እንዳለበትና ለረጅም ጊዜ በብልሽት ምክንያት ያለ ስራ የቆሙ ትልልቅ ማሽነሪዎችም እንዳሉ መታዘብ ተችለዋል::
ተቋሙ በቀጣይ በድርጅቱ የተለዩ ችግሮች ላይ በኮሌጁ ሊፈቱ የሚችሉትን በዝርዝር በመለየትና ከድርጅቱ ጋር የጋራ ስምምነት በመፈፀም የዕውቀትና የቴክኖሎጂ ሽግግር ድጋፍ እንደሚይደርግም ተገልጿል::
ኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን
ህዳር 28/2016 ዓ.ም
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እና የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ በዩኒቨርሲቲ፣ ቴሙትስና ኢንዱስትሪ ትስስር ጽንሰ ሃሳብን መሰረት ያደረገ ሁሉ-አቀፍ ቅንጅት/በጋራ ለመስራት የሚያስችል የጋራ መግባቢያ ሰነድ ተፈራረሙ::
ተቋማቱ ከዚህ ቀደም በዘርፉ የሚታዩ ችግሮችን ለመቅረፍ በተናጠል ብዙ ስራዎችን ለመስራት መሞከራቸውን ገልፀው ይህ ግን መርሀ-ግብር ከማሟላት በዘለለ በሚፈለገው ልክ ውጤት እንዳላስገኘላቸውም ገልፀዋል::
ይሁንና በዚህ አመት ሁለቱ ተቋማት በቅንጅት ሊያሰራቸው የሚችል የጋራ የስምምነት ሰነድ በማዘጋጀት እንዲሁም የሚታዩ ችግሮችን ከስር መስረታቸው በትክክል ለይቶ በማስቀመጥ ውጤታማ በሚያደርጋቸው ተግባራቶች ላይ እንደሚያተኩሩና እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል::
በተጨማሪም በኢንዱስትሪዎች ላይ ከመለዋወጫ ግብአት አንስቶ የተለያዩ የሚታዩ ችግሮች ያሉ በመሆናቸው እነዚህ ላይም ከተናጠል ይልቅ በቅንጅት ቢሰራባቸው ለችግሮቹ የመፍትሄ አካል መሆን እንደሚቻልም መግባባት ላይ የተደረሰ ሲሆን በአጠቃላይ በሰ/ኃ/ልማት፣ በቴ/ጂ ሽግግር፣ በጥናትና ምርምር... ወዘተ ትኩረት የሚደረግ መሆኑም ተገልጿል።
በቀጣይ ከሁለቱ ተቋማት የተወጣጣ ቴክኒካል ቡድን ተቋቁሞ በስምምነቱ መሰረት ስራዎች በተቀመጠላቸው ጊዜ እና በሚፈለገው ደረጃ እንዲተገበሩ ክትትልና ድጋፍ የሚያደርግም ይሆናል::
ኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን
ህዳር 27/2016 ዓ.ም
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በዘንድሮ የትምህርትና ስልጠና ዘመን የተቀበላቸውን አዲስ ገቢ ሰልጣኝ ተማሪዎች ወደ መደበኛ ስልጠና ከመግባታቸው አስቀድሞ ሰልጣኞችን በሁሉም ረገድ ዝግጁ የሚያደርጋቸውን የLife Skill ስልጠና በዛሬው እለት መስጠት ጀመረ።
በስልጠናው ሰልጣኝ ተማሪዎቹ ከ Life skill ስልጠናው በተጨማሪም ስለ ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ፖሊሲና እስትራቴጂ እንዲሁም በዘርፉ ስለሚሰጡ የሙያ መስኮች ሰፉ ያለ ማብራርያ የሚሰጣቸው መሆኑም ተገልጿል::
በዚህም ሰልጣኝ ተማሪዎቹ ሰለ ቴ/ሙ/ት/ስ ዘርፍ እንዲሁ እሁን ላይ ያለውን የገበያ ፍላጎት በጥልቅ ከተረዱና ግንዛቤውን ካገኙ በኃላ ለመሰልጠን የወሰኑትን የሙያ መስክ ምርጫቸውን ለማስተካከል በእጅጉ እንደሚረዳቸውም ይትመናል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን
ህዳር 24/2016 ዓ.ም
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የቴክኖሎጂ ሽግግርና የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ስራ ሂደት ከስራና ክህሎት ቢሮ ጋር በመተባበር በአስተዳደሩ ለሚገኙ ጀማሪ ኢንተርፕራይዞች መሰረታዊ የኢንተርፕረነርሺፕ ስልጠና ሰጠ::
በዚህ ለ 4 ቀን በቆየው ስልጠና 38 የሚሆኑ ጀማሪ የኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች የተሳተፉ ሲሆን ለተሳታፊዎች በስራ ፈጠራ እና ንግድ ክህሎት ዙሪያ ያተኮረ ስልጠና መሰጠቱንና ይህም ኢንተርፕራይዞች በሚያደርጉት የእድገት ሽግግር ላይ ወሳኝ ሚና እንደሚኖረውም ተገፅጿል::
ሰልጣኞች በበኩላቸው ይህን ስልጠና ወስደው በዕለት ተዕለት እንቅስቃሴያቸው ውስጥ ተግባራዊ እንደሚያደርጉት በመግለፅ በቴክኖሎጂ ሽግግርና የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት የሚደረጉላቸው የድጋፍ ማእቀፎችን ለመጠቀምና ራሳቸውን ለማሳደግ ፍላጎትና ተነሳሽነት እንደፈጠራላቸው ተናግረዋል።
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን
ህዳር 21/2016 ዓ.ም
Repost from Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa
መረጃውን በማድረስ ይተባበሩን!!
ከዚህ ቀደም የኢትዮጵያ አየር መንገድ ባወጣው የቅጥር ማስታወቂያ ላይ ተመዝግባችሁ የፅሁፍ ፈተና ያለፋችሁ የከተማችን ወጣቶች የኢንተርቪው ፈተና ህዳር 25/2016 ዓ.ም ጀምሮ በሰንጠረዡ በተጠቀሰው ሰዓት ስለሚሰጥ በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ እንድትገኙ ጥሪ ተላልፏል።
Repost from Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa
"ብዝሃነትና እኩልነት
ለአገራዊ አንድነት!"
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ አመራሮችና ሠራተኞች 18ኛውን የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች ቀን አከበሩ።
በዓሉ በፓናል ውይይት የተከበረ ሲሆን፣ የቢሮው ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው በመድረኩ ላይ ባደረጉት ንግግር የዘንድሮው የብሔር ብሔረሰቦች ቀን "ብዝሃነትና እኩልነት ለአገራዊ አንድነት" በሚል መሪ ቃል የሚከበር መሆኑን አውስተው፣ አገራዊ አንድነትን ለማጽናት ሕገ መንግሥቱን መሠረት በማድረግ ጥያቄዎችን በሰላማዊ አግባብ የሚያስተናግድ ሥርዓት መገንባት ቀዳሚ የመንግሥት ትኩረት እንደሆነ ተናግረዋል።
የቢሮው ምክትል ኃላፊ እና የቴክኒክና ሙያ ትምህርና ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ በበኩላቸው የብሔር ብሔረሰቦች ቀን የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች እኩልነት እና የጋራ መብታቸው የተረጋገጠበት ሕገ መንግሥት የጸደቀበትን ኅዳር 29 ቀን መነሻ በማድረግ የሚከበር መሆኑንና በሕገ መንግሥቱ የተረጋገጡ መብቶችን አስጠብቀን ልንጓዝ የምንችለው ተግባራዊ ለማድረግ ሁላችንም የድርሻችንን ስንወጣ ይሆናል ብለዋል፡፡
የውይይቱ ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያየት የብሔር ብሔረሰቦች ቀን መከበሩ የሕዝቦችን እኩልነትና ኅብረ ብሔራዊ አንድነት ለማጠናከር ጠቀሜታው የጎላ እንደሆነ ገልጸው፣ አንድነትን ለማጠናከር ሰላምን የሚያደፈርሱ አጀንዳዎችን የማስወገድ ጉዳይ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ አሳስበዋል።
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ህዳር 17/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Уже доступно! Исследование Telegram 2025 — ключевые инсайты года 
