cookie

Мы используем файлы cookie для улучшения сервиса. Нажав кнопку «Принять все», вы соглашаетесь с использованием cookies.

avatar

⚖Ethiopian law by Daniel Fikadu Law office⚖

ዳንኤል ፍቃዱ ተስፋዬ በሁሉም የፌደራል ፍርድ ቤቶች ጠበቃና የህግ አማካሪ ስልክ - 0913158507 ወይም 0978554559 Daniel Fikadu Tesfaye Certified Attorney of law at all Federal Courts of Ethiopia. Email- nurotekore@gmail. Com ⚖️⚖️Ethiopian Law by Daniel Fikadu channel ⚖️⚖️⚖️

Больше
Рекламные посты
8 658
Подписчики
+2424 часа
+1607 дней
+65530 дней

Загрузка данных...

Прирост подписчиков

Загрузка данных...

👍 2
የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር 2ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ መሰረታዊ ውሳኔዎችን በማሳለፍ ተጠናቀቀ ፤ ========================== የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር ግንቦት 03 ቀን 2016ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ የማህበሩ 2ኛ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ተካሂዷል:: ጉባኤውን በመክፈቻ ንግግር ያስጀመሩት የማህበሩ መሪ አቶ ቴዎድሮስ ጌታቸው ሲሆኑ በንግግራቸው ማህበሩ ባለፈው ሁለት አመት ተኩል ስላለፈባቸው ሂደቶች ስላከናወናቸው ተግባራት በተለይም ተቋም የመፍጠሩ ሂደት ላይ አተኩረው ፤ ከተቋም ግንባታና መዋቅር ፤ በአዋጅ ስለወሰዳቸው ሃላፊነቶች አተገባበር ፤ ከአጠቃላይ የአባላት አገልግሎት ስርዓት ፤ ከአለም አቀፍ ግንኙነትና መስል አንኳር ስኬቶችና ተግዳሮቶችን በንግግራቸው ዳሰዋል:: በመቀጠል የማህበሩ የስራ ተግባር ሪፖርት በወ/ሮ ሆሳእና ነጋሽ የፋይናንስ ሪፖርት ደግሞ በሂሳብ ባለሙያ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል:: ሌላኛው ለውይይት የቀረበው የማህበሩ ረቂቅ የመተዳደሪያ ደንብ ሲሆን ረቂቁን ያቀረቡት የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል አቶ ዮሴፍ አዕምሮ ናቸው:: በረቂቅ ደንቡ ላይ በተደረገው ውይይት ጠንካራ ሃሳቦችና ክርክሮች ተስተናግደዋል:: በተለይም የማህበሩን ፕሬዝደንቶችና የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴውን ለየብቻ ያደራጀው የደንቡ ክፍል በጉባኤው ተቀባይነት ሳያገኝ ቀርቷል:: በጠቅላላ ጉባኤው ተገኝተው ድምፅ ከሰጡ የማህበሩ አባላት ውስጥ 78% በመቶ የሚሆኑት የቀረበውን ረቂቅ ደንብ ውድቅ እንዲደረግ ድምፅ የሰጡ ሲሆን 22 በመቶ የሚሆኑት ከሚደረግ ማሻሻያ ጋር እንዲፀድቅ ድምፅ ሰጥተዋል:: በዚህም በአብላጫው ድምፅ መሰረት ቀድሞ በቀረበው አማራጭ ሃሳብ መሰረት ተደርጎ ደንቡ በድጋሚ ተዘጋጅቶ በ 1 ወር ግዜ ውስጥ እንዲጠናቀቅ ጉባኤው ውሳኔ አስተላልፎ ይህንኑ የሚያከናውኑ 13 አባላት ያሉት ኮሚቴ ሰይሟል:: ኮሚቴውም ሰብሳቢውና (ጠበቃ ፍቃዱ ጴጥሮስ) ምክትሉን(ጠበቃ ህይወት ብርሃኑ) መርጦ ለጉባኤው አሳውቋል:: ከዚሁ ጋር ተያይዞ ቀርቦ የነበረውን የምርጫ ጉዳይ ጉባኤው ባለመቀበሉ አጀንዳው ሊያልፍ ሳይችል ቀርቷል:: የክፍያ እና የተከታታይ ስልጠና መመሪያዎችም እንደአስፈላጊነቱ ታይተው ቀጣይ በሚጠራው አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ እንዲቀርቡ ውሳኔ ሰጥቷል:: በጉባኤው ላይ የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ም/ፕሬዚደንት ወ/ሮ አበባ እምቢአለን ጨምሮ የህግና ፍትህ ምርምር ኢንስቲቲዪት ም/ዋ/ዳይሬክተር እና የፖርላማ አባል አቶ ዘካሪያስ ኤርኮላ ፤ የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ም/ፕ አቶ ተኽሊት ይመስል እና የፌ/ መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ም/ፕሬዚደንት ወ/ሮ አሸነፈች አበበ ፤ የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት የህግና ፍትህ ቋሚ ኮሚቴ አባል አቶ ለማ ተሰማ እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችን ጨምሮ ከ800 በላይ የፌደራል ጠበቆችና የጥብቅና ድርጅቶች ተገኝተውበታል:: ጉባኤው ማህበሩ በተለያዩ ፈታኝ ሁኔታዎች ውስጥ ሆኖ ላስመዘገበው ጉልህ ውጤት በይፋ ምስጋናውን አቅርቧል:: መረጃውን #share #like በማድረግ እንድታጋሩልን እንጠይቃለን:: መረጃዎች በፍጥነት እንዲደርሷችሁ ገፃችንን በሚከተለው መስፈንጠሪያ ይቀላቀሉ:: ፌስቡክ- https://www.facebook.com/ethiopianbarassociation?mibextid=9R9pXO የቴሌግራም ገፅ- https://t.me/ethiopianfederalbarassociation የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር ግንቦት 05 ቀን 2016ዓ.ም አዲስ አበባ ፤
Показать все...
Log in or sign up to view

See posts, photos and more on Facebook.

👍 2 2🥴 2🥰 1
#vaccancy for lawyers
Показать все...
👍 4🤩 3 2🔥 1
የማስረጃ ምዘና ጉዳይ እና ማስረጃን እና ህግን በማዋሃድ ረገድ የሚፈፀም ግድፈት ከሰበር ሰሚው ስልጣን አንጻር ሰ/መ/ቁ. 220292 ( ያልታተመ)
*** በዳንኤል ፍቃዱ / ጠበቃና የህግ አማካሪ/ የሰበር ችሎት ቀዳሚ ተግባር የሚሆነው የበታች ፍርድ ቤቶች በፍሬ ነገር ደረጃ በማስረጃ የተረጋገጠውን መሰረት በማድረግ በሰጡት የህግ ትርጉም ውስጥ የፈፀሙት መሰረታዊ የህግ ስህተት ካለ ለይቶ በህግ አግባብ ማረም ነው፡፡ ከዚህ ባለፈ ሰበር ሰሚ ችሎት በስር ፍርድ ቤት ተመዝኖ አቋም የተያዘበትን ጉዳይ በተመለከተ በራሱ ማስረጃውን መዝኖ ውሳኔ ለመስጠት የሚያስችለው የህግ አግባብ የለም፡፡ ይህ ማለት ግን የበታች ፍርድ ቤቶች የቀረቡላቸውን ማስረጃዎችን ይዘት በአግባቡ ሳይመለከቱ ሲቀሩ፤ ወይም በማስረጃ የተረጋገጠው እና ፍርድ ቤቱ የደረሰበት ድምዳሜ የተለያዩ ሆኖ በተገኘ ጊዜ ሰበር ሰሚ ችሎት ይህንን መሰል ጉዳይ ማየት አይችልም ማለት አይደለም፡፡ የዚህ ዓይነት ሁኔታሲያጋጥም ጉዳዩ የማስረጃ ምዘና ጉዳይ ሳይሆን ማስረጃን እና ህግን በማዋሃድ ረገድ የሚፈፀም ግድፈት በመሆኑ ጉዳዩ የማስረጃሳይሆን የህግ ነጥብ በመሆኑ ስልጣን ያለውየሰበር ሰሚ ችሎት ጉዳዩን አይቶ ከማረም የሚከለክለው አይደለም፡፡
Показать все...
3
የሃይማኖት ጉዳዮችን በሚመለከት እየተረቀቀ ባለው አዋጅ ላይ ቅሬታ ቀረበ *** የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤትና የወንጌል አማኞች ካውንስል በተናጠል ለሰላም ሚኒስቴር በላኩት ደብዳቤ፣ አዲስ በመረቀቅ ላይ ያለው የሃይማኖት ጉዳዮች አዋጅ ላይ ያላቸውን ቅሬታ አሰሙ፡፡ የእስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤትና የወንጌል አማኞች ካውንስል ረቂቅ አዋጁ ባይደርሳቸውም፣ ከዚህ ቀደም የአዋጁን መንፈስ በቃል በተረዱት መሠረት ሊካተቱ ይገባቸዋል ያሏቸውን ምክረ ሐሳቦች፣ አስተያየቶችና ቅሬታዎች ለሰላም ሚኒስቴር መላካቸውን ሪፖርተር የደረሰው መረጃ ያመለክታል፡፡    የእስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ሚያዝያ 28 ቀን 2016 ዓ.ም. ለሰላም ሚኒስቴር በላከውና ሪፖርተር የተመለከተው ምክረ ሐሳብ፣ ረቂቅ አዋጁ ሙስሊም ኢትዮጵያውያን በዘመናት ትግል ለማረጋገጥ እየሞከሩ ያሉትንና በሕገ መንግሥቱ የተደነገገውን የዜጎች እኩልነትና የሃይማኖት ነፃነት መብቶችን የሚጥስ፣ ሙስሊሞች በዓለም አቀፍ ሕግ የተቀመጠላቸውን የሃይማኖት ነፃነትና ሰብዓዊ መብቶች የሚገረስስ ሆኖ አግኝቼዋለሁ ብሏል፡፡  ‹‹መንግሥት፣ የመንግሥትን ከሃይማኖት የመለያየትና የዜጎችን ሃይማኖታዊ ነፃነትና እኩልነት መብት መርሆዎች ዝርዝር ለመደንገግ የጀመረውን እንቅስቃሴ እናደንቃለን፡፡ ሆኖም ለረቂቁ ግብዓት የሚሆኑ ውይይቶች እንደሚኖሩ በመጠበቅ ላይ ባለንበት ወቅት መጀመሩን ባላወቅነው ረቂቅ ላይ ለመወያየት ሚያዝያ 3 ቀን 2016 ዓ.ም. በሰላም ሚኒስቴር መጋበዛችን ቅሬታ ፈጥሮብናል፤›› ብሏል፡፡  ምክር ቤቱ የረቂቁን ቅጂ አለማግኘቱን አስታውቆ፣ ይህ ባልሆነበት አስተያየቱን መጠየቁ ለሚያቀርበው ግብዓት ተገቢውን ትኩረት እንዳልተሰጠና ለይስሙላ መሆኑን የሚያሳይ ሆኖ አግኝቼዋለሁ በማለት ገልጿል፡፡ ምክር ቤቱ አስተያየቱን በጽሑፍ እስኪሰጥ ሳይጠበቅ የፍትሕ ሚኒስቴር ባልደረቦች ከቀናት በኋላ ወደ ክልል ከተሞች ለውይይት ማቅረብ እንደሚጀምሩ መግለጻቸውንም ጠቁሟል፡፡ በተያዘው የግንቦት ወር አጋማሽ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ፍትሕ ሚኒስቴር ረቂቁን ለማቅረብ ማቀዱን ገልጿል፡፡ ረቂቁ የሃይማኖቶችንና የሃይማኖት ተከታዮችን እኩልነት እንዳይረጋገጥ የሚያደርግ፣ የእስልምና መሠረታዊ አስተምህሮዎችን ከግምት ያላስገባ፣ ሙስሊሙን ማኅበረሰብ ከሃይማኖቱና ከዜግነት ተሳትፎው እንዲመርጥ የሚያስገድድ፣ ለመንግሥት በሃይማኖት ውስጥ ያልተገባ ተቆጣጣሪነት የሚሰጥ መሆኑን በመግለጽ ምክር ቤቱ ቅሬታውን አቅርቧል፡፡ ረቂቁ የያዛቸውን ዝርዝር ጉዳዮች በሚመለከትም ሃይማኖታዊ ምልክቶችን እንደ የቤተ እምነቱ አስገዳጅ ሕግጋቶች ልዩ ሁኔታዎችን መደንገግ ሲገባው ሃይማኖታዊ መገለጫዎችን ሙሉ በሙሉ ከትምህርት ቤትና ከሥራ ገበታ የሚያስወግዱ ድንጋጌዎችን መያዙ፣ እንዲሁም የሙስሊም ሴቶችን ሰብዓዊ መብት በግልጽና በጥቅሉ የሚጥስ መሆኑን እንደተመለከተ ምክር ቤቱ አስታውቋል፡፡ በተጨማሪም በትምህርት፣ መንግሥታዊና መንግሥታዊ ባልሆኑ ተቋማት ውስጥ የጋራ አምልኮ ተግባራትን መከልከል፣ ሙስሊሙን ማኅበረሰብ ከእምነቱና ከሥራው ወይም ከእምነቱና ከትምህርቱ እንዲመርጥ የሚያስገድድ መሆኑ፣ እንዲሁም አምልኮን ከተፈቀደለት ቦታ ውጪ ማከናወን መከልከሉ፣ የእምነት ነፃነት መብቶች አተገባበር ላይ ጫና የሚያሳድር መሆኑን ገልጿል፡፡  የእስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤትን ሐሳብ የሚጋራ ደብዳቤ ዓርብ ግንቦት 2 ቀን 2016 ዓ.ም. ለሰላም ሚኒስቴር የላከው ደግሞ የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ነው፡፡ ካውንስሉ ረቂቅ አዋጁ አባላቱን በተመለከተ የወጣውን አዋጅ ቁጥር 1208/2012 የሚቃረን መሆኑን ገልጾ፣ ሕገ መንግሥታዊ የሆኑ የእምነትና የሃይማኖት ነፃነት መብትና ሐሳብን በነፃነት የመግለጽ መብትን የሚመለከት በመሆኑ፣ ረቂቁን ለማየት እንዲሰጠው ቢጠይቅም እንዳልተሰጠው አስረድቷል፡፡ ረቂቁ በቤት ውስጥ የሚደረግን አምልኮና የአደባባይ ስብከትን የሚከለክል መሆኑን ካውንስሉ ከሰላም ሚኒስቴርና ከፍትሕ ሚኒስቴር ጋር በነበረው ውይይት ወቅት በተደረገለት ገለጻ መረዳቱን በመግለጽ፣ ይህም በቀጥታ የወንጌል አማኞችን የሚነካና ሕገ መንግሥታዊ መሠረት የሌለው መሆኑን አስታውቋል፡፡ በሕገ መንግሥቱ መሠረት ዜጎች የአምልኮ ሥርዓት ለመፈጸም በመንግሥት አካል የግድ መመዝገብ የማያስፈልጋቸው ቢሆንም፣ በረቂቁ ውስጥ ግን የነፃነቱ ሰጪና ነሺ የምዝገባው መኖር አድርጎ ማስቀመጡ ትክልል አለመሆኑን፣ እንዲሁም ከመፅደቁ በፊትም ካውንስሉ እንዲስተካከሉ በደብዳቤ የጠየቃቸው ጉዳዮች እንዲስተካከሉ አሳስቧል፡፡ የሁለቱን የእምነት ተቋማት ምክረ ሐሳብ፣ አስተያየትና ቅሬታ አስመልክቶ የሰላም ሚኒስቴር ምላሽና አስተያየት ለማካተት የተደረገው ተደጋጋሚ ጥረት አልተሳካም፡፡#Reporter
Показать все...
👍 3 2
Repost from N/a
🌟 Exciting News for Exit Exam Takers! 🌟 🌟 Don't Miss Out on Our Exclusive Two-Day Online Seminar! 🌟
Показать все...
👍 3
Repost from N/a
Are you a law graduate 🎓 gearing up for your exit exams? We've got an event tailored just for you! Join us for our highly anticipated two-day online seminar, designed to equip you with the tools, insights, and support you need to ace your exams and set yourself up for success. 📅 Dates: [May 21th&22th] 🖥 Location: Online 📅 Day One: Expert Insights from Addis Ababa University Lecturers On the first day, we're bringing in esteemed law school lecturers from Addis Ababa University to provide invaluable support and guidance. They'll share their expertise through interactive sessions, offering: ✅In-depth subject knowledge ✅Exam preparation strategies ✅Analysis of exam content ✅Interactive sessions ✅Practical advice and tips ✅Tips for navigating challenging topics ✅Personalized career advice and mentorship ✅Networking opportunities 📅 Day Two: Wisdom from High-Scoring Exit Exam Takers On the second day, we're thrilled to host last year's and previous years top-scoring exit exam takers. Learn directly from their success stories They wii provide: ✅Insights into exam formats and question types ✅Exam-taking strategies for optimal performance ✅Discussion on exam questions ✅Discussion on last year's exit exam questions ✅Question&Answer and interactive session ✅Exclusive study materials and resources This event is your secret weapon to achieving your academic goals! We've devised a method to help you cover the entire syllabus within the remaining one month before your exams. Instead of drowning in textbooks, invest in your success by attending our seminar. 🎓 Why Attend? 🧑‍🎓 Expert Guidance and interactive sessions: Gain insights and guidance from experienced guest lecturers and previous exit exam takers who have successfully navigated the exam process. 💯 Guaranteed Success: Trust us, attending this event is your surefire path to success. Don't just take our word for it; let our proven methods speak for themselves. 📝 Exclusive  Exam Preparation Resources: Access exclusive study materials, and exam-taking strategies to enhance your preparation. 🔑 Unlock Your Potential: This seminar is your key to unlocking your full potential and achieving unparalleled success in your exit exams. 🚀 Accelerate Your Progress: With just one month left, our method will help you cover the entire syllabus efficiently and effectively. 💡 Work Smarter, Not Harder: Instead of endless hours of studying, attend our event and gain the smart strategies you need to excel. 🕵️‍♂️ Exclusive Insights: Benefit from exclusive insights into the exam format, content, and expectations directly from guest lecturers and previous exam takers. 📚 Learn exactly which exam parts will be covered 🚀Gain confidence, knowledge, and a clear path to success 🕒Don't miss this golden opportunity to elevate your exam preparation and secure an amazing grade! Register now and take the first step towards a bright future in the legal profession. See you there! 💵 Only 300 birr registration fee for a wealth of benefits 📝 To register contact @elenyy 🚀 #LegalSuccess #ExamPrepExperts #LegalBridgeAssociates
Показать все...
👍 5 1
የጠበቆች ማህበር ... ስብሰባ ዛሬ ፕሬዝደንት ለመምረጥ ፣ መተዳደሪያ ደንብና መመሪያዎች ላይ ተወያይቶ ለማጽደቅ ስብሰባ ነበር ። የተሳካ አልነበረም ። ብዙ ሲጠበቅበት የነበረው ማህበር ገና ከጅምሩ ያለፕሬዝደንት ለረዥም ጊዜ መቆየቱ ከ efficiency አንጻር ብቻ ሳይሆን ለስምም ለባለሙያውና ለማህበሩ ክብርም የሚመጥን አልነበረም ፣ በበኩሌ ሁሌም ቅር ይለኝ ነበር ። በምርጫ ጊዜ የታዘብኩዋቸው ቅር ያሉኝ ጉዳዬች ዛሬም እየተልከሰከሱ ማህበሩን እየፈተኑት ይመስለኛል ። ማህበሩን ማን ፣ እነማን በብቃት ሊመሩት ይችላሉ የሚለው መመዘኛ ብቸኛ መመዘኛ ሆኖ የመምረጫ መርሀችን ካላደረግነው በስተቀር ፣ ሁሌም የሚፎከርብን ፣ በራሳችሁ ችላችሁ ማህበሩን መምራት አትችሉም የሚለውን እያረጋገጥንላቸው መሄዳችን አይቀርም ። from co regulation to self regulation የሚደረገው ጉዞ ጥላ እንዳያጠላበት ያሰጋል ። በአገራችን በመንግስትና በባለሙያው የጋራ አስተዳደር የተቁዋቁዋመ የሙያ ማህበር የለም ። የመጀመሪያው የፌዴራል ጠበቆች ማህበር ነው ። በግርድፍ ረቂቅ ሕግ ደረጃ የተሞከረው የጤና ባለሙያዎች መማክርት ጉባኤ ነበር ፣ ግን አልተሳካም ። በጤና ባለሙያዎችም በኩል ፣ ወደ self regulation የሚሸጋገር ቅድመ co regulated የሆነ ማህበር የመመስረት ፍላጎት ነበር ። እኔም በማማከሩና በሕግ ማርቀቁ ተሳታፊ የነበርኩበት የጤና ሚኒስቴር initiative ነበር ። የፌዴራል ጠበቆች ማህበር ማቁዋቁዋሚያ አዋጅ ላይ የታዩት የትርጉምና የአፈጸጸም ችግሮች መሰረታቸው በባህሪው የተለየ ህግ ከመሆኑ ፣ በተግባርም ተመሳሳይ ተሞክሮ የሌለው መሆኑ ጭምር ይመስለኛል ። የጠበቆች ማህበር በሲቪል ሶሳይቲ ማህበርነቱም ብዙ የተፈተነና የተንገራገጨ ማህበር ስለነበር ለፌዴራል ጠበቆች ማህበር መሰረት ሊሆን የሚችል ተቁዋማዊ ባህል ፣ አሰራርና አደረጃጀትንም ማውረስ አልቻለም ። ስለሆነም በሕጉም መዳበርና በተቁዋም ግንባታውም ብዙ ፈታዎችን እየተጋፈጠ መሄድ ይጠበቅበታል ። የ አንድ ወጥ የ leadership team spirit በፍጥነት መገንባት ግን የግድ ይመስለኛል ። በዚህ ፣ በተቁዋም አመራር ክህሎትና ተየያዥ የስራ አመራር ጉዳዮች ላይ አመራሩ የማኔጅመንት ስልጠናዎችን ቢወስዱ ጥሩ ይመስለኛል ። ዘመኑ በመሰል ስልጠና ክህሎትን እያዳበሩና የልምድና የእውቀትን ክፍተት እየሞሉ ብቁ ለመሆን ጥረት የሚደረግበት ነው ። የስብሰባ ቦታና ጊዜም ሌላው ጉዳይ ነው ። የመንግስትን አዳራሽ መጠቀም ፣ የውሀና ሻይ ጋጋታውን ትቶ የግማሽ ቀን ስብሰባ እያደረጉ የተንጠለጠሉ ገዳዮችን በፍጥነት እልባት እየሰጡ መሄድ ያስፈልጋል ። ጠበቃው ከግማሽ ቀን በላይ ተስብስቦ መዋል የሚችል አይመስልም ። ሁሌም የግድ ውድ ሆቴል ውስጥ መደረግ የለበትም ። በተረፈ ፣ ማህበር መምራት ከባድ ፣ ፈተናው ብዙ እንደሆነ ፣ ጊዜ ትኩረትና ኮሚትመንት እደሚጠይቅ ስለማውቀው ፣ ስራ አስፈጻሚውን ፈጣሪ ያበርታችሁ እላለሁ ... መልካም ቀሪ የስራ ዘመን ይሁንላችሁ ። #Abebe Asamere
Показать все...
👍 11
👍 1
በኢትዮጵያ ፍርድ ቤቶች የወንጀል ችሎቶች፡ ሰብአዊ መብቶች የት አሉ? ፀሓፊው፡- አልማው ወሌ (የቀድሞ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኛ) የክስ ይዘቱ ፍትሓብሔራዊ ባህርይ ስላለው የሕጋዊነት መርህን አያሟላም በሚል በመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያነት ሲነሳ ስላላው አተገባበር -የፍትሐ ብሔር ጉዳዮች ወደ ወንጀል ሲቀየሩ፡ ፍትህ ተከልክሏል ወይስ ዘገየ? ጭማቂ ሃሳብ:- ይህ ጽሑፍ የሕጋዊነት መርህ አተገባበርን እና የወንጀል ክሱን የፍትሓብሔራዊ ባህርይን በሚመለከት በኢትዮጵያ የሕግ ሥርዓት ውስጥ በወንጀል ጉዳዮች እንደ መጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያነት ሊነሱና ሊዳኙ የሚችሉትን የዳኝነት አካሄድ በወፍ በረር ይመረምራል። የሰነድ ማስረጃዎችን ችላ በማለት በአሁኑ ወቅት እንዲህ ዓይነት መቃወሚያዎችን ወደ ስረ ነገር የክርክር ደረጃ የማስተላለፍ አሠራር፣ ኢትዮጵያ ከተቀበለቻቸው ዓለም አቀፍና አህጉራዊ የሰብዓዊ መብት ሰነዶች፣ እንዲሁም ከብሔራዊ ሕጎችና በወንጀል ሕግ ፍልስፍና መርሆች ጋር የማይጣጣም ነው ሲል ይሞግታል። ሕግንና አተገባበርን  በመጠኑ ባካተተ የአስተምህሮ ጥናት ዘዴ የሕጎቹን ይዘትና መንፈስ በመተንተን የእነዚህን መርሆች በመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ የክርክር ደረጃ የበለጠ ጠንካራ እና ሰብአዊ መብትን ያከበረ የወንጀል ክርክር አመራር ስርዓት ተግባራዊነት እንዲኖር ፍርድ ቤቶች በሕግ የተጣለባቸውን ኃላፊነት ሊወጡ ይገባል በሚል ይጠቁማል፡፡ ቁልፍ ቃላት፡ የሕጋዊነት መርህ፣ ፍትሓ ብሔራዊ ባህርይ፣ የመጀመሪያ ደረጃ ተቃውሞዎች፣ ሰብዓዊ መብቶች፣ የወንጀል ሕግ፣ የፍርድ ሂደቶች፣ የሰነድ ማስረጃዎች፣ የኢትዮጵያ የሕግ ሥርዓት ፩. መግቢያ ከሕግ ውጪ ያለመታሰር፣ ፍትሃዊ ዳኝነት እና የተፋጠነ ፍትህ የማግኘት ሰብአዊ መብቶች በኢትዮጵያ ህገ መንግስት ከፍተኛ አጽንኦት ተሰጥቶአቸው ጥበቃ ያገኙ ሲሆን ኢትዮጵያ ያፀደቀቻቸው አለም አቀፍ እና አህጉራዊ የሰብአዊ መብቶች ሰነዶችን ጨምሮ የዓለም አቀፍ የሲቪል እና የፖለቲካ መብቶች ቃል ኪዳን (ICCPR) ፣ የአፍሪካ የሰዎች እና የህዝቦች  መብቶች ቻርተር  (ACHPR)፣ እና ፕሮቶኮል ለአፍሪካ የሰብአዊ እና ህዝቦች መብቶች በአፍሪካ የሴቶች መብት ቻርተር (ማፑቶ ፕሮቶኮል)። እነዚህ ሰነዶች ንፁህ ሆኖ የመገመት፣ስለ ክሱ ምንነት እና መንስኤ እንዲሁም ማስረጃ በፍጥነት እና በዝርዝር የማወቅ መብት እና መከላከያ ለማዘጋጀት በቂ ጊዜ እና ጠበቃ የማግኘት መብትን ያረጋግጣሉ ። ፍትሓዊ ዳኝነት የማግኘት ሰብአዊ መብት ጋር የተያያዘውና ሕጎቹ ከፍተኛ ትኩረት የሰጡት ጉዳይ ከሕጋዊነት መርህ ጋር የተያያዘው ጉዳይ ሲሆን ይህ መርህ አንድ ድርጊት ወይም አልድርጊት በተፈጸመበት ጊዜ ወንጀል ስለመሆኑ በግልጽ የሚደነግግ ሕግ ሳይኖር ማንም ሰው ጥፋተኛ ሊደረግ የማይገባ መሆኑን የሚያስቀምጥ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ይህ መርህ በሲቪል እና የፖለቲካ መብቶች ቃል ኪዳን (ICCPR) አንቀጽ 15(1) ፣የአፍሪካ የሰዎች እና የህዝቦች  መብቶች ቻርተር  (ACHPR)  እና የኢፌዲሪ የወንጀል ህግ አንቀፅ 2  ላይ በግልፅ ተጠብቋል።  እንዲሁም መርሁ ግልጽ እና ተገማች የሆኑ የወንጀል ሕጎች አስፈላጊነት ላይ አፅንዖት በመስጠት ግለሰቦች ሕጉን የሚያዉቁበትና ራሳቸውን ከጥፋት ሊያርቁ የሚችሉበት ስርዓት ሊኖር እንደሚገባ፤ስለ ሕጉ በግልጽ የሚያውቁበት ፍትሃዊ ማስታወቂያ እንዲኖራቸው እና ባህሪያቸውን በዚህ መሰረት ማስተካከል እንዲችሉ መደረግ እንደአለበትም የግድ ይላል፡፡ በኢትዮጵያ የወንጀል ፍትህ አስተዳደር ውስጥ የሕጋዊነት  መርህ እና ከዚሁ መርህ ጋር ተዛማጅነት ያለው የፍትሃብሔር ባህርይን የሚመለከት መርህ በወንጀል ጉዳዮች እንደ ቀዳሚ መቃወሚያዎች በብዛት ይነሳሉ። እነዚህ መቃወሚያዎች የዐቃቤ ህግን ክስ መነሻ አድርገው የሚነሱ ሲሆን ክሱ ውስጥ የተዘረዘረው ድርጊትም የወንጀል ጥፋት አለመሆኑን ወይም በፍትሐ ብሔር ህግ ስር የሚሸፈን  ስለመሆኑ በመግለጽ ሊቀርቡ የሚችሉ ናቸው፡፡ ነገር ግን ፍርድ ቤቶች በዚህ ረገድ የሚቀርቡ መቃወሚያዎችን ብዙውን ጊዜ ጎን በመተው ጉዳዮቹ በፍሬ ነገር ክርክር በማስረጃ የሚነጥሩ ናቸው በሚል የሚያልፉበት ሙሉ የሙከራ ደረጃ በማዘዋወር፣ በማስረጃነት ብቻ ወደ ጎን የሚሰለፉበት አሳሳቢ አዝማሚያ ተፈጥሯል። ይህ አሰራር ብዙውን ጊዜ ከክሱ ጋር ተያይዘው እንዲሁም ከመጀመሪያ መቃወሚያ ላይ በጽሑፍ ከሚሰጥ አስተያዬት ጋር ተያይዘው የቀረቡትን የሰነድ ማስረጃዎች ችላ በማለት እና በወንጀለኛ መቅጫ ስነ ስርዓት ስለመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ ነጥቦች አይነትና ብዛት የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት  የሰጠውን አስገዳጅ የህግ ትርጉም ለመተግባር ባለመፈለግ የተከሳሹን ፍትሃዊ ዳኝነት የማግኘት ሰብአዊ መብት ሊጣስ ይችላል። ይህ አጭር ጽሑፍ በህጋዊነት መርህ ላይ ተመስርቶ በመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያነት በሚቀርበው የወንጀል ክስ ፍትሃብሔራዊ ባህርይን በተመለከተ በዓለም አቀፍ እና በአህጉራዊ የሰብአዊ መብት ሰነዶች፣ በብሄራዊ ህጎች እና አሁን ባለው የፍርድ ቤት አሰራር መካከል ያለውን ያለመጣጣም በመመርመር ይህንን ችግር በአጭሩ ለመተንተን ያለመ ነው። የሕጎቹንና የጉዳይ  ጥናቶችን ባካተተ የአስተምህሮ ምርምር ዓለምአቀፍ እና አህጉራዊ የሰብአዊ መብት ሰነዶች፣ የኢትዮጵያ ህጎች እና በሕግ ትርጉም የተቋቋሙ የህግ መርሆዎች፤ የህጋዊነት እና የፍትሐብሔራዊ ይዘትን የሚመለከቱ መርሆዎችን እንደ መጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ በማንሳት እንዴት መተግባር እንደሚቻልና እንዴት እንደሚያስገነዝቡ፣ አሁን ያለው የአገራችን ፍርድ ቤቶች በተለይም የፌዴራል ፍርድ ቤቶች እንዲህ ያሉትን መቃወሚያዎች ወደ ሥረ ነገር የክርክር ደረጃ የማስተላለፍ ልምድና አሰራር ከእነዚህ ከተመሰረቱ መርሆች ጋር የሚጋጭ የሚሆነው በምን መንገዶች እንደሆነ፣. ይህ አሰራር በተከሳሹ ላይ የሚያስከትለው መዘዝ እና የኢትዮጵያ የወንጀል ፍትህ አስተዳደር ስርዓት  አጠቃላይ ታማኝነት ላይ ሊኖረው የሚችለውን ተጽእኖ ምንነት፣ የህጋዊነት እና የወንጀል ክስ የፍትሓብሔራዊ ይዘት ያለው ነው  በሚል በመቃወሚያነት ሲነሱ እነዚህን መርሆችን የበለጠ ውጤታማና እና መብትን ያከበረ አሰራርን ለማረጋገጥ የሚያስችል የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ የክርክር አመራር ስርዓቶችን ማሻሻል  የሚቻልባቸው መንገዶችን ያሉ መሆን ጋር የተያያዙ ጥያቄዎችን በመመስረት፣ ጭብጦቹን ከብዙ ጥቂቶቹን  ለመዳሰስና ፀሐፊው ሊሆን ይገባል በሚለው አግባብ ለመመለስ ይሞከራል፡፡ ሆኖም ለጽሑፉ መነሻ የሆኑ ተጨባጭነት ያላቸው ጉዳዮች የፍርድ ሂደቱን ያልጨረሱም ስላሉ ጽንሰ ሀሳቦቹንና የሰበር ውሳኔ ከመመርመር ውጪ ለጊዜው በዚህ ጽሑፍ ውስጥ ከመጥቀስ ተቆጥቤአለሁ፡፡ ወደፊት ጉዳዮቹ ሲያልቁ ግን ፁሑፉ ተገቢነት ያለውን የምርምር ስራ ማጣቀሻ ደንቦችን በመከተልና በርካታ መዛግብቶችን በመፈተሸ ተሻሽሎ ሊቀርብ እንደሚችል ሙሉ ተስፋ አለኝ፡፡
Показать все...