ru
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Открыть в Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Больше

📈 Аналитический обзор Telegram-канала ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Канал ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 13 342 подписчиков, занимая 1 756 место в категории Транспорт и 2 537 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 13 342 подписчиков.

Согласно последним данным от 17 июня, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 95, а за последние 24 часа — 18, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 41.14%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 15.24% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 5 485 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 2 032 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 16.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 18 июня, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Транспорт.

13 342
Подписчики
+1824 часа
+417 дней
+9530 день
Архив постов
የወልደሃኔ - ዱርጊ የመንገድ ስራ ፕሮጀክት በጥሩ እንቅስቃሴ ላይ ይገኛል ሶዶ፣ ግንቦት 1 ቀን 2016 ዓ/ም ( ኢ.መ.አ ) ፡- የደቡብ ምዕራብ ክልል (ዳውሮ ዞንን ) እና የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል (ጠንባሮ ልዩ ወረዳን) የሚያገናኘው የወልደ ሃኔ - ዱርጊ የመንገድ ስራ ፕሮጀክት በጥሩ አፈጻጸም ላይ ይገኛል ፡፡ መንገዱ በደቡብ ምዕራብ ክልል እና በመካከለኛው ኢትዮጵያ ክልል መካከል ያለውን ግንኙነት እና ተደራሽነት ለማሳደግ ያለመ ወሳኝ የመንገድ መሠረተ ልማት ነው። መንገዱ 41.013 ኪሎ ሜትር ርዝመትና በወረዳ 21.00 ሜትር ፣ በቀበሌ ከተማዎች 17.00 ሜትር እንዲሁም በገጠር ከ 8፡00 ሜትር እስከ 10.00 ሜትር ስፋት ያለውና ትራንስፖርትን ከማሳለጥ እና ለአካባቢው ኢኮኖሚያዊ እድገትን ከማስፋት አኳያ ወሳኝ ነው። የፕሮጀክቱ ወጪ 2,873,433,957.06 የኢትዮጵያ ብር ሙሉ በሙሉ የሚሸፈነው በኢትዮጵያ መንግስት ነው። ኤምሲጂ ኮንስትራክሽን ኃ/የተ/የግ/ማህ ከሜልኮን ኮንስትራክሽን ኃ/የተ/የግ/ማህ በጋራ በመሆን ስራውን በተቋራጭነት የያዘው ሲሆን በማማከሩ በኩል ቤዛ ኃ/የተ/የግ/ማህበር የተሰኘ ሀገር በቀል አማካሪ ድርጅት ከቤዛ ምህንድስና ኬንያ ሊሚትድ ጋር ከተጀመረበት ቀን ጀምሮ እስከ የካቲት 1 / 2024 ዓ.ም ድረስ ቖይታ አድርገዋል ፡፡ ከየካቲት 2 ቀን 2024 ዓ.ም ጀምሮ ደግሞ ኒች ኢንፍራስትራክቸር ኮንሰልቲንግ ኢንጂነርስ በጋራ ከሃብ ኢንጂነርስ ኮንሰልቲንግ ጋር በማገልገል ላይ ይገኛሉ ፡፡ ከፕሮጀክቱ ጅማሮ እስካሁን ድረስ የቅየሳ ስራዎች 41 ኪ.ሜ የተጠናቀቁ ሲሆን የአፈር ምርመራ ፣ የግንባታ ግብአቶች ዳሰሳና የወሰን ማስከበር የግምት ልኬት ሥራዎች ተሰርተዋል፡፡ የአፈርና የድንጋይ ቁፋሮ ፣ የኮንክሪት ጠጠር ማምረት እና የቱቦ ማምረት ፣ የአስፋልት ፕላንት ወደ ሳይቱ የማጓጓዝ እና መሰል ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ፡፡ በቀጣይ የአፈር ቁፋሮ ፣ የሰብ ቤዝ ፣ የቤዝኮርስ እና የፍሳሽ ማስወገጃ ስራዎች የሚሰሩ ይሆናል ፡፡ አርሲ ኦቻ ቀበሌ ፣ ባዛ ሾጣ ቀበሌ ፣ የቀለታ እና የገና ወረዳ መቀመጫ ከተማዎች መንገዱ በዋናነት የሚያገናኛቸው ቦታዎች ናቸው ፡፡ ፕሮጀክቱ በሚያልፍባቸው መስመሮች ውስጥ የተለያዩ የግብርና ምርቶች የሚገኙባቸው በመሆኑ እነዚህ ምርቶችም ወደ ገበያ ተደራሽ እንዲሆኑ ምቹ ሁኔታ ይፈጥርላቸዋል ፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በአካባቢው ያሉ የቱሪስት መስህቦች ተደራሽ እንዲሆኑ ዕድል ይፈጥራል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

መልካም የስቅለትና የትንሳኤ በዓል! ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የስቅለት እና የትንሳኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያለ በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የደስታና የመተሳሰ
መልካም የስቅለትና የትንሳኤ በዓል! ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የስቅለት እና የትንሳኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያለ በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የደስታና የመተሳሰብ እንዲሆንላችሁ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ይመኛል!!

ሦስት ዞኖችን የሚያገናኘው የሞርካ - ጊርጫ ጨንቻ መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት 72 በመቶ ደረሰ አዲስ አበባ ፣ ሚያዚያ 29 ቀን 2016 ዓ / ም ( ኢ.መ.አ ) ፡ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የጋሞ፣ ጎፋ እና ወላይታ ዞኖችን የሚያገናኘው የሞርካ - ጊርጫ- ጨንቻ መንገድ ስራ ፕሮጀክት አፈጻጸም 72 በመቶ ደርሷል። ይህ መንገድ 72.663 ኪ.ሜ የሚሸፍን ሲሆን የመንገዱ ስፋት በወረዳ ከተማዎች 21.5 ሜ.፤በቀበሌ ከተማዎቸ 12 ሜ. በገጠር 8 ሜ ስፋት አለው ። በአሁኑ ወቅት በመንገድ ግንባታው የ39 ነጥብ 45 ኪ.ሜ. የአስፋልት ንጣፍ ሥራ የተከናወነ ሲኾን፣ የሦስት ድልድዮች ግንባታ ሥራም ሙሉ በሙሉ ተጠናቋል። በመኾኑም ከአጠቃላይ የመንገዱ ክፍል 52 ኪሎሜትሩ ወይም 72 በመቶው ተጠናቋል። የፕሮጀክቱን ቀሪ የግንባታ ሥራ በቀጣይ በጀት ዓመት ለማጠናቀቅ ዕቅድ ተቀምጦ እየተሠራ ይገኛል። በዲታ እና ደረማሎ ወረዳዎች መካከል ያለው ተራራ ሁለቱን ወረዳዎች ለሁለት ለያይቶ የነበረ ሲሆን ፕሮጀክቱ ችግሩን በመቅረፍ ሁለቱን አርስ በእርስ በቀላሉ ከማገናኘት አኳያ ትልቅ ሚና ይጫወታል፡፡ ከኪ.ሜ 39+000 እስክ ኪ.ሜ 45+000 ያለው ለዚህ ተራራማ የመንገዱን ክፍል አስፈላጊውን የዲዛይን መፍትሄ በጥናት የመስጠት ሥራ እየተከናወነ ቢሆንም ወሰን ማስከበር ጋር በተያያዘ በአፈጻጸሙ ላይ ተጽዕኖ አሳድሯል፡፡ የሶዶ አካባቢ የግንባታ ፕሮጀክቶች ማኔጀመንት ጽ/ቤት ከአከባቢው መስተዳድር አካላት እና ከአከባቢው ነዋሪዎች ውይይቶች በማድረግ የወሰን ማስከበር ችግሩ ለመፍታት ጥረት እያደረጉ ይገኛሉ፡፡ ለመንገዱ የሚውለው ብር 1,967,496,759.60 (አንድ በሊዮን ዘጠኝ መቶ ስልሳ ሰባ ሚሊዮን አራት መቶ ዘጠና ስድስት ሺህ ሰባት መቶ ሃምሳ ዘጠኝ ብር ከ ስልሳ ሳንቲም) በኢትዮጵያ መንግስት የሚሸፈን ነው፡፡ ግንባታውን እያካሄደ ያለው ቤጂንግ አርባን ኮንስትራክሽን ግሩፕ /ቢዩሲጂ/ ሲሆን የማማከሩን ሥራ ደግሞ ኮር ኮንሰልቲንግ ኢንጂነርስ ኃላ/የተ/የግ/ማ እያከናወነ ይገኛል። ሞርካ፣ዋጫ፣ወይዛ፣ሁሉ ቆዴ፣ዛዳ፣ዶኮና ጨንቻ መንገዱ በዋናነት የሚያገናኛቸው ከተሞች ናቸው። መንገዱ ከዚህ ቀደም በጥርጊያ ደረጃ የነበረ ሲሆን በአሁኑ ወቅት በአስፓልት ኮንክሪት ደረጃ እየተገነባ ይገኛል። የዚህ መንገድ መገንባት የ127 ዓመት ዕድሜ ያላት ጨንቻ ከተማን ሐብቷንና ልምላሜዋን እንድትጠቀም ፡፡ አካባቢው ከፍተኛ የአፕል ፣ድንች ፣የስንዴ ምርት የሚገኝበት በመሆኑ ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ከማድረግም በላይ ለክልላዊና ሀገራዊ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳው ከፍተኛ ነው። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

በቡልቡላ-አላጌ-ባራ-ሚቶ መንገድ ሥራ ፕሮጀክት አስፋልት ማንጠፍ ተጀመረ አዲስ አበባ ፣ ሚያዚያ 15 ቀን 2016 ዓ.ም (ኢ መ አ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልልን ከኦሮሚያ ጋር በቅርበት በሚያገናኘው የቡልቡላ - አላጌ መንገድ ሥራ ፕሮጀክት አስፋልት ማንጠፍ ተጀምሯል፡፡ 38 ኪሎ ሜትር ርዝመትን የሚሸፍነው ይኸው የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ በመገንባት ላይ ይገኛል፡፡ ግንባታውን እያካሄደ የሚገኘው ሀገር በቀሉ የስራ ተቋራጭ ኪቢሽ ኮንስትራክሽን ሲሆን ፣ ዩናይትድ አማካሪ ማሀንዲሶች (ዩኒኮን) ደግሞ የፕሮጀክቱን የማማከርና የቁጥጥር ስራ እያከናወነ ይገኛል ። መንገዱ ከፌደራል መንግስት በተመደበ 878,514,732 (ስምንት መቶ ሰባ ስምንት ሚሊዮን አምስት መቶ አሥራ አራት ሺህ ሰባት መቶ ሰላሳ ሁለት ) ብር ወጪ ነው እየተገነባ የሚገኘው፡፡ በፕሮጀክቱ አሁን ላይ አስፋልት የማንጠፍ ሥራ የተጀመረ ሲሆን ፣ ከአጠቃላይ የመንገዱ ክፍል 8 ኪሎሜትሩን አስፋልት የማልበስ ሥራ ተሠርቷል፡፡     በተጨማሪም የ 33 ኪሎ ሜትር አፈር ሙሌት ፣ የ30 ኪሎ ሜትር ሰብቤዝ ፣ የ15 ኪሎ ሜትር ቤዝኮርስ እንዲሁም የ 72 በመቶ የስትራክቸር ሥራዎች ተሠርተዋል፡፡ ከዚህም ባሻገር የአነስተኛ እና ከፍተኛ ከልቨርቶች ግንባታ ሥራም የፕሮጀክቱ አካል ነው፡፡ ይህም የፕሮጀክቱን አጠቃላይ አፈጻጸም 62 ነጥብ 24 በመቶ ያደርሰዋል፡፡ አሁን ላይ ግንባታውን በቀጣይ ዓመት ለማጠናቀቅም ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ ነው፡፡   በመንገዱ ወሰን ውስጥ ያልተነሱ ንብረቶች ፣ የውኃ እና የመብራት መሥመሮች በፕሮጀክቱ ሂደት ላይ ተፅዕኖ እያሳደሩ ሲሆን ፣ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ቡታጅራ አካባቢ ኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ጽ/ቤት ከወረዳ ፣ ከዞን እና ክልል አመራሮች ጋር በመቀናጀት ችግሩን ለመቅረፍ ጥረት እያደረገ ይገኛል፡፡      ከባቱ -ሐዋሳ በመሰራት ላይ ካለዉን ፈጣን መንገድ ተገንጥሎ እየተካሄደ ያለው ይኸው ፕሮጀክት መነሻውን ቡልቡላ በማድረግ በመስመሩ የሚገኙትን ጂዶ ፣ አላጌ ግብርና ኮሌጅ እና ሚቶ ከተሞችን ደረጃውን በጠበቀ መንገድ ያስተሳስራል፡፡ የመንገድ ግንባታው ሲጠናቀቅ ከዚህ ቀደም ለመጓዝ ይወስድ የነበረውን የሁለት ሠዓታት የጉዞ ጊዜ ወደ ግማሽ ሠዓት ያሳጥረዋል፡፡ በተጨማሪም በአካባቢው የሚመረቱ  የበቆሎ ፣ የቦሎቄ  እና የበርበሬ ምርቶችን ወደ ገበያ  ለማውጣት ብሎም የተሻለ የጤና እና የትምህርት ተቋማት ተደራሽነትን ለማስፋት ጉልህ አስተዋፅኦ እንደሚያበረክት ይታመናል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የአዲስ-ጊቤ ወንዝ መንገድ ከባድ ጥገና በአንድ ዓመት ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሠራ ነው አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 09፣ 2016 (ኢ መአ):- የአዲስ አበባ ጅማ አውራ መንገድ አካል የኾነው የአዲስ-ጊቤ ወንዝ ኮንትራት 2 እና 3 መንገድ ከባድ ጥገና በአንድ ዓመት ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሠራ ነው። ከፍተኛ ሀገራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ማኅበራዊ ፋይዳ ያለው ይኽ ከባድ ጥገና ለግንባታ አመቺነት ሲባል በሁለት ኮንትራቶች ተከፋፍሎ ከአዲስ አበባ እስከ ጊቤ ወንዝ ድረስ ነው በመከናወን ላይ የሚገኘው። ኮንትራት-2(ኹለት) የአዲስ -ጊቤ ወንዝ የመልሶ ግንባታ ፕሮጀክት 64 ኪሎሜትር የሚሸፍን ሲኾን፥ መነሻውን ሰበታ ከተማ ዲማ ላይ በማድረግ ቆራ ከተማ ድረስ ይዘልቃል። ከባድ ጥገናውን ሀገር-በቀሉ ቤአኤካ ጠቅላላ ንግድ ሥራ ኃ/የተ/የግ/ማኅበር በማከናወን ላይ ይገኛል። የማማከር እና የቁጥጥር ሥራውን ኢንጂነር ዘውዴ እስክንድር እና ኩባንያው ኃ/የተ/የግ/ማ ይሠራል፡፡ ለግንባታው የተመደበው 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር ወጪ በኢትዮጵያ መንግስት በጀት ይሸፈናል። አሁን ላይ የአስፋልት ንጣፍ፣የጠጠርና የሌሎች የግንባታ ግብዓቶች ማምረት፣የተለዋጭ መንገድ ማዘጋጀት፣የአስፋልት ድረባ (Asphalt Overlay) ሥራዎች እተከናወኑ የሚገኙ በመኾኑ የጥገና ሥራው በተሻለ የአፈጻጸም ደረጃ ላይ ነዉ የሚገኘው። የከባድ ጥገናው ቀጣይ ክፍል የኾነው ኮንትራት-3 የቆራ-ጊቤ ወንዝ ፕሮጀክት 93 ኪሎሜትሮችን የሚሸፍን ኾኖ መነሻውን ከቆራ ከተማ በማድረግ እስከ ጊቤ ወንዝ ድረስ እየተከናወነ ይገኛል። ሀገር-በቀሎቹ ቲክስ ኮንስትራክሽን ኃ/የተ/የግ/ማኅበር ከኤም.ሲ.ጂ ኮንስትራክሽን ኃ/የተ/የግ/ማኅበር ጋር በጥምረት ከፍተኛ ጥገናውን በማካሄድ ላይ ይገኛሉ፡፡ በተመሳሳይ የማማከርና የቁጥጥር ሥራውን ኤስ ጂ ኮንሰልቲንግ ኢንጂነርስ ኃ/የተ/የግ/ማኅበር ከዴልታ ኮንሰልቲንግ ኃ/የተ/የግ/ማኅበር በጋራ ያከናውናሉ። ለመንገዱ ጥገና የሚውለው የግንባታ ወጪ አንድ ቢሊዮን ስድስት መቶ ሀምሳ አንድ ሚሊዮን ስምንት መቶ ስምንት ሺህ ሶስት መቶ ሀምሳ አንድ ብር (1,651,808,351.17) በፌደራል መንግስት በጀት ነው የተሸፈነው፡፡ አሁን ላይ የግንባታ ግብዓት የማምረት፣ ሰብ ቤዝና ቤዝ ኮርስ የማንጠፍ፣ አስፋልት የማልበስ ሥራ፣ የተበላሹ ቦታዎችን ለይቶ የመቁረጥና በአስፋልት መልሶ የመጠገን ሥራዎች እንዲሁም የአስፋልት ድረባ ሥራ (Asphalt Overlay) በመከናወን ላይ ናቸው፡፡ ባለፈው በጀት ዓመት የተስተዋሉ የሥራ ተቋራጩ የአቅም እና ግብዓት ውስንነቶች እንዲሁም አልፎ አልፎ የሚከሰቱ የፀጥታና ተያያዥ ችግሮች የፕሮጀክቱ ፈተና የነበሩ ቢኾንም፥ ችግሮቹን ለመቅረፍ በኢመአ በኩል ሠፊ ክትትልና ድጋፍ በመደረጉ በአሁኑ ወቅት ፕሮጀክቱ  በጥሩ የአፈፃፀም ሂደት ላይ ይገኛል፡፡ በአጠቃላይ ከባድ ጥገናው ሲጠናቀቅ በአዲስ አበባ-ወልቂጤ-ጅማ ኮሪደር ይስተዋል የነበረውን የትራፊክ እንቅስቃሴ መስተጓጎልና እንግልት ከመቅረፍም ባሻገር በአካባቢዉ የሚመረቱ እንደ ቡና፣ ጤፍ፣ በቆሎ፣ እንሰት፣ ሽንብራ እና አቮካዶ የመሳሰሉ  ምርቶችን በቀላሉ  ወደ ገበያ ለማቅረብ ያስችላል፡፡ ከዚህ ቀደም ለትሽከርካሪ ዕቃ መለዋወጫ የሚወጣውን አላግባብ ወጪ እና የነዳጅ ብክነት ከማስቀረቱም ባለፈ የወጪ ንግዱን በከፍተኛ ኹኔታ ያሳልጣል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

በዘጠኝ ወራት ከ10.35 ቢሊዮን ብር በላይ የመንገድ ፈንድ ገቢ ተሰበሰበ አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 7 ቀን 2016 ዓ.ም (ኢመአ)፡ በዘጠኝ ወራት ውስጥ ከተለያዩ የገቢ ምንጮች ለመንገዶች ጥገና እና የመንገድ ደህንነት ማስፈጸሚያ የሚሆን ብር 10,356,019,307.40 የመንገድ ፈንድ ገቢ ተሰብስቧል፡፡ በተሰበሰበው ገቢ የወቅታዊና መደበኛ የመንገድ ጥገናዎች ሥራዎችም ተከናውነዋል፡፡ ገቢው የተገኘው በነዳጅ ላይ ከተጣለ ታሪፍ ብር ፣ ከተሸከርካሪ ዘይትና ቅባት፣ ከመንገድ ጠቀሜታ ክፍያ ብር እና በክብደት ላይ የተመሰረተ ዓመታዊ የተሸከርካሪ ፈቃድ ማደሻ ነው፡፡ የተሰበሰበውን ገቢ ለመንገድ ጥገና ከማዋል አንፃር በዘጠኝ ወራት ጊዜ ውስጥ ባቀረቡት የክፍያ ሰርቲፊኬት መሰረት የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር(ኢመአ) ብር 4,163,410,907.23 ፣ የክልል ገጠር መንገድ ኤጀንሲዎች ብር 1,726,478,976.99 እና የከተማ መንገድ ኤጀንሲዎች ብር 916,865,104.27 እንዲሁም ለድጋፍ ሰጪ (የአማካሪ ክፍያ) ብር 17,471,811.59፣ ለመንገድ ደህንነት እና መድን ፈንድ አገልግሎት ብር 26,519,109.14 እና የባንክ ፤ለፖስታ ቤት ኮሚሽን ክፍያ ብር 12,770,080.33 በአጠቃለይ በመንገድ ጥገና ጥቅም ላይ እንዲያውሉ ብር 6,863,515,989.55 ተከፍሏቸዋል፡፡ የተመደበው በጀት ለተገቢው አገልግሎት መዋሉን ከማረጋገጥ አኳያ በኢመአ፣ በክልል እና በከተማ የመንገድ ኤጀንሲዎች በሚያስተዳድሯቸው ፕሮጀክቶች ላይ የመስክ ቅኝት የማድረግና የምህንድስና (ቴክኒካል) ኦዲት ሥራ ተከናውኗል፡፡ በተደረገው የመስክ ምልከታና የተለያዩ መደበኛ፣ ወቅታዊና ድንገተኛ የመንገድ ጥገና ሥራዎች መከናወናቸውን ማረጋገጥ ተችሏል፡፡ የመንገድ ፈንዱ መንገዶችን ከመጠበቅና ከመንከባከብ አንጻር ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል፡፡ ውድ የሀገር መዋለ ነዋይ የፈሰሰባቸው መንገዶች እንዳይጎዱ ተገቢውን ጥንገና እንዲያገኙ የማድረጉ ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ። መንገዶች ተገቢውን ጥገና በወቅቱ እንዲያገኙ እና ለመንገድና ትራፊክ ደህንነት ሥራዎች ማስፈፀሚያ በቂና የማያቋርጥ የገንዘብ ፈሰስ በማስፈለጉ ከተለያዩ የገቢ ምንጮች ገቢን ለማሰበሰብ፣ ለመመደብና ለማስተዳደር የመንገድ ፈንድ በአዋጅ ቁጥር 66/89 መቋቋሙ ይታወቃል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

ዒድ ሙባረክ!
ዒድ ሙባረክ!

የባሌ ሮቤ-ጎሮ-ሶፍ ዑመር-ጊኒር መገንጠያ 123 ኪሎሜትር አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ በዕቅዱ መሰረት እየተከናወነ ይገኛል አዲስ አበባ፣ መጋቢት 28፣ 2016 (ኢ መ አ) ፡- በኦሮሚያ ክልል የባሌ እና የምሥራቅ ባሌ ዞኖችን የሚያገናኘው የባሌ ሮቤ-ጎሮ-ሶፍ ዑመር-ጊኒር መገንጠያ 123 ኪሎሜትር አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ በዕቅድ መሰረት እየተከናወነ ይገኛል፡፡   ከአጠቃላይ የግንባታ ሥራው በአሁን ወቅት 14 በመቶው የተጠናቀቀ ሲኾን፣ ግንባታውን የሚያከናውነው ዓለም አቀፉ ቻይና ኮሙኒኬሽን ኮንስትራክሽን ካምፓኒ አሁን ላይ የ49 ኪ.ሜ የጠረጋ፣ የ56 ኪ.ሜ የቁፋሮ እና የ27 ኪ.ሜ የሙሌት ሥራዎችን አከናውኗል፡፡ በተጨማሪም የጠጠር መፍጨት፣ የወሰን ማስከበር፣ የግንባታ ቁሳቁስ መረጣ እና ምርት፣ የአፈር ቆረጣ እንዲሁም የውኃ መፋሰሻ ቱቦዎች ግንባታ ሥራ በመካሄድ ላይ ነው፡፡ የአምስት አነስተኛ እና ከፍተኛ ድልድዮች ግንባታም የፕሮጀክቱ አካል ነው፡፡ በዚህ ዓመት መጨረሻ አስፋልት የማንጠፍ ሥራ ለመጀመርም ዕቅድ ተቀምጦ ነው እየተሠራ የሚገኘው፡፡ ሀገር በቀሉ ስታዲያ ኢነጅነሪንግ ወርክስ ፕሮጀክቱን የማማከር እና ቆጣጣር ሥራ እየሠራ ይገኛል፡፡ ፕሮጀክቱ መነሻውን ከአዲስ አበባ 437 ኪሎሜትር ርቀት ሮቤ ከተማ ላይ አድርጎ ጊኒር-ራይቱ-ኢሚ መንገድ መገንጠያ ድረስ የሚዘልቅ ነው፡፡ በመኾኑም ግንባታው የሶማሌ እና ኦሮሚያ ክልሎችን የሚያገናኘው አውራ መንገድ አካል ከመሆኑም ባሻገር፣ በባሌ እና ምሥራቅ ባሌ ዞኖች የሮቤ፣ መልዩ፣ ሶፍ ዑመር እና ሌሎች በርከት ያሉ ከተሞችን በቅርበት የሚያስተሳስር ነው፡፡ የታሪካዊው ሶፍ ዑመር ዋሻ ምቹ መዳረሻ በመሆንም የቱሪዝም ዘርፉን ያነቃቃል፡፡ የትራንስፖርት ፍሰቱንም በእጅጉ በማቅለል በአካባቢው በስፋት የሚገኙትን የስንዴ፣ ገብስ እና ልዩ ልዩ ቅመማ ቀመሞች በቀላሉ ወደ ገበያ ለማቅረብ ያስችላል፡፡ መንገዱ፣ በገጠር የመንገድ ትከሻን ጨምሮ 8-10 ሜትር ስፋት ሲኖረው፣ በቀበሌ የመንገድ ትከሻና የመንገድ አካፋይን ጨምሮ 13 ሜትር ስፋት ይኖረዋል፣ በወረዳ የመንገድ አካፋይና የእግረኛ መንገድን ጨምሮ 21 ሜትር ስፋት በዞን የመንገድ አካፋይ፣ የእግረኛ መንገድና የመኪና ማረፊያ ጨምሮ 28.5 ሜትር ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ በመገንባት ላይ ይገኛል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads