ru
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Открыть в Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Больше

📈 Аналитический обзор Telegram-канала ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Канал ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 13 331 подписчиков, занимая 1 756 место в категории Транспорт и 2 541 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 13 331 подписчиков.

Согласно последним данным от 17 июня, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 95, а за последние 24 часа — 18, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 41.14%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 15.24% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 5 485 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 2 032 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 16.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 17 июня, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Транспорт.

13 331
Подписчики
+1824 часа
+417 дней
+9530 день
Архив постов
የአስፋልት መንገድ ጥገናን በተመለከተ ወቅቱ የደረሰበትን ቴክኖሎጂ ለመጠቀም የሚያስችል የግብዛቤ ማስጨበጫ ተሰጠ አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 29 ቀን 2017 ዓ.ም (ኢ.መ.አ)፡ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከቻይና ኮሙኒኬሽን ኮንስትራክሽን ካምፓኒ ጋር በጋራ በመሆን የአስፋልት መንገድ ጥገና ቴክኖሎጂ እና የተሻሻሉ የአስፋልት ጥገና ግብሃቶችን በተመለከተ SBS (Styrene S - Butadiene B - Styrene - S) የተሻሻለ አስፋልት እና Super-CRB (Cold Repair Binder) ፖሊመር ማቴሪያል ላይ ያተኮረ ስልጠና ተሰጥቷል። የስልጠናው ዋና አላማ በአሁን ወቅት የአስፋልት መንገድ ጥገና ላይ የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን ለማቃለል እና ጊዜው የደረሰበትን ቴክኖሎጂ በመጠቀም የአስፋልት መንገዶችን በተሻለ ፍጥነት፣ በንፅፅር በተሻለ ዋጋ እና በተሻለ ጥራት ለመጠገን የሚያስችል የግንዛቤ ማስጨበጫ ነው። SBS የተሻሻለ አስፋልት የተሻለ የጥገና ጥራት፣ ቀላል የሆነ የአሰራር ሂደት፣ በንፅፅር እስከ 20 በመቶ የዋጋ ቅናሽ፣ ዝቅተኛ የአካባቢ ብክለት እና በቀላሉ ለመተግበር የሚያስችል በመሆኑ የአስፋልትን ባህሪ በማሻሻል የተሻለ ውጤት ያመጣል። ይህ የተሻሻለ አስፋልት አይነት ከዚህ ቀደም በቻይና ኮሙኒኬሽን ኮንስትራክሽን ካምፓኒ አማካኝነት በአዲስ አበባ ኤርፖርት የአውሮፕላን ማረፊያ መንገድ ማሻሻያ ፕሮጀክት ላይ በተግባር ላይ ውሎ የተሻለ አፈፃፀም ማሳየቱን በስልጠናው ላይ ተገልጿል። በተመሳሳይ የቀረበው Super-CRB ፖሊመርን መጠቀም በአስፋልት ላይ በይበልጥ የሚስተዋሉትን የአስፋልት መጎድጎድ ወይም መበሳት (Pothole) እና የመንገዶች የተሽከርካሪዎችን ጎማ ተከትሎ የመሰርጎድ (Rut) ጉዳቶችን የአስፋልት መንገድ ጥገና ግብዓቶችን ከSuper-CRB ኬሚካል ጋር በማዋሀድ፣ መንገዶችን በፍጥነት፣ በንፅፅር በተሻለ ዋጋ እና በተሻለ ጥራት ለመጠገን ያስችላል። እነዚህ ቴክኖሎጂዎች በተለይ ከፍተኛ የትራፊክ እንቅስቃሴ የሚበዛባቸው መንገዶች ላይ ተግባራዊ ቢደረጉ በጥገና ወቅት የሚወስደውን ጊዜ በማሳጠር እና በተለመደው የጥገና አይነት የሚያስፈልጉ የመሳሪያ ግብሃቶችን በመቀነስ የተሻለ የአስፋልት ጥገና አፈጻጸም እንዲኖር እንዲሁም መንገዶች ተገቢውን ጥገና በተገቢው ወቅት እንዲያገኙ በማድረግ የአገልግሎት ዘመናቸውን ለማራዘም ይረዳል። በስልጠናው ላይ የመንገድ ጥገናውን በመምራትም ሆነ በማስተባበር ከፍተኛ ሚናን የሚጫወቱት የመንገድ አውታር አስተዳደር ቅ/ቢሮዎች፣ ከመንገድ ጥገና ዲስትሪክቶች እና በማዕከል የሚያስተባብሩ ከመንገድ ሀብት አስተዳደር ዘርፍ የስራ ትሥሥር ያላቸው፣ ከምርምር ማዕከል፣ ከግንባታ ፕሮጀክት ማኔጅመንት እና ከአፈፃፀም ጥራት እና ስርዓት አስተዳደር የተወጣጡ ባለሙያዎች ተሳትፈውበታል። በቀጣይም ከኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የምርምር ማዕከል ጋር በጋራ በመሆን ይህንን የአስፋልት መንገድ ጥገና ቴክኖሎጂ በተመረጡ የመንገድ ክፍሎች ላይ ተግባራዊ በማድረግ ከሀገሪቷ የመልክዓ-ምድር አቀማመጥ እና የአየር ፀባይ ጋር ተስማሚነቱን በማረጋገጥ ተጨማሪ ስልጠናዎች የሚሰጡ ይሆናል። በዘርፉ የተሰማሩ የስራ ተቋራጮችም ይህንን ቴክኖሎጂ እንዲጠቀሙ እና ባለሃብቶች ቴክኖሎጂውን በሀገር ውስጥ እንዲያመርቱ የግንዛቤ ማስጨበጫ በመስጠት በስፋት ጥቅም ላይ ማዋል ያስፈልጋል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የኦሮሚያ ክልልን ከአማራ ክልል ጋር የሚያስተሳስረው የሙከጡሪ ኮከብ መስክ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት 88 በመቶ ደርሷል አዲስ አበባ ፣ ጥቅምት 27 ቀን 2017 ዓም (ኢ መ አ):-በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን የውጫሌ ወረዳ መቀመጫ የሆነችውን የሙከጡሪ ከተማን በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን የእንሳሮ ወረዳ ለሚ ከተማን በማገናኘት እስከ ኮከብ መስክ የሚዘልቀው የሙከጡሪ ኮከብ መስክ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በአሁኑ ወቅት 88 በመቶ ደርሷል ፡፡ 59 ኪሎ ሜትር የሚረዝመው ይህ ፕሮጀክት አሁን ላይ 52 ኪሎ ሜትር ያህሉ በአስፋልት ተሸፍኗል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ሙከጡሪ ከተማ ውስጥ የመንገድ ዳር ውሃ ማፋሰሻ ክዳኖች ፣ በገጠር የመንገድ ዳር ማፋሰሻ ቦይ ፣ ለሚ ከተማ ውስጥ አደባባይ እንዲሁም አስር ሜትር የማፋሰሻ ቱቦ የመቅበር ስራ እየተገባደደ ሲሆን ፣ ፕሮጀክቱ አሁን ላይ የማገባደጃ ስራዎች ይቀሩታል፡፡ ግንባታውን እያከናወነ የሚገኘው ዓለም አቀፉ ቻይና ሪልዌይ ቁጥር ሶስት ኢንጂነሪንግ ግሩፕ ሲሆን የማማከሩንና የቁጥጥር ስራውን ኤልዳ ኢንጂነሪንግ ኮንሰልትንት ከዳምራ ኮንሰልቲንግ ጋር በጥምረት እያከናወኑት ይገኛሉ ፡፡ ለግንባታው የሚውለው ሰባት መቶ ስልሳ ስምንት ሚሊዮን ስድስት መ ሃያ ሁለት ሺ ብር በኢትዮጵያ መንግስት እየተሸፈነ ነው ፡፡ መንገዱ በገጠር 10 ሜትር ፣ በቀበሌ 12 ሜትር ፣ በወረዳ ደግሞ 21 ሜትር ስፋ እንዲኖረው ተደርጎ ነው በመገንባት ላይ የሚገኘው፡፡ መንገዱ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ በሚያልፍባቸው አካባቢዎች የሚገኙ የኦሮሚያ እና አማራ ክልል ህዝቦችን ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ግንኙነት ይበልጥ ያጠናክራል ፤ ከዚህም ባሻገር በአካባቢው የሚመረቱ የአዝርእት ምርቶችን እና ጀማ ወንዝ አካባቢ የሚገኙ የማዕድን ምርቶችን በቀላሉ ወደገበያ ለማድረስ ያስችላል፡፡ እንዲሁም የመንገድ ደረጃውን ጠብቆ መገንባት በቅርቡ ግንባታው ተጠናቆ ወደ ማምረት ሂደት የገባው በሃገሪቱ ትልቁ የለሚ ሲሚንቶ ፋብሪካ ምርቱን በቀላሉ ወደ ገበያ እንዲያቀርብ ከማድረግ አንጻር ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረክታል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

4ኛ/ የክልል ፍርድ ቤቶች በተሸሻለው አዋጅ መሰረት ከካሳ ክፍያ ጋር በተያያዘ የፌዴራል ተቋማቱ ተከፋይ የሚሆኑባቸውን ክሶች የመዳኘት ስልጣን የፌዴራል የመጀመሪያ ፍርድ ቤት መሆኑ በግልጽ የተደነገገ መሆኑን በመገንዘብ ክሶቹ በፌዴራል የመጀመሪያ ፍርድ ቤት እንዲታዩ ማድረግ የሚጠበቅባቸው በመሆኑና ለአዋጁ ተግባራዊነት የበኩላቸውን ሚና እንዲጫወቱ ተጠይቋል፤ 5ኛ/ ከሐምሌ 4 ቀን ጀምሮ የሚቀርቡ የንብረት ይነሳልኝ ጥያቄዎች የካሳ ክፍያ በነባርም ሆነ በአዳዲስ ፕሮጄክቶች ላይ ክፍያ የመፈጸም ኃላፊነት የክልልሎች በመሆኑ የማሻሻያ አዋጁ ሙሉ ለሙሉ ተግባራዊ ለማድረግ እና አዋጁ እንዲያመጣ የታሰበውን ለውጥ ለማስገኘት ሁሉም ባለድርሻ አካላት በትኩረት እንዲሰራ ተጠይቋል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

ለህዝብ ጥቅም ሲባል መሬት የሚለቀቅበት፣ ለተነሺዎች ካሳ የሚከፈልበትና ተነሺዎች መልሰው የሚቋቋሙበትን ለመወሰን የወጣው የማሻሻያ አዋጅ ቁጥር 1336/2016 ወደ ተግባር ለማስገባት ውይይት ተካሄደ አዳማ፣ ጥቅምት 21 ቀን 2017 ዓ.ም (ኢመአ)፡ ለህዝብ ጥቅም ሲባል መሬት የሚለቀቅበት፣ ለተነሺዎች ካሳ የሚከፈልበት እና ተነሺዎች መልሰው የሚቋቋሙበትን ለመወሰን የወጣው የማሻሻያ አዋጅ ቁጥር 1336/2016 ወደ ተግባር ለማስገባት ከባድርሻ አካላት ጋር በአዳማ ከተማ ውይይት ተካሄደ ። በውይይት መድረኩ ዋና ዓላማ ለህዝብ ጥቅም ሲባል መሬት የሚለቀቅበት፣ ለተነሺዎች ካሳ የሚከፈልበትና መልሰው የሚቋቋሙበትን ለመወሰን በወጣው አዋጅ ቁጥር 1161/2011 መሰረት ገማች ኮሚቴ የማቋቋም፣ ግምት የመስራትና ካሳ የመክፈል እና ንብረቶች የማስነሳት ስልጣን ለተሰጣቸው የክልል መስተዳድሮች እና ከካሳ ክፍያ ጋር የሚቀርቡ አቤቱታዎችን የመዳኘትና ውሳኔ የመስጠት ስልጣን ያላቸው የክልል ፍርድቤቶችና የፍትህ አካላት እና የፌድራል የመሰረተ ልማት ዘርጊ ተቋማትየማሻሻያ አዋጅ ቁጥር 1336/2016 ለውጥ ባደረገባቸው ኃላፊነቶች ላይ ግንዛቤ ማስጨበጥ ነው፡፡ በዚሁ መሰረት በተለይም ከግምት ሥራ ጋር በቀጥታ የሚገናኙ የክልል ርዕሰ መስተዳድሮች፣ የየመሬት አስዳደደር ቢሮዎች፣ የገጠር መሬት አስተዳደር ቢሮዎች፣ የከተማ አስተዳደር ቢሮዎች፣ የጠቅላይ ፍርድቤቶች፣ የፍትህ ቢሮዎች ፣ የተፈጥሮ ኃብት ቢሮዎች፣ የግብርና ቢሮዎች እና ከፌድራል መሰረተ ልማት ዘርጊ ተቋማትና ሌሎች ጉዳዩ የሚመለከታቸው ተቋማት መካከል የፌድራል የመጀመሪያ ፍርድቤት፣ የከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር፣ የፍትሕ ሚኒስቴር፣ የቆላማና መስኖ ሚኒስቴር ፣ የኢትዮጵያ መብራት አገልግሎት፣ የኢትዩጲያ መብራት ኃይል፣ የኢትዮ ቴሌኮም ፣ የግብርና ሚኒስቴር እና የገንዘብ ሚኒስቴር የሥራ ኃላፊዎች ተሳትፈዋል ። መድረኩን በንግግር የከፈቱት የከተማ እና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ የትምጌታ አሥራት የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራው ወደ ሁሉም ክልሎችና ከተሞች ብሎም ቀበሌዎች የማውረዱና ንቅናቄ በመፍጠር የተሟላ ግንዛቤ መፍጠር ጊዜ የማይሰጠው መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡ አያይዘውም ለሥራው ስኬታማነት ሚኒስተር መ/ቤቱ አስፈላጊውን ድጋፍ ሁሉ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን ገልጸዋል። በተጨማሪም ሁሉም ባለድርሻ አካላት የማሻሻያ አዋጁ እንዲወጣ ገፊ ምክነያት የሆኑትን እጅግ የተጋነነ ነጠላ ዋጋ፣ ምርታማነት ፣ ህገወጥ ግንባታ ፣ተገቢነት የጎደላቸው ክሶች መበራከት መሆኑን ግንዛቤ ውስጥ ማስገባት እጅግ አስፈላጊ መሆኑንና ይህንን አዋጅ ተግባራዊ በማድረግ አስከአሁን የተስተዋሉትን ከካሳ ክፍያ ጋር የተያያዙ መስመር ያልተከሉ አሰራሮችን ፈር ማስያዝ ከሁሉም ባለድርሻ አካላት የሚጠበቅ መሆኑን በአጽእኖት ገልጸዋል፡፡ በመድረኩ ዓዋጅ ቁጥር 1161/ 2011 እና አዋጅ ቁጥር 1336/ 2016 በከተማና መሰረት ልማት ሚኒሰቴር በኩል ቀርበው ሰፊ ውይይት እና ማብራርያ ተደርጎባቸዋል። በአዋጅ ቁጥር 1336/ 2016 መሠረት ከሐምሌ 4 ቀን 2016 ዓም ጀምሮ በይፋ የካሣ ክፍያ ሥርዓት ሙሉ በሙሉ መብቱ ከፌደራል ላይ ተነስቶ ለክልል መሠጠቱ ተገልጿል። በመድረኩ ላይ የማሻሻያ አዋጅ ቁጥር1336/2016 እና የተሸሻለው አዋጅ ማስፈጸሚያ ረቂቅ ደንብ በተመለከተ ገለጻ የተደረገ ሲሆን የሰነዶቹ ዋና ጭብጥ የካሳ ክፍያ የመፈጸም ኃላፊነት ከፌድራል የመሰረተ ልማት ዘርጊ ተቋማት ለክልሎች የተላለፈ መሆኑን፣ ከካሳ ክፍያ ጋር በተያያዘ የሚቀረቡ ክሶች የፌድራል ተቋማቱ ተካፋይ የሚሆኑባቸው ሆኖ ሲገኝ ክሳቸው የሚቀርበው በፌድራል የመጀመሪያ ፍረድቤት መሆኑን፣ ማናቸውም በፍረድቤት የሚሰጡ ውሳኔዎች ፍጻሜ የሚያገኙት የፌድራል የመጀመሪያ ፍርድቤት ፕሬዜደንት ትእዛዝ ሲሰጡ መሆኑን ተገልቷል፡፡ የተሸሻለውን አዋጅ መማስፈጸሚያ ረቂቅ ደንብ አስመለልክቶ በተደረገው ገለጻ የማሻሻያ ደንቡ ትኩረት ያደረገባቸው ለውጥ በተደረገባቸው ድንጋጌዎች ለአፈጻጸም በሚያመች መልኩ ዘርዘር ተገርጎ የቀረበ መሆኑና ሥራ ላይ የነበረው በሚኒስትሮች ምክረቤት የጸደቀው ደንብ ቁጥር 472/2012 ወደፊት ተሸሽሎ በሚወጣው ደንብ ተሸሽሎ አንድ የተጠቃለለ ደንብ እንደሚወጣ ተገልቷል፡፡ በአዋጆቹ እና በረቂቅ ደንቡ ዙሪያ ከተሳታፊዎች ጥያቄዎችና ገንቢ አስተያየቶች የቀረቡ ሲሆን በቀረቡት አስተያየቶችና ጥያቄዎች ላይ ማብራሪያና ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል፡፡ ከፌድራል አልሚ ተቋማት መካከል የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መሐመድ አብዱረሕማን የመንገድ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው የጊዜ ገደብ ተሰርተው እንዲጠናቀቁ በማስቻል ረገድ በግንባታ ሥፍራ ያሉ ቤቶችና ንብረቶች በአዲሱ አዋጅ መሰረት በአፋጣኝ በማንሳት ሁሉም ባለድርሻ አካላት በባለቤትነት ስሜት ኃላፊታቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል፡፡ በሌላ በኩል የማሻሻያ አዋጁ ለውጥ ያደረገበት ከካሰ ክፍያ ጋር የተያያዙ ክሶች የፌድራል ተቋማቱ ዋና መስሪያቤት በሚገኝበት የፌድራል የመጀመሪያ ፍርድ ቤት እንዲሆን ፣ በተቋማቱ ሂሳብ ላይ እግድ የመስጠት ፣ የተቋማቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚዎች ተገደው ውሳኔዎችን እንዲፈጽሙ የማድረግ ስልጣን ለፌድራል የመጀመሪያ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት የተሰጠ ቢሆንም አሁንም የክልል ፍርድ ቤቶች አዳዲስ ክሶችን እየተቀበሉ መሆኑን እና የፍርድ አፈጻጸምም በስፋት ወደ ባንክ እየተላከና በመንግስት ገንዘብ ላይ ተገቢ ያልሆነ ጫና እያሳደረ በመሆኑ የክልል ፍርድ ቤቶች በአዋጁ መሰረት ክሶችን እንዲያስተናግዱ ተጠይቋል፡፡ ከገንዘብ ሚኒስቴር የመጡት የሥራ ኃላፊ በበኩላቸው በጀትን አስመለክቶ የቀረቡትን ጥያቄዎች በተመለከተ ለከሳ ክፍያ የሚውለው ገንዘብ ሶስት ምንጮች እንደሚኖሩት አነሱም፡- የፌድራል መንግስት ለክልሎች ከሚመድበው የበጀት ድጋፍ፣ ክልሎች ከሚሰበስቡት ገቢና የፌድራል መንግስት ፕሮጄክቶችን ታሳቢ በመድረግ ከሚመድበው በጀት እንደሚሆን ገልጸው ክልሎች በራሳቸው በጀት የካሳ ክፍያ ሥራዎችን ማከናወን መጀመር እንደሚገባቸውና ጎን ለጎን ጥያቄዎችን ማቅረብ እንደሚቻል አስረድተዋል፡፡ በተጨማሪም ከፌድራል መንግስት ለካሳ ክፍያ የሚመደበው በጀት ክልሎች አቅም እየፈጠሩና ገቢያቸውን እያሳደጉ ሲሄዱ የካሳ ክፍያ ሙለለሙ በክልሎች የሚፈጸም መሆኑን መረዳት እንደሚያስፈልግ አብራርተዋል፡፡ በመድረኩ ማጠቃለያላይ ከቡር አቶ የትምጌታ አስራት የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስተር ዴታ የሚከተለውን አቅጣጫ ሰጥተዋል ፡- 1ኛ/ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በተሸሻለው አዋጅና በተደረገው የኃላፊነት ለውጥ መሰረት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ፣ 2ኛ/ ውዝፍ ክፍያ ማለት አዋጁ ከጸናበት ከሐምሌ 4 ቀን 2016 በፊት በተቋማቱ ተልከው ክፍያ በመጠባበቅ ላይ የሚገኙ መሆኑን፣ 3ኛ/በወረዳ/ከተማ አስተዳደሮች እጅ የሚገኙ የግምት ሰነዶች በክልሎች በኩል ክፍያቸው መፈጸም የሚገባው መሆኑን፣

ለህዝብ ጥቅም ሲባል መሬት የሚለቀቅበት፣ ለተነሺዎች ካሳ የሚከፈልበትና ተነሺዎች መልሰው የሚቋቋሙበትን ለመወሰን የወጣው የማሻሻያ አዋጅ ቁጥር 1336/2016 ወደ ተግባር ለማስገባት ውይይት ተካሄደ አዳማ፣ ጥቅምት 22 ቀን 2017 ዓ.ም (ኢመአ)፡ ለህዝብ ጥቅም ሲባል መሬት የሚለቀቅበት፣ ለተነሺዎች ካሳ የሚከፈልበት እና ተነሺዎች መልሰው የሚቋቋሙበትን ለመወሰን የወጣው የማሻሻያ አዋጅ ቁጥር 1336/2016 ወደ ተግባር ለማስገባት ከባድርሻ አካላት ጋር በአዳማ ከተማ ውይይት ተካሄደ ። በውይይት መድረኩ የከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር፣ የፍትሕ ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ መብራት ኃይል አገልግሎት፣ የኢትዮ ቴሌኮም ፣ የግብርና ሚኒስቴር እና የገንዘብ ሚኒስቴር የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም በተዋረድ በተቋማቱ ሥር ያሉ አቻ የክልል የሥራ ኃላፊዎች ተሳትፈዋል ። የውይይቱ ዋና ዓላማ አዋጅ ቁጥር 1161/2011 ላይ የነበረውን ከካሣ ክፍያ ጋር የተያያዙ ድንጋጌዎችና ከካሳ ክፍያ ጋር የተያያዙ ክሶች የሚዳኙበትን ሁኔታ ለመወሰን በተሻሻለው አዋጅ ቁጥር 1336/2016 መተካትን በሚመለከት ግንዛቤ ማስጨበጥ ነው፡፡ በዚህም መሠረት ለህዝብ ጥቅም ሲባል የመሬት ይዞታ የሚለቀቅበት ፣ ካሣ የሚከፈልበት ፣ እና ተነሺዎች መልሰው የሚቋቋሙበትን ሁኔታ ለመወሰን በታወጀው ዓዋጅ ዙሪያ ውይይት በማካሄድ ተሳታፊዎች ወደየክልላቸው ወስደው ግንዛቤ የሚያስጨብጡበትን ሁኔታ እንዲፈጠር ማስቻል ነው ። መድረኩን በንግግር የከፈቱት የከተማ እና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ የትምጌታ ዓሥራት የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራው ወደ ሁሉም ክልሎችና ከተሞች ብሎም ቀበሌዎች የማውረዱና ንቅናቄ በመፍጠር የተሟላ ግንዛቤ መፍጠር ጊዜ የማይሰጠው መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡ አያይዘውም ለሥራው ስኬታማነት ሚኒስተር መ/ቤቱ አስፈላጊውን ድጋፍ ሁሉ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን ገልጸዋል። በተጨማሪም ሁሉም ባለድርሻ አካላት የማሻሻያ አዋጁ እንዲወጣ ገፊ ምክነያት የሆኑትን እጅግ የተጋነነ ነጠላ ዋጋ፣ ምርታማነት ፣ ህገወጥ ግንባታ ፣ተገቢነት የጎደላቸው ክሶች መበራከት መሆኑን ግንዛቤ ውስጥ ማስገባት እጅግ አስፈላጊ መሆኑንና ይህንን አዋጅ ተግባራዊ በማድረግ አስከአሁን የተስተዋሉትን ከካሳ ክፍያ ጋር የተያያዙ መስመር ያልተከሉ አሰራሮችን ፈር ማስያዝ ከሁሉም ባለድርሻ አካላት የሚጠበቅ መሆኑን በአጽእኖት ገልጸዋል፡፡ በመድረኩ ዓዋጅ ቁጥር 1161/ 2011 እና አዋጅ ቁጥር 1336/ 2016 በፍትህ ሚኒስቴር ተወካዮች በኩል ቀርበው ሰፊ ውይይት እና ማብራርያ ተደርጎባቸዋል። በአዋጅ ቁጥር 1336/ 2016 መሠረት ከሐምሌ 4 ቀን 2016 ዓም ጀምሮ በይፋ የካሣ ክፍያ ሥርዓት ሙሉ በሙሉ መብቱ ከፌደራል ላይ ተነስቶ ለክልል መሠጠቱ ተገልጿል። በአዋጆቹ ዙሪያ ከተሳታፊዎች ጥያቄዎችና አስተያየቶች ቀርበው ማብራሪያና ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል፡፡ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መሐመድ አብዱረሕማን የመንገድ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው የጊዜ ገደብ ተሰርተው እንዲጠናቀቁ በማስቻል ረገድ በግንባታ ሥፍራ ያሉ ቤቶችና ንብረቶች በአዲሱ አዋጅ መሰረት በአፋጣኝ በማንሳት ሁሉም ባለድርሻ አካላት በባለቤትነት ስሜት ኃላፊታቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል፡፡ በሌላ በኩል የማሻሻያ አዋጁ ለውጥ ያደረገበት ከካሰ ክፍያ ጋር የተያያዙ ክሶች የፌድራል ተቋማቱ ዋና መስሪያቤት በሚገኝበት የፌድራል የመጀመሪያ ፍርድ ቤት እንዲሆን ፣ በተቋማቱ ሂሳብ ላይ እግድ የመስጠት ፣ የተቋማቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚዎች ተገደው ውሳኔዎችን እንዲፈጽሙ የማድረግ ስልጣን ለፌድራል የመጀመሪያ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት የተሰጠ ቢሆንም አሁንም የክልል ፍርድ ቤቶች አዳዲስ ክሶችን እየተቀበሉ መሆኑን እና የፍርድ አፈጻጸምም በስፋት ወደ ባንክ እየተላከና በመንግስት ገንዘብ ላይ ተገቢ ያልሆነ ጫና እያሳደረ በመሆኑ የክልል ፍርድ ቤቶች በአዋጁ መሰረት ክሶችን እንዲያስተናግዱ ተጠይቋል፡፡ በመድረኩ ማጠቃለያ ፡- 1ኛ/ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በተሸሻለው አዋጅና በተደረገው የኃላፊነት ለውጥ መሰረት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ፣ 2ኛ/ ውዝፍ ክፍያ ማለት አዋጁ ከጸናበት ከሐምሌ 4 ቀን 2016 በፊት በተቋማቱ ተልከው ክፍያ በመጠባበቅ ላይ የሚገኙ መሆኑን፣ 3ኛ/በወረዳ/ከተማ አስተዳደሮች እጅ የሚገኙ የግምት ሰነዶች በክልሎች በኩል ክፍያቸው መፈጸም የሚገባው መሆኑን፣ 4ኛ/የክልል ፍርድ ቤቶች በተሸሻለው አዋጅ መሰረት የፌዴራል ተቋማቱ ተከፋይ የሚሆኑባቸውን ክሶች የመዳኘት ስልጣን የፌዴራል የመጀመሪያ ፍርድ ቤት መሆኑ በግልጽ የተደነገገ መሆኑን በመገንዘብ ክሶቹ በፌዴራል የመጀመሪያ ፍርድ ቤት እንዲታዩ ማድረግ የሚጠበቅባቸው በመሆኑና ለአዋጁ ተግባራዊነት የበኩላቸውን ሚና እንዲጫወቱ ተጠይቋል፤ 5ኛ/ ከሐምሌ 4 ቀን ጀምሮ የሚቀርቡ የንብረት ይነሳልኝ ጥያቄዎች የካሳ ክፍያ በነባርም ሆነ በአዳዲስ ፕሮጄክቶች ላይ ክፍያ የመፈጸም ኃላፊነት የክልልሎች በመሆኑ የማሻሻያ አዋጁ ሙሉ ለሙሉ ተግባራዊ ለማድረግ እና አዋጁ እንዲያመጣ የታሰበውን ለውጥ ለማስገኘት ሁሉም ባለድርሻ አካላት በትኩረት እንዲሰራ ተጠይቋል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

ለህዝብ ቅም ሲባል መሬት የሚለቀቅበት፣ ለተነሺዎች ካሳ የሚከፈልበትና ተነሺዎች መልሰው ስለሚቋቋሙበት ለመወሰን የወጣው የመሻሻያ አዋጅ ቁጥር 1336/2016 ወደተግባር ለማስገባት ውይይት ተካሄደ አዳማ፣ ጥቅምት 21 ቀን 2017 ቀን 2016 ዓም (ኢመአ)፡ ለህዝብ ጠቅም ሲባል መሬት የሚለቀቅበት፣ ለተነሺዎች ካሳ የሚከፈልበትና ተነሺዎች መልሰው ስለሚቋቋሙበት ለመወሰን የወጣው የማሻሻያ አዋጅ ቁጥር 1336/2016 ወደተግባር ለማስገባት ከባድርሻ አካላት ጋር በ አዳማ ከተማ ውይይት ተካሄደ ። በውይይት መድረኩ የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር፣ የፍትሕ ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ መብራት ኃይል አገልግሎት፣ የኢትዮ ቴሌኮም ፣ የግብርና ሚኒስቴር እና የገንዘብ ሚኒስቴር የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም በተዋረድ በተቋማቱ ሥር ያሉ አቻ የክልል የሥራ ኃላፊዎች ተሳትፈዋል ። የውይይቱ ዋና ዓላማ አዋጅ ቁጥር 1161/2011 ላይ የነበረውን ከካሣ ክፍያ ጋር የተያያዙ ድንጋጌዎችና ከካሳ ክፍያ ጋር የተያያዙ ክሶች የሚዳኙበትን ሁኔታ ለመወሰን በተሻሻለው አዋጅ ቁጥር 1336/2016 መተካትን በሚመለከት ግንዛቤ ማስጨበጥ ነው፡፡ በዚህም መሠረት ለህዝብ ጥቅም ሲባል የመሬት ይዞታ የሚለቀቅበት ፣ ካሣ የሚከፈልበት ፣ እና ተነሺዎች መልሰው የሚቋቋሙበትን ሁኔታ ለመወሰን በታወጀው ዓዋጅ ዙሪያ ውይይት በማካሄድ ተሳታፊዎች ወደየክልላቸው ወስደው ግንዛቤ የሚያስጨብጡበትን ሁኔታ እንዲፈጠር ማስቻል ነው ። መድረኩን በንግግር የከፈቱት የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ የትምጌታ ዓሥራት የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራው ወደ ሁሉም ክልሎችና ከተሞች ብሎም ቀበሌያት የማውረዱና ንቅናቄ በመፍጠር የተሟላ ግንዛቤ መፍጠር ጊዜ የማይሰጠው መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡ ለሥራው ስኬታማነት ሚኒስተር መ/ቤቱ አስፈላጊውን ድጋፍ ሁሉ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን ገልጸዋል። በማከልም ሁሉም ባለድርሻ አካላት የማሻሻያ አዋጁ እንዲወጣ ገፊ ምክነያት የሆኑትን እጅግ የተጋነነ ነጠላ ዋጋ፣ ምርታማነት ፣ ህገወጥ ግንባታ መበራከትና ተገቢነት የጎደላቸው ክሶች መበራከት መሆኑን ግንዛቤ ውስጥ ማስገባት እጅግ አስፈላጊ መሆኑንና ይህንን አዋጅ ተግባራዊ በማድረግ አስከአሁን የተስተዋሉትን ከካሳ ክፍያ ጋር የተያያዙ መስመር ያልተከሉ አሰራሮችን ፈር ማስያዝ ከሁሉም ባለድርሻ አካላት የሚጠበቅ መሆኑን በአጽእኖት ገልጸዋል፡፡ በመድረኩ ዓዋጅ ቁጥር 1161/ 2011 እና አዋጅ ቁጥር 1336/ 2016 በፍትህ ሚኒስቴር ተወካዮች በኩል ቀርበው ሰፊ ውይይትና ማብራርያ ተደርጎባቸዋል። በአዋጅ ቁጥር 1336/ 2016 መሠረት ከሐምሌ 4 ቀን 2016 ዓም ጀምሮ በይፋ የካሣ ክፍያ ሥርዓት ሙሉ በሙሉ መብቱ ከፌደራል ላይ ተነስቶ ለክልል መሠጠቱ ተገልጿል። በአዋጆቹ ዙሪያ ከተሳታፊዎች ጥያቄዎችና አስተያየቶች ቀርበው ማብራሪያና ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል፡፡ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መሐመድ አብዱረሕማን የመንገድ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው የጊዜ ገደብ ተሰርተው እንዲጠናቀቁ በማስቻል ረገድ በግንባታ ሥፍራ ያሉ ቤቶችና ንብረቶች በአዲሱ አዋጅ መሰረት በአፋጣኝ በማንሳት ሁሉም ባለድርሻ አካላት በባለቤትነት ስሜት ኃላፊታቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል፡፡ በሌላ በኩል የማሻሻያ አዋጁ ለውጥ ያደረገበት ከካሰ ክፍያ ጋር የተያያዙ ክሶች የፌድራል ተቋማቱ ዋና መስሪያቤት በሚገኝበት የፌድራል የመጀመሪያ ፍረድቤት እንዲሆን ፣ በተቋማቱ ሂሳብላ ላይ እግድ የመስጠት ፣ የተቋማቱ ዋና ሥራአስፈጻሚዎች ተገደው ውሳኔዎችን እንዲፈጽሙ የማድረግ ስልጣን ለፌድራል የመጀመሪያ ፍርድቤት ፕሬዜደንት የተሰጠ ቢሆንም አሁንም የክልል ፍርድቤቶች አዳዲስ ክሶችን እየተቀበሉ መሆኑን እና የፍርድ አፈጻጸምም በስፋት ወደ ባንክ እየተላከና በመንግስት ገንዘብ ላይ ተገቢ ያልሆነ ጫና እያሳደረ በመሆኑ የክልል ፍርዴቶች በአዋጁ መሰረት ክሶችን እንዲያስተናግዱ ተጠይቋል፡፡ በመድረኩ ማጠቃለያ ፡- 1ኛ/ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በተሸሻለው አዋጅና በተደረገው የኃላፊነት ለውጥ መሰረት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ፣ 2ኛ/ ውዝፍ ክፍያ ማለት አዋጁ ከጸናበት ከሐምሌ 4 ቀን 2016 በፊት ወተተቋማቱ ተልከው ክፍያ በመጠባበቅ ላይ የሚገኙ ማለት መሆኑን፣ 3ኛ/በወረዳ/ከተማ አስተዳደሮች እጅ የሚገኙ የግምት ሰነዶች በክልሎች በኩል ክፍያቸው መፈጸም የሚገባው መሆኑን፣ 4ኛ/የክልል ፍርድቤቶች በተሸሻለው አዋጅ መሰረት የፌድራል ተቋማቱ ተካፋይ የሚሆኑባቸውን ክሶች የመዳኘት ስልጣን የፌድራል የመጀመሪያ ፍርድቤት መሆኑ በግልጽ የተደነገገ መሆኑን በመገንዘብ ክሶቹ በፌድራል የመጀመሪያ ፍርድቤት እንዲታዩ ማድረግ የሚጠበቅባቸው በመሆኑና ለአዋጁ ተግባራዊነት የበኩላቸውን ሚና እንዲጫወቱ ተጠይቋል፤ 5ኛ/ ከሐምሌ 4 ቀን ጀምሮ የሚቀረቡ የንብረት ይነሳልኝ ጥያቄዎች የካሳ ክፍያ በነባርም ሆነ ባዳዲስ ፕሮጄክቶች ላይ ክፍያ የመፈጸም ኃላፊነት የክልልሎች በመሆኑን የማሻሻያ አዋጁኑ ሙሉ ለሙሉ ተግባራዊ ለማድረግ እና አዋጁ እንዲያመጣ የታሰበውን ለውጥ ለማስገኘት ሁሉም ባለድርሻ አካላት በትኩረት እንዲሰራ ተጠይቋል፡፡

በዲስትሪክቱ የጥገና ስራዎች በመከናወን ላይ ይገኛሉ አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 20 ቀን 2016 ዓ.ም (ኢመአ) ፡- የኮምቦልቻ መንገድ ጥገና ዲስትሪክት የተለያዩ የመደበኛና ወቅታዊ የጥገና ስራዎች በማካሄድ ላይ ይገኛል፡፡ የኮምቦልቻ ዲስትሪክት በ2017 በጀት ዓመት የወልዲያ ከተማ አስፋልት ስራ ፕሮጀክትን ጨምሮ 1,070 ኪሎ ሜትር የመንገድ ጥገና ስራዎችን ለማካሄድ አቅዶ እየሰራ ይገኛል፡፡ በበጀት ዓመቱ እነዚህን የጥገና እና የግንባታ ስራዎች ለማካሄድ ለዲስትሪክቱ የተመደበው ጠቅላላ የገንዘብ መጠን 1,234,465,659 (አንድ ቢሊየን ሁለት መቶ ሰላሳ አራት ሚሊየን አራት መቶ ስልሳ አምስት ሺህ ስድስት መቶ ሀምሳ ዘጠኝ ብር) ነው፡፡ በዚህም ረገድ በበጀት ዓመቱ አራት ወራት ውስጥ 387,161,309 ብር ወጪ በማድረግ 320 ኪሎ ሜትር የሚሸፍኑ በርካታ ስራዎችን በራስ ሀይል ለማከናወን ተችሏል፡፡ በተጨማሪም ቴዎድሮስ ስሜነህ ጠቅላላ የስራ ተቋራጭ እና ኢትዮ ካናዲያን ቢዝነስ ግሩፕ በተባሉ የግል የስራ ተቋራጮች እንዲሁም በአማራ መንገድ ስራዎች ድርጅት 16,110,103 ብር ወጪ በማድረግ 13.88 ኪሎ ሜትር የጥገና ስራዎችን ለማከናወን ተችሏል፡፡ በአጠቃላይ በዲስትሪክቱ ባለፉት የበጀት ዓመቱ አራት ወራት ውስጥ 403,271,412.99 ብር ወጪ በማድረግ 333.67 ኪሎ ሜትር ወይም የዕቅዱን 89.39 በመቶ ስራ ለማከናወን ተችሏል፡፡ በአካባቢው አልፎ አልፎ የሚስተዋሉ የጸጥታ እና የወሰን ማስከበር ችግሮች በዲስትሪክቱ ስራዎች ላይ ተፅዕኖ ቢያሳድሩም ፤ ዲስትሪክቱ እነዚህን ችግሮች በመቋቋም በርካታ ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

CALL FOR PAPERS Office of the Conference Secretariat Ethiopian Roads Administration (ERA), Ras Abebe Aregay Street, Post Office Box: 1770, Website: www.iloethiopia2025.gov.et

በበጀት አመቱ በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች ለመንገዶች ጥገና ተገቢዉ ትኩረት ተሰጥቶ ይሰራል አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 6፣ 2017 (ኢ መ አ):- በበጀት አመቱ በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች ለመንገዶች ጥገና ተገቢዉ ትኩረት ተሰጥቶ ይሰራል፤ ለመንገዶች ጥገና የሚውል መዋእለ ነዋይ የማሰባሰብ ሥራም ይከናወወናል ። በአዋጅ ቁጥር 66/1989 ተቋቁም የመንገድ ጥገና ገቢ የማሰባሰብ ተግባራትን ያከናውን የነበረው የኢትዮጵያ መንገድ ፈንድ ጽህፈት ቤት በአዋጅ ቁጥር 1263/2014 ከየካቲት 1 ቀን 2014 ዓም ጀምሮ ከኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ጋር መቀላቀሉን ሥራው በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የመንገድ ፈንድ ዳይሬክቶሬት አማካኝነት እየተከናወነ ይገኛል፡፡ የመንገዶች ጥገና ሥራው በዋና በዋናነት በፌዴራል ደረጃ በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር፣ በሁለቱ የከተማ አስተዳደሮች፣ በክልሎችና በክልሎቹ በሚገኙ ዋና ዋና ከተሞች የሚከናወን ነው፡፡ የመንገድ ፈንድ ገቢ የሚሰበሰበው ለመንገድ ጥገና ከተጣለ የነዳጅ ታሪፍ፣ ተሽከርካሪ ዘይት እና ቅባት ሽያጭ ላይ ከተጣለ ታሪፍ፣ ከመንገድ ጠቀሜታ ክፍያ፣ በክብደት ላይ የተመሠረተ ዓመታዊ የተሽከርካሪ ፈቃድ ማደሻ ክፍያ እንዲሁም በሕግ ከተፈቀደ ክብደት በላይ በመጫን ከሚጣል ቅጣት ላይ ነው። በተለያዩ መንገዶች ገቢ ከመሰብሰብ ባለፈም የተሰበሰበውን ገንዘብ ለመንገድ ኤጀንሲዎች በተቀመጠላቸው ቀመር መሠረት ማከፋፈል እና ለመንገድ ኤጀንሲዎች የተሰጠው ገንዘብ ለታለመት ዓላማ መዋሉን የመከታተል ሥራ ይሰራል። በተጨማሪም ፈንዱ በ2017 በጀት ዓመት ክብደት ላይ የተመሠረተ ዓመታዊ የተሽከርካሪ ማደሻ ክፍያ በዲጅታል አማራጭ እንዲጀመር ለማድረግ የሚያስችሉ የተለያዩ እንቅስቃሴዎችን እየተደረጉ ይገኛሉ። የመንገድ ፈንድ በከፍተኛ የሀገር ሀብት የተገነቡ መንገዶች እና ድልድዮች በተቀመጠላቸው የዲዛይን ዕድሜ መሠረት እንዲያገለግሉ፣ አስፈላጊው ጥገና እንዲደረግላቸው እና ተገቢውን አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ፣ ለፌዴራል (ለመንገድ ጥገና ዲስትሪክቶች )፣ ለከተማ እና ክልል መንገድ ኤጀንሲዎች በየዓመቱ የበጀት ድልድል ያደርጋል። በዚህ ዓመትም የመንገድ መልሶ ግንባታ (Rehabilitation)፣ የመንገድ ማሻሻያ (Upgrading) ሥራ ቁልፍ የትኩረት መስኮች ላይ የተለያዩ ግቦችን ተቀምጠው እየተሠራ ይገኛል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የሳውላ -ቃቆ ሎት-2 የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት እየተካሄደ ይገኛል ጂንካ፣ ጥቅምት 4 ቀን 2017 ዓ.ም (ኢ መ አ) ፡ በደቡብ ኦሞ ስር የሚገኘው የሳውላ -ቃቆ ሎት- ሁለት መንገድ ፕሮጀክት በራስ ሀይል ነው እየተካሄደ የሚገኘው ። የግንባታው አሁናዊ አጠቃላይ አፈፃፀም 64 በመቶ የደረሰ ሲሆን ይህንኑ እንቅስቃሴ አጠናክሮ ለመቀጠል እየተሰራ ነው። በእስካሁኑ የግንባታ እንቅስቃሴ ከተሰሩ ስራዎች ውስጥ የአፈር ቆረጣ እና የሙሌት የድሬኔጅ ፣ የሰቤዝ ፣የግንብ ፣እንዲሁም የቤዝ ኮርስ ስራዎችን በመሰራት ላይ ነው ። 29 ነጥብ7 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነው የሳውላ -ቃቆ የመንገድ ፕሮጀክት በግራቭል እና ዲቢኤስቲ ደረጃ በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ሶዶ ዲስትሪክት በራስ ሀይል እየተገነባ ነው። ፕሮጀክቱን ለማካሄድ አገልግሎት ላይ የሚውለውን 442,339,654.92 ብር የሚሸፈነው ኢትዮጵያ መንግስት ነው። ከዚህ ቀደም ምንም አይነት የመንገድ መሰረተ ልማት ያልተዘረጋበት መንገድ በመሆኑ ለመንገዱ ተጠቃሚዎች እጅግ አስቸጋሪ ሆኖ ቆይቷል። የሳውላ- ቃቆ መንገድ ፕሮጀክት ተገንብቶ ሲጠናቀቅ ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ እና ማኅበራዊ ጠቀሜታን የሚያስተናግድ ይሆናል። ይህ ፕሮጀክት ከአዲስ አበባ- ጂንካ ለመጓዝ በኮንሶ አርባምንጭን በማቋረጥ 784 ኪሎ ሜትር ይወስድ የነበረ ሲሆን የመንገዱ መገንባት ከጂንካ -ቃቆ- ሳውላ- በወላይታ ሶዶ -አዲስ አበባ ለመሄድ በተሽከርካሪ እስከ 150 ኪሎ ሜትር ያሳጥረዋል። የመንገዱ መገንባት በርካታ ዞኖችን ወረዳዎችን እና ቀበሌዎችን እንደ ጫሊ፣ በኒታ፣ አሾ እና ሌሎችንም በመንገድ መሰረተ ልማት የሚያገናኝ ይሆናል። ይህ መንገድ የተሽከርካሪዎችን የጉዞ ጊዜን በማሳጠር ያሰቡት ቦታ መድረስ ከማስቻሉም ባለፈ ካላስፈላጊ የተሽከርካሪ መለዋወጫ ወጪ በመቀነስ መንገዱ የጎላ አስተዋጾዖ ይኖረዋል። በዞኑ በስፋት የሚገኘውን የማር እና የሰብል ምርቶችን እንደ በቆሎ ማሽላ እንዲሁም የቅባት እህሎችን የለውዝ ምርት ውጤቶችን ወደ ማዕከላዊ ገበያ በጥራት እና በፍጥነት በማድረስ አምራችና ሸማቾችን ያገናኛል። በመንገድ ፕሮጀክቱ ውስጥ አነስተኛ፣ ከፍተኛ ፍሳሽ ማስተላለፊያ ቱቦዎች፣ ከልቨርቶች እንዲሁም የድልድዮች ግንባታ ተካቶ እየተሰራ ይገኛል፡፡ በኢትዮጵያ የኮንስትራክሽን ዲዛይን እና ሱፐር ቪዥን ስራዎች ኮርፖሬሽን ፕሮጀክቱን የማማከር እና የመቆጣጠር ሥራ እያከናወነ ይገኛል። የመንገድ ፕሮጀክቱ ግንባታ የጎን ስፋት ትካሻን ጨምሮ በከተማ 14 ሜትር ስፋት ሲኖረው በገጠ 7 ሜትር ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ በመገንባት ላይ ነው። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads