ru
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Открыть в Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Больше

📈 Аналитический обзор Telegram-канала ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Канал ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 13 475 подписчиков, занимая 1 732 место в категории Транспорт и 2 491 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 13 475 подписчиков.

Согласно последним данным от 29 июня, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 209, а за последние 24 часа — 5, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 36.12%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 15.66% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 4 868 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 2 111 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 11.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 30 июня, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Транспорт.

13 475
Подписчики
+524 часа
+987 дней
+20930 день
Архив постов
የሶዶ-ዲንኬ 86 ነጥብ 22 ኪ.ሜ አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ በማጠቃለያ ምዕራፍ ላይ ይገኛል የወላይታ እና ጋሞ ዞኖችን የሚያገናኘው የሶዶ-ዲንኬ 86 ነጥብ 22 ኪ.ሜ አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ በማጠቃለያ ምዕራፍ ላይ ይገኛል። በፕሮጀክቱ አሁን ላይ የ75 ነጥብ 74 ኪ.ሜ አስፋልት የማንጠፍ ሥራ የተከናወነ ሲሆን፥ ከአጠቃላይ የግንባታ ሥራው 92 በመቶው ተጠናቅቋል። ቀሪ የግንባታ ሥራዎችን እስከ ታኅሳስ ወር 2016 ለማጠናቀቅ ዕቅድ ተቀምጧል። በተጨማሪም የ ሥድስት ድልድዮች፣ ከልቨርቶች፣ የሥምንት ኪ.ሜ የመንገድ ትከሻ እንዲሁም የ 28 ኪ.ሜ የውኃ መፋሰሻ ግንባታ ሥራ ተጠናቅቋል። የሰብቤዝ እና ቤዝኮርስ ሥራ እየተከናወነ ይገኛል። ግንባታውን ቻይና ሬይልዌይ ሰቨንዝ ግሩፕ ከአፍሪካ ልማት ባንክ በተገኘ 1,054,003,610.30 (አንድ ቢሊዮን ሃምሳ አራት ሚሊዮን) ብር ወጪ እያከናወነ ይገኛል፡፡ የማማከር እና የቁጥጥሩን ሥራ የሱዳኑ ኒውቴክ ኮንሰልቲንግ ግሩፕ ከሀገር በቀሉ ኔት ኮንሰልት ኃ/የተ/የግ/ማኅበር ጋር በጥምረት ይሠራሉ፡፡ በፕሮጀክቱ የከተማ ክልል ማለትም በሶዶ እና ሠላም በር ከተሞች ከወሰን ማስከበር ጋር በተያያዘ የተነሱ ጉዳዮች በወቅቱ እልባት አለማግኘታቸው፣ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ እንዲሁም የግንባታ ዕቃዎች የግብዓት እጥረት እና የዋጋ መናር፣ በግንባታው ሂደት ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ አሳድረዋል። ከወሰን ማስከበር ጋር በተገናኘ የተነሱ ጉዳዮችን ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት ችግሩን መቅረፍ ተችሏል፡፡ በሥራ ተቋራጩ በኩል  ከገንዘብ ፍሰት ጋር የተያያዙ ችግሮቹን ቀርፎ ግንባታውን እንዲያፋጥን፥ በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር አስፈላጊው ድጋፍ እና ክትትል ተደርጓል፡፡ የመንገዱ የቀድሞ ይዞታ በጠጠር ደረጃ የነበረ እና በተለያዩ ጊዜያት የመሸርሸር አደጋ እየደረሰበት የትራንስፖርት አገልግሎቱን ፈታኝ አድርጎት ቆይቷል፡፡ በመሆኑም ሥፍራው ካለው ዕምቅ የተፈጥሮ ሀብት እና በርካታ ሀገራዊ ፋይዳ አንፃር በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ እየተገነባ ይገኛል፡፡ ፕሮጀክቱ ዕውን ሲሆን የኹለቱን ዞን ወንድማማች ሕዝቦች የእርስ በእርስ ግንኙነት ይበልጥ ያጠናክራል፡፡ በአካባቢው የሚመረቱትን እንደ ቡና፣ ካዛባ፣ በቆሎ፣ ስንዴ፣ ጤፍ እና ቅቤ ምርቶች ወደ መሐል ገበያ ለማቅረብ ከፍተኛ ፋይዳ ይኖረዋል፡፡ ከዚህም ባለፈ መንገዱ የማዜ ብሔራዊ ፓርክ መዳረሻ እንደመሆኑ ፓርኩን ለቱሪስቶች ምቹ በማድረግ ረገድ አስተዋጾው የጎላ ነው፡፡ የጤና፣ የትምህርት እና ሌሎች መሰል የማኅበራዊ ተቋማት ተደራሽነትን ያሰፋል፡፡ መንገዱ በከተማ 12 ሜትር የመኪና መንገድ፣ 2.5 ሜትር የፓርኪንግ መስመር (በሁለቱም አቅጣጫ)፣ 3.5 ሜትር የእግረኛ መንገድ (በሁለቱም አቅጣጫ) እና 2 ሜትር የመንገድ አካፋይ አለው፡፡ እንዲሁም በወረዳ መቀመጫ 14 ሜትር የመኪና መንገድ እና 2.5 ሜትር የእግረኛ መንገድ (በሁለቱም አቅጣጫ) ይኖረዋል፡፡ የዚሁ መንገድ ቀጣይ ምዕራፍ የዲንኬ-ሳውላ ኮንትራት ኹለት አስፋልት መንገድ በግንባታ ሒደት ላይ እያለ ከአፈጻጸም ጋር ባጋጠሙ ችግሮች ግንባታው እንዲቋረጥ መደረጉ ይታወቃል፡፡ በአሁኑ ጊዜም ግንባታውን ለማስቀጠል እንዲቻል ጥሩ አፈጻጸም ያላቸው የሥራ ተቋራጮች እንዲጫረቱ የተጋበዙ ሲሆን ሒደቱንም በማጠናቀቅ በአዲሱ በጀት ዓመት ግንባታው እንደሚጀመር ይጠበቃል፡፡

በፀጥታ ችግር ተስተጎጉሎ የነበረው ኮንትራት 2 አንገረብ-አሽሬ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት አሁን ላይ በጥሩ አፈፃፀም ላይ ይገኛል። የአይከል-ዙፋን-አንገረብ ኮንትራት 2 አንገረብ-አሽሬ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት 71.5 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለውና ከመንግስት በተመደበ በጀት በ1,955,438,532.41 (አንድ ቢሊዮን ዘጠኝ መቶ ሃምሳ አምስት ሚሊዮን አራት መቶ ሰላሳ ስምንት ሺህ አምስት መቶ ሰላሳ ሁለት ብር ከአርባ አንድ ሳንቲም ) በአስፋልት ደረጃ እየተገነባ ይገኛል። ፕሮጀክቱ የሚካሄድበት መልክኣ ምድራዊ አቀማመጥ 10.5 ኪሎ ሜትር ወይም 14.75% ሜዳማ (Flat ) ፣ 17.2 ኪሎ ሜትር ወይም 24.17% ተራራማ (Mountainous) ፣ 32.00 ኪሎ ሜትር ወይም 44.98% ዳገታማ (Rolling) እና 7.4 ኪሎ ሜትር ወይም 10.40% ሸንተራራማ (Escarpment) ነው። የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ በመካሄድ ላይ የሚገኘው ቻይና ዉዪ በተባለ ዓለም አቀፍ የስራ ተቋራጭ ድርጅት ነው። ሮድ ዲዛይን ኤንድ ዴቨሎፕመንት ኮንስልታንት ኃ.የተ.የግ.ማ ደግሞ የመንገድ ግንባታውን ጥራት በመቆጣጠር እና በማማከር ላይ ይገኛል። መንገዱ በወረዳ 21.5 ሜትር ፣ በቀበሌ 9.5 ሜትር እና በገጠር ከ 7.5 እስከ 8.25 ሜትር ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ በመገንባት ላይ ነው፡፡ ከዚህ ቀደም በከፊል በገጠር መንገድ ደረጃ የነበረው ይኸው መንገድ በአሁኑ ወቅት ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳው ከግምት ውስጥ ገብቶ በአስፋልት ደረጃ በመገንባት ላይ ይገኛል፡፡ ፕሮጀክቱ የአፈር ጠረጋ ፣ ቆረጣና ሙሌት ፣ የሰብ ቤዝ ፣ የቤዝ ኮርስ ፣ የአስፋልት ንጣፍ ፣ የስትራክቸር ፣ የሰባት ድልድዮች እና ተጨማሪ የውሃ መተላለፊያ ቦይ ግንባታዎችን ፣ የትራፊክ ምልክቶችን የመትከል እና ሌሎች ልዩ ልዩ ስራዎችን ባካተተ መልኩ ነው በመገንባት ላይ የሚገኘው፡፡ ከፕሮጀክቱ ጅማሮ አንስቶ እስካሁን የስድስት ትላልቅ ድልድዮች ግንባታ የተጠናቀቀ ሲሆን ፣ የ50 ኪሎ ሜትር አስፓልት ስራም አልቋል። ከዚህም ባሻገር ከ80% በላይ የፕሮጀክቱ የአፈር ሙሌት እና ቆረጣ ስራ ተጠናቋል። የስራ ተቋራጩ በቀሪዎቹ ቀጣይ ጊዜአት የመንገድ ላይ ምልክቶችን በመትከል ፣ ኪሎ ሜትር 76 አካባቢ የድንጋይ ቁፋሮ በመጨረስ ፣ ኪሎ ሜትር 70+180 አካባቢ የሚገኘውን ድልድይ ግንባታ በማጠናቀቅ እና ቀሪ የአስፋልት ንጣፍ ስራዎችን በማካሄድ አጠቃላይ የመንገድ ግንባታ ስራውን በሰኔ ወር 2016 ዓ.ም እንደሚያጠናቅቅ ይጠበቃል። ፕሮጀክቱ በሚካሄድበት አካባቢ ተፈጥሮ የነበረው የፀጥታ ችግር ፤ ከወሰን ማስከበር ጋር የተያያዙ ችግሮች ፤ እንዲሁም በሀገር አቀፍ ደረጃ ተፈጥሮ የነበረው የሲሚንቶ አቅርቦት እጥረት በፕሮጀክቱ አፈጻጸም ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ቢያሳድሩም እነዚህን ችግሮች በከፊል በመቀረፋቸው በአሁኑ ወቅት ፕሮጀክቱ በጥሩ አፈፃፀም ላይ ይገኛል። ፕሮጀክቱ የሚካሄድበት አካባቢ የሰሊጥ ፣ የጥጥ ፣ የማሽላ እና የቦሎቄ ምርቶች በስፋት የሚመረቱበት ባለ ብዙ ፀጋ ቦታ ነው። የመንገድ ፕሮጀክቱ ከሌሎች ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳዎች ባሻገር ይህንኑ ታሳቢ ተደርጎ እና የአካባቢው አርሶ አደሮች ምቹ የትራንስፖርት አገልግሎት በመጠቀም ከምርቶቻቸው ተገቢውን ጥቅም እንዲያገኙ ለማስቻል ታስቦ ነው በመገንባት ላይ የሚገኘው፡፡ ከዚህም ባሻገር የማሰሮ እና የአሸሬ ወረዳዎችን እንዲሁም የዙፋን ፣ የማይነገድ እና የዶጋው ቀበሌዎችን በአቋራጭ በማገናኘት ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ መስተጋብራቸውን ይበልጥ ያጠናክራል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የኦሞ-ሳይ እና ሌፍት ካናል ብሪጅ (ሎት-1) መንገድ ፕሮጀክት በጥሩ አፈጻጸም ላይ ይገኛል ጅንካ፣ ግንቦት 29፣ 2015 (ኢመአ)፡ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል በቤንች ማጂ ዞን በማጂ ወረዳ እየተገነባ ያለው የኦሞ-ሳይ እና ሌፍት ካናል ብሪጅ (ሎት-1) በዕቅዱ መሰረት እየተከናወነ ይገኛል፡፡ መንገዱ 68 ኪ.ሜ ርዝመት ያለው ሲሆን ለፕሮጀክቱ የሚያስፈልገው ወጪ ብር 1,882,967,504.80 ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያ መንግስት የተሸፈነ ነው፡፡ ግንባታውን ዮቴክ ኮንስትራክሽን ኃ/የተ/የግ/ማህበር የተባለ የሥራ ተቋራጭ በማከናወን ላይ የሚገኝ ሲሆን የማማከሩን ሥራ ደግሞ ቤስት ኮንሰልቲንግ ኢንጂነርስ ኃ/የተ/የግ/ማህበር እያከናወነ ይገኛል፡፡ ግንባታው የተጀመረው ታህሳስ 17 ቀን 2014 ዓ.ም ሲሆን የፕሮጀክቱ አሁናዊ ገጽታ በኪ.ሜ. 14.54 እና በመቶኛ፡ 21.39 ነው፡፡ ከፕሮጀክቱ ጅማሮ እስካሁን የዲዛይን፣ የለውጥ መንገድ የጠረጋ፣ የአፈር ቆረጣ እና የአፈር ሙሌት ስራዎች ተሰርተዋል፡፡ መስመሩ ከዚህ በፊት ደረጃውን የጠበቀ የመንገድ አውታር ያልተዘረጋበት ሲሆን መንገዱ ለአካባቢው ሕብረተሰብ ሆነ ለሀገራችን ያለው ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ፋይዳ ከግምት ውስጥ በማስገባት በአስፓልት ኮንክሪት ደረጃ እየተገነባ ይገኛል፡፡ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ በዋናነት ደቡብ ምዕራብ ኦሞ ዞን እና ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል (ማጂን ጨምሮ ሌሎች የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ አካባቢዎችን) እንዲሁም ዋና መንገዶችን በማገናኘት ለአካባቢው ማህበረሰብ ብሎም ለሀገሪችን ከፍተኛ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ጠቀሜታን ያለው ነው፡፡ የፕሮጀክቱ መነሻ የኦሞ-ወንዝ የሚያቋርጥበት ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በስፋት የግብርና ምርቶች በተለይም በአካባቢው ለተገነቡ የስኳር ፋብሪካ ግብዓቶችን እንዲሁም የስኳር ምርቶችን በቤንች ማጂ በኩል ወደ ተለያዪ የአገራችን ከተሞች በተሻለ የጊዜ ፍጥነት ለማድረስ ከፍተኛ ጥቅም ይኖረዋል፡፡ በተጨማሪም የአሞ ብሔራዊ ፓርክ የቱሪዝም መዳረሻ የሚገኝበት አካካቢ ከመሆኑ አንፃር ለአካባቢው ብሎም ለሀገሪቷ ቱሪዝም ትልቅ ፋይዳ አለው፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

ከአምቦ እስከ ጉደር ከተማ የሚዘልቀው የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በአሁኑ ወቅት በጥሩ አፈፃፀም ላይ ይገኛል። የአምቦ-ጉደር የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት 19 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለውና በመንግሥት በተመደበ 1,038,722,506.06 (አንድ ቢሊዮን ሰላሳ ስምንት ሚሊዮን ሰባት መቶ ሃያ ሁለት ሺህ አምስት መቶ ስድስት ብር ከዜሮ ስድስት ሳንቲም) በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ እየተገነባ ነው። የአምቦ-ጉደር የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በመካሄድ ላይ የሚገኘው በኦሮሚያ ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ነው። የመንገድ ግንባታውን ጥራት በመቆጣጠር ረገድ ደግሞ ፕሮሚነንት ኢንጅነሪንግ ሶሉሽንስ በአማካሪነት በመሳተፍ ላይ ይገኛል፡፡ መንገዱ 14 ሜትር ስፋት አንዲኖረው ተደርጎ በመገንባት ላይ የሚገኝ ሲሆን ፣ በሁለቱም አቅጣጫ 2.5 ሜትር የዕግረኛ መንገድ እና 2.5 ሜትር አካፋይ እንዲኖረው ተደርጎ ነው በመገንባት ላይ የሚገኘው፡፡ መንገዱ ከዚህ ቀደም በአስፋልት ደረጃ ተገንብቶ የነበረ ቢሆንም ፣ ነባሩ መንገድ እጅግ የተጎዳ በመሆኑ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳው ከግምት ውስጥ ገብቶ በአሁኑ ወቅት በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ በመገንባት ላይ ነው፡፡ ፕሮጀክቱ የአፈር ቆረጣ ፣ የስትራክቸር ፣ የአስፋልት ንጣፍ ፣ የአራት ድልድዮች ግንባታ ፣ የሰቤዝ እና የቤዝ ኮርስ ስራዎችን እንዲሁም ልዩ ልዩ ግንባታዎችን (የመንገድ ምልክቶችን መትከል ፣ መንገድ ቀለም መቀባት) ባካተተ መልኩ ነው በመገንባት ላይ የሚገኘው፡፡ ከፕሮጀክቱ ጅማሮ አንስቶ አስካሁን የድልድይ እና የፍሳሽ ውሃ ማስወገጃ ፣ አፈር ቆረጣ ፣ የሰቤዝ እና የቤዝ ኮርስ እንዲሁም አስፋልት የማንጠፍ ስራዎች ተከናውነዋል፡፡ በዚህም መሰረት የፕሮጀክቱ የእስካሁን አፈፃፀም 46 በመቶ ወይም 9 ኪሎ ሜትር ስራው ተጠናቋል፡፡ ግንባታው በመጪው 2016 ዓ.ም ይጠናቀቃል ተብሎ ይታመናል፡፡ የስራ ተቋራጩ በአሁኑ ወቅት ቀሪ የቁፋሮ ስራ ፣ የአስፋልት ንጣፍ ፣ የሰቤዝ እና የቤዝ ኮርስ ንጣፍ ፣ የስትራክቸር ፣ የትራፊክ ምልክቶችን የመትከል እንዲሁም መንገዱን ቀለም የመቀባት ስራ ለማከናወን አቅዶ በመንቀሳቀስ ላይ ነው፡፡ ከወሰን ማስከበር ጋር በተያያዘ የተለያዩ ችግሮች የነበሩ ቢሆንም እነዚህን ችግሮች በመቅረፍ ግንባታው በጥሩ ሁኔታ እየተካሄደ ይገኛል፡፡ መንገዱ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ አምቦ እና ጉደር ከተሞችን ከማገናኘት ባሻገር ሀገር አቋራጭ መንገድ በመሆኑ ለሀገሪቱ ትልቅ ፋይዳ ያስገኛል፡፡ በተጨማሪም በአካባቢው የተፈጥሮ ፍል ውሃ እና በፕሮጀክቱ አቅራቢያ የሚገኝ የወንጪ ሃይቅ የሚገኝ በመሆኑ ፤ የመንገዱ መገንባት ለቱሪስት መዳረሻነትም ከፍተኛ ሚና ይኖረዋል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የአፍሪካ ልማት ባንክ ልኡካን ቡድን የአዳማ-አዋሽ የፍጥነት መንገድን ጎበኙ :: አዳማ ፣ ግንቦት 22 ቀን 2015 ዓም (ኢመአ) ፡ የአፍሪካ ልማት ባንክ ልኡካን ቡድን እና የኢመአ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች የአዳማ ኪሎ ሜትር 60 ( የአዳማ አዋሽ ) የፍጥነት መንገድን ጎበኙ ። የኢትዮ- ጅቡቲ ትራንስፖርት ኮሪደር አካል የሆነው የአዳማ አዋሽ የፍጥነት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በሀገራችን ከሚገኙ ወሳኝና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታቸው ጉልህ ከሆኑ መንገዶች አንዱ ነው ። መንገዱ ሦስት ክልሎችን ማለትም የኦሮሚያ ፣ የአፋርና የአማራ ክልሎችን ያስተሳስራል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የመንገዱ ጅማሮ ከአዲስ አበባ 90 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ሆኖ ከአዲስ አበባ - አዳማ ድረስ ያለውን የፍጥነት መንገድ የሚያያይዝና የሚያስቀጥል ነው ። 60 ኪሎ ሜትር የሚረዝመውን የፍጥነት መንገድ ግንባታ የሚያከናውነው JMC Projects / India / Ltd. ከLongjiaw Road and Bridge co. Ltd. ጋር በጋራ በመሆን ነው ። የማማከር እና የቁጥጥር ሥራውን ደግሞ LASA ( Lea Associates South Asia PVT ከ UNICONW ( United Consulting Engineers PLC ) ጋር በጋራ በመሆን በማካሄድ ላይ ይገኛል ። በአሁኑ ወቅት 30.5 ኪሎ ሜትር የአፈር ጠረጋ ስራው ያለቀ ሲሆን ፣ 3.4 ኪሎ ሜትር የአፈር ሙሌትም ተጠናቋል ። እንዲሁም የካፒንግ ሌየር ፤ ሰብ ቤዝ ፣ ቤዝ ኮርስ ስራዎች ፣ የውሃ መፋሰሻ ቱቦዎች እንዲሁም ለተሽከርካሪ መተላለፊያ የሚውሉ ተገጣጣሚዎችን ( Precast Elements ) የማምረት ስራ እየተከናወነ ይገኛል ። በእስካሁንም ከአጠቃላይ ስራው 9.73 በመቶ ተከናውኗል ። ለፍጥነት መንገዱ የሚውለው መዋለ ንዋይ በአፍሪካ ልማት ባንክ እና በኢትዮጵያ መንግስት የሚሸፈን ሲሆን ፣ ስራውን በበላይነት የሚቆጣጠረው የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ነው። የመንገዱ ግንባታ ወጪም ስድስት ቢሊዮን ስድስት መቶ ሰማንያ ስምንት ሚሊዮን አራት መቶ ሃምሳ ስድስት ሺህ አምስት መቶ ስልሳ አምስት ብር ከሰባ አራት ሳንቲም (6,688,456,565.74 ) ነው :: የአፍሪካ ልማት ባንክ ልኡካን ቡድንና የኢመአ አመራር አካላት የአዳማ አዋሽን የፍጥነት መንገድ ከጎበኙ በኋላም በአዳማ ከተማ የግማሽ ቀን ውይይት አድርገዋል ። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

ኢትዮጵያን ከኤርትራ ጋር የሚገናኘው የአሰብ ኮሪደር (ሜሎዶኒ መገንጠያ -ማንዳ-ቡሬ) የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በጥሩ አፈፃፀም ላይ ይገኛል፡፡ ፕሮጀክቱ 71 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለውና በመንግሥት በተመደበ 2,085,985,162.61 (ሁለት ቢሊዮን ሰማንያ አምስት ሚሊዮን ዘጠኝ መቶ ሰማንያ አምስት ሺህ አንድ መቶ ስልሳ ሁለት ብር ከስልሳ አንድ ሳንቲም) በአስፋልት ኮንክሪት እና በሲሚንቶ ኮንክሪት ንጣፍ ደረጃ እየተገነባ ነው። ይህ መንገድ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ በሀገራዊ እና ቀጠናዊ ትስስሩ ረገድ ጉልህ ሚና ይኖረዋል። ፕሮጀክቱ የሚካሄድበት መልክኣ ምድራዊ አቀማመጥ ሜዳማ ፣ ዳገታማ እና ተራራማ ሲሆን ፤ ከአዲስ አበባ 787 ኪሜ ርቀት ላይ ከኤሊ ዳር ከተማ 16 ኪሜ በኃላ ጀምሮ ኢትዮ ኤርትራ ድንበር ላይ ያበቃል፡፡ የአሰብ ኮሪደር (ሜሎዶኒ መገንጠያ ማንዳ ቡሬ) የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በመካሄድ ላይ የሚገኘው ሻንዶንግ ሉሽያዎ ግሩፕ ካምፓኒ ሊሚትድ በተባለ የውጭ ሀገር የሥራ ተቋራጭ ድርጅት ነው። የመንገድ ግንባታውን ጥራት በመቆጣጠር ረገድ ደግሞ ስሜክ ኢንተርናሽናል ፕራይቬት ሊሚትድ እና ቫልዩ ኢንጅነሪንግ ኃ/የተ/የግ/ማህበር በንኡስ አማካሪነት በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ፡፡ መንገዱ ትከሻን ጨምሮ በገጠር፡- 10 ሜትር እና በቀበሌ ከተሞች ደግሞ 21.5 ሜትር ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ በመገንባት ላይ ነው፡፡ ከዚህ ቀደም በከፊል በጠጠር ደረጃ ተገንብቶ አገልግሎት ሲሰጥ የቆየው ይኸው መንገድ ፤ በአሁኑ ወቅት ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳው ከግምት ውስጥ ገብቶ በአስፋልት ኮንክሪት እና በሲሚንቶ ኮንክሪት ንጣፍ ደረጃ እየተገነባ ነው። ፕሮጀክቱ የአፈር ጠረጋ ፤ ቆረጣ እና ሙሌት ፤ ሰብቤዝ ፤ ቤዝ ኮርስ ፤ የአስፋልት ንጣፍ ፤ የሲሚንቶ ኮንክሪት ንጣፍ ፤ የአራት ድልድዮች ግንባታ ፤ እንደ ፓይፕ ፣ ስላብና ቦክስ ከልቨርቶች ያሉ የውሃ ማስተንፈሻ ስራዎችን እንዲሁም የመንገድ ምልክቶችን መትከል እና የመንገድ ቀለም መቀባት የመሳሰሉ ሌሎች ልዩ ልዩ ተግባራትን ባካተተ መልኩ ነው በመገንባት ላይ የሚገኘው፡፡ ከፕሮጀክቱ ጅማሮ አንስቶ አስካሁን 35 ኪሎ ሜትር (50%) የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት ስራ የተጠናቀቀ ሲሆን ፤ 18 ኪሎ ሜትር (26%) የሳብቤዝ ስራውም አልቋል። ከዚህም ባሻገር 5 ኪ.ሜ (7%) የቤዝ ኮርስ ስራ የተጠናቀቀ ሲሆን ፤ የአስፋልት እና የሲሚንቶ ኮንክሪት ንጣፍ ስራ ለመጀመር የሚያስችል የዝግጅት ስራዎች ተጠናቀዋል፡፡ በተጨማሪም የአራት ድልድዮች የዲዛይን ስራ የተጠናቀቀ ከመሆኑም ባሻር ፤ 27% እንደ ፓይፕ ፣ ስላብና ቦክስ ከልቨርቶች የመሳሰሉ የውሃ ማስተንፈሻ ስራዎች ተከናውነዋል። በዚህም መሰረት ግንባታው በመጪው ሀምሌ ወር 2016 ዓ.ም ይጠናቀቃል ተብሎ ይታመናል፡፡ ባለፉት ጊዜያት እንደሀገር የተከሰተው ከፍተኛ የሲሚንቶ እጥረት፤ በሰሜኑ የሃገራችን ክፍል በነበረው ጦርነት ምክንያት የግንባታ ግብአቶችን ወደ ሳይት ማስገባት አለመቻል እና በኢትዮ ኤርትራ ጦርነት ወቅት ተቀብረው ያልመከኑ ፈንጂዎች መኖር በግንባታ ሂደቱ ላይ ተፅዕኖ ቢያሳድሩም ፤ እነዚህን ችግሮች በመቋቋም ግንባታው በጥሩ ሁኔታ እየተካሄደ ነው፡፡ ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ የኢትዮጵያ እና ኤርትራ ህዝቦችን ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ መስተጋብር በማጠናከሩ ረገድ አማራጭ መንገድ ሆኖ ያገለግላል፡፡ በተጨማሪም የአካባቢው ነዋሪዎች የትምህርት ፣ የጤና እንዲሁም መሰል ግልጋሎቶችን በቀላሉ እንዲያገኙ ጉልህ አስተዋፅኦ ያበረክታል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ ቢሾፍቱ፣ ግንቦት 14 ቀን 2015 ዓም (ኢመአ)፡ ለትግራይ ክልል መንገዶች ባለስልጣን እና የበኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ለየአዲግራት ዲስትሪክት ሠራተኞች እና የ
+3
የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ ቢሾፍቱ፣ ግንቦት 14 ቀን 2015 ዓም (ኢመአ)፡ ለትግራይ ክልል መንገዶች ባለስልጣን እና የበኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ለየአዲግራት ዲስትሪክት ሠራተኞች እና የሥራ ኃላፊዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ፡፡ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናው በዋናነት በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል በነበረው የጸጥታ ችግር ምክንያት የነበረውን አለመረጋጋት ታሳቢ ያደረገ የሥነ ልቦና ዝግጅት እንዲኖር ማስቻል ነው፡፡ የሥራ ኃላፊዎቹና ሰራተኞቹ በሰሜኑ የሀገራችን አካባቢ በተከሰተው ግጭት የተጎዱና ከአገልግሎት ውጪ የነበሩ መንገዶችና ድልድዮች ወደ ቀድሞ አገልግሎታቸው ለመመለስ በሚደረገው ጥረት አስፈላጊውን የስነልቦና ዝግጅት ማድረግ የሚገባቸው መሆኑንም በመድረኩ ተገልጿል፡፡ ቀጣይነት እንደሚኖረው በተገለጸው በዚህ የመጀመሪያ የስልጠና መድረክ ላይ የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዲኤታ ኢ / ር ወንድሙ ሴታ ፣ የትግራይ ክልል የገጠር መንገድ ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር አርአያ ግርማይና የኢመአ አመራር አካላት ተገኝተዋል ። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

ኢትዮጵያን ከጅቡቲ ጋር በአቋራጭ የሚያስተሳስረው የአሳይታ-አፋምቦ-ጅቡቲ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በመፋጠን ላይ ነው። የአሳይታ - አፋምቦ - ጅቡቲ ድንበር የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት 49 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለውና በመንግሥት በተመደበ 1,676,348,103.83 (አንድ ቢሊዮን ስድስት መቶ ሰባ ስድስት ሚሊዮን ሶስት መቶ አርባ ስምንት ሺህ አንድ መቶ ሶስት ብር ከሰማንያ ሶስት ሳንቲም ) በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ እየተገነባ ይገኛል። ይህ መንገድ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ በሀገራዊ እና ቀጠናዊ ትስስሩ ረገድ ጉልህ ሚና ይኖረዋል። ፕሮጀክቱ የሚካሄድበት መልክኣ ምድራዊ አቀማመጥ ሜዳማ ፣ ሸንተራራማ እና ተራራማ ሲሆን ፤ ከአዲስ አበባ በ663 ኪሎ ሜትር ርቀት አሳይታ ከተማ ላይ ጀምሮ ኢትዮ ጅቡቲ ድንበር ላይ ያበቃል፡፡ የአሳይታ-አፋምቦ-ጅቡቲ ድንበር የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በመካሄድ ላይ የሚገኘው አሰር ኮንስትራክሽን ኃ/የተ/የግ/ማህበር በተባለ ሀገር በቀል ድርጅት ነው። የመንገድ ግንባታውን ጥራት በመቆጣጠር ረገድ ደግሞ ይዲዲያ ኢንጅነሪንግ ኮንሰልታንስ ኃ/የተ/የግ/ማህበር በአማካሪነት በመሳተፍ ላይ ይገኛል፡፡ መንገዱ ትከሻን ጨምሮ በገጠር፡- 10 ሜትር ፣ በዞን፡- 21.5 ሜትር ፣ በወረዳ ደግሞ 19 ሜትር ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ በመገንባት ላይ ይገኛል ፡፡ መንገዱ ከዚህ ቀደም በከፊል በጠጠር ደረጃ ተገንብቶ አገልግሎት ሲሰጥ የቆየ ሲሆን ፣ በአሁኑ ወቅት ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳው ከግምት ውስጥ ገብቶ በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ በመገንባት ላይ ይገኛል፡፡ ፕሮጀክቱ የአፈር ጠረጋን ፣ ቆረጣ እና ሙሌት ፣ የሰብቤዝ ፣የቤዝ ኮርስ ፣የአስፋልት፣የሶስት ድልድዮች ፣ የውሃ ማስተንፈሻ (ፓይፕ ፣ ስላብና ቦክስ ከልቨርቶች) ስራዎችን እንዲሁም የጎርፍ መከላከያ እና ልዩ ልዩ ግንባታዎችን (የመንገድ ምልክቶችን መትከል፣መንገድ ቀለም መቀባት) ባካተተ መልኩ ነው በመገንባት ላይ የሚገኘው፡፡ ከፕሮጀክቱ ጅማሮ አንስቶ አስካሁን 48 ኪሎ ሜትር (98%) የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት ስራ የተጠናቀቀ ሲሆን ፣ 47 ኪሎሜትር (97%) የሳብቤዝ ስራውም አልቋል፡፡ ከዚህም ባሻገር የፕሮጀክቱ 20 ኪሎሜትር (41%) የቤዝ ኮርስ ስራ የተጠናቀቀ ሲሆን ፣ 95% የሶስት ድልድዮች ስራ እና 73% የውሃ ማስተንፈሻ (ፓይፕ ፣ ስላብና ቦክስ ከልቨርቶች) ስራዎች ከመጠናቀቃቸው ባሻገር የአስፋልት ግንባታ ስራም ተጀምሯል ። በዚህም መሰረት የፕሮጀክቱ የእስካሁን አፈፃፀም 40 ኪሎሜትር ወይም 82% በመቶ ተከናውኗል፡፡ ግንባታው በመጪው መስከረም ወር 2016 ዓ.ም ይጠናቀቃል ተብሎ ይታመናል፡፡ የስራ ተቋራጩ በቀሪ ጊዜያት ውስጥ 27% የውሃ ማፋሰሻ ስራዎችን ፣ ሙሉውን የአስፋልት ስራ እና ሌሎች ልዩ ልዩ ስራዎችን (የትራፊክ ምልክቶች መትከል እና መንገዱን ቀለም የመቀባት ስራ) ለማከናወን አቅዶ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል፡፡ ባለፉት ጊዜያት እንደሀገር የተከሰተው ከፍተኛ የሲሚንቶ እጥረት ፤ በሰሜኑ የሃገራችን ክፍል በነበረው ጦርነት ምክንያት የግንባታ ግብአቶችን ወደ ሳይት ማስገባት አለመቻል ፤ ከወሰን ማስከበር ጋር በተያያዘ ችግሮች መኖራቸው እና አንዳንድ የአካባቢው ግለሰቦች ከመንገድ ስራው ጋር ባልተያያዘ ምክንያት ተደጋጋሚ የስራ ማስቆም አዝማሚያዎች የነበሩ ቢሆንም እነዚህን ችግሮች በመቋቋም ግንባታው በጥሩ ሁኔታ እየተካሄደ ይገኛል፡፡ በአካባቢው የአዋሽ ተፋሰስን ተከትሎ የአሳይታ እና አፋምቦ ወረዳዎች ለመስኖ ግብርና እጅግ አመቺ በመሆናቸው የሚመረቱትን የግብርና ውጤቶች በቀላሉ በጅቡቲ በኩል ወደ ውጪ ለመላክ የመንገዱ መገንባት አይነተኛ ሚና ይኖረዋል፡፡ በተጨማሪም በአካባቢው ማምረት ከሚቻለው ምርት በከፊል እንደ ስኳር ፣ ስንዴ ፣ ሰሊጥ ፣ ጥጥ ፣ ቴምር እና መሰል የግብርና ምርት ለማከናወን አመቺ ሲሆን ፣ የመንገድ ፕሮጀክቱ ከሌሎች ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳዎች ባሻገር ይህንኑ ታሳቢ ተደርጎ በመገንባት ላይ ይገኛል፡፡ በጅቡቲ በኩል የሚገነባው ቀጣይ የመንገድ ክፍል ሲጠናቀቅ ከዴቼቶ-ጋላፊ በተጨማሪ ኢትዮጵያን ከጅቡቲ ጋር በየብስ የሚያገናኝ አማራጭ መንገድ ሆኖ ያገለግላል። በአካባቢው የአዋሽ ተፋሰስን ተከትሎ የአፋምቦ ሀይቅ የሚገኝ ሲሆን ፤ ለቱሪስት መዳረሻነትም ከፍተኛ ፋይዳ ይኖረዋል ተብሎ ይታመናል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የመካነ-እየሱስ/እስቴ-ስማዳ 50 ነጥብ 5 ኪ.ሜ አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ በፍፃሜ ምዕራፍ ላይ ይገኛል። አዲስ አበባ፣ ግንቦት 04፣ 2015(ኢመአ):- በደቡብ ጎንደር ዞን የመካነ-እየሱስ/እስቴ-ስማዳ 50 ነጥብ 5 ኪ.ሜ አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ በፍፃሜ ምዕራፍ ላይ ይገኛል። አሁን ላይ ከአጠቃላይ የግንባታ ሥራው 86 በመቶው ተከናውኗል። ቀሪ ሥራዎቹን በሚቀጥሉት አምስት ወራት ውስጥ ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሠራ ነው። ከጠቅላላው የመንገዱ ክፍል 47 ኪሎ ሜትሩን አስፋልት ማልበስ ተችሏል። በተጨማሪም የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት፣ የሰብቤዝ እና ቤዝኮርስ፣ የሾልደር፣ የውኃ መፋሰሻ፣ የድልድይ እንዲሁም የማጠናቀቂያ ሥራዎች እየተሠሩ ነው፡፡ ግንባታውን ዓለም አቀፉ 'ቻይና ኮሙኒኬሽን ኮንስትራክሽን ካምፓኒ' እያከናወነ ይገኛል። ለግንባታው የሚውለው 1,925,451, 264.41 (አንድ ቢሊዮን ዘጠኝ መቶ ሃያ አምስት ሚሊዮን አራት መቶ ሃምሳ አንድ ሺህ) ብር በፌደራል መንግስት ነው የሚሸፈነው። 'ፕሮሚናንት ኢንጅነሪንግ ሶሉሽንስ' ግንባታውን የመቆጣጠር እና የማማከር ሥራ እየሠራ ይገኛል። አካባቢው ካለው በርካታ አገራዊ፣ ማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ አንፃር በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ ነው እየተገነባ የሚገኘው፡፡  በፕሮጀክቱ የከተማ ክልል ላይ ከወሰን ማስከበር ጋር ተያይዞ የተፈጠረው ችግር በግንባታ ሥራው ላይ እክል ፈጥሮ የነበረ ቢሆንም፥ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከወረዳ የመስተዳድር አካላት ጋር በመቀናጀት ችግሩን መፍታት ተችሏል፡፡  ከዚህም ባለፈ የአካባቢው አስቸጋሪ የመልካ-ምድራዊ አቀማመጥ እንዲሁም የግንባታ ዕቃዎች የግብዓት ዕጥረት እና የዋጋ መናር በግንባታው ወቅት የገጠሙ ተግዳሮቶች ናቸው፡፡ የእስቴ-ስማዳ አስፋልት መንገድ ፕሮጀክት ከአዲስ አበባ 657 ኪ.ሜ ርቀት እስቴ ከተማ ላይ ጀምሮ ወገዳ ከተማ ድረስ ይዘልቃል፡፡ ፕሮጀክቱ ዕውን ሲሆን በሥፍራው የሚገኙትን ትንንሽ መንደሮች ደረጃውን በጠበቀ መንገድ በማገናኘት ወደ ከተማ የሚያድጉበትን ምቹ ዕድል ይፈጥራል፡፡የሕዝብ ለሕዝብ ትስስሩን በማሳለጥም የተለያዩ የማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ መስተጋብሮችን ያጠናክራል፡፡ በአካባቢው በስፋት የሚመረቱትን ጤፍ፣ ስንዴ፣ ገብስ፣ ሽንብራ፣ ኑግ፣ ባቄላ፣ ጓያ፣ ድንች እና መሰል የግብርና ምርቶች ገበያ በፍጥነት እና በጥራት ማድረስ ያስችላል፡፡