ru
Feedback
ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች እና መዝሙሮች / Orthodoxsawi temehertoch (mezmuroch)

ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች እና መዝሙሮች / Orthodoxsawi temehertoch (mezmuroch)

Открыть в Telegram

በዚህ ቻናል ላይ ማንኛውንም ☦☦የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ስርአትን የጠበቁ ✥ አስተምሮቶችን ✟ ❖ ስብከቶችን ✟ ❖ መዝሙሮችን ✟ ❖ መንፈሳዊ መጽሐፍቶችን ያገኛሉ።☨☨ "መፅሐፍ ቅዱስን ወዳጅህ አድርገው አንተ የቃሉ ወዳጅ ስትሆን እግዚአብሔር ደግሞ የልቡ ወዳጅ ያደርግሀል።"      /አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ/

Больше
1 295
Подписчики
-224 часа
-17 дней
-1430 день
Архив постов
🌿 በመከራ ቀን ጥራኝ ! #ለእግዚአብሔር የምስጋናን መሥዋዕት ሠዋ ፤ ለልዑልም ጸሎትህን ስጥ ። በመከራ ቀን ጥራኝ እኔም አድንሃለሁ አንተም ታከብረኛለህ ። (መዝ 49(50)፥14-17) #በእውነት ! እንደ ጌታ በመከራ ቀን ጥራኝ የሚል ማን ይሁን ?! ያውም እኮ ምንም አድርገህለት ደግሞም ምንም እንድትሰጠው አይደለም ጠራኝ አድንህማለሁ የሚልህ ምስጋናን እና ጸሎትን እንድትሰጠው ብቻ እንጂ ! #እኛ ብንሆን በመልካሙ ቀን ነው እንጂ በመከራ ቀን ጥራኝ እንል ይሆን ? ደግሞስ ቢሆን በመከራው ቀን ለሚጠራን ሰው ምላሽ የምንሰጠው ምን በመፈለግ ይሆን ?! እንጃ ፤ ብቻ ግን እርሱ ክርስቶስን በመከራ ቀን ጥራው እርሱም ያድንሃል አንተም ታከብረዋለህ ! #በእውነት እንደ ጌታ በመከራ ቀን ጥራኝ የሚል ማን ይሁን ?! 🙏 ጌታ ሆይ ! በመከራዬ ቀን እጠራሃለው ፤ አንተም ታድነኛለህ ፤ እኔም አከብርሃለሁ ! #ሰኔ / 30 / 2018 ዓ.ም #አንቀጸ አድኅኖ ሰ/ት/ቤት #5 ሰዓት 🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿 https://t.me/ankets_adeheno

🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿 🌿 ወጣቶችን ይወዳል ! #ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ የተሰቀለው ገና ወጣት ሳለ ነው ። #ጌታ ሞቶ የተነሳው የአዋቂነት የእድሜ ደረጃ ውስጥ ሳይገባ በወጣትነት ዕድሜ ነበር ፤ ምክንያቱም እርሱ ወጣቶችን ይወድ ስለነበር ነው ። (ታድሮስ ያዕቆብ ማላቲ) #እርሱ (ክርስቶስ) ሕዝቦቹ ሁሉ የወጣትነትን ሕይወት በወጣት መንፈስና ልብ እንዲኖሩት ይፈልጋል ። ... - የክርስቶስ ደቀመዛሙርትና ሐዋርያት የኖሩት ድካምንና መከራን ሁሉ ድል በነሳ ብርቱ የወጣትነት መንፈስ ነው ። #ሰማያዊው የእኛ ሙሽራ ቤተ ክርስቲያኑ በመንፈስ ቅዱስ ሕያውና ብርቱ ሆና ማየት ነው የሚፈልገው ። - እርሱ ቤተ ክርስቲያኑ ያለ ማቋረጥ ወጣት ስትሆን  አንድ ወጣት የወጣትነት ሚስቱን ሲያገባ የሚደሰተውን ያህል እርሱም በእርሷ (በቤተ ክርስቲያን) ይደሰታል ። (ምሳ 5፥18) 👉 ሥጋችሁ ከእግዚአብሔር የተቀበላችሁት በእናንተ የሚኖረው የመንፈስ ቅዱስ ቤተ መቅደስ እንደ ሆነ አታውቁምን? (1ኛ ቆሮ 6፥19-20) #ግንቦት 25 / 2018 ዓ.ም #አንቀጸ አድኅኖ ሰ/ት/ቤት #ጌታ ሆይ የወጣትነት ዘመናችንን ባርክ 🙏 🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿 https://t.me/ankets_adeheno

🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿 🌿  ዝክረ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ 👉 ለምን የጸኑትን (ቅዱሳንን) እናስባለን (እንዘክራለን) ? #ክርስቶስን በማመን እንጸና ዘንድ ነው ። 🙏 በመጀመሪያ እራሱን አሳልፎ እስኪሰጥልን ድረስ የወደደንን እና ስለ እኛ መዳን ሲል በመከራ መስቀል የጸናውን ኢየሱስ ክርስቶስን እንመልከት ። 🙏 ከዚህም ጋር የክርስቶስ ፍቅርና ውለታ ገብቷቸው መስቀላቸውን ተሸክመው እርሱን በመከተል የጸኑትን ማወቅ በጣም ጠቃሚ ነውና እነርሱን እንመልከት ። 👉 እነዚህን ሐሳቦች መጽሐፍ ቅዱስም ስለሚደግፈን ነው የጸኑትን ምናስበው ። #በነፍሳችሁ ዝላችሁ እንዳትደክሙ፥ ከኃጢአተኞች በደረሰበት እንዲህ ባለ መቃወም የጸናውን አስቡ። (ዕብ 12፥3) (ዕብ 13፥7 ዋኖቻችሁን አስቡ) ይለናል ። 🌿 በልቤ ከተማ ተመላለስበት የሚለው መዝሙር እና ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ በልቤ ከተማ ተመላለስበት ይረጋል ህይወቴ አንተ ስታርፍበት ወደ እልፍኜ ግባ እረፍ በምንጣፌ እንዳመልክህ ጌታ እንባዬን አርግፌ 👉 ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ስለ ንስሐና ስለ ልብ ንጽሕና ሲያስተምር ፣ #የሰው ልጅ ልብ ክርስቶስ የሚኖርባት "ታላቅ ከተማ" ወይንም "የንጉሥ እልፍኝ" መሆን እንዳለባት ይናገራል። 🙏 ክርስቶስ በልብ ሲነግሥ በሕይወት ውስጥ ያለው ዓለማዊ ማዕበል ሁሉ ጸጥ ይላል። 🙏 በተጨማሪም ማልቀስና እንባን ማፍሰስ የነፍስን እድፍ አጥቦ ንጉሡ ክርስቶስ የሚያርፍበትን ምንጣፍ ማዘጋጀት እንደሆነ ይገልጻል። 👉 እናም በተጨማሪም በንስሐ ትምህርቱ ላይ እንዲህ ይላል ፦ "እንባ የነፍስ መታጠቢያ ነው፤ ልክ እንደ ከባድ ዝናብ አየሩን እንደሚያጠራው ሁሉ ፣ ከልብ የሚፈልቅ እንባም የልብን ከተማ ከኃጢአት ጢስ ያጠራታል። ያን ጊዜ ንጉሡ ክርስቶስ በዚያ ያርፋል።" 🌿  አንደኛ ዘማች ባለፀጋ ስትሆን ድሆች ከበውሃል ለንግስና ዙፋን አህያን መርጠሃል አጀብ አትፈልግም አውቅሃለሁ ጌታ ብቻህን ነበረ ደጄን ስትመታ ለጠላት አሰራር ዋሻ የሆንኩትን ስራኝ እንደገና ቤተመቅደስህን 👉 እዚህ ላይም  ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ስለ ክርስቶስ የሆሳዕና ጉዞ (በአህያ ላይ ስለመቀመጡ) ሲያስተምር፣ የጌታን ፍጹም ትሕትና ያደንቃል። #ክርስቶስ በምድር ላይ ሳለ የፈለገው ዓለማዊ "አጀብ" (የሰራዊት ክብር) ሳይሆን የሰውን ልብ ብቻ ነበር። 🙏 በኃጢአት ምክንያት "የወንበዴዎች ዋሻ" የሆነውን የሰውን ማንነት "ወደ እግዚአብሔር ቤተመቅደስነት" ለመቀየር እርሱ ራሱ በደጃችን ይቆማል። 👉 እናም የማቴዎስን ወንጌል በተረጓመበት ክፍሉ እንዲህ ይላል ፦ "ክርስቶስ በአህያ ላይ የተቀመጠው እኛን በትሕትና ሊገዛን ነው፤ እርሱ የነፍሳችንን ደጅ ይንኳኳል። አንተ ግን ልብህን የወንበዴና የሰይጣን ዋሻ አታድርገው፤ እርሱ በደሙ የቀደሳት መቅደስ ናትና።" 🌿 ሁለተኛ ዘማች ድንግዝግዝ ኑሮዬ በምራቅህ ይብራ ጨለማ አይዝህም አንተ ስትሰራ ማረኝ ያሉት እጆች ሲያጨበጭቡልህ ሰምቼ አልቀረሁም በብርሃን አየሁህ 👉 ይህም አዝማች በዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 9 ላይ ያለውን በጭቃና በምራቅ የተፈወሰውን የዕውሩን ታሪክ ያስታውሰናል። #ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ስለዚህ ተአምር ሲያስተምር፣ - የክርስቶስ ምራቅና ጭቃ መለኮታዊ የመፍጠር ኃይል እንዳለው እና ድንግዝግዝ የሆነውን የሰውን ልጅ የመንፈስ ዕውርነት እንደሚያበራ ይናገራል። - በዓይን ማየት ብቻ ሳይሆን "በእምነት ብርሃንነት" ክርስቶስን ማወቅ እውነተኛ ማየት ነው። 👉 እዚላይም የዮሐንስን ወንጌል በተረጎመበት ክፍሉ እንዲህ ይላል ፦ "ጌታ ዕውሩን በምራቅና በጭቃ የፈወሰው፣ በመጀመሪያ አዳምን ከምድር  ያበጀው እጅ የእርሱ እጅ መሆኑን ሊያሳየን ነው። እርሱ ወደ ጨለማው  ሕይወታችን ሲመጣ ድንግዝግዙ ሁሉ ይበራል፤ እውነተኛውንም ብርሃን እናያለን።" 🌿 ሦስተኛ ዘማች ማዕበል ህይወቴ ግራ ቀኝ የሚለው እንደምን ይረጋል ጌታዬ ሳታዘው ተራመድ በልቤ በሞገስ በግርማ ኢየሱስ ነህ አንተ የምስኪኑ ማማ 👉  እዚ ላይም ቅዱስ ዮሐንስ ወደ ስደት ሊሄድ ሲል፣ ዓለማዊው ማዕበል ግራና ቀኝ ሲያናውጠው ለሕዝቡ ያስተማረው ትምህርት ይህንን የመዝሙር ስንኝ ይመስላል። #ክርስቶስ በማዕበል ላይ እንደሚራመድ፣ በልባችን ማዕበል ላይ ሲራመድ ሕይወት ትረጋለች ። እርሱ "የምስኪኖች መጠጊያ ማማ" ነው። ይል ነበር ። 👉 በተጨማሪም ከግዞት (ከስደት) በኋላ በሚል ትምህርቱ እንዲህ ይላል ። "ሕይወታችሁ በማዕበል ቢናወጥ አትፍሩ። ክርስቶስ በማዕበሉ ላይ ይራመዳል፤ ባሕሩንም ጸጥ ያደርገዋል። እርሱ የማይናወጥ አለትና የደካሞች መጠጊያ ማማ ነው!" 🌿 አራተኛ ዘማች ከያዕቆብ ጉድጓድ ብቀዳም አብዝቼ ዛሬም በጥማት ነኝ ከቶ መች ረክቼ የህይወት ውሃ ምንጭ ነፍስን የምትመልስ በበረሃው ልቤ ለዘላለም ፍሰስ 👉 ይህ ዘማችም  ከሳምራዊቷ ሴት ታሪክ (ከዮሐ 4) የተወሰደ ነው። #ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ "የያዕቆብ ጉድጓድ" የሚለውን - ለምድራዊ ሀብት፣ - ለሥልጣንና - ለዓለማዊ ደስታ ምሳሌ አድርጎ ይተረጉመዋል። #የዚህ ዓለም ተድላና ደስታ ጊዜያዊ ጥማትን እንጂ የነፍስን ዘላለማዊ ጥማት ሊያረካ አይችልም። #የነፍስን በረሃ የሚያረካው ራሱ ክርስቶስና ከመንፈስ ቅዱስ የሚገኘው "የሕይወት ውኃ" ብቻ ነው። 👉 አሁንም የዮሐንስን ወንጌል በተረጎመበት ክፍሉ እንዲህ ይላል ፦ "የዚህ ዓለም ደስታ እንደ ያዕቆብ ጉድጓድ ውኃ ነው፤ ትጠጣዋለህ፣ ግን እንደገና ትጠማለህ። ክርስቶስ የሚሰጠው ውኃ ግን በሰው ልብ ውስጥ ለዘላለም የሚፈልቅ የሕይወት ምንጭ ነው፤ ነፍስንም ከኃጢአት በረሃነት ወደ ገነትነት ይለውጣታል።" 🙏  እንኳን ለቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ዓመታዊ የእረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ። መልካም በዓል ። 🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿 https://t.me/ankets_adeheno

🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿 🌿 "አብ ፀሃይ ነው ፣ ወልድ ፀሃይ ነው ፣ መንፈስ ቅዱስ ፀሃይ ነው" እንዳለ አባ ሕርያቆስ ከሦስቱ አካል አንዱ አካል ፀሃየ ጽድቅ ክርስቶስ ሊወጣባት ዛሬ ሰማይ (ድንግል ማርያም) ለተገኘችበት ማለትም ለተወለደችበት በዓል እንኳን አደረሰን አደረሳችሁ ። ታዲያ "ዛሬ" በሚል ርእስ የሆነች ትንሽ ነገር ልል ወደድኩ ፦ 🌿 ዛሬ #ዛሬ ሰማያዊው አዳም (ክርስቶስ) የሚያድርባት ሰማይ (ማርያም) የተገኘችበት ቀን ነው !!! ታዲያ ከዚች ከምትናፈቅ ሰማይ ጋር በሰማያዊት ኢየሩሳሌም ለመኖር እራሳችንን በንስሐ እና በቅዱስ ቁርባን እናዘጋጅ ። #ከኢያቄምና ከሐና የተገኘችው ደመና (ማርያም) "ዛሬ" ተገለጠች ፤ እርሷም የሕይወትን ዝናብ (ክርስቶስን) ለዓለም ታዘንባለች !!! ታዲያ እኛነታችንን ወደዚህች ደመና እናስጠጋ ከእርሷ በሚዘንበው ዝናብ (ክርስቶስ) አማካኝነት  30 ፣ 60 ፣ 100 ያማረ ፣ የተወደደ የንስሐን ፍሬ እናፈራ ዘንድ ። 🙏 ጌታ ሆይ ! ፀሃየ ጽድቅ (የጽድቅ ፀሃይ) ለተባልክ ላንተ ሰማይህ ስለ ሆነችው እናትህ ስትል ደግሞም የዓለምን ንዳድ ታቀዘቅዝ ዘንድ ለአንተ ዝናብ (ክርስቶስ) ደመና ስለሆነችህ እናትህ ስትል እኛን ልጆችህን ማረኝ ፣ በመንግስትህም አስበን 🙏 #መልካም በዓል #ግንቦት 1 / 2018 ዓ.ም #አንቀጸ አድኅኖ (ሰሪቲ) https://t.me/ankets_adeheno 🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿

🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿 🌿 ክህደት ከፈጸመ በኋላ ይሁዳን ያነጋገረው የክስ ድምጽ ። #ትዝ ይላችሁ ከሆነ ይሁዳ ጌታውን ከሸጠ (ክህደትን ከፈጸመ) በኋላ በውስጡ ይሰማው የነበረው የክስ ድምጽ እንደ ጴጥሮስ ወደ ሕይወት (ወደ ንስሐ¹) የመራው አልነበረም ፤ ራሱን ወደ ማጥፋት ወደ ሞት መራው እንጂ² ። #ጴጥሮስ  ይሰማው  የነበረው የመሐሪው የክርስቶስ ድምጽ ነበር³ ፤ ይሁዳ ግን ይሰማው የነበረው አይምርህም የሚለው የከሳሽ የዲያብሎስ ድምጽ ነበር ! #እኛስ ከስህተት ፣ ከኃጢአት ፣ ከበደል በኋላ በውስጣችን የሚሰሙን ድምጾች የሚወስዱን ፣ የሚመሩን ወዴት ነው ? ወደ ሞት ወይስ ወደ ሕይወት ? ማለትም ዳግም ወደ ኃጢአት ወይስ ወደ ንስሐ ? #ይህን እናስተውል  ከስህተት ፣ ከጥፋት (ከኃጢአት) በኋላ በውስጣችን "ይህን ጥፋት ፣ ይህን ስህተት ፣ ይህን ኃጢአት ምንብለህ ለንስሐ አባትህ ትናገረዋለህ ፤ አታፍርም ፤ ይህን ኃጢአትማ እግዚአብሔር ይቅር አይልህም" የሚል ድምጽ ከሆነ የሚሰማን አስተውሉ ይህ አይነት ድምጽ "ክህደት ከፈጸመ በኋላ ይሁዳን ያነጋገረው የክስ ድምጽ ነው" ይህ ደግሞ እንደ ጴጥሮስ ወደ ሕይወት ወደ ንስሐ ሳይሆን የሚመራን ፤ እንደ ይሁዳ ንስሐ ወዳለመግባት ፣ ወደ ሞት  ነው የሚወስደን ። #ታዲያ ምንም ያክል ኃጢአት ብንሰራ ፤ ብቻ እንደ ጴጥሮስ በተሰበረ ልብ በእንባ ሆነን ፤ ኃጢአታችንን አምነን ፤ በንስሐ አባታቸን በኩል ከቅዱስ ዳዊት ጋር እግዚአብሔርን እንዲህ እንበለው  "አቤቱ እንደ ቸርነትህ መጠን ማረኝ ፤ እንደ ምሕረትህም ብዛት መተላለፌን ደምስስ። ከበደሌ ፈጽሞ እጠበኝ ፤ ከኃጢአቴም አንጻኝ ፤ እኔ መተላለፌን አውቃለሁና ኃጢአቴም ሁልጊዜ በፊቴ ነውና። አንተን ብቻ በደልሁ በፊትህም ክፋትን አደረግሁ"⁴ እንበለው ያኔ ማሐሪ ነውና ይምረናል ፣ ይቅር ባይ ነውና ይቅር ይለናል ። ¹ንስሐ ማለት ማዘን ፣ መጸጸት ፣ መቆጨት ፣ መለወጥ❨ጠብቆ ይነበብ❩ ፣ አስተሳሰብን መቀየር ማለት ነው ። ²ማቴ 27፥3-5 ³ማቴ 26፥75 ⁴መዝ 50፥1-4 #ሚያዚያ 28 / 2018 ዓ.ም #አንቀጸ አድኅኖ ሰ/ት/ቤት (ሰሪቲ) #6:30 ቀን #አቤቱ በመንግስትህ አስበኝ 🙏 🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿

🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿 🌿 Nyaatawwan Sooma Guddaa Keessa Dhorkaman: ❌ Aarii (ቁጣ) ❌ Hinaaffaa (ቅናት) ❌ Hamii (ሐሜት) ❌ Haaloo (በቀል) ❌ Jibba (ጥላቻ) ⚠️ Nyaatawwan summaa'oo ta'an kunniin gara jireenya keessaniitti akka hin galle eeggachuun sooma keessan qulqulleessaa! 📌 Yaadadhaa : Gochaawwan kunniin yeroo soomaa alattis ta'ee gonkumaa kan hin eeyyamamne yoo ta'an, keessattuu yeroo soomaatti ammoo gatii dadhabbi keessanii waan dhabsiisaniif jabeessanii dhorkamaniiru። 🙏 Sooma Eebbaa fi Kan nagaa Nuuf Haa Taasisu! ✍️ Diyaaqon Abeel Kaasaahun 🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿 https://t.me/ankets_adeheno

🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿 🌿 በዐቢይ ጾም የተከለከሉ ምግቦች፦ ❌ ቁጣ ❌ ቅናት ❌ ሐሜት ❌ በቀል ❌ ጥላቻ ⚠️ እነዚህ አደገኛና መርዛማ "ምግቦች" ወደ ሰውነትዎና ወደ ነፍስዎ እንዳይገቡ በመከላከል ጾምዎን ይቀድሱ! 📌 አስታውሱ ፦ እነዚህ ድርጊቶች በፍስክም ጊዜ ጨርሶ የማይፈቀዱ ቢሆንም፤ በጾም ወቅት ግን የድካማችንን ዋጋ ሙሉ ለሙሉ ስለሚያሳጡ አጥብቀው ይከለከላሉ። 🙏 የበረከትና የሰላም ጾም ያድርግልን! ✍️ ዲያቆን አቤል ካሣሁን 🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿 https://t.me/ankets_adeheno

🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿 #እንኳን ለዐቢይ ጾም በሰላም አደረሰን ! #ለጾም  የበረታ ሰውነት #ለጸሎት የሚተጋ ልብ #በጎ የሚያደርግ ህሊና  #መልካም የሚያይ ዐይን  #በደልን የሚረሳ አዕምሮ #ይቅርታ የሚጠይቅ አንደበት #የተቸገሩትን የሚረዳ  እጅ  እንዲኖረን  እግዚአብሔር  ይርዳን ። እንደ ሰው አስበን እንደ ክርስቲያን መኖሩን ያድለን #ጾሙ ለሀገር ምሕረት የሚወርድበት ፣ ሕሙማን የሚፈወሱበት ፣  ሕዝቦች እርስበርሳችን ቸርነት የምናደርግበት ፣ ቅንነት የሚገዝፍበት ፣ ጸሎታችን የሚሰማበት ፣ ሞት የሚደነግጥበት ጾም ያድርግልን ። #ጾም ጸሎታችንን የቅዱሳን አምላክ እግዚአብሔር ይቀበልልን አሜን 🙏 🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿 https://t.me/ankets_adeheno

🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿 "ጌታችን ተርቦ ሳለ ምሥዋዑ በወርቅ ቢንቆጠቆጥ ምን ጥቅም አለው? #ስለዚህ ከኹሉም በፊት ጌታችን ተርቦ ስታገኘው አብላውና ከዚያም ምሥዋዑን አስጊጠው
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿 "ጌታችን ተርቦ ሳለ ምሥዋዑ በወርቅ ቢንቆጠቆጥ ምን ጥቅም አለው? #ስለዚህ ከኹሉም በፊት ጌታችን ተርቦ ስታገኘው አብላውና ከዚያም ምሥዋዑን አስጊጠው፡፡ ነገር ግን እርሱ አንድ ኩባያ ውኃ እንኳን ሳያገኝ አንተ ጽዋዑን የወርቅ ጽዋ ታደርገዋለህን? ምንድን ነው ጥቅሙ? #እርሱ ገላውን የሚሸፍንበት ልብስ አጥቶ አንተ ምሥዋዑን በወርቅ ልብስ ታስጌጣለህን? ምንድን ነው በቁዔቱ? እስኪ ንገረኝ: እርሱ የሚበላውን አጥቶ አንተም ረሀቡን ሳታስታግስለት ወደ ቤተ መቅደሱ መጥተህ ምሥዋዑን በብር ስታስጌጠው የሚያመሰግንህ ይመስልሃልን? እንዲያውም አይቈጣምን? #አንዲት ቁራጭ ጨርቅ ለብሶ ብርድና ሐሩር እያፈራረቀ ሲያቆራምደው እየተመለከትከው ምንም ልብስ ሳትሰጠው በቤተ መቅደስ መጥተህ "ይህ ስጦታ ለጌታዬ ክብር ነው" ብለህ ምሥዋዑን በወርቅ ብታስጌጠው ጌታችን አንደ ተሳለቅህበትና እንደ ሰደብኸው ከዚህም የባሰ በደል እንደ ፈጸምህ የማይቈጥረው ይመስልሃልን?" #ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ፥ የማቴዎስ ወንጌል፥ ድር. 50:4 🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿 https://t.me/ankets_adeheno

🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿 #እንኳን አደረሳችሁ !!! #ድንግል ማርያም በእረፍቷ ቀን ኃይልን በምታደርግ ጸሎቷ ከኃጢያት ፣ ከክፋት ታሳርፈን ። #መልካም በዓል ! 🌿🌿🌿🌿
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿 #እንኳን አደረሳችሁ !!! #ድንግል ማርያም በእረፍቷ ቀን ኃይልን በምታደርግ ጸሎቷ ከኃጢያት ፣ ከክፋት ታሳርፈን ። #መልካም በዓል ! 🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿 https://t.me/ankets_adeheno