cookie

Мы используем файлы cookie для улучшения сервиса. Нажав кнопку «Принять все», вы соглашаетесь с использованием cookies.

avatar

ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች እና መዝሙሮች / Orthodoxsawi temehertoch (mezmuroch)

በዚህ ቻናል ላይ ማንኛውንም ☦☦የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ስርአትን የጠበቁ ✥ አስተምሮቶችን ✟ ❖ ስብከቶችን ✟ ❖ መዝሙሮችን ✟ ❖ መንፈሳዊ መጽሐፍቶችን ያገኛሉ።☨☨ "መፅሐፍ ቅዱስን ወዳጅህ አድርገው አንተ የቃሉ ወዳጅ ስትሆን እግዚአብሔር ደግሞ የልቡ ወዳጅ ያደርግሀል።"      /አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ/

Больше
Рекламные посты
1 027
Подписчики
Нет данных24 часа
+47 дней
+1630 дней

Загрузка данных...

Прирост подписчиков

Загрузка данных...

Фото недоступноПоказать в Telegram
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿 #ወንድሞቼ! ከእናንተ መካከል አንድ አይነ ሥውር ሰው ወደ ጉድጓድ ገብቶ ሊወድቅ ሲል እጁን ዘርግቶ የማይደግፈው ማን ነው? ታድያ ወንድሞቻችንና እህቶቻችን በልቡናቸው ታውረው ወደ ሲዖል ጉድጓድ ለዘለዓለም ሲወድቁ እንደ ምን እጃችንን የበለጠ አይዘረጋም?ወገኖቼ!በነፍስም በሥጋም የታመመ ሰውን ስታዩ "ይህ የእኔ ሥራ አይደለም: የቀሳውስትና የመነኮሳት ሥራ እንጂ፡፡ ምክንያቱም ሚስት አለችኝ: ልጆችንም አሳድጋለሁ" አትበሉ፡፡ እስኪ ምሳሌ መስዬ ልጠይቃችሁ እናንተም መልሱልኝ፡፡ አንድ ትልቅ በወርቅ የተሞላ ሳጥን ወድቆ ብታዩ "ይህ እኔን አይመለከተኝም፡ ሌሎች መጥተው ያንሡት እንጂ" ትላላችሁን? ግራ ቀኛችሁን አይታችሁ በፍጥነት የምታነሡት አይደለምን? ይህ ወደ ዘለዓለም ጉድጓድ እየወደቀ ያለው ወንድማችሁም ከዚያ ወርቅ በላይ ውድ የእግዚአብሔር ሀብት ነውና አንሡት እንጂ የበለጠ  እንዲወድቅ አትግፋት፡፡ እግዚአብሔር ይህን በተመለከተ በአፈ ያዕቆብ እንዲህ ብሏልና፡- "ወንድሞቻችን ሆይ! ከእናንተ ወገን ከጽድቅ ወጥቶ የበደለ ቢኖር መክሮ አስተምሮ ከበደሉ የመለሰው ቢኖር ራሱን አንድም ወንድሙን ከሞት እንዳዳነ ይወቅ፡፡ የራሱን አንድም የወንድሙን ብዙ ኃጢአቱን እንዳስተሠረየ ይወቅ፡፡ አንድም የወንድሙን ነፍስ እንዳዳነ ይወቅ"(ያዕ.5:19-20)፡፡ #ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ 🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿 https://t.me/ankets_adeheno
Показать все...
Фото недоступноПоказать в Telegram
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿 #አንድ አረጋዊ እንዲህ አሉ ፦”ልጆቼ ሆይ፦ ራሳችሁን መለወጥ ሳትችሉ የሌላን ሰው ነፍስ ማዳን ወይንም ሰወችን መርዳት አትችሉም፤ ነፍሳችሁ በልዩ ልዩ ምስቅልቅል ውስጥ ሆናም የሌላውን ሰው መንፈሳዊነት ስርአት ማስያዝ አይቻላችሁም፤ እናንተ ራሳችሁ የውስጥ ሰላም ከሌላችሁ ለሌሎች ሰላምን ማስገኘት አትችሉም ፤ ብዙውን ጊዜ የሰወችን በኛ ምክንያት ለበጎ ነገር መነሳሳትና ነፍሳቸውም ወደ እግዚአብሄር መቅረብ የምናየው ወደ በጎ ይቀርቡ ዘንድ በአፍ በምንነግራቸው ነገር ሳይሆን በእኛ ላይ በተግባር በሚገለጥ የመንፈስ ፀጋና ስጦታ ነው፡፡ ሌሎች ሰወችም ህይወታቸው ለበጎ ነገር እንዲነሳሳና እንዲለወጥ በእኛ ህይወት ሲማሩ እኛ እንኳን ላናየውና ላንረዳው እንችላለን፡፡" 🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿 https://t.me/ankets_adeheno
Показать все...
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿 #በደብረ_ምጥማቅ_ተገለጠች ከግንቦት 21 ጀምሮ እስከ 25 ድረስ ለአምስት ተከታታይ ዕለታት፥ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በደብረ ምጥማቅ መገለጥ ይከበራል። በደብረ ምጥማቅ በዘይቱን ማርያም ቤተ ክርስቲያን ጉልላት ላይ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በ1968 በግብጽ ተገልጣለች። ይህ በእርግጥ ብዙ መልእክታት ያሉት ጉዳይ መኾኑ ለማንም ግልጽ ነው። ካልኾነማ ደርሶ ለምን ተገለጠች? እንዲሁ ያለ ምንም ዓላማ ነውን? የሚልና መሰል ጥያቄዎችን ያስነሣልና። የአንድን ክስተት መልስ አለማወቅ በራሱ ጉዳዩን ቀሊል ሊያደርገው እንደማይችል ልብ እንበል። መገለጧ ለምን እንደ ኾነ የማይታወቅ ቢኾን እንኳን፡ መልእክት የሌለው የመኾኑ ማስረጃ ሊኾን አይችልም። ስለዚህ የእመቤታችንን መገለጥ ቀለል አድርገን ማለፍ ያለብን መስሎ አይታየኝም። ++++++++  +++++++  ++++++++++ እመቤታችን በደብረ ምጥማቅ በዘይቱን ማርያም ቤተ ክርስቲያን ጉልላት ላይ ትገለጽ ነበር። የምትገለጥ የነበረውም በብርሃንና አስደናቂ በኾነ ውበት ነው። አንዳንዴ ከመስቀሉ ሥር ስትሰግድ ትታያለች፤ አንዳንዴ ልጇን ወዳጇን ታቅፋው ትታያለች። ቅዱሳን መላእክት ክንፎቻቸውን ዘርግተው፣ ያመሰግኗታል፤ ይጋርዷታልም። ሰማዕታት ይሰግዱላታል፤ ምስጋናና ክብር ያቀርቡላታል። ጻድቃን ደናግላን፣ ቅዱሳን በሙሉ ያደንቋታል። በአጭሩ አማናዊቷ ቤተ ክርስቲያን ትገለጣለች ማለት ነው። ይህን ኅብረቲዊነት መመልከት እንዴት ያረካ ይኾን! የክርስቲያን ናፍቆቱ ወደዚህ ማኅበር ውስጥ ከመግባት በቀር ምን ሊኾን ይችላል! እንግዲህ ይህን አስደናቂ መገለጥ እንዴት በመጨመጨ ዐይን ልናየውና መልእክቱን ልንዘነጋ እንችላለን? ተስፋችንስ ከንቱ አለመኾኑን ከዚህ በላይ ምን ማሳያ እንሻለን! ይሄን አንድነት ከጥልቅ ልባችን እንድንመኝ ለማድረግና፡ ዓለም ጣዕሟ ከዚህ ኅብረት አንጻር መራራ መኾኑን ተረድተን ወደዚህ ኅብረት ለመግባት መትጋት፣ መውደድና መፈለግ አለብን! ++++  +++++++  +++++++  +++++++ እመቤታችን የተገለጠችው በጉልላቱ ላይ ነው። ይህን ስናስተውል፡ በአእምሯችን ውስጥ የመንፈሳዊነትን ከፍታን ማየት እንችላለን። ወደ ላይ ማየት! እመቤታችን ቅድሰት ድንግል ማርያምን በምድራዊ አስተሳሰብ ውስጥ መፈለግ የለብንም። በሌላ በማንኛው ዓለማዊ ነገር ውስጥ የምናገኛት አይምሰለን። እመቤታችን ያለችው በጉልላቱ ላይ ነው። ከፍ ባለ መንፈሳዊ ሕይወትና የቀና አስተሳሰብ ላይ እርሷን በእርግጥም እናገኛታለን። ስለዚህ ወደ ላይ እንውጣ! በእርሷ ቤተ ክርስቲያን እርሷን እንያት! በእርሷ ቤተ ክርስቲያን ወስጥ ተገኝተን በኃጢአታችን ምክንያት እርሷን ሳናይ እንደ መቅረት ያለ ምን ጉዳት አለ! ስለዚህ ከፍ እንበል። አልእሉ አልባቢክሙ "ልቡናችሁን ከፍ ከፍ አድርጉ" አእምሩ ኀበ ዘትቀውሙ "የቆማችሁበትን አስተውሉ" ተንሥኡ ለጸሎት ወይም ተንሥኡ ለነጽሮተ ምሥጢር "ለጸሎት ተነሡ፡ ወይም ምሥጢር ለማየት ተነሡ" እንግዲህ እነዚህ ወደ ላይ ማንሻዎች ናቸው። እመቤታችንን በእነዚህ መነሻዎች ከፍ ብለን እንመልከታት!! +++++ +++++  +++++   ++++++++++ የእመቤታችን መገለጥ ለኃጥኡም ለጻድቁም፣ ለአማኙም ለከሐዲው መኾኑ ደግሞ ሌላው አስደናቂው ነገር ነው። ርኅርኂተ ሕሊና መኾኗን ያመለክታል። የቆሰሉ ነፍሳትን ሕሊናት ለማከም፣ ለሚያምኑት መጽናኛ ልትኾን ተገለጠች። ከእስላሞችም እንዲያዩአት ፈቀደች። ቅድስና የሌለው ሊያያት የማይገባ ሲኾን፡ መሐሪት ስለ ኾነች ለአሕዛብም ታየች። ለእኛስ መች ታየች ብለው ከማመን እንዳይዘገዩ፣ አንድም አፍቃሪተ ሰብእ መኾኗ እንዲረዳን!! እርሷ ከእኛ የሌለች መስሎን በቀቢጸ ተስፋ እንዳንፍገመገም ጠበቀችን። በእርግጥም የሔዋን ጠበቃ የተባለችው የሔዋን ጠበቃ ብቻ ስለ ኾነች ሳይኾን በእርሷ አንጻር የእኛም ጠበቃ መኾኗን ለማመልከት እንጂ። ብዙዎች ከአሕዛብ ወገን ተደነቁ፡ ወደ እውነተኛው በረትም በጥምቀት በር ገቡ። እርሷን ካዩ በኋላ በውጪ መቅረት አልኾነላቸውምና! እመቤታችን ኾይ ለአሕዛብም ጭምር መገለጥሽ አስደንቆናል! በዚያውም ምንም ኃጥእ ብንኾን ከፈለግንሽ የምናገኝሽ መኾኑ ተረድቶናል። እኛን ኃጥአንንም ሳትንቂን በልባችን ውስጥ ተገለጪ! +++++ ++++    +++++++++  ++++++ በተደጋጋሚ መገለጧ ደግሞ ፍጹም ጊዜ ጥርጣሬን የሚያርቅ። ኹል ጊዜም በቃል ኪዳኗ የምትረዳን መኾኗን እንድንገነዘብ ያደርገናል። አንዴ ታይታን ተጠራጥረን፡ በድጋሚ ታይታን ከጥርጥር የምንወጣ እንኖራለንና። ምልጃዋ ለልጇቿ የማይቋረጥ መኾኑንም እናስተውላለን። ከዚሁ ጋር ተያይዞ ለረጅም ሰዓት (2-3 ሰዓት) መታየቷም በአንድ በኩል የእርሷ መገለጥ ምትሐት አለመኾኑን፡ በሌላ በኩል እኛን የምትፈልገንና ፍለጋዋም ጽኑ መኾኑን ይረዳኛል። እንግዲያውስ እርሷ እየፈለገችን ወዴት እንሮጣለን! እንዴት ከእርሷ ይልቅ ኃላፊ ነገሮችን ልናስቀድም እንችላለን? እንዴትስ በእርሷ ጨክነን ሰዓት የለኝም እያልን ከቅድስት ቤተ ክርስቲያን እንቀራለን? ወዳጆች ሆይ ይህ የእመቤታችን መገለጥ አሕዛብ የመለሰ መኾኑን ስትሰማ ከኃጢአት መንገድ መመለስና ንስሓ መግባት እንዳለብህ አይረዳህምን? ኋለኞቹ አሕዛብ በመገለጧ በር በኩል ወደ ጽድቅ ሲገቡ ፊተኞቹ እኛ በኃጢአት መስኮት ስለ ምን እንወጣለን? ++++++  +++++++  +++++++  +++++ የእመቤታችን መገለጥ ውስጥ፡ ከመስቀል ስር ኾና መታየቷ ቀራንዮን በሕሊችን ውስጥ ለመቅረጽ ካልኾነ በቀር ምን ሊኾን ኖሯል! ወዳጄ ነገረ ማርያምን ስታይ በእርሱ ውስጥ ወደ ቀራንዮ ትገሰግሳለህ! የእናትነቷን ፍቅር ከመስቀሉ ስር ዝቅ ብለህ ትጠጣለህ። ቅዱሳን መላእክት ሲያመስግኗት አይተህ፡ በቸልታ ያሳልፍካቸውን ጊዜያት በማሰብ ታዝናለህ! በክንፎቿ ሲጋርዷት አይተህ በልብህ ውስጥ ፍቅሯን ሰውረህ ጣዕሟን በአንደበትህ በአስደናቂ ምስጋና ታጣጥማለህ!! ልጇን ታቅፋው ስትገለጥ አይተህ ያለ እርሷ ልጇን የማታገኝ መኾኑን ትረዳለህ። ስለዚህ ወደ ጉልላቱ እመቤታችን ስትገለጥ ተመልከትና አንተም ጣዕሟን በአንደበትህ ለዓለም ግለጥ። አፍህን በዘፈን አታቆሽሸው፣ በሐሜትም አታዝገው፣ በጫጫታም አታጨቅየው፣ በቅድስት ድንግል ማርያም ምስጋና አስውበው እንጂ። +++++  ++++++   ++++++  +++++++ በጉልላቱ ላይ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ታይታ አሕዛብን እንዳሳመነች፡ አንተም እርሷን በሕይወትህ ግለጣት፡ እንደ እርሷ ሰውን ሁሉ ያለ አድልዎ ውደድ! ማንንም አትጥላ! የሚጠሉህን ክርስትናን ገልጠህ ወደ በረቱ ሰብስባቸው። ኃጢአትን ፈጽሞ ጥላት፣ ከጠማማ ጋር አትጣመም። በእውነትና በንጽሕና መንገድ በመጓዝ በሰውነትህ ውስጥ ማርያማዊ ጣዕም ያለውን ሕይወት ግለጥ። ሰውነትህ የማርያማዊነት ፍቅር መውጫ ጉልላት ይኹንና እርሷን ባንተ ውስጥ አይተው እርስ በእርስ በክርስቲያናዊ ፍቅር ይፋቀሩ ዘንድ! ክርስትና ማለት የቤተ ክርስቲያንን ፍቅር የመግለጥ ሕይወት ነው። የእመቤታችን ምልጃ ከሁላችን ጋር ይኹን አሜን! 🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿 https://t.me/ankets_adeheno
Показать все...
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿 #ተአምራትን ማድረግ ትፈልጋላችሁን ? 👉 እንኪያስ በዘፈን የደነቆረን ጀሮ መዝሙር       እንዲሰማ አድርጉት ፡፡ 👉 ሴትን በመመኘት የታወረው ዐይን ፈጣሪውን       እንዲያይ አድርጉት ፡፡ 👉 በስርቆት የሰለለ እጅ በምጽዋት እንዲዘረጋ       አድርጉት ፡፡ 👉 ወደ ኃጢአት ቤት በመሄድ ሽባ የሆነውን እግር       ወደ እግዚአብሔር ቤት እንዲሮጥ አድርጉት ፡፡ 👉 ሐሜትን በማውራት ዲዳ የሆነውን ከንፈር       መልካም  ንግግርን እንዲናገር አድርጉት ፡፡ #ከተአምራት ሁሉ የበለጠ ተአምር ይሄ ነው ፡፡ #ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ 🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿 https://t.me/ankets_adeheno
Показать все...
Фото недоступноПоказать в Telegram
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿 #ኢየሱስ ናትናኤልን ወደ እርሱ ሲመጣ አይቶ ስለ እርሱ። ተንኰል የሌለበት በእውነት የእስራኤል ሰው እነሆ አለ ።" (የዮሐንስ ወንጌል 1:48) #ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በከበረ ሐዋርያ ጸሎት ይማረን ለሁላችንም የሐዋርያው በረከት ትድረሰን ለዘለዓለሙ አሜን !!! #እንኳን ለሐዋርያው ለቅዱስ ናትናኤል ዓመታዊ የእረፍት በዓል አደረሳቹ አደረሰን 🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿 https://t.me/ankets_adeheno
Показать все...
Фото недоступноПоказать в Telegram
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿 #ሩፋኤል ሆይ መንፈሳዊ ሐኪም ነህና ደዌ ኃጢአት እንዳያሰቃየኝ ፍቱን መድኃኒትህን ቀብተህ አድነኝ #መልክአ ቅዱስ ሩፋኤል 🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿 https://t.me/ankets_adeheno
Показать все...
Фото недоступноПоказать в Telegram
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿 #ትጒህ በጸሎት #አቡነ ተክለሃይማኖት እየረዱ (ረድ ሆነው ) ሰባት ሰባት ጊዜ ዳዊትን ያደርሱ ነበር (ማር ይስሐቅ ገፅ 77 / ገድለ ተክለሃይማኖት ) #አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቡልጋ ደብረ ጽላልሽ ወይም ዞረሬ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን የሰበካ ክልል ከአባታቸው ከካህኑ ቅዱስ ጸጋ ዘአብና ከእናታቸው ቅድስት እግዚእ ኃረያ መጋቢት 24 ቀን ተፀንሰው፤ በ1197 ዓ.ም ታኅሣሥ 24 ቀን ተወለዱ፡፡ በተወለዱ በሦስት ቀናቸው ከእናታቸው እቅፍ ወርደው «አሐዱ አብ ቅዱስ፣አሐዱ ወልድ ቅዱስ፣ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ» ብለው ሥላሴን አመስግነዋል፡፡ ወላጆቻቸውም ፍስሐ ጽዮን አሏቸው፡፡ ትርጓሜውም የጽዮን ተድላዋ ደስታዋ ማለት ነው፡፡ በወላጅ አባታቸው በካህኑ ቅዱስ ጸጋ ዘአብ ግብረ ዲቁናን ሥርዓተ ቤተክርስቲያንን ሲያጠኑ ቆይተው በአሥራ አምስት ዓመታቸው ከእስክንድርያው ሊቀ ጳጳስ አቡነ ቄርሎስ /ጌርሎስ/ ዲቁናን ተቀብለዋል፡፡ #አባታችን ከመነኮሱም በኋላ በዳዊት ጸሎት ከነቢያት ምስጋና ሌሊቱን ሙሉ ይተጉ ነበር በያንዳንዱ መዝሙርም አሥር አሥር ስግደትን ይሰግዱ ነበር፡፡  ለ22 ዓመት ቆመው በመጸለይ የአንድ እግራቸው አገዳ ተሠበረ ደቀ መዝሙሮቻቸው በጨርቅ ጠቅልለው ቀበሩት፡፡ በአንድ እግራቸው ለ7 ዓመት በጸሎት ቆሙ በጠቅላላው ለ29 ዓመት በጸሎት ከቆሙ በኋላ በ99 ዓመት ከ10 ወር ከ10 ቀን ነሐሴ 24 ቀን 1290 ዓ.ም አረፉ አባታችን ባረፉ 54 ዓመት  በ1344 ዓ.ም ለአባታችን ለአቡነ ሕዝቅያስ ተገልጸው አጽማቸው ከደብረ አስቦ ወደ ደብረ ሊባኖስ ግንቦት 12 ቀን እንዲፈልስ አድርገዋል፡፡ በረከታቸው በእኛ አድራ ትኑር ✍️ አምኃ ሥላሴ / መኩሪያ ተስፋዬ 🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿 https://t.me/ankets_adeheno
Показать все...
Фото недоступноПоказать в Telegram
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿 #ተወዳጆች ሆይ! እግዚአብሔር እነዚህን መከራዎች ያመጣው የእናንተን ግድየለሽነት ለማራቅና ከእንቅልፋችሁ እንድትነቁ ብሎ ነው #ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ 🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿 https://t.me/ankets_adeheno
Показать все...
የከበረ ዮሐንስም ንጉሥ ሆይ እንዲህ አትበል እንዲህ አንተ እንደምትለው አይደለም የከበረች ድንግል እመቤታችንስ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሆድዋ ውስጥ በነበረ ጊዜ የእርሱ ኅብረ መልክ በሚለዋወጥ ጊዜ ከእርሱ ጋር መልኳ ይለወዋወጥ ነበር። በንጹሕ ብርሌ ውስጥ ውኃ በጨመሩ ጊዜ ውኃ መስሎ እንደሚታይ ወይን ጠጅም ቢጨምሩ ያንኑ መስሎ እንደሚታይ ወይም ከውስጡ በተጨመረው ቀይም ቢሆን ቀልቶ እንደሚታይ ቅጠልያም ቢገባበት ቅጠልያ መስሎ እንደሚታይ። ድንግልም በሆድዋ ውስጥ የልጅዋ መልክ በሚለዋወጥ ጊዜ ከእርሱ ጋራ መልኳ ይለዋወጥ ነበር። እንደ ሮማን አበባ የምትቀላበት ጊዜ አለ እንደናርዶስም የምታብለጨልጭበት ጊዜ አለ የለመለመ ቅጠል የምትመስልበትም ጊዜ አለ ከወለደች በኋላ ግን አልተለወጠችምና ዮሴፍ በአንድ በቀድሞው ኅብረ መልኳ ተወስናለት መልኳን ተረዳ ማለት ነው አለው። በዚያን ጊዜ በንጉሥ አዳራሽ ውስጥ ከወርቅ የተሠራ የእመቤታችን አምላክን የወለደች የድንግል ማርያም ሥዕል ነበረችና አፈ ወርቅ ዮሐንስ ልሳነ ወርቅ ዮሐንስ አፈ በረከት ዮሐንስ መልካም ተናገርክ የሚል ቃል ከእርሷ ወጣ። ንጉሡና ከእርሱ ጋር ያሉት በሰሙ ጊዜ እጅግ አደነቁ እግዚአብሔርንም አመሰገኑት በዚያን ጊዜ ንጉሥ አዝዞ ወርቅ ሠሪ አስመጥቶ ለከበረ ዮሐንስ የወርቅ ልሳን አሠርቶ ለሚያየው ሁሉ መታሰቢያ ምልክት ሊሆን አምላክን ከወለደች ከእመቤታችን ከድንግል ማርያም ሥዕል ዘንድ ሰቀለው። ቅዱስ ዮሐንስንም ከዚያች ቀን ወዲህ ልሳነ ወርቅ ብሎ ጠራው አፈ ወርቅም ተብሎ እስከዛሬ ተጠራ። #ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሱ ጸሎትና ምልጃ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። #ስንክሳር_ዘወርኀ_ግንቦት 🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿 https://t.me/ankets_adeheno
Показать все...