ru
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Открыть в Telegram

📈 Аналитический обзор Telegram-канала EEP Communication

Канал EEP Communication (@eepcommuication) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 15 698 подписчиков, занимая 8 062 место в категории Технологии и приложения и 2 174 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 15 698 подписчиков.

Согласно последним данным от 01 сентября, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 139, а за последние 24 часа — 1, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 28.75%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 16.42% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 4 513 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 2 578 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 10.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
EEP Communication

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 02 сентября, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Технологии и приложения.

15 698
Подписчики
+124 часа
+277 дней
+13930 дней
Архив постов
ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ የከተማዋን የኃይል አቅርቦት አቅም በአራት እጥፍ ያሳድጋል ……...///……… የደሴ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት ሲጠናቀቅ የከተማዋን የኃይል አቅርቦት አቅም በአራት እጥፍ እንደሚያሳድግ የትራንስሚሽን ቢዝነስ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አስታወቁ። በምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚው ኢንጂነር አንዱዓለም ሲዓ የተመራ የልዑካን ቡድን በመገንባት ላይ ያለውን የደሴ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት በመስክ በመገኘት ገምግሟል። ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚው በጉብኝቱ ወቅት እንደገለፁት ከተሞቻችን የሚያስፈልጋቸውን የኤሌክትሪክ ኃይል ለማሟላት ተቋሙ ከመቼውም ጊዜ በላይ በቁርጠኝነት እየተንቀሳቀሰ ነው፡፡ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ሲጀምር የደሴ ከተማን የኤሌክትሪክ ፍላጎት አቅም ለሚቀጥሉት 20 ዓመታት መሸከም የሚችል ነው ብለዋል፡፡ ፕሮጀክቱን በተያዘው በጀት ዓመት መጨረሻ አጠናቆ ወደ ሥራ ለማስገባት ዕቅድ መያዙን የጠቀሱት ኢንጂነር አንዱዓለም የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩን ለመገንባት ከተማ አስተዳደሩ ለካሳና ተያያዥ ጉዳዮች አፋጣኝ ምላሽ በመስጠት አስፈላጊውን እገዛ እንዲያደርግ ጠይቀዋል። እንደ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚው ገለፃ ለፕሮጀክቱ ግንባታ የሚያስፈልጉ ተጨማሪ የኤሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎችን በቅርቡ ወደ ሳይት የማጓጓዝ ሥራዎች ይጀመራሉ፡፡ ፕሮጀክቱ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ብቻ አይደለም ያሉት ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚው ከተማ አስተዳደሩ የግንባታውን ሂደት በቅርበት እየተከታተለ እገዛ እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ የደሴ ከተማ አስተዳደር ተወካይ ከንቲባ ኮማንደር ሰዒድ ዓሊ እንደገለፁት በከተማዋ የሚስተዋለውን የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት እና ፍላጎት ያለመጣጣም ችግር  ለመቅረፍ ከተማ አስተዳደሩ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጋር በቅርበት ይሰራል፡፡ ከፕሮጀክቱ ጋር ተያይዘው ለሚነሱ ጥያቄዎች አፋጣኝ ምላሽ ለመስጠት ከተማ አስተዳደሩ ከመቼውም ጊዜ በላይ ቁርጠኛ መሆኑን አረጋግጠዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 28 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+6

ተቋሙ ከ8 መቶ ሺህ ብር በላይ በሚገመት ወጪ የትምህርት ግብዐቶች ድጋፍ አደረገ ‎........///........ ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በደሴ ከተማ አስተዳደር ስር ለሚገኘው የጢጣ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የተለያዩ የትምህርት ግብዐቶችን ድጋፍ አደረገ። ‎ ‎ድጋፉን የተቋሙ የትራንስሚሽን ቢዝነስ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አንዱዓለም ሲዓ ለከተማ አስተዳደሩ ተወካይ ከንቲባ ኮማንደር ሰዒድ አሊ አስረክበዋል። ‎ ‎የደሴ ከተማ አስተዳደር ተወካይ ከንቲባ ኮማንደር ሰዒድ ዓሊ በርክክብ ሥነ ሥርዓቱ ላይ እንደተናገሩት ድጋፉ በትምህርት ቁሳቁስ እጥረት ምክንያት ተማሪዎች ትምህርታቸውን እንዳያቋርጡ እገዛ ያደርጋል። ‎ ‎የተደረገው ድጋፍ ወቅቱን የጠበቀ በመሆኑ የትምህርት ግብዓቶችን መግዛት ለማይችሉ ወላጆች ትልቅ እፎይታን የሰጠ ነው ብለዋል። ‎ ‎የጢጣ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከደሴ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ፕሮጀክት አቅራቢያ እንደሚገኝ የጠቀሱት ተወካይ ከንቲባው ይህም ህብረተሰቡ በፕሮጀክቱ ላይ የእኔነት ስሜት እንዲሰማው እንደሚያደርግ አብራርተዋል። ‎ ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለትምህርት ዕድገት እያበረከተ ያለውን አስተዋፅኦ አድንቀው በቀጣይ መሰል ድጋፎችን አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል። ‎ ‎በተቋሙ የዋና ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኸኝ እንደተናገሩት ትምህርት አምራች ትውልድን ለመፍጠር ትልቅ መሳሪያ መሆኑን ስለሚረዳ ከትምህርት ገበታቸው የራቁ ተማሪዎችን ለመመለስ እየተደረገ ያለውን ጥረት ተቋሙ ይደግፋል። ‎ ‎ድጋፉ 250 ለሚደርሱ የጢጣ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች የጽህፈት መሳሪያዎች እና የደብተር መያዣ ቦርሳዎችን ያካተተ ሲሆን ለዚህም ተቋሙ 825 ሺህ ብር ወጪ ማደረጉን ተናግረዋል። ‎ ‎ተቋሙ የትምህርት ጥራትን ለማረጋጋጥ በትውልድ ልማት ሥራዎች ላይ አሻራውን እያሳረፈ እንደሚገኝ ጠቅሰው በቀጣይም መሰል ድጋፎችን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል። ‎በርክክብ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የከተማ አስተዳደሩ የትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊዎች እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ተወካዮች ተገኝተዋል። ‎ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 27 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+4

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እውቅና ተሰጠው …....///…..... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2017 በጀት ዓመት በወጪ ንግድ ያስመዘገበውን ከፍተኛ ገቢ ተከትሎ ከኢ.ፌዲሪ. ንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር እውቅና አግኝቷል፡፡ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በ2017 በጀት ዓመት “የኢትዮጵያን ይግዙ” በሚል መሪ ቃል ባዘጋጀው 2ተኛው የንግድ ሳምንት መርሀ ግብር በወጪ ንግድ ዘርፍ ለተገኘው ስኬታማ ውጤት ተቋማት በወጪ ንግድ ገቢ አፈፃፀምን መሰረት ያደረገ የእውቅና መርሀግብር አካሂዷል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2017 በጀት ዓመት ከወጪ ንግድ ብቻ ከ118 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ማግኘቱን ይፋ ማድረጉ ይታወሳል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 27 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

የሙስና መጠቆሚያ መተግበሪያ ይፋ ሆነ፤ …..///….. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሙስናና ብልሹ አሰራሮችን ምስጢራዊነቱን በጠበቀ መልኩ ለመጠቆም የሚያስችል መተግበሪያ (https://Whistleblowing.eep.com.et) ወደ ሥራ መግባቱን የተቋሙ የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና መከታተያ መምሪያ ዳይሬክተር ገለፁ፡፡ ዳይሬክተሩ አቶ ደረጀ አጥናፌ እንደገለፁት መምሪያው በተቋሙ የሚስተዋሉ የሙስናና ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የተቋሙን አፈፃፀም ለማሳደግ የሚያስችሉ የተለያዩ ተግባራትን እያከናወነ ነው፡፡ ችግሩን አስቀድሞ ለመከላከል የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችን ከማከናወን በተጨማሪ ሠራተኞችና ባለድርሻ አካላት ምስጢራዊነቱን በጠበቀ መልኩ ጥቆማ ለመስጠት የሚያስችል መተግበሪያ በተቋሙ መበልፀጉን የጠቆሙት ዳይሬክተሩ መተግበሪያው በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂና በሳይበር ደህንነት መምሪያዎች ተረጋግጦ ሥራ ላይ እንዲውል ይሁንታ ማግኘቱንም ተናግረዋል፡፡ ጥቆማው የተፈጸመው ወይም ሊፈጸም የታሰበው ድርጊት ምን እንደሆነ፣ የተጠርጣሪ ሙሉ ስም፣ መለያ ቁጥር እና የሚሠራበት የሥራ ክፍል፣ በድርጊቱ የተገኘ ወይም ወደ ፊት ሊገኝ የሚችል ጥቅም እንዲሁም የደረሰ ወይም ሊደርስ የሚችል ጉዳት ማካተት እንዳለበትም ተናግረዋል። በተቋሙ የሠራተኞች እና የሥራ መሪዎች የሥነ-ምግባር ደንብ አንቀጽ 22 ንዑስ አንቀጽ 2 መሠረት የሚቀርቡ ጥቆማዎች እውነተኛ፣ ያልተዛባ፣ ከበቀል የፀዳ፣ አሳሳች ያልሆነ እና ምክንያታዊ በሆነ እምነት ላይ የተመሠረተ መሆን እንደሚኖርበትም አስገንዝበዋል። መተግበሪያው ሠራተኞች እንዲሁም ማንኛውም አካል ባሉበት ቦታ ሆነው ያለምንም ተፅዕኖ ጥቆማ ለመስጠት እንደሚያስችላቸው የጠቆሙት አቶ ደረጀ ጠቋሚው ፈቃደኛ ከሆነ በአካል ቀርቦ ስለ ጉዳዩ ማስረዳት እና የምርመራ ሂደቱን ማገዝ እንደሚችልም ተናግረዋል፡፡ የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በበኩላቸው ተቋሙ አብዛኛውን በጀቱን ለኃይል መሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ግንባታ እንደሚያውል ገልፀዋል፡፡ ይህ በጀት ለታለመለት ዓላማ እንዲውልና ፕሮጀክቶች ከሙስናና ብልሹ አሰራር በፀዳ መልኩ በታቀደላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የቁጥጥር ሥራው መጠናከር እንዳለበት አስገንዝበዋል፡፡ በመሆኑም የተቋሙ ሠራተኞች እንዲሁም ጥቆማ ያለው አካል በበለፀገው መተግበሪያ ትክክለኛ ጥቆማ በመስጠት የበኩላቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ አሳስበዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 27 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

የተቋሙ ከፍተኛ የሥራ መሪዎች ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት ደሴ ገቡ ‎……..///…….. ‌‎በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የትራንሚሽን ቢዝነስ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አንዱዓለም ሲዓ የተመራ የልዑካን ቡድን ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት ደሴ ከተማ ገብቷል። ‎ ‎ኢንጂነር አንዱዓለም እና ልዑካቸው ኮምቦልቻ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የደሴ ከተማ አስተዳደር ተወካይ ከንቲባ ኮማንደር ሰዒድ አሊ አቀባበል አድርገውላቸዋል። ‎ ‎ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚው እና ልዑካቸው በአንድ ቀን የሥራ ጉብኝታቸው የደሴ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት እንቅስቃሴን ጨምሮ የችግኝ ተከላ እና የአቅመ ደካማ ቤቶች ዕድሳት እንዲሁም ለተማሪዎች የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 27 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+5

ሁሉም  የሥራ መሪ ለተቋሙ ስኬት በቁርጠኝነት ሊሰራ እንደሚገባ ተገለፀ …….///……. የኤሌክትሪክ ኃይል መሠረተ ልማት ለሁለንተናዊ  ዕድገት ቁልፍ ሚና ያለው መሆኑን በመረዳት መላው የተቋሙ የሥራ መሪዎች በዘርፉ የተያዙ ዕቅዶችን ለማሳካት በቁርጠኝነት ሊሰሩ እንደሚገባ የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ አሳሰቡ። በግሪድ ስትራቴጂ፣ በሰው ሀብት ልማት፣ በስነምግባር እና በለውጥ ሥራ አመራር ላይ በማተኮር ለተቋሙ የስራ መሪዎች ለሁለተኛ ዙር እየተሰጠ ያለው ስልጠና ማጠናቀቂያ መርሃግብር ላይ የተገኙት ኢንጂነር አሸብር የሥራ መመሪያ ሰጥተዋል። ዋና ሥራ አስፈፃሚው እንደገለፁት የበጀት ዓመቱ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታን በስኬት አጠናቀን በምረቃ ዋዜማ ላይ የምንገኝበት መሆኑ ልዩ ያደርገዋል። በዚህ ስኬት ይበልጥ በመነሳሳት የ2018 በጀት ዓመት በሁሉም የሥራ ዘርፎች ያቀድናቸውን ግቦች ለማሳካት በቁርጠኝነት ሌት ተቀን ልንሰራ ይገባል ብለዋል። በዚህ በጀት ዓመት ከባለፉት ዓመታት የላቀ ውጤት ማስመዝገብ እንደሚጠበቅ ያሳሰቡት ኢንጂነር አሸብር ሁሉም የሥራ መሪ መተማመንን መሠረት ያደረገ የቡድን ሥራ በተቀናጀ መልኩ ማከናወን እንደሚኖርበት አሳስበዋል። የተቋሙ የሰው ሀብት ሥራ አስፈጻሚ አቶ አታላይ አበበ በበኩላቸው የተቋም መዋቅር በሥራ ላይ የሚውለው የተቋሙን ዓላማ ለማሳካት መሆኑን ገልፀዋል። በመዋቅር ትግበራ ወቅት የታዩ ክፍተቶች በቀጣይ በተግባር ሂደት አስፈላጊነታቸው እየተገመገመ ውሳኔ የሚሰጥ መሆኑን በአጽንኦት ተናግረዋል። የዋና ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኸኝ ሁሉም የሥራ መሪ ኃላፊነት በተሞላበት እና በተጠያቂነት መንፈስ ሥራውን ሊያከናውን እንደሚገባ አሳስበዋል። የተቋሙን ውጤታማነት ለማሳደግ በተነሱ አስተያየቶች እና ጥያቄዎች ላይ የተቋሙ ከፍተኛ የሥራ መሪዎች ምላሽ ሰጥተዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 26 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+8

የ2018 በጀት ዓመት በኤሌክትሪክ ዘርፍም የማንሰራራት ዓመት ይሆናል ........///...... በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተከናወነ ያለውን የማንሰራራት ዘመን በኃይል ዘርፉም እውን ለማድረግ በትኩረት እንደሚሰራ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ስራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ተናግሩ። ዋና ሥራ አስፈፃሚው እንደገለፁት የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ዕድገት እና የኤሌክትሪክ ኃይል ልማት በእጅጉ የተቆራኙ በመሆናቸው የሀገሪቱን የኃይል ፍላጎት ሊያሟላ የሚችል የኃይል መሠረተ ልማት መገንባት ያስፈልጋል። ለተቋሙ የሥራ መሪዎች ለሁለተኛ ዙር እየተሰጠ በሚገኘው ሥልጠና የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት ኢንጂነር አሸብር ሀገሪቱ የምትፈልገውን የኃይል ፍላጎት ሊያሟላ የሚችል፤ የተቋሙን ራዕይ እና ተልዕኮ በውል የተረዳ የሥራ መሪ ያስፈልጋል ብለዋል። የሁሉም ዘርፍ የሥራ መሪዎች ራሳቸውን በእውቀት እና ክህሎት በማብቃት በስራ ክፍላቸው የሚገኙ ሠራተኞችን ማብቃት እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 26 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+3

የኃይል ማከፋፊያ ጣቢያው ግንባታ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ጀመረ .....….///…...... የደጀን ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የትራንስሚሽን ቢዝነስ አስታወቀ። በትራንስሚሽን ቢዝነስ የፕሮጀክት ማኔጅመንት 2 ሥራ አስኪያጅ አቶ መሐመድ ሽኩር እንዳስታወቁት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው ከ90 ሜጋ ዋት በላይ የመሸከም አቅም ያላቸው አንድ ባለ 63 እና አንድ ባለ 50 ሜጋ ቮልት አምፒር ትራንስፎርመሮች አሉት፡፡ ጣቢያው ሁለት ባለ 230 ኪሎ ቮልት ጥንድ ገቢ መስመር እና አምስት ባለ 33 እንዲሁም አምስት ባለ 15 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች እንዳሉት ተናግረዋል። እንደ አቶ መሐመድ ገለፃ የማከፋፈያ ጣቢያው መገንባት በአካባቢው ይስተዋል ለነበረው የኤሌክትሪክ አቅርቦት ችግር መፍትሔ በመስጠት የግሪድ ሥርዓቱን ከማጠናከሩም ባሻገር  በደጀን እና አካባቢው ለሚገኙ ኢንዱስትሪዎች አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ ያስችላል፡፡ በተቋሙ የደጀን የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ ተቆጣጣሪ አቶ ግርማ ብርሃኑ በበኩላቸው እንደገለፁት ጣቢያው ከ2013 ዓ.ም ጀምሮ ግንባታው ሲከናወን ቆይቷል። የፕሮጀክቱ ሙሉ የፋይናንስ ወጪ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መሸፈኑን የገለፁት አቶ ግርማ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው በይፋ ሥራ መጀመር ለተቋሙና ለአካባቢው ማህበረሰብ እፎይታ የፈጠረ መሆኑን ተናግረዋል። የደጀን- ደብረማርቆስ የኃይል ማስተላለፊያ መስመርና የደብረ ማርቆስ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የማስፋፊያ ሥራ ከሁለት ሳምንት በፊት ግንባታቸው ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት መጀመራቸውንም ነው ያስታወሱት። የደጀን-ደብረ ማርቆስ የኃይል ማከፋፈያና ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት የግንባታ ሥራ በተቋሙ የኮንስትራክሽን ማኔጅመንት መምሪያ የተከናወነ ሲሆን በዕቃ አቅርቦቱ በኩል ደግሞ ፓወር ቻይና የተባለ ኩባንያ ተሳትፎ ማድረጉ ተገልጿል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 26 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

አመራሩ ተቋማዊ ለውጡን በብቃት የመምራት የወል ኃላፊነት አለበት - ‎ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ‎.....///.... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በየደረጃው የሚገኙ ‎አመራሮች ተቋማዊ ለውጡን በብቃት በመምራት ህዳሴን የመሰሉ ዘመን ተሻጋሪ ሥራዎችን የመስራት የወል ኃላፊነት እንዳለበት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ገለጹ። ‎ ‎በተቋሙ የስትራቴጅክ ዕቅድ፣ በሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና፣ በለውጥ ሥራዎች እንዲሁም በስትራቴጅክ ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዙሪያ ለሥራ አመራሩ የተሰጠው የሁለት ቀን የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተጠናቋል። ‎ ‎በሥልጠናው ማጠቃለያ ላይ ሠልጣኝ አመራሮቹ ከመዋቅር፣ ከሥራ ልምድ አያያዝና ከዕድገት፣ ከቅንጅታዊ አሰራር፣ ከኮሙዩኒኬሽን፣ ከብልሹ አሰራር፣ ከግምገማ እና ከተጠያቂነት፣ ከሥራ አፈፃፀም እንዲሁም ከጥቅማ ጥቅም ጋር በተያያዘ ጥያቄዎችንና አስተያየቶችን አንስተዋል። ‎ ‎ሥልጠናው አመራሩ ሚናውን አውቆ የውሳኔ አሰጣጡን በማሳደግ ተቋሙን የሚያሻግሩ ተግባራትን በህብረት ለመስራት የሚያነሳሳ ነው ብለዋል። ‎ ‎መሰል የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠናዎች በአመራሩ መካከል ያለውን መግባባትንና ቅንጅታዊ አሰራርን የሚያሳድግ በመሆኑ ቀጣይነት ባለው መልኩ በዕቅድ ተይዞ መሰራት እንዳለበትም አንስተዋል። ‌‎ በተቋሙ የትራንስሚሽን ቢዝነስ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አንዷለም ሲዓ አመራሩ ለተቋሙ ስኬትና ድክመት ኃላፊነት እንዳለበት አውቆ በቁርጠኝነት በመተጋገዝና በመተጋገል መንፈስ መስራት አለበት ብለዋል፡፡ በተቋሙ የሚከናወኑ ሥራዎች በማስተዋወቅ፣ የአገልግሎት አሰጣጣጡን በማዘመን እና በሥሩ ያሉ ሠራተኞችን በአርያነት በመምራት በኩል ሁሉም አመራር ኃላፊነቱን በአግባቡ መወጣት እንዳለበትም አስገንዝበዋል፡፡ የሰው ሀብት ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚ አቶ አታላይ አበበ መዋቅሩ ሥራን ማዕከል ባደረገ መልኩ ተቋማዊ ውጤታማነት ለማሳደግ፣ ሀብትን በአግባቡ ለመጠቀም ታስቦ መሰራቱንና ጥያቄዎች ካሉ በሂደት እንደሚታዩ አንስተዋል፡፡ አመራሩ ሠራተኞችን በተሠጣቸው የሥራ ዕቅድና ደረጃ መሠረት በአግባቡ የመመዘን፣ ሌሎችን የማብቃት እንዲሁም ለሥራ የተሰጠውን ሀብት በአግባቡ የማስተዳደርና የመጠቀም ኃላፊነት በአግባቡ እንዲወጡም ጠይቀዋል፡፡ ‎የተሻለ አፈጻጸም ያላቸውን ሠራተኞችና የሥራ ክፍሎችን ለማበረታታት የሽልማት እና የእውቅና ሥርዓት ተግባራዊ ለማድረግ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን አብራርተዋል፡፡ ‎የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በበኩላቸው እንደገለጹት የ2018 በጀት ዓመት የተቋሙ የግሪድ ስትራቴጂ ትግበራ የመጨረሻው ዘመን መሆኑን ታሳቢ በማድረግ አመራሩ ሥራ ቆጥሮ አቅዶ መስራት አለበት፡፡ ‎ አመራሩ ህዳሴን መሰል ዘመን ተሻጋሪ አሻራዎችን ለመስራት ‎በጊዜ የለኝም መንፈስ በመግባባት እንዲሁም የተቋሙን ጥቅም በማስቀደም እና ሥራን ማዕከል በማድረግ ተጠያቂነትን በማስፈን ሊሰራ ይገባል ብለዋል፡፡ ሥራዎቻችንን በአግባቡ ኮሙዩኒኬት ማድረግ አለመቻል አመራሩ ለተቋሙ ያለው የእኔነት ስሜት ላይ ጥያቄ የሚያስነሳ ነው ያሉት ኢንጂነር አሸብር አመራሩ በሥሩ ያለውን ሀብትና ሠራተኛ በብቃት በመጠቀምና በመምራት ለተቋሙ ዘብ መቆም እንዳለበት ገልፀዋል፡፡ በተቋሙ የተፈጠሩ የኮሙዩኒኬሽን ፕላትፎርሞች ሥራን ማዕከል በማድረግ በአግባቡና በሥርዓት መጠቀም አስፈላጉ በመሆኑ ያለው ክፍተት መታረም እንዳለበት አሳስበዋል፡፡ አመራሩ ብልሹ አሰራሮችን በማስወገድ ተቋማዊ ለውጡን በብቃት የመምራት የወል ኃላፊነት አለበት ያሉት ዋና ሥራ አስፈፃሚው መሰል ስልጠናዎችን በማጠናከርና ሕግን የተከተለ አሳታፊ የግምገማ ሥርዓት በመዘርጋት ለተሻለ ውጤት እንዲተጋ ጥሩ አቅርበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 23 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+8

አመራሩ የስልታዊ ኮሙዩኒኬሽን ጽንሰ ሀሳብን ተገንዝቦ ለውጤታማነት መስራት ይጠበቅበታል .......///......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልን ውጤታማ ለማድረግ በየደረጃው የሚገኘው የሥራ መሪ የስልታዊ ኮሙዩኒኬሽን ጽንሰ ሀሳብንና ለተቋም የሚኖረውን ሚና ተገንዝቦ መስራት እንደሚጠበቅበት በተቋሙ የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ አሳሰበ። የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን ስለ ስልታዊ ኮሙዩኒኬሽን ጽንሰ ሀሳብና አስፈላጊነት እንዲሁም በተቋም ላይ ስልታዊ ኮሙዩኒኬሽን ምን መምሰል እንዳለበት ለተቋሙ የሥራ መሪዎች ማብራሪያ ሰጥተዋል። ዳይሬክተሩ በማብራሪያቸው የተቋሙ የኮሙዩኒኬሽን ሥርዓት ከርዕይ፣ ተልዕኮ እና ዓላማዎቹ ጋር የተያያዘ መሆን እንዳለበት እና ምን አይነት መረጃ ለማን፣ መቼና ለምን ማስተላለፍ እንደሚገባ ቀድሞ መለየት እንደሚያስፈልግ አስረድተዋል። ስልታዊ ኮሙዩኒኬሽን ተቋሙን ለማስተዋወቅና ገፅታውን ለመገንባት ከማገዙም ባለፈ ውስጣዊ ግንኙነትን ለማጠናከር፣  በተቋሙ ላይ የኢንዱስትሪ ሰላምን ለማስፈን፣ ከደንበኞች ጋር መልካም ግንኙነትን ለመፍጠር፣ አስተሳሰብን ለመቅረፅ እና ሠራተኛው በተቋሙ በሚተላለፈው መልዕክት ላይ ድርሻ እንዳለው ለማሳወቅ እንደሚረዳ ተናግረዋል። ተቋሙ የሚፈልገው ለውጥ ላይ እንዲደርስ ስልታዊ ኮሙዩኒኬሽን ከፍተኛ ሚና እንዳለው የተናገሩት አቶ ሞገስ አመራሩም  ሚናውን በመረዳት ማንኛውን ነገር ስልታዊ በሆነ አግባብ ኮሙዩኒኬት ማድረግ ይጠበቅበታል ብለዋል። በተቋሙ ውስጥ ውጤታማ የሆነ የኮሙዩኒኬሽን ሥራ ለማከናወን መረጃ በወቅቱ የሚገኝበት ሥርዓት ያለመጠናከሩ፣ ከሥራ ክፍሎች፣ ከሚዲያና ባለድርሻ አካላት ጋር  ወጥ ግንኙነት ያለመፈጠሩ፣ ሙያዊ ለሆኑ አንዳንድ ቃላት አቻ ትርጉም ለማግኘት አስቸጋሪ መሆኑ፣ የአመራሮች የሚዲያ አጠቃቀም ግንዛቤ ክፍተት መኖርና የመሳሰሉት ችግሮቹ  እንዳሉ አብራርተዋል። የተቋም የኮሙዩኒኬሽን ሥራ የአንድ ክፍል ብቻ ባለመሆኑ ችግሮቹን በመቅረፍ ተቋሙን ውጤታማ ለማድረግ ሁሉም የሥራ መሪ የስልታዊ ኮሙዩኒኬሽን ጽንሰ ሀሳብንና ለተቋም የሚኖረውን ሚና ተገንዝቦ በጋራና በቁርጠኝነት መስራት እንደሚኖርበት ዳይሬክተሩ አሳስበዋል። በዕለቱም ከተቋም ገፅታ ግንባታና ማስተዋወቅ፣ ከተቋሙ ሠራተኞች የማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀምና ተጠያቂነት ጋር በተያያዘ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ከተሳታፊዎች ቀርበዋው ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል። በውይይቱ ማጠቃለያ ላይ ሀሳብ የሰጡት የኮርፖሬት ገቨርናንስና ኮምፕሊያንስ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ዱጉማ ነዳ በበኩላቸው ተቋሙን ለማስተዋወቅና ገፅታውን ለመገንባት የተቋሙን ስያሜ እስከመቀየር ያሉ የመፍትሔ ሀሳቦች መቅረባቸውን አስታውቀዋል። ሁሉም አመራር የኮሙዩኒኬሽን ሥራ የተቋሙን ተልዕኮ ለማሳካት የሚኖረውን ሚና ተገንዝቦ መረጃ ከመስጠት ጀምሮ ክፍሉን በአግባቡ መጠቀም እንደሚገባ አሳስበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 23 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+9