ru
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Открыть в Telegram

📈 Аналитический обзор Telegram-канала EEP Communication

Канал EEP Communication (@eepcommuication) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 15 530 подписчиков, занимая 8 328 место в категории Технологии и приложения и 2 176 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 15 530 подписчиков.

Согласно последним данным от 06 июля, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 6, а за последние 24 часа — -3, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 27.84%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 16.05% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 4 323 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 2 492 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 10.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
EEP Communication

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 07 июля, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Технологии и приложения.

15 530
Подписчики
-324 часа
-97 дней
+630 день
Архив постов
vlcsnap-2021-01-28-10h17m30s0.png6.36 KB

20210126_164650.jpg1.58 KB

20210126_164643.jpg1.78 KB

20210126_164641.jpg2.21 KB

20210126_164636.jpg2.10 KB

20210126_164624.jpg1.88 KB

20210126_164618.jpg2.13 KB

ጣቢያው አገልግሎቱን በብቃት፣ በጥራትና በተገቢው መንገድ እየሠጠ ነው ………..///……….. የማስፋፈያ እና የአቅም ማሳደግ ሥራዎች የተሠሩለት የመቱ ባለ 230/66/33/15 ኪ.ቮ. ማከፋፈያ ጣቢያ ተገቢውን አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን የማከፋፈያ ጣቢያው ኃላፊ አቶ ሰለሞን ጎሳ ገለጹ፡፡ አቶ ሰለሞን እንደገለፁት በ1984 ዓ.ም. ከሶር ኃይል ማመንጫ በ66 ኪ.ቮ. መስመር ኃይል በመቀበል ለመቱ እና ለአካባቢው በ15 ኪ.ቮ. ኃይል በመስጠት በይፋ ሥራ የጀመረው ማከፋፈያ ጣቢያው እስከ 2002 ዓ.ም ድረስ አገልግሎት ሲሰጥ ቆይቷል፡፡ ይሁንና በ2002 ዓ.ም. ማከፋፈያ ጣቢያው በተደረገለት የማስፋፈያና የአቅም ማሣደግ ሥራ ኃይል የመቀበል አቅሙን ወደ 232 ኪ.ቮ ለማድረስ መቻሉን ኃላፊው ገልጸዋል፡፡ ከአቅም ማሳደግ ሥራው በኋላ ማከፋፈያ ጣቢያው አምስት ባለ 15 ኪ.ቮ እና ሦስት ባለ 33 ኪ.ቮ. ወጪ መስመሮች እንዲኖረው መደረጉን አንስተዋል፡፡ ከበደሌ ማከፋፈያ ጣቢያ በጥንድ ባለ 230 ኪ.ቮ መስመር የሚቀበለውን ኃይል ባሉት አምስት ባለ 15 ኪ.ቮ. እና ሁለት ባለ 33 ኪ.ቮ. ወጪ መስመሮች በኢሉባቡር ዞን የሚገኙትን 13 ወረዳዎችና ከተሞች እንዲሁም አንዱን ባለ 33 ኪ.ቮ ደግሞ በደቡብ ክልል ለሚገኘው የማሻ ወረዳ ኃይል ለመስጠት ማስቻሉን አስረድተዋል፡፡ ጣቢያው በ2008 ዓ.ም. በተደረገለት ተጨማሪ የማስፋፈያ ሥራ በጥንድ ባለ 230 ኪ.ቮ ወጪ መስመር ለጋምቤላ ክልል ኃይል እየሰጠ ይገኛል ፡፡ ከአዲስ አበባ በ525 ኪ.ሜትር ርቀት ላይ በኦሮሚያ ክልል ኢሉባቦር ዞን በመቱ ከተማ የሚገኘው የመቱ ባለ 230/66/33/15 ኪ.ቮ. ከፍተኛ ማከፋፈያ ጣቢያ አገልግሎቱን በብቃት፣ በጥራትና በተገቢው መንገድ እየሠጠ ይገኛል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 05 ቀን 2013 ዓ.ም

mm.jpg0.60 KB

m.jpg0.35 KB

20210115_145749.jpg3.44 MB

20210115_145617.jpg3.39 MB

20210115_095924.jpg3.19 MB

የሰኮሩ እና የጅማ 2 ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ የኃይል ስርጭት በማሳለጥ ደረጃ ጉልህ ሚና በመጫወት ላይ ናቸው ………..////…………… የሰኮሩ ባለ 400 ኪ.ቮ እና የጅማ 2 ባለ 230 ኪ.ቮ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያን የኃይል ስርጭት በማሳለጥ በኩል ጉልህ ሚና በመጫወት ላይ መሆናቸውን የጣቢያዎቹ ሥራ አስኪያጆች አስታውቀዋል፡፡ የሰኮሩ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ሥራ አስኪያጅ አቶ አንድነት ማሞ እንደተናገሩት የሰኮሩ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በሀገሪቱ ካሉ ግዙፍ ጣቢያዎች አንዱ መሆኑንና በአማካኝ 120 ሜጋ ዋት ኢነርጂ የመሸከምና ማስተላለፍ አቅም ያለው ነው፡፡ ጣቢያው ለወልቂጤ፣ ለጅማ፣ በደሌ፣ ሚዛን፣ መቱ፣ ጋምቤላ፣ ነቀምት እና በአቅራቢው ለሚገኙ አካባቢዎች የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ አውታሮችን በማንቀሳቀስ ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ በማበርከት ላይ እንደሚገኝ ስራ አስኪያጁ አስታውቀዋል፡፡ እንደ አቶ አንድነት ገለፃ ጣቢያው ሶስት ወጪ መስመሮች ያሉት ሲሆን ለጌዶ፣ ወልቂጤና ጂማ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች 230 ኪ.ቮ ኢነርጂ በማቅረብ ላይ ነው፡፡ በሌላ በኩል በ2007 ዓ.ም አገልግሎት መስጠት የጀመረው የጂማ ቁጥር 2 ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ለጂማ ዩኒቨርሲቲ፣ ለሰርቦ ፣ለጂማ ውሃ አገልግሎት እና ለቆጪ ከተማ የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ ከፍተኛ አስተዋጽኢ እያበረከተ መሆኑንን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አቶ ይልማ አበበ ገልፀዋል፡፡ አንድ ፓወር ትራንስፎርመርና ሁለት አውቶ ትራንስፎርመር ያሉት ይህ ጣቢያ ለአጋሮ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ 230 ኪ.ቮ፣ ለጂማ ቁጥር 1 እና ለአባ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ደግሞ 132 ኪ.ቮ በማቅረብ ላይ እንደሚገኝ ነው አቶ ይልማ የተናገሩት፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 02 ቀን 2013 ዓ.ም

11.jpg0.24 KB

ተቋሙ በጅማ ከተማ አዲስ ህንፃ ሊያስገነባ ነው ………./////………… በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የደቡብ ምዕራብ ሪጅን ሰብስቴሽንና ትራንስሚሽን ኦፕሬሽንና ጥገና ቢሮ በጅማ ከተማ አዲስ ባለ 8 ፎቅ ህንፃ ሊያስገነባ መሆኑን ገለጸ፡፡ የቢሮው ዳይሬክተር አቶ ደረጄ ገዛኽኝ እንደተናገሩት ህንፃው የሚገነባበት 2 ሺህ 500 ካሬ መሬት ቀደም ሲል የዲዝል ጄኔሬተር የሠራተኞች መኖሪያ የነበረ ነው፡፡ የግንባታው ቦታ የአፈር ጥናትና የዲዝይን ሥራዎች መጠናቀቁንና በቅርቡም ጨረታ በማውጣት ወደ ግንባታ ለመግባት የተለያዩ ሥራዎች እየተሠሩ ይገኛል ብለዋል፡፡ ለቅይጥ አገልግሎት ለማዋል ለታሰበው ህንፃ ግንባታ የሚሆን 98 ሚሊዮን ብር በጀት በተቋሙ እንደሚሸፈን ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል፡፡ እንደ አቶ ደረጃ ገለፃ ግንባታው ሲጠናቀቅ እስከ 5ኛ ፎቅ ድረስ ለተለያየ አገልግሎት መስጫነት በማከራየት የተቋሙን ገቢ ለማሳደግ ታቅዷል፡፡ ከ5ኛ ፎቅ በላይ ያለውን ደግሞ ሪጅኑን አሁን ካለበት የኪራይ ህንፃ በማውጣት ለተለያዩ የአስተዳደር እና የአገልግሎት ሥራዎች በመጠቀም የኪራይ ወጪን ለመቀነስ መታሰቡን አቶ ደረጄ አብራርተዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 01 ቀን 2013 ዓ.ም

photo content
+7

በትግራይ ክልል በተካሔደው የህግ ማስከበር ዘመቻ ከ240 ሚሊዬን ብር በላይ የሚገመት የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች ላይ ጉዳት ደርሷል ............/////........ በትግራይ ክልል በተካሔደው የህግ ማስከበር ዘመቻ ወቅት ከ240 ሚሊዬን ብር በላይ የሚገመት የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች ላይ ጉዳት መድረሱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ ፡፡ የተቋሙ የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮነን እንደገለፁት በህግ ማስከበር ዘመቻው ወቅት በርካታ መሠረተ ልማቶች ላይ ጉዳት ደርሷል፡፡ የሰሜን ሪጅን በተከዜ እና አሸጎዳ የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ውስጥ የሚገኙትን ሁለት ስዊችያርዶች ጨምሮ 17 የሚሆኑ የኃይል ማፋፈያ ጣቢያዎች እንዳሉት የጠቆሙት አቶ ሞገስ ከነዚሁ ውስጥ ሶስቱ ባለ 66 ኪሎ ቮልት፣ አምስቱ ባለ 132 ኪሎ ቮልት እንዲሁም የተቀሩት ሰባቱ ደግሞ ባለ 230 ኪሎ ቮልት መሆናቸውን አብራርተዋል፡፡ በማከፋፈያ ጣቢያዎቹና በኃይል ማስተላለፊያ መስመሮቹ ላይ የተለያየ መጠን ያላቸው ጉዳቶች በመድረሱ በክልሉ ለተወሰኑ ጊዜያት የኤሌክትሪክ ኃይል ተቋርጦ መቆየቱን አስታውሰዋል፡፡ በክልሉ የተለያየ አቅም ያላቸው 1 ሺህ 727 ኪሎ ሜትር ርዝመት የሚሸፍኑ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ይገኛሉ ያሉት ኃላፊው በህግ ማስከበር ዘመቻው ወቅት በዋናነት በኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች እና በኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች ላይ ጉዳት መድረሱን ጠቁመዋል፡፡ በሰባት የኃይል ማስተላለፊያ ተሸካሚ ምሰሶዎች ላይ ጉዳት መድረሱን እና በኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ ከፍተኛ የሆነ የመበጣጠስና የኢንሱሌተሮች መሰባበር አደጋዎች እንዳጋጠሙ ገልፀዋል፡፡ የጉዳት መጠኑም በገንዘብ ሲተመን 67 ነጥብ አምስት ሚሊዬን ብር እንደሆነ ነው መግለጫው ያመለከቱት፡፡ በወልቃይት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የሠራተኞች መኖሪያ ቤት፣ ቢሮዎች፣ የዕቃ ግምጃ ቤቶች እና የመለዋወጫ ዕቃዎች ላይ ጉዳት ደርሷል ያሉት አቶ ሞገስ ግምታቸው 15 ሚሊዬን ብር የሚደርስ 5 ተሸከርካሪዎችና የጫኗቸው የመለዋወጫ ዕቃዎች በጁንታው መዘረፋቸውን አንስተዋል፡፡ የተዘረፉት የመለዋወጫ ዕቃዎች በተጀመሩት የጥገና ሥራዎች ላይ አሉታዊ ጫና ከማሳደራቸውም ባሻገር ተቋሙን ለተጨማሪ ወጪ እንደዳረጉትም ነው የተናገሩት፡፡ ለመለዋወጫ እና ሌሎች ተጓዳኝ ዕቃዎች የወጣው ወጪም ከ 11 ሚሊዬን ብር እንደሆነ ነው ያስታወቁት፡፡ እንደ አቶ ሞገስ ገለፃ በኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ላይ የሚገኙና ኢትዮ-ቴሌኮም ከፍተኛ የድምፅ እና የዳታ አገልግሎት የሚሰጥባቸው የኦ.ፒ.ጂ. ደብሊው ፋይበር መስመሮች ላይ ጉዳት ደርሷል። በዚህም 178 ኪሎ ሜትር የሚደርስ የኦ.ፒ.ጂ. ደብሊው ፋይበር እንዲሁም 43 የሚሆኑ የኦ.ፒ.ጂ. ደብሊው ፋይበር ሳጥኖች ላይ ጉዳት መድረሱን ኃላፊው ገልፀዋል፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘ በኃይል መሠረተ ልማቶቹ ላይ ጉዳት በመድረሱ ምክንያት ተቋሙ ኤሌክትሪክ በማቅረብ ሊያገኝ ይችል የነበረውን 146 ነጥብ 2 ሚሊዬን ብር የሚገመት ገንዘብ ሊያጣ መቻሉን ተናግረዋል፡፡ በክልሉ ከኃይል ሽያጭ ይገኝ የነበረና የባከነ 245 ነጥብ 5 ሚሊዬን ኪሎ ዋት ሰዓት ኢነርጂ በገንዘብ ሲሰላ ከ140 ሚሊየን ብር በላይ ይሆናል ብለዋል፡፡ አቶ ሞገስ እንዳሉት በክልሉ በተካሔደው የህግ ማስከበር ዘመቻ ተቋሙ በአጠቃላይ ከ240 ሚሊዬን ብር በላይ የሚገመት ኪሳራ ገጥሞታል። በሪጅኑ ካለው 1727 ኪሎ ሜትር የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ውስጥ 2 መቶ ኪሎ ሜትር የሚሆነው ብቻ የፍተሻና ጥገና ስራ እንደሚቀረው እንዲሁም የሁመራ እና መሰቦ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች የፍተሻና ጥገና ስራ ተጠናቆ ኃይል ለመስጠት ዝግጁ መሆኑ በመግለጫው ተጠቅሷል። የወልቃይት ማከፋፈያ ጣቢያ ግን መለዋወጫ ዕቃ ስለሚያስፈልገው ከውጭ ለማስገባት በሂደት ላይ ነው። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 30 ቀን 2013 ዓ.ም

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ አፈጻጸም 78 ነጥብ 3 በመቶ ደረሰ ………………..///…………. ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ አፈጻጸም 78 ነጥብ 3 መድረሱን የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚ
ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ አፈጻጸም 78 ነጥብ 3 በመቶ ደረሰ ………………..///…………. ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ አፈጻጸም 78 ነጥብ 3 መድረሱን የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ ገለፁ። ሚኒስትሩ ባለፉት ስድስት ወራት የተከናወኑትን ተግባራትና የህዳሴ ግድብን የግንባታ ሂደት በተመለከተ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ ዶክተር ስለሺ በመግለጫቸው እንዳመለከቱት የግድቡ ግንባታ የሲቪል ስራዎች አፈጻጸም 91 በመቶ ደርሷል። አጠቃላይ የግድቡ ግንባታ አፈጻጸም ደግሞ 78 ነጥብ 3 በመቶ መድረሱን አመልክተዋል። በቀጣይ ወራት የግድቡን ሁለተኛ ዙር የውሃ ሙሌት ለማሳካት እንደሚሰራም ጠቁመዋል። ግድቡ ለተፋሰሱ አገሮች ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ እንዳለው የተናገሩት ኢንጂነር ስለሺ፤ “የግድቡ ግንባታ ሰኔ ወር ላይ ከነበረበት አፈጻጸም የ4 ነጥብ 05 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል” ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 28 ቀን 2013 ዓ.ም

photo content