ru
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Открыть в Telegram

📈 Аналитический обзор Telegram-канала EEP Communication

Канал EEP Communication (@eepcommuication) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 15 548 подписчиков, занимая 8 340 место в категории Технологии и приложения и 2 158 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 15 548 подписчиков.

Согласно последним данным от 26 июня, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 27, а за последние 24 часа — -7, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 26.05%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 16.01% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 4 053 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 2 491 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 8.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
EEP Communication

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 27 июня, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Технологии и приложения.

15 548
Подписчики
-724 часа
+147 дней
+2730 день
Архив постов
ተቋሙ በ2016 በጀት ዓመት ከ10 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል ፈጥሯል ……..///……. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በመላ ሀገሪቱ እያከናወናቸው በሚገኙ የኃይል ማመንጫ፣ ማስተላለፊያ መስመር፣ ማከፋፈያ ጣቢያ እና በሌሎች ፕሮጀክቶች 10 ሺህ 548 ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠሩን በተቋሙ የኮርፖሬት ፕላኒንግ ዘርፍ አስታወቀ፡፡ የዘርፉ ሥራ አስፈጻሚ አቶ አንዱአለም ሲዓ እንዳስታወቁት ተቋሙ የኃይል መሰረተ ልማት ፕሮጀክቶችን ለማስፋፋት እያከናወነ ካለው ሥራ ጎን ለጎን ለዜጎች የሥራ ዕድል በመፍጠር ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ይገኛል፡፡ ተቋሙ የኃይል መሰረት ልማትን ከማስፋፋት በተጨማሪ በሥራ ዕድል ፈጠራ ላይ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ የገለጹት ሥራ አስፈጻሚው በተጠናቀቀው በጀት ዓመትም ለ13 ሺህ 197 ዜጎች የሥራ ዕድሎችን ለመፍጠር ታቅዶ ሲሰራ ነበር ብለዋል፡፡ በበጀት ዓመቱ በመላ ሀገሪቱ ሲከናወኑ በነበሩ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ለ1 ሺህ 710 ሰዎች በቋሚነት፣ለ 8 ሺህ 389 ሰዎች በጊዜያዊነት እንዲሁም ለ 449 ሰዎች በኮንትራት የሥራ ዕድል ሲፈጠር ከእነዚህ መካከል 1 ሺህ አርባ የሚሆኑት ሴቶች መሆናቸውንም አቶ አንዱአለም ጠቅሰዋል፡፡ ይህም ተቋሙ በሀገሪቱ ያለውን የሥራ አጥ ቁጥር በመቀነስ በኩል የራሱን አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ያሳያል ብለዋል፡፡ ተቋሙ በበጀት ዓመቱ ለማከናወን ያቀዳቸውን ሥራዎችን በአግባቡ ለመፈጸም የፋይናንስ እጥረትና የጸጥታ ችግሮች እንቅፋት እንደነበሩ የተናገሩት አቶ አንዱአለም ይህም በሥራ ዕድል ፈጠራው ላይ የራሱ የሆነ ተፅዕኖ ስለማሳደሩ ተናግረዋል፡፡ በተያዘው የበጀት ዓመት ይጀመራሉ ተብለው የታቀዱ አዳዲስ ፕሮጀክቶችን ጨምሮ በግንባታ ላይ ባሉት ነባር ፕሮጀክቶች 15 ሺህ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል ለመፍጠር መታቀዱንም ሥራ አስፈጻሚው ጠቁመዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጳጉሜን 5 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

የኃይል መሰረተ ልማት ስርቆትን ለመከላከል ከብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ጋር እየተሰራ ነው .......///...... በኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች ላይ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተበራከተ የመጣውን ስርቆት ለመከላከል ከብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ጋር በቅንጅት እየሰራ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ። በተቋሙ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ክትትልና ቁጥጥር ቢሮ ተወካይ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዋለ ታምሬ እንዳስታወቁት በኃይል መሠረተ ልማቶች ላይ የሚፈፀሙ ስርቆቶችን ለመከልከል ተቋሙ የተለያዩ ሥራዎችን ሲያከናውን ቆይቷል። ይሁንና ስርቆቱ እየተስፋፋ በመምጣቱና በተቋሙ አቅም ብቻ ውጤት ማምጣት ባለመቻሉ በአሁኑ ወቅት ከብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ጋር በቅንጅት መስራት የሚያስችል አሰራር መዘርጋቱን ጠቅሰዋል፡፡ ቅንጅታዊ አሰራሩ ስርቆትን ቀድሞ ለመከላከል፣ ስርቆት የሚፈጸሙ አካላትን በመከታተል በቁጥጥር ስር ለማዋልና በተጠርጣሪዎች ላይ በህጉ መሰረት አስፈላጊውን እርምጃ ለመውሰድ የሚያግዝ መሆኑን ሥራ አስኪያጁ አመልክተዋል፡፡ አገልግሎቱ ስርቆቱ የሚያደርሰውን የጉዳት መጠን በመገንዘብ በአሁኑ ወቅት ኃላፊነት ወስዶ እየሰራ ይገኛል ያሉት አቶ ዋለ በቅርቡም ችግሩ በሚፈታበት ጉዳይ ላይ ከክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች ጋር ውይይት ማካሄዱን አስታውሰዋል፡፡ በውይይቱ ላይ በተደረሰው መግባባት መሰረት ሁሉም ክልል የየራሱን ኃላፊነት ወስዶ ወደ ሥራ መግባቱንም ጠቁመዋል። በስርቆት ምክንያት የኃይል መቆራረጥ እየተበራከተ በመምጣቱ ችግሩን ለመቅረፍ ተቋሙ መሠረተ ልማቱን የሚከታተልና የሚቆጣጠር የሥራ ክፍል በማዋቀር ላይ እንደሚገኝም ተናግረዋል፡፡ የሚቋቋመው የሥራ ክፍል ትኩረት የሚሹ መስመሮችን የመለየት፣ መረጃዎችን በማደራጀት ለአገልግሎቱ ሪፖርት የማድረግና የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮችን የማዘጋጀት ሥራዎችን እንደሚያከናውን አስረድተዋል። እንደ አቶ ዋለ ገለፃ የሥራ ክፍሉ በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች መዋቅር በመዘርጋት በየደረጃው ከሚገኙ የክልል መስተዳደር እና የጸጥታ አካላት እንዲሁም ከተቋሙ ሪጅኖች ጋር በቅንጅት ይሰራል፡፡ የስርቆት መከላከል ሥራው በሁሉም የሀገሪቱ ክፍል በሚገኙ የኃይል መሰረተ ልማቶች ላይ የሚከናወን ቢሆንም የውጪ ኃይል ትስስር እየተከናወነ ያለባቸው መስመሮችን ጨምሮ 21 ትኩረት የሚሹ መስመሮች ተለይተው ወደ ሥራ ተገብቷል፡፡ ሥራ አስኪያጁ እንዳሉት ከአገልግሎቱ ጋር መስራት ከተጀመረ ወዲህ በነሐሴ ወር ብቻ በህብረተሰቡ ጥቆማ በአዲስ አበባ የረር፣ በኦሮሚያ ባቱ እና በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ቡኢ- ቡታጂራ አካባቢዎች በስርቆት የተጠረጠሩ ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር ማዋል ተችሏል፡፡ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶችን በመጠበቅ ስርቆት የሚፈጽሙ ተጠርጣሪዎችን ለጸጥታ አካላት እንዲጠቁም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ በኃይል መሰረተ ልማቶች ላይ በተፈጸመ ስርቆት በ2015 በጀት ዓመት ከ732 ሚሊዮን ብር በላይ እንዲሁም በ2016 በጀት ዓመት 817 ሚሊዮን ብር ኪሳራ መደርሱ ከዚህ በፊት መዘገባችን ይታወሳል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጳጉሜን 4 ቀን 2016 ዓ.ም

#የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል

በኃይል ማስተላለፊያ ምሰሶ ተሸካሚ ብረቶች ላይ የስርቆት ወንጀል ሲፈፅም የነበረ ግለሰብ እጅ ከፈንጅ ተያዘ ………./////……… በከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ ምሰሶ ተሸካሚ ብረቶች ላይ የስርቆት ወንጀል ሲፈፅም የነበረ ግለሰብ እጅ ከፈንጅ መያዙን የምስራቅ አንድ ሪጅን የኃይል ማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ አስታወቀ። በመምሪያው የኃይል ማስተላለፊያዎች የጥገና ክፍል ተወካይ ሥራ አስኪያጅ አቶ አየለ አዱላ እንደገለፁት ተጠርጣሪው 28 የኃይል ማስተላለፊያ ምሰሶ ተሸካሚ ብረቶችን ሲሰርቅ በአካባቢው የፀጥታ አካላት እጅ ከፍንጅ ተይዟል። የስርቆት ወንጀሉ በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር መልካ ቀበሌ ልዩ ስሙ ጎላ ደን በሚባል አካባቢ በሁርሶ- አዲጋላ- ጅቡቲ የባቡር እና የኤሌክትሪክ እንዲሁም በሁርሶ- ድሬዳዋ ቁጥር-3 ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ ምሰሶ ተሸካሚ ብረቶች ላይ መፈፀሙን ተናግረዋል። ሪጅኑ በሦስቱ የከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ ባደረገው የፍተሻ ሥራ 502 የምሰሶ አካላት እና 62 የምሰሶ መወጣጫ መከላከያ ብረቶች ላይ ስርቆት መፈፀሙን አቶ አየለ ጠቁመዋል። እንደ ተወካይ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ ከሁርሶ- አዲጋላ- ጅቡቲ ባለ 230 ኪሎ ቮልት በሚሄደው መስመር በሚገኙ 10 የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች ላይ ብቻ 450 ብረቶች ለስርቆት መዳረጋቸውን አብራርተዋል። ሪጅኑ በሚያስተዳድራቸው የኃይል ማስተላለፊያ መስመር የምሰሶ አካላት ላይ በየጊዜው ተደጋጋሚ የስርቆት ወንጀሎች እንደሚፈፀምባቸውም ነው የጠቆሙት። መሰረተ ልማቶቹን ከስርቆት ለመታደግ በየደረጃው ከሚገኙ የዞን፣ ወረዳና የቀበሌ፣ የፀጥታና የፍትህ አካላት እንዲሁም የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር ተከታታይና ቀጣይነት ያለው የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎች መሰራት እንዳለባቸው ተናግረዋል። የመልካ ጀብዱ ፖሊስ ጣቢያ የወንጀል ምርመራ ቡድን ኃላፊ ኢንስፔክተር ዓለሙ በየነ እንደገለፁት ኑሬ ጀማል የተባለ ተጠርጣሪ በኃይል ማስተላለፊያ ምሰሶዎች ላይ በመውጣት ብረቶቹን ሲፈታ በአካባቢው በሚገኙ የፀጥታ አካላት እጅ ከፈንጅ ተይዟል። በኃይል ምሰሶ ተሸካሚ ብረቶች ላይ ስርቆት ሲፈፅሙ ከነበሩት መካከል አንዱ ማምለጡን የገለፁት ኢንስፔክተሩ በአሁኑ ወቅት በየአካባቢው በሚገኙ የፀጥታ አካላት ጥብቅ ክትትል እየተደረገበት እንደሚገኝም ጠቅሰዋል። የምርመራ ቡድኑ ወንጀሉን ሲፈፅም በተያዘው ተጠርጣሪ ላይ የሰነድና የሰው ምስክሮችን በማስረጃነት እያደራጀ እንደሚገኝም ጠቁመዋል። በአካባቢው በከፍተኛ ወጪ ተገንብተው አገልግሎት እየሰጡ በሚገኙ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶች ላይ የስርቆት ወንጀል በሚፈፅሙ አካላት ላይ የሚወሰዱ እርምጃዎች ጠንካራ መሆናቸውን የገለፁት ኢንስፔክተር ዓለሙ ወንጀሎቹን ለመከላከል ሁሉም ዜጋ ኃላፊነቱን መወጣት እንዳለበትም አሳስበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጳጉሜን 4 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+6

photo content
+1

ትናንት ማምሻውን በአዲስ ዌስት ሜክሲኮ ማከፋፈያ ጣቢያ አጋጥሞ የነበረውን የኃይል መቋረጥ ለማስተካከል ከለሊቱ 8:00 ሰዓት ጀምሮ የተደረገው ጥገና በምስል "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮ
+9
ትናንት ማምሻውን በአዲስ ዌስት ሜክሲኮ ማከፋፈያ ጣቢያ አጋጥሞ የነበረውን የኃይል መቋረጥ ለማስተካከል ከለሊቱ 8:00 ሰዓት ጀምሮ የተደረገው ጥገና በምስል "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጳጉሜን 3 ቀን 2016 ዓ.ም

ማምሻውን አጋጥሞ የነበረው የኃይል መቋረጥ ተስተካክሏል .........///......... በከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ ማምሻውን አጋጥሞ የነበረው ብልሽት በጊዜያዊነት ተስተካክሎ ከአዲስ
ማምሻውን አጋጥሞ የነበረው የኃይል መቋረጥ ተስተካክሏል .........///......... በከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ ማምሻውን አጋጥሞ የነበረው ብልሽት በጊዜያዊነት ተስተካክሎ ከአዲስ ዌስት ሜክሲኮ ማከፋፈያ ጣቢያ ኃይል ሲያገኙ የነበሩ አካባቢዎች ኃይል መልሰው አግኝተዋል። በመስመሩ ብልሽት ምክንያት ከቀኑ 9:10 ሰዓት ጀምሮ እስከ ምሽት 1:40 ሰዓት ድረስ በሜክሲኮ፣ ለገሀር ፣ መስቀል አደባባይ፣ ቦሌ ደንበል፣ ልደታ፣ ብሔራዊ፣ ሳር ቤት እና አካባቢዎቻቸው ተቋርጦ የነበረው ኤሌክትሪክ አገልግሎት ተመልሷል። ችግሩን በጊዜያዊ መፍትሔ ለመፍታት የተሞከረ በመሆኑ ለሊት ከ6:00 ሰዓት ጀምሮ ለጥገና ሥራ ኃይል ሊቋረጥ የሚችል በመሆኑ ደንበኞች ይህን ተረድተው በትዕግስት እንዲጠብቁ እናሳስባለን። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጳጉሜን 2 ቀን 2016 ዓ.ም

በስርቆት ምክንያት የተቋረጠው የአሶሳ የኃይል አቅርቦት ተመልሷል ………////………. ከመንዲ አሶሳ በተዘረጋው ባለ 132 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ በተደጋጋሚ በተፈፀመ ስርቆት ምክንያት በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ለሳምንታት ተቋርጦ የቆየው የኃይል አቅርቦት ተመልሳል፡፡ በብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል የሪል ታይም ሥራ አስኪያጅ አቶ ጉልላት እንግዳ እንደገለፁት ከመስመሩ ኃይል ሲያገኙ የነበሩት የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መዲና አሶሳን ጨምሮ ሌሎች የክልሉ ከተማዎችና ወረዳዎች እንዲሁም በኦሮሚያ ክልል የመንዲ ከትናንት እኩለ ቀን ጀምሮ ኃይል አግኝተዋል። የኤሌክትሪክ መሰረተልማት ስርቆቱ በክልሉ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ ማሳደሩን ያስታወሱት አቶ ጉልላት በየደረጃው ያሉ የመስተዳድር አካላት እና ህብረተሰቡ መሰረተ ልማቱን ከስርቆትና ከጉዳት እንዲጠብቅ ጥሪ አቅርበዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጳጉሜን 2 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

ከአላማጣ ባህር ዳር በተዘረጋው መስመር ላይ በደረሰ ጉዳት በአካባቢው ኃይል ተቋርጧል ………///………. ከአላማጣ ባህር ዳር በተዘረጋው መስመር ላይ በደቡብ ጎንደር ዞን ጉና ወረዳ እርጋ ቀበሌ ልዩ ስሙ ክምር ድንጋይ መግቢያ አካባቢ በደረሰ ጉዳት በአካባቢው ኃይል መቋረጡን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰሜን ምዕራብ ሪጅን ማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽም መምሪያ አስታወቀ፡፡ የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ውበት አቤ እንደገለፁት በደረሰው ጉዳት የተነሳ በደብረታቦርና ንፋስ መውጫ በእስቴና አንዳቤት እንዲሁም በጋሸና አካባቢ ኃይል ተቋርጧል፡፡ የመስመሩ መቋረጥ ከስርቆት ጋር የተያያዘ መሆን አለመሆኑን ለማረጋገጥ የፍተሻ እና የጥገና ሥራ እንደሚሰራ ዳይሬክተሩ ተናግረዋል፡፡ በብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል የሪል ታይም ኦፕሬሽን ሥራ አስኪያጅ አቶ ጉልላት እግዳ በበኩላቸው የመስመሮች በተለያየ ምክንያት መቋረጥ ሲስተሙ ከመጠን በላይ ቮልቴጅ እንዲኖረው ሊያስገድድ እና ለኃይል መቆራረጥ ምክንያት ሊሆን አንደሚችል ገልፀዋል፡፡ ቀደም ሲል የተከዜ የውሃ ኃይል ማመንጫ ግድብ በክረምቱ ዝናብ የተነሳ የያዘውን ውሃ ለማስተንፈስ ኃይል ማምረት በማቆሙና አሁን ደግሞ የአላማጣ ኮምቦልቻ መስመር በመቋረጡ ከደብረብርሃን ጀምሮ ኮምቦልቻ፣ አላማጣ፣ መቀሌና ሌሎች የትግራይ ከተሞች የሲስተም አለመረጋጋት ስለሚያጋጥም የኃይል መቆራረጥ ሊያጋጥም እንደሚችል ጠቅሰዋል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ የክረምቱ ዝናብ ያስከተለውን የውሃ ሙላት ለማስተንፈስ በሚለቀቀው ውሃ የተነሳ በጊዜያዊነት አገልግሎት አቋርጦ የነበረውን የተከዜ የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ለአዲስ ዓመት መልሶ ሥራ ለማስጀመር የሚያስችሉ ሥራዎች መጀመራቸውን የኃይል ማመንጫዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ አስታውቋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጳጉሜን 2 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የሁሉም ኢትዮጵያውያን አሻራ ያረፈበት የትውልዱ የቃልኪዳን ሐውልት እና የመሻገር ትዕምርት ነው ……..///…… የመሻገር ቀን "የመሻገር ጥሪቶች የአዲስ ብርሃን ወረቶች" በሚል መሪ ሀሳብ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ እና በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ እና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ በተገኙበት በሳይንስ ሙዚየም ተከብሯል፡፡ በዕለቱ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስቴር ተመስገን ጥሩነህ የሁሉም ኢትዮጵያዊያን አሻራ ያረፈበትና የትውልዱ የቃልኪዳን ሃውልት የሆነው ታላቁ የህዳሴ ግድብ ከለውጥ በፊት በገጠመው የአሰራርና የአመራር ውስንነት ምክንያት በሚፈለገው ልክ እየሄደ አልነበረም፡፡ የለውጡ መንግስት በወሰደው ብልህና ቆራጥ የአመራር ውሳኔ ግድቡ ኃይል ወደ ማመንጨት በማሸጋገር የሉዓላዊነታችን መገለጫና የመሻገር ትዕምርት አንዲሆን ተደርጓል ነው ያሉት። እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ያሉ የታዳሽ ኃይል ፕሮጀክቶችን እንዳንሰራ ጫናዎች ነበሩ ያሉት ክቡር ምክትል ጠቅላይ ሚኒስቴሩ ኢትዮጵያ ወደ ብልጽግና ማማ የሚያሻግራትን የራሷን የተፈጥሮ ሀብቶች መጠቀሟን አጠናክራ ትቀጥላለች ብለዋል፡፡ በዕለቱ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልን ጨምሮ በታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ላይ በገንዘብ፣ በጉልበት፣ በእውቀት ለተሳተፉ አካላት በተወካዮቻቸው አማካኝነት  ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዕውቅና ተሠጥቷቸዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጳጉሜን 1 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+8

የሥራ ቅጥር ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከላይ ለተዘረዘሩት ክፍት የሥራ መደቦች ሥራ ፈላጊዎችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም ከላይ የተዘረዘሩ መስፈርቶች የምታሟሉ አመልካቾች ከ
የሥራ ቅጥር ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከላይ ለተዘረዘሩት ክፍት የሥራ መደቦች ሥራ ፈላጊዎችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም ከላይ የተዘረዘሩ መስፈርቶች የምታሟሉ አመልካቾች ከታች በተገለፁት አማራጭ ሊንኮች በመጠቀም የተዘጋጀው ቅጽ የሚጠይቀውን መረጃዎች በሙሉ በትክክል በኦንላይን ሞልቶ በመላክ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡ https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSeEVEqNCJp4lnQDmXcj0cXlAe9aeIlkxP4YDD7e7CtKD_pI0g/viewform https://forms.gle/9dUZ3dyPPY7rHtkT8 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጳጉሜ 1 2016 ዓ.ም

የመሻገር ቀንን አስመልክቶ ተቋማችን በታላቁ የህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት ላይ ላከነወነው ሥራ ዕውቅና ተብርክቶለታል። ተቋሙ ለተሰጠው እውቅና መላው የተቋሙ ሠራተኞችና በግድቡ ግንባታ ሥራ ላይ ለተሳተፋችሁ
የመሻገር ቀንን አስመልክቶ ተቋማችን በታላቁ የህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት ላይ ላከነወነው ሥራ ዕውቅና ተብርክቶለታል። ተቋሙ ለተሰጠው እውቅና መላው የተቋሙ ሠራተኞችና በግድቡ ግንባታ ሥራ ላይ ለተሳተፋችሁ አካላት እንኳን ደስ አላችሁ!!! "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጳጉሜን 1 ቀን 2016 ዓ.ም

ተቋሙ በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት ላይ እያከናወነ ላለው ሥራ  ዕውቅና ተሰጠው ........///........ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት እና በማስተላለፊያ መስመሩ ግንባታ ሥራ ላይ እያከናወነ ላለው ሥራ በመሻገር ቀን በዓል ላይ ዕውቅና ተሰጥቶታል። ዕውቅናው ተቋሙ ፕሮጀክቱን ከነበረበት ችግር አላቆ ኃይል ለማምረት እንዲበቃና አሁን ለደረበት ደረጃ እንዲደርስ ለማድረግ ባከናወነው ሥራ ፕሮጀክቱን የማሻገር ማሳያ በማድረጉ የተበረከተ ነው። የዕውቅና ዋንጫውን ከኢፌዲሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ እጅ የተረከቡት የተቋሙ የኢንጂነሪንግ ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚና የዋና ሥራ አስፈፃሚ ተወካይ አቶ ውድነህ የማነ ናቸው። ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተጨማሪ በግድቡ ግንባታ ዙሪያ የተለያየ አስተዋፅዖ ላበረከቱ ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ በኢፌዴሪ ፌደሬሽን ም/ቤት በኩል፣ ለፀጥታ አካላት፣ ለፋይናንስ፣ ለሚዲያና ለሃይማኖት ተቋማት፣ ለዳያስፖራ አባላትና ለሌሎችም ዕውቅና ተሰጥቷቸዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጳጉሜን 1 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+7

የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ኃይል ማመንጫ ግድብ የመሻገር ዘመን ማብሰሪያ ነው፤ ……//…… ዛሬ ጳጉሜን 1 የመሻገር ቀን "የመሻገር ጥሪቶች የአዲስ ብርሃን ወረቶች" በሚል መሪ ኃሳብ በመላ አገሪቱ እየተከበረ ይገኛል፡፡ እለቱን በማስመልከት ከኢትዮጵያ ዜና አገልግሎታ ጋር ቆይታ ያደረጉት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ኢትዮጵያ የተለያዩ ጫናዎችን ተቋቁማ ለስኬት ያበቃችው የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ኃይል ማመንጫ ግድብ የመሻገር ዘመን ማብሰሪያ መሆኑን ገልጸዋል። ባለፉት የለውጥ ዓመታት በተወሰደ ፈጣን የማሻሻያ ርምጃ የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ኃይል ማመንጫ ግድብ ወደ ማጠናቀቂያ ምዕራፍ ላይ መድረሱን የተናገሩት ዋና ሥራ አስፈጻሚው አሁን ላይ ግድቡ ከአንድ ሺ ሜጋ ዋት በላይ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት ጀምሯል ብለዋል። ከለውጡ በፊት ግድቡ በውድቀት አፋፍ ላይ እንደነበር ገልጸው በግድቡ ላይ የተሰራው የማሻሻያ ሥራ እንደ ሀገር ፈተናዎችን ተቋቁሞ ወደ ስኬት ማማ መውጣት እንደሚቻል ያሳየ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የግድቡ ግንባታ ሲጀመር ከተለያዩ አካላት ከፍተኛ ጫና እንደነበረ ያስታወሱት ኢንጅነር አሸብር የሕዳሴ ግድብ ኢትዮጵያውያን ፈተናዎችን በጋራ በማሰለፍ ወደ ብልፅግና ማማ የወጡበት የታሪክ እጥፋት መሆኑንም ጠቁመዋል። ኢንጂነር አሸብር የሕዳሴው ግድብ ግንባታ የኢትዮጵያ ሕዝብ ገንዘቡን እውቀቱንና ጉልበቱን ያፈሰሰበት አንጡራ ኃብት በመሆኑ የግድቡ ስኬት በሌሎች አገራዊ ፕሮጀክቶች ላይ መድገም እንደሚገባ ተናግረዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጳጉሜ 1 2016 ዓ.ም