ru
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Открыть в Telegram

📈 Аналитический обзор Telegram-канала EEP Communication

Канал EEP Communication (@eepcommuication) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 15 544 подписчиков, занимая 8 333 место в категории Технологии и приложения и 2 158 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 15 544 подписчиков.

Согласно последним данным от 27 июня, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 10, а за последние 24 часа — -16, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 25.06%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 16.33% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 3 895 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 2 539 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 7.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
EEP Communication

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 28 июня, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Технологии и приложения.

15 544
Подписчики
-1624 часа
-97 дней
+1030 день
Архив постов
photo content
+4

በኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች የተከናወኑ የጥገና ሥራዎች አስተማማኝ ኃይል ለማምረት አስችለዋል …….//…… በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የተከናወኑ የጥገና ሥራዎች የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች አስተማማኝ የኃይል ምርት እንዲያመርቱ ማስቻሉን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኃይል ማመንጫዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ አስታወቀ፡፡ በዘርፉ የቴክኒካል ድጋፍ እና አገልግሎት መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ዘላለም ባይለየኝ እንዳስታወቁት በ2016 በጀት ዓመት በኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች የኃይል ምርቱን አስተማማኝ የሚያደርጉ የቅድመ መከላከል፣ የፍተሻ እና የትንበያ ጥገና ሥራዎች ተከናውነዋል፡፡ በዚህም የኃይል ማመንጫዎች ጣቢያዎችን ዝግጁነት አፈፃፀም 94 በመቶ ማሳካት ተችሏል ብለዋል፡፡ በበጀት ዓመቱ በግልገል ጊቤ 2 እና 3፣ መልካ ዋከና፣ ጣና በለስ፣ ፊንጫ፣ ተከዜ፣ ረጲ፣ ቆቃ እንዲሁም አዳማ 1 እና አሸጎዳ ንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎችን ጨምሮ በሁሉም የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ዓመታዊ የጥገና ሥራዎች እና የፍተሻ ሥራዎች በተያዘላቸው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት መከናወናቸውን ጠቁመዋል፡፡ እነዚህ የጥገና ሥራዎች መከናወናቸው የማያቋርጥ እና አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማምረት ማስቻሉንና በዚህም በ2015 በጀት ዓመት ከነበረው የኃይል ምርት በ16 ነጥብ 3 በመቶ ዕድገት ማሳየቱን ዳይሬክተሩ አብራርተዋል፡፡ በበጀት ዓመቱ ለጣቢያዎቹ የጥገና ሥራ የሚያስፈልጉ የመለዋወጫ ዕቃዎች ከተለያዩ ድርጅቶች ጋር በተደረገ ስምምነት መሰረት እና በተለያዩ መንገዶች መቅረቡንም አስታውሰዋል፡፡ እንደ አቶ ዘላለም ገለጻ በበጀት ዓመቱ ከጥገና ሥራዎች በተጨማሪ የጣቢያዎቹን የኦፕሬሽንና የጥገና ሥራ ለማዘመን የሚያስችሉ የተለያዩ ተግባራት ተከናውነዋል፡፡            በዚህም የበለስ፣ ግልገል ጊቤ 1 እና 2 ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎችን ስካዳ ለማሻሻል እና ለማዘመን አንድሪዝ ሃይድሮ እና ቮይት ሃይድሮ ከተባሉ ኩባንያዎች ጋር ውል ተፈርሞ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። አቶ ዘላለም አክለውም በጊቢ 3 ኃይል ማመንጫ ጣቢያ የመረጃ አያያዙን ለማዘመንና የእያንዳንዱን ማሽን ታሪክ በተገቢ ሁኔታ ለማደራጀት እንዲሁም በሥራ ቦታው ላይ የማሽኑን ማኑዋል፤ የጥገና ታሪክ እና ከዚህ በፊት ያጋጠሙ ችግሮችን በሳይት ለሁሉም ቴክኒካል ሠራተኛ ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችል ሥርዓት መተግበሩንም ተናግረዋል፡፡ በተጠናቀቀው የ2016 በጀት ዓመት 20 ሺ 596 ነጥብ 38 ጌጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ማምረት ተችሏል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሀምሌ 27 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

በጣቢያው ሠራተኞች የተለያዩ የጥገና ሥራዎች ተከናውነዋል .......//....... በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የግድቡን ደህንነት ለመጠበቅ እና አስተማማኝ የኃይል ምርት ለማቅረብ ያስቻሉ የጥገና ሥራዎች በጣቢያው ሠራተኞች መከናወናቸውን የግልገል ጊቤ 1 የውኃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ገለጸ። በጣቢያው የጥገና ክፍል ኃላፊ አቶ ታምሩ ለገሰ እንደገለጹት በበጀት ዓመቱ በጣቢያው የጥገና ክፍል ሠራተኞች ሳምንታዊ እና ወርሃዊ የቅድመ መከላከል፣ የፍተሻ፣ የትንበያና የሁኔታ አመላካች ጥገና ሥራዎች ተከናውነዋል። የጥገና ሥራዎቹ በተርባይኖች፣ በግድቡ፣ በስዊችያርድ 15 ኪሎ ቮልት መስመር፣ በጣቢያው የተፋሰሰ ስርዓት እና በ15 ኪሎ ቮልት ስዊችጊር ፓኔል ላይ መከናወናቸውን ጠቁመዋል። በጣቢያው ሶስቱም ዩኒቶች ላይ ዓመታዊ የፍተሻ እና ጥገና ስራዎች እንዲሁም የተለያዩ የማሻሻያ ስራዎች ተከናውነዋል። እንደ አቶ ታምሩ ገለፃ ስርቆት ተፈጽሞበት የነበረውን የግድቡ የውሃ መቆጣጠሪያ እና የኮሙዩኒኬሽን ኬብል እንዲሁም ከግድብ ስዊችያርድ የሚሄደው 15 ኪሎ ቮልት መስመር እና የወደቁ 5 ታወሮችን በከፍተኛ ርብርብ በመጠገን ወደ አገልግሎት ማስገባት ተችሏል ብለዋል። የጥገና ሥራዎች በጣቢያው የጥገና ሠራተኞች አቅም መከናወኑ የተናገሩት አቶ ታምራት ይህም ተቋሙን ከከፍተኛ ወጭ ከማዳኑም በላይ ሠራተኞች አዳዲስ ልምድ እንዲያገኙ እድል የፈጠረ መሆኑን ተናግረዋል። በበጀት ዓመቱ የተከናወኑት የጥገና ሥራዎች የኃይል ማመንጫ ግድቡን ደህንነት በመጠበቅ እና የኦፕሬሽን ሥራዎችን በማሳለጥ የኃይል ምርቱ አስተማማኝ እንዲሆን ማድረጉን አብራርተዋል። እንደ አቶ ታምሩ ገለጻ በዝናብ ወቅት ከፍተኛ የኃይል ጭነት በማስተናገድ ግድቡ ሞልቶ እንዳይፈስና በበጋ ወቅት የግድቡ ውሃ እንዳያልቅ የኃይል ጭነት በማመጣጠን የግድቡን ውሃ በአግባቡ መጠቀም የሚስችሉ ተግባራት በመከናወን ላይ ናቸው፡፡ 184 ሜጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም ያለው የግልገል ጊቤ 1 የውኃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ከ1996 ዓ.ም ጀምሮ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሀምሌ 26 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+9

photo content
+1

የሥራ ቅጥር ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መሰረታዊ ሠራተኛ ማህበር የሰራተኞች ክበብ ከዚህ በታች ለተዘረዘሩት ክፍት የሥራ መደቦች ሥራ ፈላጊዎችን አወዳድሮ በኮንትራት መቅጠር ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም መስፈርቱን የምታሟሉ አመልካቾች ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የሥራ ቀናት ኮተቤ ብረታብረት በሚገኘው ዋና መስሪያ ቤት አዲሱ አዳራሽ እየመጣችሁ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሐምሌ 26 ቀን 2016 ዓ.ም

በጥናት ከተለዩት የተቋሙ ስጋቶች መካከል 62 በመቶዎቹ ላይ እርምጃ ተወስዷል ……..//……... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በጥናት ከለያቸው ተቋማዊ ስጋቶች መካከል 62 በመቶዎቹ ላይ እርምጃ መውሰዱን የኮርፖሬት ስጋት ፋይናንስና ኢኮኖሚ መምርያ አስታወቀ፡፡ የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ እንዳለ ማሞ እንደገለጹት መምረያው በ2016 በጀት ዓመት አጠቃላይ የተቋሙን ስጋቶች ለመለየት የሚያስችል ጥናት አካሂዶ ነበር፡፡ በጥናቱ መሰረት ከአሁን ቀደም በሁሉም የሥራ ሂደቶች ከተለዩ 138 የተቋም ስጋቶች በተጨማሪ 16 አዳዲስ ስጋቶች ተለይተዋል ብለዋል፡፡ እንደ ዳይሬክተሩ ገለፃ የተለዩት ስጋቶች ከፋይናንስ፣ ከመደበኛ ሥራ፣ ከሰው ኃይል፣ ከዘመናዊ ቴክኖሎጂ አጠቃቀም፣ ከዕቃ አቅርቦት፣ ከሥራ ላይ ደህንነት፣ ከሕግ እና ደንብ፣ ከተቋሙ ውጭ በሆኑ ምክንያቶች እና ከግል አልሚዎች ጋር የተያያዙ ናቸው፡፡ ከተለዩት ስጋቶች መካከል 111 የሚሆኑት የስጋት ደረጃቸው ከፍተኛ በመሆኑ በ 79 ስጋቶች ለይ እርምጃ እንደተወሰደና ቀሪ 32 ስጋቶችን በቀጣይ ለማስወገድ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የተቋም ስጋቶች ተብለው የተለዩ ጉዳዮች በተቋሙ ሁሉም የሥራ ሂደቶች ሲገለፁ 154 ቢደርሱም በዋና ዋና ስጋቶች አንፃር በዘጠኝ መደቦች የተጠቃለሉ መሆናቸውንም ጠቁመዋል፡፡ በበጀት ዓመቱ በዘጠኙ መደብ በጥናት ከተለዩት ስጋቶች መካከል 62 በመቶዎቹ ላይ እርምጃ የተወሰደ ሲሆን እንዲሁም የሰጋት ደረጃቸው ከፈተኛ የነበሩት ስጋቶች ላይ በአማካኝ 71 በመቶ እርምጃ ተወስዷል፡፡ ተቋሙ ጊዜውን የጠበቀና ዘመናዊ በሆነ መልኩ ስጋቶችን በመለየት፣ በመከታተል እና መረጃዎችን በማደራጀት ለውሳኔ ሰጪ አካላት በተሳለጠ መልኩ ለማቅረብ የሚያስችሉ ዘመናዊ አሰራሮችን ከኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ ኦሪን ኮንሰልቲንግ እና ኢሰሪ ኢስተርን አፍሪካ ከተባሉ ድርጅቶች ጋር እየተገበረ መሆኑንም አስታወቀዋል፡፡ በተጨማሪም ስጋቶቹ ዳግመኛ እንዳይከሰቱ የማስወገድ፣ በተቋሙ ሊፈቱ የማይችሉ ስጋቶችን ወደ ሶሰተኛ ወገን የማሰተላለፍ፣ በተቋም ስጋት ማቅለያ መንገድ ስጋቶችን የማስወገድ እና ተቋሙን ጫና የማይከቱትን መቀበል ላይ ትኩረቱን ያደረገ ስትራቴጅ ተቀርጾ በመተግበር ላይ ይገኛል፡፡ የስትራቴጅው መተግበር የተቋሙን የስጋት ሁኔታ በመገምገም ባለድርሻ አካላት ተቋሙን የሚያግዙ መመርያዎችና ህጎችም እንዲወጡ ያስቻለ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ አቶ እንዳለ እንዳሉት ከተቋሙ ሁሉም የሥራ ክፍሎች የተወጣጡ ባለሙያዎች እና የሥራ ኃላፊዎች ከኮርፖሬት አመራር ጋር የሚገናኝ የስጋት ባለቤት ተዋቅሮ በኢትዮጵያ አየር መንገድ እና በአዲሰ አበባ ዩንቨርስቲ ንግድ ሥራ ኮሌጅ ሥልጠና መሰጠቱን ገልጸዋል፡፡ ይህም ቅንጅታዊ አሰራሮችን በማሳደግ በየሥራ ክፍሉ ያሉ የተቋም ስጋቶችን በመለየት መፍትሄ ለመስጠት ጉልህ ሚና መጫወቱን ጠቁመዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሀምሌ 26 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

የሳፕ ፕላንት ሜንቴናንስ ሞጁል ሲተገበር የጥገናና ኦፕሬሽን ስራዎችን ያዘምናል ……….///……... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጥገናና ኦፕሬሽን ሥራዎች ለማዘመን በተዘጋጀው የፕላንት ሜንቴናንስ ሞጁል ላይ ለሁሉም የሪጅን ዳይሬክተሮች ሥልጠና እየተሰጠ መሆኑን በኃይል ማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፊያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ የቴክኒካል ድጋፍ ቢሮ አስታወቀ፡፡ የቢሮው ሥራ አስኪያጅ አቶ ነፃነት መላኩ እንደገለፁት የማከፋፈያ ጣቢያዎችን እና የማስተላለፊያ መስመሮችን ኦፕሬሽንና ጥገና ለማሳለጥ የሚያግዝ የፕላንት ሜንቴናንስ ሞጁል የመጀመሪያ ዙር ሥልጠና መሰጠት ተጀምሯል፡፡ ሥልጠናው የሳፕ ፕላንት ሜንቴናንስ ሞጁልን ተግባራዊ በማድረግ የሪጅኖችን የአሰራር ሥርዓት ለማዘመን፣ ጠንካራ የሀብት ቁጥጥር ሥርዓት ለመዘርጋት፣ ወጭ ለመቀነስ እና ሥራን ለማቀላጠፍ አስተዋፅኦው ከፍ ያለ መሆኑን ጠቅሰዋል። በቢሮው ኤሌክትሪካል መሀንዲስ እሌኒ ሲሳይ በበኩላቸው የፕላንት ሜንቴናንስ ሞጁል የማስተላለፊያና ማከፋፈያ ጣቢያዎችን ንብረቶች የሚመዘግብ ከመሆኑም ባሻገር የጥገና ሥራዎችን በዕቅድ ላይ ተመስርቶ ለማከናወን ፋይዳው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል። ሥልጠናው ሪጅኖች የጥገና ሥራዎቻቸውን በምን መልኩ በሳፕ ፕላንት ሜንቴናንስ እንደሚያካሂዱ ግንዛቤ ለመፍጠር ያለመ ነው ብለዋል፡፡ በቀጣይ ከሪጅኖች የተውጣጡ እና ለፕላንት ሜንቴናንስ ሞጁል ጠቃሚ ዳታዎችን ሲሰበስቡ የነበሩ ባለሙያዎችና የሪጅኖቹ የጥገና ባለሙያዎች ጨምሮ በተዋረድ እስከ ታች ድረስ ሥልጠናው እንደሚሰጥ ተነግሯል፡፡ በተመሳሳይ በማዕከላዊ ሁለት ሥር ለሚገኙ የማከፋፊያ ጣቢያ ኃላፊዎች የሳፕ ፕላንት ሜንቴናንስን ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል የቅድመ ዝግጅት ሥልጠና እየተሰጠ ነው፡፡ በዘርፉ የሳፕ ትግበራ ኮሚቴ አባል አቶ ወልዳይ ገብረትንሳዔ እንደተናገሩት ሥልጠናው የጣቢያ ኃላፊዎች የሳፕ ፕላንት ሜንቴናንስን ተግባራዊ በማድረግ የኦፕሬሽንና የጥገና ሥራዎችን ለማቀላጠፍና ለማዘመን ያግዛቸዋል፡፡ የስልጠናው አስተባባሪ አቶ ቢኒያም ጸጋዬ በበኩላቸው የሳፕ ፕላንት ሜንቴናንስ መተግበር በጣቢያዎቹ በማንዋል የሚሰሩ አሰራሮችን በማስወገድ ጊዜንና ወጭን ብሎም የመብራት መቆራረጥ ድግግሞሹን በቀነሰ መልኩ ሥራዎችን ለማከናወን ይረዳል ብለዋል፡፡ አስተባባሪው አክለውም የጥገና ሥራዎች በሲስተም የተደገፈ የመረጃ ሥርዓት እንዲኖራቸውና ወጥ አሰራር እንዲተገበር ጉልህ ሚና እንደሚኖረው ገልጸዋል፡፡ ሥልጠናዎቹ በኃይል ማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፊያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ቴክኒካል ድጋፍ ቢሮ ከሰው ኃይል ስልጠናና ልማት ቢሮ ጋር በመተባበር የተዘጋጁ ናቸው፡፡ ለአስር ቀናት የሚቆየው ሥልጠና በጥገና የአሰራር ሥርዓት፣ በመለዋወጫ ዕቃዎች አቅርቦት እና ተያያዥ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ትኩረት ያደርጋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሀምሌ 25 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+9

የሳፕ ፕላንት ሜንቴናንስ ሞጁል ሲተገበር የጥገናና ኦፕሬሽን ስራዎችን ያዘምናል ……….///……... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጥገናና ኦፕሬሽን ሥራዎች ለማዘመን በተዘጋጀው የፕላንት ሜንቴናንስ ሞጁል ላይ ለሁሉም የሪጅን ዳይሬክተሮች ሥልጠና እየተሰጠ መሆኑን በኃይል ማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፊያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ የቴክኒካል ድጋፍ ቢሮ አስታወቀ፡፡ የቢሮው ሥራ አስኪያጅ አቶ ነፃነት መላኩ እንደገለፁት የማከፋፈያ ጣቢያዎችን እና የማስተላለፊያ መስመሮችን ኦፕሬሽንና ጥገና ለማሳለጥ የሚያግዝ የፕላንት ሜንቴናንስ ሞጁል የመጀመሪያ ዙር ሥልጠና መሰጠት ተጀምሯል፡፡ ሥልጠናው የሳፕ ፕላንት ሜንቴናንስ ሞጁልን ተግባራዊ በማድረግ የሪጅኖችን የአሰራር ሥርዓት ለማዘመን፣ ጠንካራ የሀብት ቁጥጥር ሥርዓት ለመዘርጋት፣ ወጭ ለመቀነስ እና ሥራን ለማቀላጠፍ አስተዋፅኦው ከፍ ያለ መሆኑን ጠቅሰዋል። በቢሮው ኤሌክትሪካል መሀንዲስ እሌኒ ሲሳይ በበኩላቸው የፕላንት ሜንቴናንስ ሞጁል የማስተላለፊያና ማከፋፈያ ጣቢያዎችን ንብረቶች የሚመዘግብ ከመሆኑም ባሻገር የጥገና ሥራዎችን በዕቅድ ላይ ተመስርቶ ለማከናወን ፋይዳው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል። ሥልጠናው ሪጅኖች የጥገና ሥራዎቻቸውን በምን መልኩ በሳፕ ፕላንት ሜንቴናንስ እንደሚያካሂዱ ግንዛቤ ለመፍጠር ያለመ ነው ብለዋል፡፡ በቀጣይ ከሪጅኖች የተውጣጡ እና ለፕላንት ሜንቴናንስ ሞጁል ጠቃሚ ዳታዎችን ሲሰበስቡ የነበሩ ባለሙያዎችና የሪጅኖቹ የጥገና ባለሙያዎች ጨምሮ በተዋረድ እስከ ታች ድረስ ሥልጠናው እንደሚሰጥ ተነግሯል፡፡ በተመሳሳይ በማዕከላዊ ሁለት ሥር ለሚገኙ የማከፋፊያ ጣቢያ ኃላፊዎች የሳፕ ፕላንት ሜንቴናንስን ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል የቅድመ ዝግጅት ሥልጠና እየተሰጠ ነው፡፡ በዘርፉ የሳፕ ትግበራ ኮሚቴ አባል አቶ ወልዳይ ገብረትንሳዔ እንደተናገሩት ሥልጠናው የጣቢያ ኃላፊዎች የሳፕ ፕላንት ሜንቴናንስን ተግባራዊ በማድረግ የኦፕሬሽንና የጥገና ሥራዎችን ለማቀላጠፍና ለማዘመን ያግዛቸዋል፡፡ የስልጠናው አስተባባሪ አቶ ቢኒያም ጸጋዬ በበኩላቸው የሳፕ ፕላንት ሜንቴናንስ መተግበር በጣቢያዎቹ በማንዋል የሚሰሩ አሰራሮችን በማስወገድ ጊዜንና ወጭን ብሎም የመብራት መቆራረጥ ድግግሞሹን በቀነሰ መልኩ ሥራዎችን ለማከናወን ይረዳል ብለዋል፡፡ አስተባባሪው አክለውም የጥገና ሥራዎች በሲስተም የተደገፈ የመረጃ ሥርዓት እንዲኖራቸውና ወጥ አሰራር እንዲተገበር ጉልህ ሚና እንደሚኖረው ገልጸዋል፡፡ ሥልጠናዎቹ በኃይል ማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፊያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ቴክኒካል ድጋፍ ቢሮ ከሰው ኃይል ስልጠናና ልማት ቢሮ ጋር በመተባበር የተዘጋጁ ናቸው፡፡ ለአስር ቀናት የሚቆየው ሥልጠና በጥገና የአሰራር ሥርዓት፣ በመለዋወጫ ዕቃዎች አቅርቦት እና ተያያዥ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ትኩረት ያደርጋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሀምሌ 25 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

ተቋሙ በጎፋ ዞን በመሬት መንሸራተት አደጋ ለተጎዱ ወገኖች ድጋፍ አደረገ .........///……... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰ ድንገተኛ የመሬት መንሸራተት አደጋ ለተጎዱ ወገኖች የአንድ ሚሊዮን ብር ድጋፍ አደረገ። የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር እና በስሩ የሚገኙ ተጠሪ ተቋማት በዞኑ በተከሰተው ተፈጥሯዊ አደጋ ለተጎዱ ወገኖች የሚውል ድጋፍ በኢ.ፌ.ዲ.ሪ የአደጋ ስጋትና አመራር ኮሚሽን በኩል በዛሬው ዕለት አድርገዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልም በዋና ሥራ አስፈፃሚው ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በኩል ለተጎጂዎች እንዲደርስ የአንድ ሚሊየን ብር ቼክ ለኮሚሽኑ አስረክቧል። በእርዳታ ርክክብ ሥነ ስርዓቱ ላይ ንግግር ያደረጉት የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር አቶ ሀብታሙ ኃይለሚካኤል እንደገለፁት በዞኑ በደረሰው የመሬት መንሸራተት አደጋ ሳቢያ የበርካታ ወገኖቻችን ህይወት በማለፉ አዝነናል። በአስተዳደሩ ስር የሚገኙት ተጠሪ ተቋማት ከሚሰሯቸው የንግድና የልማት ሥራዎች ጎን ለጎን በርካታ የማህበራዊ ኃላፊነት ተግባራት ላይ በንቃት እየተሳተፉ እንደሚገኙ ጠቅሰዋል። አስተዳደሩና ተጠሪ ተቋማቱ በዞኑ ተከስቶ በነበረው ተፈጥሯዊ አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች የሚውል የ10 ነጥብ 7 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ማድረጋቸውንም ተናግረዋል። በቀጣይም ጉዳት የደረሰባቸውን የማህበረስብ ክፍሎች በዘላቂነት ለማቋቋም በሚደረገው ጥረት ውስጥ አስተዳደሩና ተጠሪ ተቋማቱ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንደሚያደርጉም ዋና ዳይሬክተሩ ገልፀዋል። የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፉን ከአስተዳደሩና ከተጠሪ ተቋማቱ የተረከቡት የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የአደጋ ስጋትና አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር ሽፈራው ተ/ማሪያም (ዶ/ር) እንደገለፁት በዞኑ ሁለት ቀበሌዎች ላይ በደረሰው አደጋ የ243 ሰዎች ህይወት አልፏል። በአደጋው ጉዳት የደረሰባቸውን የህብረተሰብ ክፍሎች በዘላቂነት ለማቋቋም ለሚደረገው ጥረት ሁሉም ዜጋ የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ አሳስበዋል። የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር እና ተጠሪ ተቋማቱ ላደረጉት የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፍ ጉዳት በደረሰባቸው የዞኑ ነዋሪዎችና በኮሚሽኑ ሥም ምስጋናቸውንም አቅርበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሀምሌ 24 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+6

ጣቢያው ለበርካታ ከተሞች እና ፋብሪካዎች ኃይል በማቅረብ ላይ ነው ……..///……. የደብረብርሃን ቁጥር 2 ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በአቅራቢያው ላሉ ከተሞች እና ፋብሪካዎች ኃይል በማከፋፈል ላይ እንደሚገኝ የጣቢያው ኃላፊ አስታወቁ፡፡ ኃላፊው አቶ ዳኜ ይታገሱ እንደተናገሩት ጣቢያው ለደብረብርሃን ኢንዱስትሪ ፓርክ፣ በአቅራቢያው ለሚገኙ በርካታ ፋብሪካዎች፣ ለደብረብርሃን፣ ለእነዋሪ፣ ደነባ፣ መንዲዳ፣ ጅሁር፣ ሀገረማርያም፣ ሸኖ እና ጫጫ ከተሞች በቀን እስከ 48 ሜጋ ዋት ኃይል በማቅረብ ላይ ይገኛል። በተጨማሪም በዳታ ማይኒንግ ለተሰማሩ የውጭ ኩባንያዎች በቀን እስከ 20 ሜጋ ዋት ኃይል በማቅረብ የውጭ ምንዛሪ እያስገኘ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡ እንደ ኃላፊው ማብራሪያ ጣቢያው በ 33 ኪሎ ቮልት ዘጠኝ ወጪ መስመሮች እንዲሁም በ15 ኪሎ ቮልት ስምንት ወጪ መስመሮች አሉት፡፡ በቅርቡ ወደ ምርት ሥራ ይገባል ተብሎ ለሚጠበቀው የለሚ ሲሚንቶ ፋብሪካ በ 230 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመር ለመዘርጋት ቅድመ ዝግጅት ላይ መሆኑንም ነው አቶ ዳኜ ያብራሩት፡፡ በ2011 ዓ.ም በይፋ ተመርቆ አገልግሎት መስጠት የጀመረው የደብረብርሃን ቁጥር 2 ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ሁለት ባለ 125 ሜጋ ቮልት አምፒር እና ሁለት ባለ 63 ሜጋ ቮልት አምፒር አቅም ያላቸው ትራንስፎርመሮች አሉት፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሀምሌ 24 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+4

ተቋሙ ኮንትራት በመውሰድ ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አዲስ የማከፋፈያ ጣቢያ እየገነባ ነው . .. ....///........ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ኮንትራት በመውሰድ በአዲስ አበባ ከተማ ዓለም ባንክ አካባቢ አዲስ የማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ መጀመሩን በተቋሙ የራስ ኃይል ግንባታ መምሪያ አስታወቀ፡፡ በመምሪያው የፕሮጀክት ማኔጅመንት II ሥራ አስኪያጅ አቶ ተድላ ሰይፉ እንደገለፁት የግንባታ ስምምነቱ 33 ኪ.ቮ አቅም ያለውን የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ገንብቶ ማስረከብ ነው፡፡ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ወጪ እየተገነባ የሚገኘው ፕሮጀክቱ 31 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር አጠቃላይ በጀት የተያዘለት መሆኑን አቶ ተድላ ተናግረዋል፡፡ የፕሮጀክቱ ሥራ የሲቪል፤ የኤሌክትሮ ሜካኒካል እንዲሁም የፍተሻ እና የሙከራ ሥራዎችን እንደሚያካትትም ነው የገለፁት፡፡ እንደ አቶ ተድላ ገለፃ ተቋሙ አሁን የጀመራቸው ግንባታዎች ላለፉት በርካታ ዓመታት ለውጭ ሀገር የሥራ ተቋራጮች ይሰጡ ነበር፡፡ ይሁንና ከግንባታ እስከ ፍተሻ ያለው ሥራ በሀገር ውስጥ አቅም በመሰራቱ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ከማስቀረቱም ባሻገር ግዙፍ ፕሮጀክቶችን ለመገንባት የሚያስችል መደላድል እንደሚፈጥር አብራርተዋል፡፡ የፕሮጅክቱ ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ዮሐንስ መልካሙ በበኩላቸው የፕሮጀክቱ ግንባታ ግንቦት 2016 ዓ.ም መጀመሩን እና በስድስት ወራት ውስጥ ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡ እንደ ኢንጂነር ዮሐንስ ገለፃ አጠቃላይ የፕሮጀክቱ አፈፃፀም ከ41 በመቶ በላይ የደረሰ ሲሆን የመቆጣጠሪያ ክፍል፣የስዊች ጊር ስትራክቸር፣ የትራንስፎርመር ማስቀመጫ ግንባታ ስራዎች ተከናውነዋል፡፡ ለኤሌክትሮ ሜካኒካል ሥራዎች የሚያስፈልጉ ግብአቶችን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት እንደሚያቀርብ የገለፁት የፕሮጀክቱ የሳይት መሀንዲስ አቶ ሶፎኒያስ ካሱ በበኩላቸው ፕሮጀክቱ ለ55 የአካባቢው ነዋሪዎች የሥራ ዕድል መፍጠሩን ተናግረዋል፡፡ ማከፋፈያ ጣቢያው ስምንት ወጪ መስመሮች ሲኖሩት ግንባታው ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ሲጀምር በአካባቢው ያለውን ከፍተኛ የኃይል ጫና ከማቃለሉም ባሻገር ከጣቢያው 50 ኪ.ሜ ዙሪያ ለሚገኙ ፋብሪካዎች እና ከተሞች አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ ያስችላል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሀምሌ 18 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+2

photo content
+9