ru
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Открыть в Telegram

📈 Аналитический обзор Telegram-канала EEP Communication

Канал EEP Communication (@eepcommuication) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 15 544 подписчиков, занимая 8 333 место в категории Технологии и приложения и 2 158 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 15 544 подписчиков.

Согласно последним данным от 27 июня, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 10, а за последние 24 часа — -16, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 25.06%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 16.33% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 3 895 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 2 539 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 7.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
EEP Communication

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 28 июня, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Технологии и приложения.

15 544
Подписчики
-1624 часа
-97 дней
+1030 день
Архив постов
photo content

የታሪፍ ክለሳው የኃይል ዘርፉ ላይ መሰረታዊ ለውጥ ለማምጣት አስፈላጊ ነው .....//..... የታሪፍ ክለሳው በኃይል ልማት ዘርፉ ላይ መሰረታዊ ለውጥ ለማምጣት አስፈላጊ መሆኑን የታሪፍ ክለሳ የጥናት ቡድን ገለጸ። የጥናት ቡድኑ አባልና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የፋይናንስ አስተዳደር ዳይሬክተር አቶ አለማየሁ መንግስቱ የታሪፍ ክለሳው ያስፈለገበትን ምክንያት የሚዳስስ የጥናት ጽሁፍ አቅርበዋል። በጥናት ጽሁፉ ላይ እንደተጠቀሰው የኃይል ሽፋኑንና የተቋማቶቹን የፋይናንስ ቁመና ለማሻሻል፣ በማስተላለፊያና ማሰራጫ መስመሮች ላይ ያለውን ብክነት ለመቀነስ፣ የኃይል ፍላጎትን ለማሟላት፣ የአገልግሎቱን ጥራት ለማዘመን እና የኃይል ኤክስፖርቱን በማሳደግ ዘርፉን ለመደጎም የታሪፍ ማሻሻያው አስፈላጊ ነው። በሀገሪቱ አሁን ላይ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተደራሽነት 55 በመቶ መሆኑን የገለፁት አቶ ዓለማየሁ ሽፋኑን ወደ 74 በመቶ ለማሳደግ የታሪፍ ማሻሻያው ወሳኝ መሆኑን ጠቁመዋል። እንደ አቶ አለማየሁ ገለጻ በሥራ ላይ ያለው ታሪፍ ለተቋሙ ገቢ ማደግ ድርሻ ቢኖረውም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ላለፉት 6 ዓመታት በአማካይ በየዓመቱ ለ26 ቢሊዮን ብር ኪሳራ ሲዳረግ ቆይቷል ብለዋል። እንደ አቶ ዓለማየሁ ገለፃ ተቋሙ እንደ አዲስ ከተቋቋመበት ከ2006 ዓ.ም ጀምሮ 177 ቢሊዮን ብር ጠቅላላ ኪሳራ አጋጥሞታል። በሀገሪቱ ከፍተኛ የኃይል ተጠቃሚ ኢንዱስትሪዎች ፍላጎት አሁን ካለበት ከ3 ሺ 271 ጊጋ ዋት ስዓት ወደ 5 ሺ 205 ጊጋ ዋት ስዓት ለማሳደግና የመካከለኛና ዝቅተኛ ኃይል ተጠቃሚ ኢንዱስትሪዎችን የኃይል ፍላጎት ደግሞ ከ739 ጊጋ ዋት ሰዓት ወደ 3 ሺ 260 ጊጋ ዋት ስዓት ለማሳደግ ከፍተኛ ፋይናንስ እንደሚፈልግ ጠቁመዋል። የታሪፍ ማሻሻያው የኃይል መቆራረጥ ድግግሞሹን በከፍተኛ ደረጃ በመቀነስ በሀገሪቱ ያለውን የኃይል ፍላጎት ጥያቄ አስተማማኝ በሆነ መልኩ በመፍታት የኢንዱስትሪዎችን የማምረት አቅም ለማሳደግ ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረው አብራርተዋል። በማስተላለፊያ መስመሮች ላይ ያለውን ብክነት አሁን ካለበት ከ7 በመቶ ወደ 5 በመቶ እንዲሁም በማሰራጫ መስመሮች ላይ ያለውን ብክነት ከ18 በመቶ ወደ 12 በመቶ በመቀነስ በአገልግሎት ዘርፍ የሚታዩ የአገልግሎት ችግሮችን ለመቅረፍ የታሪፍ ማሻሻያው አስፈላጊ መሆኑም አብራርተዋል። የኃይል ኢንቨስትመንቱን በማሳደግ በአሁኑ ወቅት ለውጪ ሀገራት የሚቀርበውን አንድ ሺ 665 ጊጋ ዋት ስዓት የኃይል መጠን በአማካኝ በየዓመቱ 22 በመቶ ለመጨመር ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። ይህም ከሀገር ውስጥ ደንበኞች የሚጠበቀውን ተሰብሳቢ ዓመታዊ ገቢ ዝቅ በማድረግ የሀገር ውስጥ ደንበኞችን ታሪፍ ለመደጎም የሚያስችል ነው ብለዋል። አሁን በሥራ ላይ ያለው ታሪፍ በሀገር ውስጥና በውጭ አገራት ባለው የዋጋ ንረት ምክንያት አቅሙ ከ35 በመቶ በላይ መቀነሱን የገለጹት አቶ አለማየሁ የታሪፍ ክለሳው የኃይል ኢንቨስትመንቱን ለማሳደግ ይረዳል ነው ያሉት። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia      ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power   ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ  www.eep.com.et     ሰኔ 08 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+6

የታሪፍ ማሻሻያ ባለመደረጉ ተቋሙ ለኦፕሬሽንና የጥገና ሥራዎች በየዓመቱ በአማካይ 26 ቢሊየን ብር ኪሳራ እያስተናገደ ነው ...///... በ2011 ዓ.ም የተተገበረው ታሪፍ ላይ ማሻሻያ ባለመደረጉ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለኦፕሬሽንና የጥገና ሥራዎች በየዓመቱ በአማካይ 26 ቢሊየን ብር ኪሳራ እያስተናገደ መሆኑን የተቋማቱ የታሪፍ ክለሳ የጥናት ቡድን አስታወቀ። የጥናት ቡድኑ አባልና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የፋይናንስ አስተዳደር ዳይሬክተር አቶ ዓለማየሁ መንግስቱ እንደገለፁት በሥራ ላይ ባለው ታሪፍ ሁለቱ የኃይል አቅራቢ ተቋማት የኦፕሬሽንና የተወሰኑ የፕሮጀክት ወጪዎችን በመጠኑ መሸፈን ችለዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የታሪፍ ማሻሻያ ከተደረገ በኋላ ከ6 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር ተነስቶ በየዓመቱ በአማካይ የ5 ቢሊየን ብር ዕድገት እያሳየ በአሁኑ ወቅት ወደ 29 ቢሊየን ብር መድረሱን አቶ አለማየሁ ተናግረዋል። እንደ ጥናት ቡድኑ አባል ገለፃ ተቋሙ ባለፉት አራት ዓመታት ከሰበሰበው ገቢ ውስጥ በየዓመቱ አማካይ የ5 ቢሊየን ብር ገቢ ዕድገት እያሳየ ነው። ይሁንና በሚያከናውናቸው የፕሮጀክት ግንባታ፣ የኦፕሬሽንና የጥገና ሥራዎች በየዓመቱ በአማካይ 26 ቢሊየን ብር ኪሳራ እያስተናገደ መሆኑን ጠቅሰዋል። የታሪፍ ማሻሻያው መተግበር ከጀመረ ወዲህ 1 ሺህ 347 ከተሞችን በኤሌክትሪክ ተደራሽ ማድረግ እንደተቻለ የጠቆሙት አቶ ዓለማየሁ የኃይል ተጠቃሚ ደንበኞች ቁጥር በ1 ነጥብ 8 ሚሊየን ጭማሪ ማሳየቱን ተናግረዋል። ባለፉት አራት ዓመታት በአገልግሎት አሰጣጥና የአከፋፈል ሒደቶች ላይ ይነሱ የነበሩ ቅሬታዎችን ለመፍታት የዲጂታላይዜሽን ሥራዎች መጀመራቸውን አመልክተዋል። ይሁን እንጂ ላለፉት 6 ዓመታት በሥራ ላይ የቆየው ታሪፍ የኃይል አቅራቢ ተቋማቱ በፋይናንስ እንዲጠናከሩና የአገልግሎት አሰጣጣቸውን እንዲያሻሽሉ እገዛ ቢያደርግም የሚፈለገውን ለውጥ ማምጣት እንዳልቻለ ነው አቶ ዓለማየሁ የገለፁት። በአሁኑ ወቅት በትግበራ ላይ ያለው የኃይል ሽያጭ ታሪፍ ዓለም ከደረሰበት የኢኮኖሚ ዕድገት ጋር ተመጣጣኝ ባለመሆኑ በኃይል አቅራቢ ተቋማቱ የፋይናንስ ቁመና ላይ ከፍተኛ ጫና ማሳደሩን አብራርተዋል። በቀጣይ ተቋማቱ የተሻለ አገልግሎት ለመስጠትና ተደራሽነታቸውን ለማሰፋት የታሪፍ ክለሳ ተዘጋጅቶ ለአስተያየት መቅረቡን የጥናት ቡድኑ አባል ተናግረዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 07 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+7

የታሪፍ ማሻሻያው ወቅቱን ጠብቆ አለመደረጉ የኃይል አቅራቢ ተቋማቱን ለኪሳራ ዳርጓል .....//.... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ባዘጋጁት የታሪፍ ክለሳ ምክረ ሀሳብ ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር በአድዋ ሙዚየም የስብሰብ አዳራሽ እየመከሩ ነው። በውይይቱ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን የዋና ዳይሬክተር ተወካይ አቶ በላይነህ ግዛው አሁን በሥራ ላይ ያለው ታሪፍ ላለፉት አስራ ሁለት ዓመታት ለውጥ ያልተደረገበት በመሆኑ የኃይል አቅራቢ ተቋማቱን ለኪሳራ መዳረጉን ገልጸዋል። በሀገሪቱ እያደገ የመጣውን የኃይል ፍላጎት ጥያቄ ለማሟላትና የተሻለ የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ የአገልግሎት ተደራሽነቱን ለማስፋት የሚያስችል የኤሌክትሪክ ታሪፍ መዘጋጀቱን ተናግረዋል። የታሪፍ ማሻሻያው አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ፤ የጥገና ሥራዎችን ለማከናወን፣ የኃይል አማራጮችን ለማስፋት እንዲሁም የኃይል ኤክስፖርት ዘርፉን በማሳደግ የመሰረተ ልማት ማስፋፋት ስራውን የሚያግዝ መሆኑን ጠቁመዋል። የውይይት መድረኩ ዓላማ በተዘጋጀው የታሪፍ ማሻሻያ ጥናት ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት የሚሰጡ አስተያየቶችን ለማሰባሰብና ግልጽነት ለመፍጠር መሆኑን አቶ በላይነህ ተናግረዋል። የታሪፍ ማሻሻያው በሚቀጥሉት ሳምንታት ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ይቀርባል ተብሎ ይጠበቃል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia      ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power   ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ  www.eep.com.et     ሰኔ 07 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+9

የታሪፍ ማሻሻያ ጥናቱ የህብረተሰቡን የመክፈል አቅም ያገናዘበ ነው ........//......... የታሪፍ ክለሳ ጥናቱ ዝቅተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚጠቀሙ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ መሆኑን የሁለቱ የኃይል አቅራቢ ተቋማት ዋና ሥራ አስፈፃሚዎች አስታወቁ። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ፧ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እንደተናገሩት ኢትዮጵያ በኤሌክትሪክ አቅርቦት ተደራሽነት ዝቅተኛ አፈፃፀም ካላቸው ሀገራት ተርታ የምትሰለፍ ናት። ተቋሙ የኃይል አቅርቦቱን በስፋት ተደራሽ ለማድረግ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ የሚያስፈልጋቸውን ግብዓቶች እንደሚጠቀም ነው የተናገሩት። ባለፉት ዓመታት በሥራ ላይ የቆየው ታሪፍ የኃይል አቅራቢ ተቋማቱ በፋይናንስ እንዲጠናከሩና የአገልግሎት አሰጣጥ ደረጃቸውን እንዲያሳድጉ እገዛ ቢያደርግም የሚፈለገውን እንዳላመጣ ዋና ሥራ አስፈፃሚው ገልፀዋል። እንደ ኢንጅነር አሸብር ገለፃ የውጭ ምንዛሪ በየጊዜው እያሳየ ያለው ዕድገት በኃይል ማመንጫ፣ ማስተላለፊያና ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታዎች ላይ አሉታዊ ጫና አሳድሯል። ሁለቱ የኃይል አቅራቢ ተቋማት የኤሌክትሪክ ሽፋንን እና የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራትን ለማሳደግ ለሚያከናውኗቸው ተግባራት የታሪፍ ማሻሻያው አስፈላጊ እንደሆነም ነው አፅዕኖት የሰጡት። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሽፈራው ተሊላ በበኩላቸው በሀገር አቀፍ ደረጃ የህብረተሰቡን የኃይል ፍላጎት ጥያቄ ለማሟላት ከ26 ቢሊየን ብር በላይ ፋይናንስ የሚጠይቁ ፕሮጀክቶች እየተከናወኑ ነው። ተቋሙ እየተስተዋሉ የሚገኙ የኃይል መቆራረጦችን ለመቅረፍም የመሰረተ ልማት ማዘመን፣ የደንበኞች አገልግሎት አሰጣጥ፣ የውስጥ አቅምን እና የፋይናንስ ቁመናን የማሳደግ ሥራዎች እያከናወነ እንደሚገኝም ነው ዋና ሥራ አስፈፃሚው የጠቆሙት። የአዲስ አበባን የኤሌክትሪክ ኔትወርክ ለማሻሻል እየተከናወነ የሚገኘው ፕሮጀክት ሦስተኛው ደረጃ ላይ መድረሱን አቶ ሽፈራው አመልክተዋል። እንደ ዋና ሥራ አስፈፃሚው ገለፃ ተቋሙ የአገልግሎት አሰጣጥ ተደራሽነቱን አጠናክሮ መቀጠል እንዲያስችለው የታሪፍ ክለሳው ተግባራዊ መደረግ አለበት። የታሪፍ ማሻሻያው የህብረተሰቡን የመክፈል አቅም ያገናዘበና የአገልግሎት አሰጣጡን የሚያሳድግ እንደሆነም ነው ያብራሩት። የነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን የኢነርጂ ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ አህመድ ሰኢድ እንደገለፁት የታሪፍ ማሻሻያው በየአራት ዓመቱ መከለስ የሚገባው ቢሆንም ሳይሻሻል በመቆየቱ በኃይል አቅራቢ ተቋማቱ ላይ ከፍተኛ ችግር ፈጥሯል። በባለሥልጣኑ በመመሪያ ቁጥር 008/2014 መሠረት የታሪፍ ክለሳ ሲደረግ ኃይል አቅራቢ ተቋማቱ የኦፕሬሽን ወጪያቸውን እንዲሸፍኑ የሚያደርግ ታሪፍ መዘጋጀት እንዳለበት እንደሚደነግግም ተናግረዋል። የኃይል አቅራቢ ተቋማቱ በፋይናንስ እና በአሰራር ጠንካራ ሆነው የኤሌክትሪክ ተደራሽነትን ለማስፋት እንዲችሉ የታሪፍ ክለሳው ተገቢና ወቅቱን የጠበቀ መሆን እንዳለበት ነው አቶ አህመድ የገለፁት። የምክክር መድረኩ ዛሬም ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እና ባለድርሻ አካላት ጋር ይቀጥላል። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 07 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+5

ተቋማቱ የታሪፍ ክለሳ ጥያ ቄ ከማቅረባቸው በፊት መውሰድ ያለባቸውን እርምጃ በሙሉ ወስደዋል .........///......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪከ ኃይልና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የታሪፍ ክለሳ እንዲደረግ ለመንግስት ጥያ ቄ ከማቅረባቸው በፊት መውሰድ ያለባቸውን እርምጃዎች በሙሉ መውሰዳቸውን የታሪፍ ክለሳ የጥናት ቡድኑ አስታወቀ። የጥናት ቡድኑ አባልና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የፋይናንስ አስተዳደር ዳይሬክተር አቶ ዓለማየሁ መንግስቱ እንደገለፁት ተቋማቱ አፈፃፀማቸውን ለማሻሻል የውስጥ አሰራራቸውን ማዘመንና ወጪ መቀነስ ላይ ትኩረት አድረገው ሲሰሩ ቆይተዋል። የተቋማቱን የፋይናንስ ጤናማነት ማሻሻል፣ ብድርን ወደ መንግስት ማዞር፣ ከመንግስት ቀጥታና ተዘዋዋሪ ድጋፍ ማግኘትና ሌሎች ተጨማሪ ርምጃዎች መወሰዳቸውን አቶ ዓለማየሁ ተናግረዋል። ከሀገር ውስጥና ከውጭ አበዳሪዎች በአነስተኛ ወለድ የሚገኘውን ብድር በመጠቀም ተቋማቱ አዳዲስ መሰረተ ልማት ሲገነቡ፣ አቅም የማሳደግ ስራ ሲሰሩና አገልግሎቱን ሲሰጡ እንደቆዩ ጠቁመዋል። በቀጣይ የተሻለ አገልግሎት ለመስጠትና ተደራሽነትን ለማስፋት በማሰብ የታሪፍ ክለሳ መዘጋጀቱን ገልፀዋል። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 06 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+1

የታቀደው የታሪፍ ክለሳ የኢነርጂ ዘርፉን ለማሳደግ እና አገልግሎቱን ለማሻሻል  ከፍተኛ ሚና ይኖረዋል ……...///……… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ያዘጋጁት ረቂቅ የኃይል ሽያጭ ታሪፍ ክለሳ የኢነርጂ ዘርፉን ለማሳደግ ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረው የሁለቱ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች አስታወቁ። ተቋማቱ የኃይል ሽያጭ ታሪፍን ለማሻሻል በጋራ ባዘጋጁት ምክረ-ሃሳብ ከሚዲያ ባለሙያዎችና ባለድርሻ አካላት ጋር በአድዋ ሙዚየም የስብሰባ አዳራሽ ምክክር አካሂደዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልን ተቋማዊ ገፅታና ለታሪፍ ክለሳው መነሻ የሆኑትን ጉዳዮች ለመድረኩ ያቀረቡት የተቋሙ የኮርፖሬት ፕላኒንግ ሥራ አስፈፃሚ አቶ አንዱዓለም ሲዓ እንደገለፁት በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ ከውሃ 4 ሺህ 820 ሜጋ ዋት፣ ከንፋስ 404 ሜጋ ዋት እና ከእንፋሎት 32 ሜጋ ዋት ኃይል እያመነጨች ትገኛለች። የከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ዝርጋታ ከ20 ሺህ 200 በላይ ኪሎ ሜትር መድረሱን የጠቀሱት አቶ አንዱዓለም በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ በአፍሪካ 3ኛው የኤሌክትሪክ ኃይል ቋት የምታስተዳድር ሀገር መሆኗንም ተናግረዋል። እንደ ሥራ አስፈፃሚው ገለፃ ተቋሙ አጠቃላይ ሀብቱ 672 ቢሊየን ብር ቢደርስም 367 ቢሊየን ብሩ በዕዳ የተመዘገበ ነው። አነስተኛ የሀገር ውስጥ የነፍስ ወከፍ የኤሌክትሪክ ፍጆታ፣ ዝቅተኛ የኃይል ተደራሽነትና የማመንጨት አቅም፣ አስተማማኝ ያልሆነ የኃይል አቅርቦት እንዲሁም ያልተቀላጠፈ አሰራር የኃይል ልማት ዘርፉ ማነቆዎች መሆናቸውን ነው የገለፁት። ለዘመናት የተከማቸውን ዕዳ ማቃለል፣ በፕሮጀክቶች አፈፃፀም ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን መቅረፍ እና ተጠናቀው አገልግሎት የሚሰጡበትን አሰራር መዘርጋት ከተተገበሩ የሪፎርም ተግባራት መካከል እንደሚጠቀሱ አመልክተዋል። ተቋሙ በ2021 ዓ.ም የግል ባለሃብቱን በማሳተፍ የኃይል ማመንጨት አቅምን ወደ 17 ሺህ ሜጋ ዋት ከፍ ለማድረግ ዕቅድ ይዞ እየተንቀሳቀሰ እንደሚገኝ ያብራሩት ሥራ አስፈፃሚው ከውሃ 6 ሺህ 166 ሜጋ ዋት፣ ከንፋስ 2 ሺህ 255 ሜጋ ዋት፣ ከእንፋሎት 1 ሺህ 500 ሜጋ ዋት እንዲሁም ከፀሐይ 975 ሜጋዋት ተጨማሪ ኃይል ለማግኘት እንደሚሰራ ጠቁመዋል። እንደ አቶ አንዱዓለም ገለፃ በ2023 ዓ.ም የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችን ወደ 30 ሺህ 345 ኪሎ ሜትር እንዲሁም የማከፋፈያ ጣቢያዎችን ብዛት ወደ 323 ከፍ ለማድረግ ዕቅድ ተይዟል። እንደ ሥራ አስፈፃሚው ገለፃ ተቋሙ ለኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ግንባታ ከ200 ቢሊየን ብር እንዲሁም ለማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶች ከ25 ቢሊየን ብር በላይ በጀት ያስፈልገዋል። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የለውጥና መልካም አስተዳደር ዳይሬክተር አቶ እሱባለው ጤናው በበኩላቸው የኃይል ሽያጭ ታሪፉ ከ2011 ዓ.ም ከተሻሻለ በኋላ በየዓመቱ በአማካይ ከ350 ሺህ በላይ አዳዲስ ደንበኞችን የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል። ይሁን እንጂ የኤሌክትሪክ ተደራሽነትን ለማሳደግ መሰራት ካለባቸው ሥራዎች አንፃር አሁንም በዝቅተኛ ደረጃ ላይ የሚገኝ መሆኑን ዳይሬክተሩ አንስተዋል። እንደ አቶ እሱባለው ገለፃ አሁን ተግባራዊ እየተደረገ ባለው የኃይል ሽያጭ ታሪፍ ከ 8 ሺህ አምስት መቶ በላይ ቀበሌዎችን የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ለማድረግ እስከ 27 ዓመት ሊወስድ ይችላል። ተቋሙ ኪሳራ ላይ ነው ባይባልም ዓመታዊ የተጣራ ትርፉ ግን አራት ትራንስፎርመሮችን እንኳ መግዛት የማያስችል መሆኑን ነው ያብራሩት። የታሪፍ ማሻሻያው የአገልግሎት አሰጣጡን ለማሻሻል፣ ተደራሽነቱን ለማስፋት፣ ሀገራዊ እና የተባበሩት መንግስታት የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንዳለውም ነው የሁለቱ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች አመልክተዋል። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 06 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+6

የኃይል ሽያጭ ታሪፍን ለማሻሻል የቀረበ ምክረ-ሃሳብ ላይ ውይይት እየተደረገ ነው .....///..... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት  የኃይል ሽያጭ ታሪፍን ለማሻሻል በጋራ ባዘጋጁት ምክረ-ሃሳብ ከተለያዩ የሚዲያ ባለሙያዎችና ባለድርሻ አካላት ጋር በአድዋ ሙዚዬም የስብሰባ አዳራሽ ምክክር ጀምረዋል። የምክክር መድረኩ በኢነርጂ ዘርፉ አጠቃላይ ነባራዊ ሁኔታ፣ በቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች እንዲሁም በኤሌክትሪክ አገልግሎት የታሪፍ ጥናት ላይ ያተኮረ ነው። መድረኩን በንግግር የከፈቱት የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሳህረላ አብዱላሂ  እንደተናገሩት ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ኃይል ለማመንጨትና ለማሰራጨት ኃላፊነት የተሰጣቸው ባለፈቃድ መስሪያ ቤቶች ያቀረቡትን የብሔራዊ ግሪድ ታሪፍ ገምግሞ የውሳኔ ሃሳብ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ያቀርባል። ባለሥልጣኑ በአገልግሎት ሰጪ ተቋማቱ፣ በተጠቃሚውና በመንግሥት በኩል ያሉ ፍላጎቶችን በህግ አግባብና በታሪፍ መገምገሚያ መስፈርት መሠረት ሚዛናዊ ውሳኔ እንደሚያቀርብ ተናግረዋል። የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነትን ፍትሃዊና ሚዛናዊ በሆነ መልኩ ለማዳረስ በሚደረገው ጥረት ውስጥ የሶስቱንም አካላት ፍላጎት አስጠብቆ ለማስቀጠል አዳጋች የሆኑ የዘርፉ ዕድገት ማነቆዎች በርካታ መሆናቸውን ዋና ዳይሬክተሯ ጠቁመዋል። እንደ ዋና ዳይሬክተሯ ገለፃ ባለፉት ሁለት ዓመታት መከለስ የነበረበት የኤሌክትሪክ ታሪፍ ያለ ማሻሻያ በመቆየቱ ሳቢያ ኃይል አቅራቢ ተቋማቱን ለኪሳራ የዳረገና በአገልግሎት አሰጣጥ ጥራት ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ያሳደረ ሆኖ ተገኝቷል። የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ፍላጎት ከጊዜ ወደጊዜ እያደገ መምጣቱን የጠቆሙት ወ/ሮ ሳህረላ ይሁን እንጂ ለኃይል አቅራቢ ተቋማቱ የታሪፍ ማሻሻያ ባለመደረጉ አዳዲስ መሰረተ ልማቶችን ለመገንባት የፋይናንስ እጥረት እንዲገጥማቸውና ከፍተኛ የዕዳ ጫና ውስጥ እንዲዘፈቁ  ምክንያት እንዳደረጋቸው እንረዳለን ብለዋል። በአሁኑ ወቅት ባለሥልጣን መስሪያ ቤቱ የኃይል አቅራቢ ተቋማቱ የታሪፍ ጥናት አዘጋጅተው ባቀረቡት መሠረት የታሪፍ ቅድመ ግምገማ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል። የታሪፍ ማሻሻያው አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ፤ አስቸኳይ ጥገናዎችን ለማካሔድ፤ አዳዲስ ፕሮጀክቶችን ለመገንባትና የኃይል አማራጮችን ለማስፋት እንዲሁም የኃይል ኤክስፖርት ዘርፉን ለማሳደግ እንደሚያግዝ ጠቁመዋል። የሚዲያ አካላት የታሪፍ ማሻሻያው አስፈላጊነትን በበቂ ሁኔታ በማስረዳትና ለማህበረሰቡ በማስገንዘብ የበኩላቸውን እንዲወጡ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። በምክክር መድረኩ ላይ የሁለቱ ተቋማት የመሰረተ ልማትና የፋይናንስ ቁመናን የተመለከቱ ጉዳዮች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል። በቀጣይ ቀናትም ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ተመሳሳይ ምክክር በማድረግ ተጨማሪ ግብዓት የማሰባሰብ ሥራ የሚሰራ ይሆናል። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 06 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+8

የጫካን ፕሮጀክት የኃይል መሰረተ ልማት ግንባታ ሥራ እስከ ነሐሴ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው …………///………. በጫካ ፕሮጀክት የተጀመረውን የኃይል ማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፊያ ጣቢያ ግንባታ እስከ ነሐሴ 2016 ዓ.ም ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፊያ ጣቢያዎች ግንባታ ዘርፍ ገለጸ፡፡ በዘርፉ የፕሮግራም 1 ፕሮጀክት አስተዳደር 3 ቢሮ ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ የትናየት ይመር እንደገለጹት በጫካ ፓርክ ፕሮጀክት ክልል የሚያልፉ የማስተላለፊያ መስመሮችን ከፓርኩ ማስተር ፕላን ጋር በማጣጣም መስመሮችን የማዛወርና በጊዜያዊነት ለኃይል አቅርቦት የሚያገለግል የተንቀሳቃሽ ማከፋፊያ ጣቢያ ተከላ እየተከናወነ ይገኛል፡፡ የግንባታ ሥራው በጫካ ፓርክ አቋርጦ የሚያልፈውን የኮተቤ - ቤላ ባለ 132 ኪሎ ቮልት ማስተላለፊያ መስመር የማዛወር ሥራ የሚይዝ ነው፡፡ ግንባታው የ3 ነጥብ 9 ኪሎ ሜትር የመሬት ውስጥና የ0 ነጥብ 9 ኪሎ ሜትር የአየር ላይ (ኦቨር ሄድ) መስመር ዝርጋታ እንዲሁም የ0 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የኮንዳክተር ቅየራ ሥራዎችን እንደሚያጠቃልል ገልጸዋል፡፡ እንደ ወ/ሮ የትናየት ገለፃ ከኮተቤ - አያት ከተዘረጋው ባለ 132 ኪሎ ቮልት መስመር ላይ 0 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትሩን በመሬት ውስጥ የመቀየር ሥራ በተጓዳኝ እንደሚከናወን ጠቁመዋል፡፡ በተመሳሳይ የኮተቤ - አዲስ ኢስት ባለ 132 ኪሎ ቮልት ጥምር የማስተላለፊያ መስመርን የማዛወር ሥራ እንደሚከናወን የገለጹት ወ/ሮ የትናየት ይህም የ1 ነጥብ 6 ኪሎ ሜትር የመሬት ውስጥ እና የ1 ነጥብ 4 ኪሎ ሜትር የአየር ላይ መስመር ዝርጋታ ሥራን እንደሚያካትት አብራርተዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት ለኮተቤ - ቤላ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የመስመር ማዛወር ሥራ የሚያስፈልጉ ዕቃዎች ሙሉ በሙሉ ተመርተው ወደ ሀገር ውስጥ መግባታቸውን ተናግረዋል፡፡ ከቤላ እስከ ጫካ ተንቀሳቃሽ ማከፋፊያ ጣቢያ ያለው የ0 ነጥብ 6 ኪሎ ሜትር የማስተላለፊያ መስመር የተከላ እና ፍተሻ ሥራ መጠናቀቁንና የተንቀሳቃሽ ማከፋፊያ ጣቢያው የፍተሻ ሥራ መጀመሩን ሥራ አስኪያጇ አስታውቀዋል፡፡ ለኮተቤ - አዲስ ኢስት መስመር ማዛወር ከሚያስፈልጉ 6 የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሰሶዎች የአራቱ የተከላ ሥራ ተጠናቆ ኮንዳክተር የመዘርጋት ስራ መጀመሩን እንዲሁም ቀሪ ሁለት ምሰሶዎች የከፍተኛ መስመር ኃይል ማቋረጥ ስለሚጠይቁ መሬት ላይ ቀድመው መሰራት ያለባቸው ሥራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኙ ገልጸዋል፡፡ የፕሮጀክቱ የማስተላለፊያ መስመር ግንባታ ሥራ TBEA በተባለ የቻይና ሥራ ተቋራጭ ኩባንያ አማካኝነት እየተከናወነ መሆኑን ወ/ሮ የትናየት ተናግረዋል፡፡ እንደ ሥራ አስኪያጇ ገለፃ በተቋሙ የራስ ኃይል ግንባታ መምሪያ በኩል የተንቀሳሽ ማከፋፈያ ጣቢያ ሲቪል ስራ እንዲሁም ከኮተቤ ጫካ በነባር ምሰሶዎች ላይ የጥገና እና የማስተላለፊያ መስመር ዝርጋታ ስራ እየተከናወነ ነው፡፡ አሁን ባለው ፕሮጀክቱ የሥራ ወሰን መሰረት የመሬት ውስጥ መስመር ዝርጋታ ስራ ላይ የክረምቱ የአየር ሁኔታ ተፅዕኖ የማያሳድር ከሆነ ሥራዎችን እስከ ነሐሴ 2016 ዓ.ም. ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የፕሮጀክቱ አጠቃላይ ወጭ 370 ሚሊየን ብር የሚገመት ሲሆን ሙሉ ወጪው በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሚሸፈን ይሆናል፡፡ “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 05 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+6

በቀጣይ ለሚገነቡ ፕሮጀክቶች በሥራ ላይ ያለው የታሪፍ ምጣኔ እንቅፋት እንዳይሆን ስጋት ፈጥሯል ………..///……. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በነደፈው የሶስት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ለመገንባት ዕቅድ ይዟል፡፡ ከዕቅዶች መካከል አስራ ስድስቱ ፕሮጀክቶች የተቋሙን አሰራር ከማዘመን እና ሀብትን በአግባቡ ለመጠቀም ታስቦ የተቀረፁ ፕሮጀክቶች ሲሆን ፕሮጀክቶቹን ለማስፈፀም እስከ ዘጠና ስድስት ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ያስፈልጋል፡፡ በተቋሙ የሚተገበሩ ሰላሳ ሶስት የሚደርሱ የማስተላለፊያ እና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶች ደግሞ የሚያስፈልጋቸው የካፒታል መጠን 767 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ነው፡፡ በስትራቴጂክ ዕቅድ ዘመኑ በግል ባለሀብቱ ሊገነቡ በዕቅድ ከተያዙ ፕሮጀክቶች መካከል ከአምስት የፀሀይ ፕሮጀክቶች 775 ሜጋ ዋት፤ እንዲሁም ከስድስት የንፋስ ፕሮጀክቶች 825 ሜጋ ዋት ለማመንጨት ታቅዷል፡፡ በግል ባለሀብቱ ለሚገነቡ ፕሮጀክቶች የሚያስፈልገው የካፒታል መጠንም 1 ነጥብ 5 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር እንደሚደርስ ተገምቷል:: እነዚህ ሁሉ እንዳሉ ሆነው አሁን ያለው በሀገሪቱ በሥራ ላይ ያለው የታሪፍ ምጣኔ አነስተኛ መሆንና የኦፕሬሽንና የጥገና ወጪን ለመሸፈን አለማሰቻሉ በትግበራው ላይ እንቅፋት ከመሆን ባለፈ የግል አልሚውን ለመሳብ አስቸጋሪ እንዳይሆን ስጋት ፈጥሯል፡፡ “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 05 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+1

እያደገ የመጣውን የኃይል ፍላጎት ለማሟላት በርካታ ሥራዎች መሥራት ይገባል ……….///……….. የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ዕድገት ተከትሎ እየመጣ ያለውን ከፍተኛ የኃይል ፍላጎት ለማሟላት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በርካታ ሥራዎች እየሰራ ይገኛል፡፡ በዓመት በአማካይ በ6 በመቶ እያደገ የሚሄደውን የከፍተኛ ኃይል ተጠቃሚ የኢንዱስትሪ ደንበኞችን ፍላጐት ለማሟላት የኃይል አቅርቦቱ አሁን ካለበት 3 ሺህ 271 ጊጋ ዋት ሰዓት ወደ 5 ሺህ 205 ጊጋ ዋት ሰዓት ማሳደግ ያስፈልጋል፡፡ በተመሳሳይ በየዓመቱ በአማካይ በ20 በመቶ እንደሚያድግ የተተነበየውን የመካከለኛና ዝቅተኛ ኢንዱስትሪዎች የኃይል አጠቃቀም አሁን ካለበት 739 ጊጋ ዋት ሰዓት ወደ 3 ሺህ 285 ጊጋ ዋት ሰዓት ማድረስ ይገባል፡፡ ከዚህ ባልተናነሰ በአገልግሎቱ ዘርፉ ውስጥ የሚታዩ የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራትና አስተማማኝነት ችግሮችን በማስወገድ፣ የኃይል መቆራረጥ ድግግሞሽና ቆይታና በማስተካከል የደንበኞችን እርካታ ማሻሻል ትኩረት ሊሰጠው የሚገባ ጉዳይ ሆኖ ተገኝቷል፡፡ እንደ ሀገር የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ግንባታ፣ ኦፕሬሽንና ጥገና ወጪን ታሳበ ያደረገ ታሪፍ ቢተገበር አገልግሎቱን ለማሻሻልና ተደራሽነቱን ለማሳደግ እንደሚያግዝ ይታመናል፡፡ “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 04 ቀን 2016 ዓ.ም