ru
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Открыть в Telegram

📈 Аналитический обзор Telegram-канала EEP Communication

Канал EEP Communication (@eepcommuication) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 15 695 подписчиков, занимая 8 017 место в категории Технологии и приложения и 2 152 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 15 695 подписчиков.

Согласно последним данным от 31 августа, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 142, а за последние 24 часа — 2, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 30.85%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 16.42% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 4 842 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 2 578 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 10.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
EEP Communication

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 01 сентября, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Технологии и приложения.

15 695
Подписчики
+224 часа
+237 дней
+14230 день
Архив постов
"ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ብዙ መከራዎችን እና ፈተናዎችን አልፈን አንድነታችን ያጸናንበት ነው" - አብርሃም በላይ (ዶ/ር) ........///....... ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ብዙ ፈተናዎችን በማለፍ  ወደ ብልጽግና የምናደርገው የጋራ ጉዞ ቃል ኪዳንናችን ያጸናንበት ነው ሲሉ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ አብርሃም በላይ (ዶ/ር) ገለጹ። ሰብሳቢው አብርሃም በላይ (ዶ/ር) የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ መጠናቀቁንና ለምርቃት መብቃቱን አስመልክቶ ተቋሙ ባዘጋጀው የምስጋና መርሐ ግብር ላይ በግንባታው ሂደት አስተዋጽዖ ለነበራቸው በሙሉ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። በመልዕክታቸውም የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ጠንካራ አመራርን፣ ሙያዊ አስተዳደርን፣ ከመንግሥት፣ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና ከጠቅላላ የፕሮጀክቱ ሠራተኞች ጽኑ ቁርጠኝነትን የጠየቀ መሆኑን ገልጸዋል። ግድቡ ኢትዮጵያዊያን ተባበርን ከሠራን ቀጣይ የልማትና የብልጽግና እጣ ፈንታችንን በራሳችን የምንወስን መሆናችንን ያረጋገጥንበት ነው ብለዋል፡፡ የግድቡ ግንባታ ከሲቪልና ኤሌክትሮ መካኒካል ሥራዎች ጀምሮ የሚመነጨውን ኃይል ወደ ብሔራዊ የኃይል ቋት እስከማስገባት ድረስ የገጠሙትን ውስብስብ ተግዳሮቶች ተሻግሮ ለምርቃት መብቃቱ ለኢትዮጵያዊያን ትልቅ የመቻል ማሳያ መሆኑንም ነው ያብራሩት። ኢትዮጵያውያን የማይጠናቀቅ የሚመስለውን ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት ከፕሮጀክት በላይ ደምቆ እንዲጠናቀቅ ማድረጋቸው አዲስ ጅማሮ እንጂ የመጨረሻ እንዳልሆነም ተናግረዋል። ከዚህ በፊት የነበሩ ትውልዶች ሁሉ አስበው  ያልቻሉትን እና አቅደው ያላሳኩትን ፕሮጀክት ማጠናቀቅ መቻሉን የጠቀሱት ዶ/ር አብርሃም ይህን ያሳካው ያሁኑ ትውልድ ዕድለኛ መሆኑን አስረድተዋል። ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የተባበረ ርዕይ እና ቆራጥነት በብሔራዊም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ አስደናቂ ውጤቶችን ማስመዝገብ እንደምንችል ያሳየንበት ነው ሲሉ  ገልጸውታል። በምስጋና መርሃ ግብሩ ላይ  ለዚህ ታላቅ ስኬት የህይወት መስዋዕትነት የከፈሉትን ጨምሮ በየደረጃው አስተዋጽኦ ላደረጉ አመራሮችና ሠራተኞች፣ የተቋሙ የሥራ አመራር ቦርድ አባላት፣ ልዩ ልዩ ተቋማት እና ለመላው ኢትዮጵያዊያን ታላቅ ምስጋና አቅርበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መስከረም  27 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+8

‎በግድቡ ግንባታ ላይ አበርክቶ ለነበራቸው ተቋማትና ግለሰቦች እውቅና ተሰጠ ‎…....///…..... ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ  ወቅት የተለያየ አበርክቶ  ለነበራቸው ተቋማትና ግለሰቦች እውቅና ሰጠ። መርሐ ግብሩ የተከናወነው  የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በስኬት  በመጠናቀቁ አስተዋጽዖ የነበራቸው አካላትን ለማመስገን ነው። የእውቅና ምስክር ወረቀቱንና የተዘጋጀውን ሜዳሊያ የሰጡት የዕለቱ የክብር እንግዳና የተቋሙ የሥራ አመራር ቦርድ ስብሳቢ አብርሃም በላይ (ዶ/ር) እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ናቸው። በዕውቅና መርሃ ግብሩ ላይ የኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት፣ የፌዴሬሽን ም/ቤት እና  ሁሉም ክልሎችና ከተማ መስተዳድሮችን ጨምሮ እንዲሁም ለተለያዩ የሥራ ተቋራጮች፣ ተቋማትና ግለሰቦች እውቅናና ተሰጥቷል። በተጨማሪም በግድቡ ዙሪያ የሚገኙ እና የታላቁን የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ በቅርበት በመደገፍ እና ትብብር በማድረግ በስኬት እንዲጠናቀቅ ምቹ ሁኔታ ለፈጠሩ  የአካባቢው የመስተዳድር አካላት እና ተቋማት እውቅናና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል። ‎💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” ‎ ‎📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric ‎📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication ‎📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia ‎📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power ‎📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ‎📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ‎📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ‎መስከረም 27 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+4

ግድቡ የትውልዱ የአንድነትና የአይበገሬነት ማሳያ እንዲሁም የማንሰራራት ዘመናችን ጅማሮ ትዕምርት ነው -ኢንጂነር አሸብር ባልቻ …..///……  የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅ የሁሉም ኢትዮጵያውያን የአንድነትና የአይበገሬነት ማሳያ እንዲሁም የማንሰራራት ዘመናችን ጅማሮ ትዕምርት መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅን አስመልክቶ ያዘጋጀው የምስጋና ፕሮግራም  የተቋሙ ሥራ አመራር ቦርድ፣ ሠራተኞችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም ተካሂዷል፡፡ በፕሮግራሙ ላይ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጅነር አሸብር ባልቻ እንደገለጹት ዓለም ሰው ሰራሽ አስተውሎትን ጨምሮ በቴክኖሎጂ ርቆ በሄደበት በ21ኛው ክፍለ ዘመን ከ45 በመቶ በላይ የሆነው የኢትዮጵያ ሕዝብ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽ አይደለም፡፡ ዓባይ ወንዝ ላይ ከ86 በመቶ በላይ ድርሻ ያላት ኢትዮጵያ በድህነቷና በዲፕሎማሲያዊ ጫናዎች ምክንያት ድንበር ተሻጋሪ ወንዞቿን ተጠቅማ የኃይል አቅርቦቷን በማሟላት ከድህነትና ኋላ ቀርነት ለመላቀቅ ሳትችል መቆየቷን አስታውሰዋል፡፡ መንግስትም የተፈጥሮ ሀብታችንን በመጠቀም ችግሩን በዘላቂነት ለመቅረፍ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያንን በማስተባበር ግድቡን በራስ አቅም ገንብቶ ማጠናቀቁን ገልጸዋል፡፡ ‎የግድቡ ምርቃት ኢትዮጵያውያን በርካታ ችግሮች ቢኖሩብንም በትብብርና በሕብረት ከተነሳን የተፈጥሮ ሀብታችንን ተጠቅመን ከመልማትና የብርሃን ምንጭ ከመሆን የሚያግደን አንዳች ምድራዊ ኃይል አለመኖሩን በተግባር ለሁሉም ያሳየ ብሔራዊ ፕሮጀክት መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ በተጨማሪም የሕዳሴ ግድብ ኢትዮጵያውያን ትልልቅ ፕሮጀክቶችን መጀመር ብቻ ሳይሆን መጨረስ እንደምንችል ማሳየት የቻለ እንዲሁም ጨለማ እና ድህነትን ለማፍረስ የተሰነዘረ ሀገራዊ መዶሻ ነውም ብለዋል። የግድቡ ግንባታ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ ተቋሙ የግንባታውን ሂደቱን በመምራት፣ የኃይል ማመንጫ ተርባይኖችን በመትከል፣ ከግድቡ የመነጨውን ኃይል ከሀገሪቱ የኃይል ቋት ጋር በማስተሳሰር ኃላፊነቱን በብቃት ሲወጣ መቆየቱን አስታውሰዋል። ህዳሴ እንደ ሀገር የነበረውን ከ5 ሺህ ሜጋ ዋት ያልበለጠውን ኃይል የማምረት አቅም ወደ 10 ሺህ ሜጋ ዋት በላይ እንዳደረሰው የጠቆሙት ኢንጂነር አሸብር ይህም ተቋሙ የኃይል ተደራሽነት ሽፋኑን አሁን ካለበት 54 በመቶ ወደ 78 በመቶ ለማሳደግ የያዘውን ዕቅድ ለማሳካት እና በየዓመቱ በአማካይ በአስር በመቶ እያደገ የሚገኘውን የኃይል ፍላጎት ለመመለስ እንደሚያስችለው ተናግረዋል፡፡ ተቋሙ የአፍሪካ የታዳሽ ኃይል ማዕከል በመሆን የአፍሪካ አህጉርን በመሰረተ ልማት የማስተሳሰር አጀንዳ 2063 ዕቅድን ለማሳካት የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ተጠናቆ ወደ ሥራ መግባት ከፍተኛ ድርሻ ያበረክታል ብለዋል። የግድቡ መጠናቀቅ ኃይል ከማመንጨት ባሻገር ግብርናን በማዘመን፣ ቱሪዝምን በማስፋፋት፣ የአሳ ሀብትን በማሳደግ፣ ዲፒሎማሲያዊ አቅምንና ብሔራዊ አንድነትን በማጎልበት በኩል ከፍተኛ ሚና ይኖረዋል ያሉት ዋና ሥራ አስፈጻሚው ከፕሮጀክቱ በቀጣይ መሰል ትውልድ ተሻጋሪ ትልልቅ ሀገራዊ ፕሮጀክቶች በራስ አቅም ገንብቶ መጨረስ የሚያስችል ዕውቀትና ልምድ የተገኘበትም መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡ የኢትዮጵያዊነትና የኢትዮጵያ ከፍታ ለሚታይበት እንዲሁም የትውልዱ ብሔራዊ ፕሮጀክት ለሆነው የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ የኃይል ማመንጫ ግድብ መጠናቀቅ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ግለሰቦችና ተቋማት እንዲሁም መላው የኢትዮጵያ ሕዝብና መንግስት በተቋሙ ሥም ምስጋና አቅርበዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መስከረም 27 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+8

‎የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የምስጋና ፕሮግራም በአደዋ መታሰቢያ ሙዚየም እየተካሄደ ነው ‎….///…. ‎የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅን አስመልክቶ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ያዘጋጀው የምስጋና ፕሮግራም በአድዋ መታሰቢያ ሙዚየም እየተካሄደ ነው፡፡ ‎ ‎በፕሮግራሙ ላይ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ የተቋሙ ሥራ አመራር ቦርድና ሠራተኞች እንዲሁም የተለያዩ ተቋማት ተወካዮችን ጨምሮ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡ ‎ ‎በመርሃ ግብሩ ላይ የግድቡን የግንባታ ሂደት የሚያሳይ ዶክመንተሪ የሚቀርብ ሲሆን በግድብ ግንባታው አስተዋጽኦ ለነበራቸው ግለሰቦችና ተቋማትም እውቅናና ሽልማት ይሰጣል፡፡ ‎ ‎ፕሮግራሙ በተመሳሳይ ዕለት በሁሉም የኃይል ማመንጫዎች፣ በሪጅኖች እና ማከፋፈያ ጣቢያዎችም በድምቀት እየተከበረ ይገኛል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መስከረም 27 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+5

የተቋሙ አመራርና ሠራተኞች የአድዋ መታሰቢያ ሙዚየምን ጎበኙ .......///........ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መጠናቀቅን አስመልክቶ ባዘጋጀው የምስጋና መርሀ ግብር ላይ ለመታደም የተገኙ አመራሮችና ሠራተኞች የአድዋ መታሰቢያ ሙዚየምን ጎበኝተዋል። በተቋሙ የትራንሚሽን ቢዝነስ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አንዱዓለም ሲዓ በጉብኝቱ ወቅት እንደገለጹት የአድዋ ድል ሀገርን ለማጽናት ሲባል ለነጻነት የተከፈለ የደም ዋጋና የጽናት ተምሳሌት የሆነ የጥቁር ህዝቦች ቀንዲል ነው። ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ደግሞ ኢትዮጵያውያን ለሁሉን አቀፍ ዕድገት በአንድነትና በትብብር በመቆም የገነቡት የጽናት ተምሳሌት ፕሮጀክት ነው። አድዋ ሀገርን ለማጽናት የተደረገ ተጋድሎ ሲሆን ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ደግሞ በኢነርጂ ዘርፉ ራስን ከመቻል ባሻገር ለጎረቤት ሀገራት ኃይል በማቅረብ ቀጣናዊ ትስስርን ለማጠናከር የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል። ሠራተኞች በበኩላቸው ዳግማዊ አድዋ በሆነው ታላቁ የህዳሴ ግድብ ግንባታ ላይ  የተለያየ ድርሻ ያላቸው አመራርና ሠራተኞች የአድዋን መታሠቢያ መጎብኘታቸው ልዩ ስሜት እንደፈጠረባቸው ተናግረዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መስከረም  27 ቀን 2018 ዓ.ም 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መስከረም 27 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+8

የኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት ክቡር አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ በሕዝብ ተወካዮች እና የፌዴሬሽን ምክር ቤቶች የ2018 ዓ.ም የሥራ ዘመን የጋራ የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ላይ የኃይል ዘርፉን በተመለከተ ካነሷቸው ነጥቦች መካከል ….///…. 📌 በአዲሱ ዓመት መባቻ የበርካታ ዓመታት የቁጭታችንና የጥረታችን ውጤት የሆነውን የታላቁ ኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ያስመረቅንበት ይህ ዘመን በታሪካችን ውስጥ በጉልህ የሚወሳ አዲስ ምዕራፍ ነው፡፡ 📌 በ2018 የኃይል ተደራሽነትን ለማሳደግ መንግስት ትኩረት ሰጥቶ ይሰራል፡፡ 📌 የሕብረተሰቡን የኃይል ፍላጎት ለማሟላት የሚያስችሉ የታዳሽ ኃይል ፕሮጀክቶች በቀጣይ ዓመታት በበቂ ይገነባሉ፡፡ 📌 ለውጭ ንግድ(ኤክስፖርት) የሚበቃ የኤሌክትሪክ አቅርቦት በማሳደግ ለቀጣናዊ የኢኮኖሚ ትስስር መሰረት ይጣላል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መስከረም 26 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+2

የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ ....///.... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልኢንቫሮሜንታሊስት I (ዲ1)' ሶሾሎጂስት I (ዲ1) እናኦኮፔሽናል ኸልዝ እና ሴፍቲ ኦፊሰር I (ዲ1) የስራ መደቦች ላይ ሰራተኞ
+4
የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ ....///.... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልኢንቫሮሜንታሊስት I (ዲ1)' ሶሾሎጂስት I (ዲ1) እናኦኮፔሽናል ኸልዝ እና ሴፍቲ ኦፊሰር I (ዲ1) የስራ መደቦች ላይ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር በነሀሴ 01 ቀን 2017 ዓ.ም የውጭ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወቃል፡፡ በዚሁ መሰረት ከላይ ስማችሁ የተገለጸ አመልካቾችሰኞ ጥቅምት 03 ቀን 2018 ዓ.ም ጠዋት 2፡30 ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ  ኮተቤ ብረታ ብረት ፊት ለፊት በሚገኘው በዋናው መ/ቤት መሰብሰቢያ አዳራሽ የጽሁፍ ፈተና የሚሰጥ በመሆኑ ለፈተና እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 28 ቀን 2017 ዓ.ም

ተቋማቱን ውጤታማ ለማድረግ የዩኒቨርሲቲ ኢንዱስትሪ ትስስርን ማጠናከር ይገባል ….///….. ብቃት ያለው ባለሙያ በማፍራት ተቋማቱን ውጤታማ ለማድረግ የዩኒቨርሲቲና ኢንዱስትሪ ትስስሩን ማጠናከር እንደሚያስፈልግ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የጅማ ዩኒቨርሲቲ የሥራ ኃላፊዎች ተናግረዋል። የሥራ ኃላፊዎቹ በሁለቱ ተቋማት መካከል ያለው የትብብር ሥራ ተጠናክሮ በሚቀጥልበት ጉዳዮች ላይ ውይይት አካሂደዋል። የጅማ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ጀማል አባፊጣ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት የተቋማትን ውጤታማነት ለማረጋገጥ የዩኒቨርሲቲና የኢንዱስትሪ ግንኙነትን በማጠናከር በትብብር መስራት ያስፈልጋል ብለዋል። ዩኒቨርሲቲው በኃይል ልማት ዘርፉ ላይ የራሱን አስተዋፅኦ ለማበርከት ከተቋሙ ጋር አሁን ካለው የትብብር ሥራ በተጨማሪ በሌሎች የተለያዩ የሥራ መስኮች ላይ በጋራ የመስራት ፍላጎት እንዳለው ጠቁመዋል። በኃይል ልማት ዘርፉ ወቅቱን የዋጀ የስልጠናና የትምህርት ሥርዓት ለመዘርጋት ተቋማቱ ከፕሮግራም ቀረፃ ጀምሮ በጋራ መስራት ይጠበቅባቸዋል ብለዋል። በዩኒቨርሲቲው የአስተዳደር እና ልማት ምክትል ፕሬዚዳንት ፕሮፌሰር ገመቺስ ፊሌ ዩኒቨርስቲያቸው በውሃ ምህንድስና፣ በግድብ ክትትልና ደህንነት፣ በአካባቢያዊ ተፅዕኖ ግምገማ ጥናት፣ በአቅም ግንባታና ስልጠና፣ በማህበረሰብ ልማትና ግንኙነት እንዲሁም በቴክኖሎጂና ፈጠራ ጉዳዮች ለይ ከተቋሙ ጋር በትብብር የመስራት ፍላጎት እንዳለው አብራርተዋል። በተጨማሪም አካባቢን መልሶ በማቋቋም፣  ከዘርፋ ጋር በተገናኙ ፖሊሲዎች ቀረፃና አስተዳደር ፣ በሥራ ፈጠራና ኢኖቬሽን ማዕከል /ልህቀት/ማቋቋም፣ በሥራ ላይ ልምምድና የተማሪዎች የፕሮጀክት ሥራ፣ በአውደ ጥናት፣ ኮንፈረንስ እና መሰል ጉዳዮች ላይ  በጋራ ለመስራት ፍላጎት እንዳለውም ምክትል ፕሬዚዳንቱ ገልፀዋል። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጄነሬሽን ቢዝነስ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ኤፍሬም ወ/ኪዳን ሁለቱ ተቋማት በትብብር የሚሰሩባቸው በርካታ ጉዳዮች እንዳሉ ገልፀው ትብብሩ ተቋሙ የያዘውን ሀገራዊና ቀጣናዊ ዕቅድ ለማሳካት ሚናው የጎላ ነው ብለዋል። የሁለቱን ተቋማት ባለሙያዎች ለማብቃት የዩኒቨርሲቲ ኢንዱስትሪ ትስስሩን በተግባር ማጠናከር እንደሚገባና ለዚህም ተቋሙ ዝግጁ መሆኑን አንስተዋል። በተቋሙ የኮርፖሬት ፋይናንስና ሀብት አስተዳደር ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ደመረ አሰፋ በበኩላቸው ተቋሙ ከዩኒቨርሲቲው ጋር አብሮ ለመስራት ፈቃደኛ  መሆኑን አረጋግጠው ይሁንና ትብብሩ ቀጣይነት ያለው እንዲሆን፤ ከቀረቡ ሀሳቦች መካከል በጋራ ሊሰራባቸው የሚገቡ ጉዳዮች በተቋሙ በዝርዝር ተለይተው እንደሚቀርቡ አስታውቀዋል። ከዚህ በፊት ከተለያዩ ተቋማት ጋር በተለዩ ጉዳዮች በትብብር ለመስራት ዕቅድ ቢያዝም ስምምነቶች ከወረቀት ውጭ በተጠናከረ መልኩ በአግባቡ ባለመተግበራቸው የሚፈለገው ውጤት እንዳይመጣ አድርጎታል ያሉት ደግሞ የኮይሻ ማመንጫ ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ አቶ መብራቱ ተሾመ ናቸው። ስለሆነም የትብብር ሥራው ውጤታማ እንዲሆን ሁለቱ ተቋማት በጋራ የሚሰሩባቸውን ጉዳዮች በግልፅ በማስቀመጥ ተግባራዊነቱ ክትትል የሚደረግበት የጋራ ሥርዓት መዘርጋት ይኖርባቸዋል ብለዋል። የኢትዮ ፓወር አካዳሚ ዳይሬክተር ወንድወሰን ካሳ (ዶ/ር) ተቋሙ በዘርፋ ብቁ ባለሙያዎችን ለማፍራት የሚያስችለውን ኢንስቲትዩት ለማቋቋም እየሰራ ነው ብለዋል። ባለሙያዎቹ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሚሆኑበትን የብቃት ማረጋገጫ እንዲያገኙ የሚያስችል የትምህርት ፕሮግራም እንዲከፈት ተቋሙ ፍላጎት እንዳለው የተናገሩት ዳይሬክተሩ ይህ ወደተግባር እንድለወጥ የትብብር ሥራው ወሳኝ ስለመሆኑም አስታውቀዋል። ሁለቱ ተቋማት በትብብር የመስራት ፍላጎትቻውን ለማጠናከር የያዙትን ዕቅድ ተግባራዊ ለማድረግሥራውን የሚከታተሉ የሥራ ኃላፊዎችን መድበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication to 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መስከረም 26 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+8

ከተረዳዳንና ከተባበርን የማይሳካ ነገር እንደማይኖር በኮይሻ አካባቢ የተገኘው ውጤት ማሳያ ነው ...............//.......... ከተረዳዳንና ከተባበርን የማይሳካ ነገር እንደማይኖር በጎፋ ዞን መለኮዛ ወረዳና አካባቢው የተገነቡ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች ማሳያ ናቸው ሲሉ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ኢንጂነር ዳግማዊ አየለ ገለፁ። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና ዊ ቢውልድ ኩባንያ የጋራ ትብብር በጎፋ ዞን መለኮዛ ወረዳ ባንካ ቀበሌ ባንካ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት ላይ የተገነቡ የመማሪያ ክፍሎች በዛሬው እለት ተመርቀዋል። ምርቃቱ ላይ የተገኙት የጎፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ኢንጂነር ዳግማዊ አየለ እንደተናገሩት አካባቢው የበርካታ ተፈጥሮ  ፀጋዎች ባለቤት ቢሆንም ባለው የመሰረተ ልማት እጥረት ምክንያት ጥቅም ላይ ሳይውል ቆይቷል። ይሁንና የኮይሻ ፕሮጀክት በአካባቢው ከመጣ በኋላ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የዊ ቢውልድ ኩባንያ ባከናወኗቸው የመሠረተ ልማት ግንባታዎች የአካባቢው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት እየተነቃቃ ይገኛል ብለዋል። በዛሬው እለት ለምረቃ የበቁ የመማሪያ ክፍሎች በአካባቢው ያለውን የትምህርት ተደራሽነት በማስፋት በእውቀት የታነፀ ትውልድ ለመፍጠር ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወቱም ተናግረዋል። እንደ ዋና አስተዳዳሪው ገለፃ ፕሮጀክቱ ከመሰረተ ልማት ግንባታ ሥራዎች ባለፈ በዞኑ በሚከሰቱ የተፈጥሮ አደጋዎች ላይ ሰብዓዊ ድጋፎችን በማድረግ የማህበረሰብ አለኝታነቱን እያሳየ ይገኛል። ተቋማቱ እያደረጉ ላሉት ሁሉን አቀፍ ድጋፍም አመስግነዋል። "ከተባበርንና በጋራ ከቆምን ሀገር መለወጥ እንደምንችል በአካባቢው ከተገኘው ውጤት ተገንዝበናል" ያሉት ኢንጂነር ዳግማዊ ሀገሪቱ ያላትን ፀጋ ጥቅም ላይ ለማዋል ሁሉም በአንድነትና በትብብር መስራት እንደሚጠበቅበትም አስገንዝበዋል።  በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮይሻ ፕሮጀክት የአካባቢያዊና ማህበራዊ ጉዳዮች ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ግዛቸው ደሳለኝ ፕሮጀክቱ በአካባቢው መተግበር ከጀመረ ወዲህ ከ1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር በላይ የሚገመቱ የጤና፣ የውሃ፣ የመንገድ፣ የትምህርት ወዘተ መሰረተ ልማቶችን በመገንባት የአካባቢውን ማህበረሰብ ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን አስታውሰዋል። በጅማ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን ሲከታተሉ በቆዩ የፕሮጀክቱ ሠራተኞች እየተመራ ለምረቃ የበቁት የትምህርት መማሪያ ክፍሎች ተቋሙ ለማህበራዊ ኃላፊነት ሥራዎች የሰጠውን ትኩረት የሚያሳይ መሆኑን ተናግረዋል። በትምህርት ቤቱ ላይ ለተገነቡ አራት የመማሪያ ክፍሎች እና አንድ የአስተዳደር ቢሮ 17 ነጥብ 6  ሚሊዮን ብር  ወጭ መደረጉን ጠቁመዋል። የተማሪዎቹ አስተባባሪ አቶ ኤሊያስ ኤካ በበኩላቸው ተማሪዎች በአካባቢው ያለውን የትምህርት ተደራሽነት እጥረት ከግንዛቤ በማስገባት የትምህርቱ አካል የሆነውን የማህበራዊ ኃላፊነት ሥራ በትምህርት ዘርፍ ላይ ማድረጋቸውን ገልፀዋል። ለመማሪያ ክፋሎቹ ግንባታ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልና የኮይሻ ፕሮጀክት ሥራ ተቋራጩ ዊ ቢውልድ ኩባንያ በገንዘብ፣ በጥሬ ዕቃ እና በሰው ሀይል ድጋፍ ማድረጋቸውን ጠቁመው ለተደረገላቸው ድጋፍም ተቋማቱን አመስግነዋል። በዕለቱ ለትምህርት ቤቱ ግንባታ አስተዋፅኦ ላደረጉ አካላት እውቅና ተሰጥቷል። በምረቃ ሥነ- ሥርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ተወካይና የጄነሬሽን ቢዝነስ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ኤፍሬም ወ/ኪዳን እና የጅማ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት  ጀማል አባፊጣ(ዶ/ር) ጨምሮ የተቋሙ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የዩኒቨርሲቲው የሴኔት አባላት፣ የአካባቢው የመስተዳደር አካላት፣ የአካባቢው የሀገር ሽማግሌዎችና የትምህርት ቤቱ ማህበረሰብ አካላት ተገኝተዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication to 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መስከረም 25 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+9

ተመራቂዎች ያገኙትን ዕውቀት ከልምዳቸው ጋር አቀናጅተው በአግባቡ ሥራ ላይ ማዋል ይጠበቅባቸዋል- ኢንጅነር ኤፍሬም ወ/ኪዳን ሠራተኞች በትምህርት ቆይታቸው ያገኙትን ዕውቀት ወደ ተግባር በመለወጥ ሀገራዊ ግደታቸውን በአግባቡ መወጣት እንደሚጠበቅባቸው በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጄነሬሽን ቢዝነስ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አሳሰቡ። ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚው ኢንጂነር ኤፍሬም ወ/ ኪዳን ለተመራቂ የኮይሻ ፕሮጀክት ሠራተኞች የእንኳን ደሥ አላችሁ መልዕክት ባስተላለፉበት ወቅት እንደገለጹት ተቋሙ የአፍሪካ የታዳሽ ኃይል ማዕከል የመሆን ራዕዩንና የያዘውን የስትራቴጂክ ዕቅድ ለማሳካት ብቃት ያለው የሰው ኃይል ያስፈልጋል። በዚህም ተቋሙ ከአጫጭር ስልጠናዎች በተጨማሪ ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በመተባበር የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎችንና የፕሮጀክት ሠራተኞችን አቅም ለማሳደግ ትኩረት ሰጥቶት እየሰራ ይገኛል ብለዋል። የጅማ ዩኒቨርሲቲ በተቋሙ የሰው ኃይል ልማት ላይ የበኩሉን አሻራ እያሳረፈ ከሚገኙ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት መካከል አንዱ መሆኑን አስታውሰው በአሁኑ ወቅትም ተቋሙ ከዩኒቨርሲቲው ጋር ያለውን ትበብር በማጠናከር የኮይሻ ፕሮጀክት ሠራተኞች ከመደበኛ ሥራቸው ጎን ለጎን የሁለተኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን በሥራ ቦታቸው ላይ ሆነው  እንዲከታተሉ በማድረግ ማስመረቅ ተችሏል ብለዋል። የትምህርት መርሃ ግብሩ የሥራ ልምድን ከንድፈ-ሀሳብ ባጣመረ መልኩ በመሠጠቱ  ለተቋሙ ብቃት ያለው ሠራተኛ በማፍራት በኩል ከፍተኛ ሚና እንዳለው የተናገሩት ኢንጂነር ኤፍሬም ተማሪዎች ከፕሮጀክቱ ጋር ተያያዥነት ባላቸው ጉዳዮች ላይ የሰሩዋቸው የመመረቂያ ጽሑፎች ለተቋሙ በግብዓትነት እንደሚያገለግሉም አስታውቀዋል ። ዩኒቨርስቲው የተቋሙን ሠራተኞች አቅም ለማሳደግ እያደረገ ላውን ጥረት እና የዛሬ ተመራቂዎች ለስኬት እንዲበቁ ላበረከተው አስተዋፅኦ አመስግነው ተቋሙ በቀጣይ በሰው ኃይል ልማትና በሌሎች መስኮች ከዩኒቨርስቲው ጋር የሚኖረውን ትብብር አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ኢንጂነር ኤፍሬም አረጋግጠዋል። በቀጣይ በተለያዩ የሥራ ቦታዎች ያሉ ሠራተኞችን አቅም በማሳደግ ብቁ የሰው ኃይል ለማፍራት የትምህርት እድሉ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል። ተመራቂዎቹ በትምህርት ቆይታቸው ያገኙትን ዕውቀት ከልምዳቸው ጋር በማቀናጀት በፕሮጀክቱ ቆይታም ሆነ ወደፊት  በሚሰማሩበት የሥራ መስክ የተጣለባቸውን  ኃላፊነት በአግባቡ እንዲወጡ  ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚው አሳስበዋል። የጅማ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ጀማል አባፊጣ (ዶ/ር) በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲው  "በማህበረሰብ ውስጥ ነን" በሚል መርሁ  የማህበረሰብ አገልግሎቶቹን እያከናወነ  እንደሚገኝ ገልፀው ለፕሮጀክቱ ሠራተኞች የተሰጠው የትምህርት ፕሮግራም ዩኒቨርሲቲው የማህበረሰቡ መሆኑን በተግባር ማረጋገጥ የተቻለበት ነው ብለዋል። ኮይሻ ፕሮጀክት የሀገራችን የማንሰራራት ያረጋግጣሉ ብሎ ዩኒቨርሲቲው ከለያቸው ፕሮጀክቶች አንዱ በመሆኑ የሠራተኞቹን አቅም ለማሳደግ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። በዚህም የፕሮጀክቱን ሠራተኞች ከሥራቸው ጎን ለጎን በሥራ ቦታቸው ላይ ሄዶ በማስተማር ማስመረቅ መቻሉን አስረድተው በዘርፉ ብቃት ያለው ባለሙያ ለማፍራት ዩኒቨርሲቲው ከተቋሙ ጋር ያለውን ትብብር አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል። ከተመራቂ ሠራተኞች መካከል ኤሊያስ ኤካ እና ተወዳጅ በቀለ  እንደተናገሩት ትምህርቱ  በመደበኛ ሥራቸው ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ሳያሳድርባቸው አጠናቀው በመመረቃቸው ደስታቸውን ገልፀዋል፡፡ በትምህርት ቆይታቸው ለሥራቸው ግብዓት የሚሆኑ ተጨማሪ እውቀቶችን እንዳገኙ የገለፁት ተመራቂዎቹ  የተከታተሉት የትምህርት መስከ በሥራቸው ላይ ውጤታማ  እንዲሆኑ እንደሚረዳቸውም አስረድተዋል፡፡ በሥራ ቦታቸው ላይ ሆነው ትምህርቱን እንዲከታተሉ ተቋሙና ፕሮጀክቱ ላደረጉላቸው ድጋፎች አመስግነው  የተጣለባቸውን ኃላፊነት በአግባቡ ለመወጣት በቁርጠኝነት እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication to 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መስከረም 25 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+3

photo content
+9