ru
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Открыть в Telegram

📈 Аналитический обзор Telegram-канала EEP Communication

Канал EEP Communication (@eepcommuication) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 15 537 подписчиков, занимая 8 329 место в категории Технологии и приложения и 2 179 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 15 537 подписчиков.

Согласно последним данным от 03 июля, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 31, а за последние 24 часа — -1, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 26.36%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 16.21% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 4 097 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 2 520 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 10.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
EEP Communication

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 04 июля, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Технологии и приложения.

15 537
Подписчики
-124 часа
-167 дней
+3130 день
Архив постов
ክለቡ ፕሪሚየር ሊጉን ከተቀላቀለ 10 ሚሊዮን ብር ሽልማት ይጠብቀዋል …….///……… የኢትዮ- ኤሌክትሪክ ስፖርት ክለብ የወንዶች እግር ኳስ ቡድን ፕሪሚየር ሊጉን ከተቀላቀለ 10 ሚሊዮን ብር ሽልማት እንደሚሰጠው ቃል ተገባለት ፡፡ የስፖርት ክለቡ የቦርድ ሊቀመንበር አቶ ጫላ አማን ሒልተን ሆቴል በተከናወነው የማበረታቻ መርሀግብር ላይ እንደገለፁት የወንዶች እግር ኳስ ቡድን የመጀመሪያውን ዙር ከምድቡ አንደኛ ሆኖ መጨረሱ የሚበረታታ ነው፡፡ በውድድር ዓመቱ ክለቡ የተሻለ ውጤት በማስመዝገብ ፕሪሚየር ሊጉን የሚቀላቀል ከሆነ 10 ሚሊዮን ብር በስጦታ እንደሚበረከትለት የቦርድ ሊቀመንበሩ ቃል ገብተዋል። የክለቡ የቦርድ አባል አቶ መንግሥቱ አባይነህ በበኩላቸው የክለቡን የቀደመ ዝና ለመመለስ የአደረጃጀት እና የአሠራር ማዘመን ስራዎች መከናወናቸውን ተናግረዋል። እንደ አቶ መንግሥቱ ገለፃ የአሠራርና የአደረጃጀት ስራዎች በመሠራታቸው አበረታች ውጤቶች እየተመዘገቡ መሆኑን ገልፀዋል። ሒልተን ሆቴል በተከናወነው የማበረታቻ መርሀግብር የክለቡ የቦርድ አባላት፣ የክለቡ ተጫዋቾች እና አሰልጣኞች፣ ጥሪ የተደረገላቸው የስፖርት ቤተሰቦች እና የሚዲያ አካላት ተገኝተዋል። የኢትዮ ኤሌክትሪክ የወንዶች እግር ኳስ ቡድን ለሁለተኛው ዙር ጨዋታ የቅድመ ዝግጅት ልምምዱን ጎፋ በሚገኘው የክለቡ ሜዳ በመስራት ላይ ይገኛል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 18 ቀን 2014 ዓ.ም

photo content
+1

በጥራት አስተዳደር ሥርዓት ትግበራ የውስጥ ኦዲት ሥልጠና በመሰጠት ላይ ነው ……..///………. ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከተለያዩ የሥራ ክፍሎች ለተውጣጡ ሠራተኞች በጥራት አስተዳደርና ኦዲት ሥርዓ
በጥራት አስተዳደር ሥርዓት ትግበራ የውስጥ ኦዲት ሥልጠና በመሰጠት ላይ ነው ……..///………. ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከተለያዩ የሥራ ክፍሎች ለተውጣጡ ሠራተኞች በጥራት አስተዳደርና ኦዲት ሥርዓት ትግበራ ያተኮረ ሥልጠና በመሰጠት ላይ ይገኛል፡፡ ሥልጠናው የተቋሙን የጥራት አስተዳደር ሥርዓት አፈፃፀም ኦዲት የሚያደርጉ ባለሙያዎችን ለማብቃት እንደሚረዳ በተቋሙ የኳሊቲ አሹራንስ ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ረድኤት ምናለ ገልፀዋል፡፡ ኃላፊዋ እንደገለፁት አጠቃላይ የጥራት አስተዳደር ሥርዓትና የኦዲት መርሆዎችን በመተግበር የተቋሙን የአገልግሎት ጥራት ለማሳደግ፣ ወጪዎችን ለመቀነስ እና ምርታማነትን ከፍ ለማድረግ የሥልጠናው መሰጠት የጎላ ድርሻ ይኖረዋል። የሥልጠናው ተሳታፊዎች የጥራት አስተዳደር ሥርዓት ጽንሰ ሐሳቦችን በመረዳት የተቋሙን ዓመታዊ የሥራ አፈፃፀም ኦዲት ያደርጋሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ወ/ሮ ረድኤት ገልፀዋል። ሥልጠናው ኬ.ፒ.ኤም. ጂ (KPMG) በተሰኘ የተቋሙ የጥራት አስተዳደር ሥርዓት ትግበራ አማካሪ አማካኝነት እየተሰጠ ሲሆን ከዛሬ ጀምሮ እስከ ጥር 20 ቀን 2014 ዓ.ም ድረስ ይቆያል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 16 ቀን 2014 ዓ.ም

በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የምዕራብ ሪጅን ትራንስሚሽንና ሰብስቴሽን ጥገናና ኦፕሬሽን ዳይሬክተር የነበሩት አቶ ቶማስ መለሰ ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው በ 34 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም ተ
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የምዕራብ ሪጅን ትራንስሚሽንና ሰብስቴሽን ጥገናና ኦፕሬሽን ዳይሬክተር የነበሩት አቶ ቶማስ መለሰ ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው በ 34 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም ተለይተዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራርና ሠራተኞች በአቶ ቶማስ ህልፈት የተሰማቸውን ሀዘን እየገለፁ ለቤተሰቦቹና ለወዳጅ ዘመዶቹ መጽናናትን ይመኛሉ።

እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀት በዓል በሰላም አደረሳችሁ
እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀት በዓል በሰላም አደረሳችሁ

በወልድያ ከተማ ተቋርጦ የነበረው የኤሌክትሪክ ኃይል ዳግም አገልግሎት መስጠት ጀምሯል። ጉዳት የደረሰባቸውን የሥርጭት ትራንስፎርመሮች በመቀየር፣ የተሰረቁ ትራንስፎርመሮችን እና ሌሎች ግብዓቶችን በመተ
+2
በወልድያ ከተማ ተቋርጦ የነበረው የኤሌክትሪክ ኃይል ዳግም አገልግሎት መስጠት ጀምሯል። ጉዳት የደረሰባቸውን የሥርጭት ትራንስፎርመሮች በመቀየር፣ የተሰረቁ ትራንስፎርመሮችን እና ሌሎች ግብዓቶችን በመተካት አገልግሎቱ እንዲጀምር መደረጉን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኀይል የከፍተኛ ኤሌክትሪክ መስመር የቴክኒክ ድጋፍ ኃላፊ አቶ ተስፋዬ መንግሥቱ ተናግረዋል። አሸባሪው የትግራይ ወራሪ ቡድን ወልድያ ከተማን ጨምሮ በዞኑ ባሉ ከተሞች የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ላይ ያደረሰው ጉዳት እና ውድመት ከፍተኛ ቢሆንም በተቋሙ የሥራ ኃላፊዎች እና በሠራተኞቹ ከፍተኛ ርብርብ ወደ ሥራ ማስገባት መቻሉን ኀላፊው ገልጸዋል። በቀጣይም ሌሎች አካባቢዎችን አገልግሎት እንዲያገኙ ለማድረግ እየተሠራ መሆኑንም ኃላፊው መግለፃቸውን የአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ከስፍራው ዘግቧል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 07 ቀን 2014 ዓ.ም

+1
የጥገና ሥራውን በተመለከተ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የወልዲያ ዲስትሪክት ኃላፊ - አቶ ሽመልስ ወ/ሰማያት እና በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመር ጥገና የቴክኒክ ድጋፍ ኃላፊ - አቶ ተስፋዬ መንግስቱ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የቴክኒክ ባለሙያዎች ከደሴ እስከ ወልዲያ ሲያከናወኑ የቆዩትን ጉዳት የደረሰባቸውን የኤሌክትሪክ መስመሮች ጥገና ካጠናቀቁ በኋላ ደስታ
+6
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የቴክኒክ ባለሙያዎች ከደሴ እስከ ወልዲያ ሲያከናወኑ የቆዩትን ጉዳት የደረሰባቸውን የኤሌክትሪክ መስመሮች ጥገና ካጠናቀቁ በኋላ ደስታቸውን በከፍተኛ ስሜት ገልፀዋል።

ከደሴ እስከ ወልዲያ ያሉት ከተሞች ኤሌክትሪክ አግኝተዋል ….…….///……….. ከደሴ እስከ ወልዲያ ሲከናወን የቆየው ጉዳት የደረሰባቸውን የኤሌክትሪክ መስመሮች የመጠገን ሥራ ትናንት ምሽት ተጠናቆ ከተሞቹ ዛሬ ከ 10:05 ጀምሮ ኃይል አግኝተዋል። ጥገናው ትናንት ምሽት ቢጠናቀቅም መስመሩ በሚያልፍበት አካባቢ በደሴ እና በሀይቅ መካከል እንዲሁም መርሳ አካባቢ የበቀለ ዛፍ ከመስመሩ ጋር ተገናኝቶ ባለመቆረጡ የተነሳ ኤሌክትሪክ ማገናኘት አልተቻለም ነበር። ይሁንና ዛሬ ዛፎቹ በመቆረጣቸውና ኃይል ለመስጠት የሚያግድ ነገር ባለመኖሩ ከተሞቹ ኤሌክትሪክ ማግኘት ችለዋል። በተያያዘ ዜና ለወልዲያ ከተማና አካባቢው አገልግሎት ሲሰጥ ቆይቶ የተዘረፈው ተንቀሳቃሽ ማከፋፈያ ጣቢያ የሚሰጠውን አገልግሎት የሚተካ ዘላቂ ሥራ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጀምሯል። የተጀመረው ሥራ በቀጣዮቹ ከአራት እስከ አምስት ወራት ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ ከፍተኛ ኃይል ለመስጠት የሚያስችል ነው። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 07 ቀን 2014 ዓ.ም

የደሴ - ወልዲያ የኤሌክትሪክ መስመር ጥገና እየተገባደደ ነው፤ ፍተሻው በስኬት ከተጠናቀቀ እስከ ወልዲያ ድረስ ያሉት ከተሞች በሰዓታት ውስጥ ኤሌክትሪክ ሊያገኙ ይችላል ….…….///……….. ከደሴ እስከ ወልዲያ ሲከናወን የቆየው ጉዳት የደረሰባቸውን የኤሌክትሪክ መስመሮች የመጠገን ሥራ እየተገባደደ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመር ጥገና የቴክኒክ ድጋፍ ኃላፊ ገልፀዋል፡፡ ኃላፊው አቶ ተስፋዬ መንግስቱ እንዳስታወቁት እስከዛሬ ድረስ በተከናወነው ጥገና ጉዳት የደረሰበት መስመርና ምሰሶ ከ97 በመቶ በላይ ተጠናቋል፡፡ ቀሪ ሥራዎችን በርብርብ በማጠናቀቅ እስከ ወልዲያ ድረስ ያሉት ከተሞች ማምሻውን አልያም እስከ ነገ እኩለ ቀን ድረስ መብራት እንዲያገኙ ይደረጋል ብለዋል፡፡ እንደ ኃላፊው ገለፃ ከደሴ እስከ ወልዲያ ባሉት ከተሞች የሚያልፉት የሥርጭት መስመሮችና ምሰሶዎች በጦርነቱ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸውና አንዳንዶቹም ያረጁ በመሆናቸው ከፍተኛ ጥገና የሚፈልጉ ናቸው፡፡ በመሆኑም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጥገና ባለሙያዎች ተቋሙ ከሰጣቸው ተልዕኮ በተጨማሪ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎትን የጥገና ባለሙያዎች በማገዝ ሥራው እንዲፈጥን ለማድረግ የቅንጅት ሥራ መሥራታቸውን ተናግረዋል፡፡ የጥገና ባለሙያዎቹ እገዛ ባያደርጉ ኖሮ ከተሞቹን ለማገናኘት የሚደረገው ጥረት ተጨማሪ ቀናትን ይፈልግ እንደነበር ገልፀዋል፡፡ ሽብርተኛው የህወኃት ቡድን ለወልዲያና አካባቢው አገልግሎት ሲሰጥ የነበረውን ተንቀሳቃሽ የማከፋፈያ ጣቢያ ሙሉ በሙሉ ነቅሎ በመውሰድ ወልዲያና በዙሪያው ያሉ ከተሞች ኤሌክትሪክ እንዳያገኙ ማድረጉን መግለፃችን ይታወሳል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 06 ቀን 2014 ዓ.ም

photo content
+6

photo content

ተቋሙ በህልውና ዘመቻው ለተሳተፉ የዘማች ቤተሰቦች ድጋፍ አደረገ ……////……. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አሸባሪው የህወኃት ቡድን የአማራና አፋር ክልሎችን በወረራ በያዘበት ወቅት የተደረገውን ሃገራዊ ጥሪ ተቀብለው በህልውና ዘመቻው ለተሳተፉ የተቋሙ ሠራተኛ ቤተሰቦች የበዓል መዋያ የጥሬ ገንዘብ ድጋፍ አድርጓል፡፡ የተቋሙ የድጋፍ አሰባሳቢ ኮሚቴ የሀገሪቱን ሉዓላዊነት ለማስጠበቅ ለራሳቸው ህይወት ሳይሳሱና ከቤተሰባቸው ተለይተው በህልዉና ዘመቻው ላይ ለተሳተፉ የተቋሙ ሠራተኞች ምስጋና አቅርቧል፡፡ በህልውና ዘመቻው በመሳተፍ ላይ ለሚገኙ 8 የተቋሙ ሠራተኛ ቤተሰቦች ከተቋሙ ሠራተኞች በማሰባሰብ ለእያንዳንዳቸው የ10 ሺህ ብር ድጋፍ እንዲሰጥ በመወሰን ገንዘቡን በአዲስ አበባ ለሚገኙ የዘማች ቤተሰቦች አስረክቧል፡፡ በተመሳሳይም በክልሎች ለሚገኙ የዘማች ቤተሰቦች በአካውንታቸው ገንዘቡ ገቢ መደረጉንም አስታውቋል፡፡ ተቋሙ ያደረገው ድጋፍ የስራ ባልደረቦቻቸው ከቤተሰቦቻቸው ተለይተው በሀገራዊ ግዳጅ ላይ ቢገኙም ለቤተሰባቸው ያለውን አጋርነት ለማሳየትና መሆኑን ገልጿል፡፡ ሁሉም ሰው ለሀገር ህልውና ዘብ ለቆሙት የዘማች ቤተሰቦች የሚያስፈልጋቸውን ነገር በማድረግ አለኝታነቱን እንዲያሳይ ኮሚቴው ጥሪ አቅርቧል፡፡ ድጋፍ ከተደረገላቸው የዘማች ቤተሰቦች መካከል ወ/ሮ ጽጌ ነብሮ እንደተናገሩት ባለቤታቸው የሀገሪቱን ሉዓላዊነት ለማስጠበቅ ከጎናቸው ቢለይም የሥራ ባልደረቦቹ ባሳዩት አጋርነት ደስተኛ መሆናቸውን በመግለጽ ተቋሙ ላደረገው ድጋፍም ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡ ወ/ሮ ሀና ብርሃኑ በበኩላቸው ባለቤታቸው ሀገሩን ከሁሉ በማስቀደም ሲዘምት ተቋሙ ከጎናችን በመቆሙ ደስተኛ ነን ብለዋል፡፡ ተቋሙ ከዚህ በፊት ለመከላከያ ሰራዊት ከሠራተኞቹ ደመወዝ 50 ሚሊዮን እና ከተቋሙ ካዝና 25 ሚሊዮን ብር እንዲሁም በአማራ ክልል በጦርነቱ ምክንያት ለተፈናቀሉ የህብረተሰብ ክፍሎች የሚውል የዓይነት እና የጥሬ ገንዘብ ድጋፍ ማድረጉ ይታወሳል፡፡ በአፋር ክልል በጦርነቱ ምክንያት ለተፈናቀሉ የህብረተሰብ ክፍሎች የሚውል የተለያዩ ድጋፎችን ለማስረከብ ዝግጅት መጠናቀቁንም ለማወቅ ተችሏል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 27 ቀን 2014 ዓ/ም

photo content
+2

በግብዓት አቅርቦት ችግር ተቀዛቅዞ የቆየው ፕሮጀክት እየተፋጠነ ነው ……///…….. በግንባታ ግብዓት አቅርቦት ችግር ምክንያት ተቀዛቅዞ የነበረው የደጀን- ደብረ ማርቆስ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት ግንባታ መቀጠሉን የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጁ አስታወቁ፡፡ የማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክቱ የሳይት አስተባባሪ አቶ እንዳለ ላቀው እንዳስታወቁት የመስመሩ የግንባታ ሥራ ጥር 2013 ዓ.ም በይፋ የተጀመረ ቢሆንም በግንባታ ዕቃዎች አቅርቦት ምክንያት ከመጋቢት 2013 ዓ.ም ጀምሮ የግንባታ ስራው ተቋርጦ ቆይቷል፡፡ እንደ አቶ እንዳለ ገለጻ ለማስተላለፊያ መስመሩ ምሶሶ መትከያ የሚያገለግሉ ጉድጓዶች ተቆፍረው የነበረ ቢሆንም በአቅርቦት ችግር ምክንያት በወቅቱ ሊተከሉ ባለመቻላቸው ተደፍነዋል፡፡ በአሁኑ ሰዓት የአቅርቦት ችግሩ በመፈታቱ የተደፈኑ ጉድጓዶችን ዳግም የመቆፈር ስራ ተጀምሯል ብለዋል፡፡ ማስተላለፊያ መስመሩ 48 ነጥብ 6 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ሲሆን 111 ምሶሶዎች እንደሚተከሉ እና ሥራው 15 በመቶ ላይ መድረሱን አቶ እንዳለ ተናግረዋል፡፡ በተያያዘ ዜና ከሰኔ 2013 ዓ.ም ጀምሮ በክረምት መግባትና በግንባታ ግብዓት አቅርቦት ችግር የተነሳ የግንባታ ስራው ሙሉ በሙሉ ተቋርጦ የቆየው የደጀን የማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት ግንባታ በይፋ መቀጠሉን የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጁ አስታውቀዋል፡፡ ሥራ አስኪያጁ አቶ ሚሊዮን ታምራት እንደገለፁት አጋጥሞ የነበረው የሲሚንቶ እና የብረት የአቅርቦት ችግር መፍትሄ በማግኘቱ ከጥቅምት 2014 ዓ.ም መጨረሻ ጀምሮ የፕሮጀክቱ የግንባታ ሥራ እንዲቀጥል ተደርጓል፡፡ የማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቱ አንድ ባለ 63 ሜጋ ቮልት አምፔርና አንድ ባለ 50 ሜጋ ቮልት አምፔር ትራንስፎርመሮች የሚገጠሙለት ሲሆን አምስት ባለ 15 እና አምስት ባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች ይኖሩታል፡፡ ፕሮጀክቱን በ14 ወራት ውስጥ ለማጠናቀቅ ዕቅድ ተይዞለት የነበረ ቢሆንም በአሁኑ ሰዓት የማከፋፈያ ጣቢያው ግንባታ 32 በመቶ ላይ ይገኛል፡፡ የግንባታ ስራው በአቅርቦት ችግር ምክንያት በታሰበው መልኩ መከናወን ባለመቻሉ ቀሪ ስራዎችን እስከ ህዳር 2015 ዓ.ም ለማጠናቀቅ ተጨማሪ ጊዜ መሰጠቱን ፕሮጀክት ቢሮው አስታውቋል፡፡ ከ1 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት የተያዘለትን ፕሮጀክት የግንባታ ስራ የተቋሙ የትራንስሚሽን ሰብስቴሽን ኮንስትራክሽን የራስ ኃይል ቢሮ እንዲሁም የማማከር ስራውን የተቋሙ ኢንጅነሪንግ ቢሮ በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡ ፕሮጀክቱ ለደጀን ከተማና በአካባቢው ለሚገኙ ቀበሌዎችና ከተማዎች እንዲሁም በአካባቢው ለተገነቡና በመገንባት ላይ ለሚገኙ የተለያዩ ኢንዱስትሪዎች የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ በአካባቢው የሚስተዋለውን የኃይል አቅርቦት ችግር ይፈታል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 25 ቀን 2014 ዓ/ም

photo content
+3

ስለተቋማችን በመገናኛ ብዙኃን የወጡ ዘገባዎች ተቋማቱ ለተፈናቀሉ ወገኖች በጥሬ ገንዘብና በአይነት 20 ሚሊየን ብር ድጋፍ አደረጉ አዲስ ሚዲያ ኔትወርክ (ኤ ኤም ኤን) ታህሳስ 22/2014 የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽንና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል በአማራ ክልል ለተፈናቀሉ ወገኖች በጥሬ ገንዘብና በአይነት 20 ሚሊየን ብር ድጋፍ አደረጉ። ተቋማቱ ድጋፉን ለአማራ ክልል አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ኮሚሽን ዛሬ አስረክበዋል። ከድጋፉ መካከል በአይነት 13 ሚሊዮን ብር ያበረከተው ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ሲሆን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል ደግሞ 4 ሚሊየን ብር ግምት ያለው የአይነትና በጥሬ ገንዘብ 3 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አድርጓል። በተቋማቱ የተደረገው አይነት ድጋፍ የህፃናት አልሚ ምግብ፣ የምግብ ዘይት፣ አልባሳትን ያካተተ ነው። የክልሉ አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ማስተባበሪያ ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ዘላለም ልጃለም በርክክብ ስነ ስርአቱ ላይ እንዳሉት፤- የሽብር ቡድኑ ወረራ ፈፅሞባቸው በነበሩ አካባቢዎች በርካታ ዜጎች የአስቸኳይ የምግብ እርዳታ ይፈልጋሉ። በሽብር ቡድኑ ወራራ 2 ነጥብ 3 ሚሊዮን ዜጎች መፈናቀላቸውንና 9 ነጥብ 1 ሚሊዮን ዜጎች ደግሞ ባሉበት ሆነው ለምግብ እህል እጥረት የተጋለጡ መሆናቸውን ኢዜአ ዘግቧል። ኢትዮጵያን በዘላቂነት እናልማ! የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ! ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ! የአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ መረጃዎችን በማህበራዊ ሚዲያዎቻችን ባሉበት ሆነው ይከታተሉ፤ በዮቱብ https://www.youtube.com/channel/UC9lAZ1l0TvJG65R-QeCDHkg በፌስቡክ https://www.facebook.com/Amnaddistv በቴሌግራም https://t.me/addismedianetwork በትዊተር https://twitter.com/AmnAddis

ስለተቋማችን በመገናኛ ብዙኃን የወጡ ዘገባዎች https://www.facebook.com/EBCzena/posts/5171186062913228

ስለተቋማችን በመገናኛ ብዙኃን የወጡ ዘገባዎች https://www.amharaweb.com/የኢትዮጵያ-ኤሌክትሪክ-ኀይል-ለተፈናቀሉ/