ru
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Открыть в Telegram

📈 Аналитический обзор Telegram-канала EEP Communication

Канал EEP Communication (@eepcommuication) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 15 544 подписчиков, занимая 8 357 место в категории Технологии и приложения и 2 176 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 15 544 подписчиков.

Согласно последним данным от 01 июля, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 22, а за последние 24 часа — 4, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 25.24%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 16.50% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 3 921 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 2 563 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 9.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
EEP Communication

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 02 июля, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Технологии и приложения.

15 544
Подписчики
+424 часа
-357 дней
+2230 день
Архив постов
ጠንካራ ተቋማዊ ባህል መገንባቱ የተቋሙን ስትራቴጂክ ግብ ለማሳካት ያግዛል ........ ///......... ጠንካራ ተቋማዊ ባህል መገንባት የተቋሙን ውጤታማነት ለማሳደግና ስትራቴጂክ ግቦቹን ለማሳካት እንደሚያግዘው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ፡፡ የኮርፖሬት ቢዝነስ ባህልን ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ትኩረቱን ያደረገ ሥልጠና ለተቋሙ የሥራ ኃላፊዎች በሒልተን ሆቴል ተሰጥቷል፡፡ በስልጠናው ላይ የተገኙት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አሸብር ባልቻ እንዳስታወቁት የተቋሙን ስትራቴጅክ ግብ ለማሳካትና ውጤታማነት ለማሳደግ የኮርፖሬት ቢዝነስ ባህልን ማጠናከርና መገንባት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡  ሥልጠናውን ለአዘጋጀው አካል ምስጋና ያቀረቡት ዋና ሥራ አስፈፃሚው ሥልጠናው ጠንካራና ግልጽ የሆነ ተቋማዊ ባህል ለመገንባት እንደሚያግዝ ተናግረዋል፡፡ ከሥልጠናው የተገኘውን ልምድና ዕውቀት ተጠቅሞ ተቋማዊ ባህሎችን ማጠናከርና ክፍተቶችን መሙላት እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡ በተቋሙ የሠው ኃይል ሥራ አስፈጻሚ አቶ አታላይ አበበ በበኩላቸው ሥልጠናው በተቋሙ የተሻለ ተቋማዊ ባህል እንዲኖር ለማድረግ እና የኮርፖሬት ቢዝነስ ባህልና የሠራተኛውን ተሳትፎ ለማሳደግ እንደሚያግዝ ተናግረዋል፡፡ እንደ አቶ አታላይ ገለጻ ለአንድ ተቋም ውጤታማነት እና ግቡን ለማሳከት ጠንካራ ተቋማዊ ባህል መኖር፣ የተቋም ስትራቴጂካዊ ግብና አወቃቀር እንዲሁም የሰው ሀብት ከፍተኛ ሚና ይኖራቸዋል፡፡ በተቋሙ ውስጥ ያሉ ባህሎችን ለማወቅ የዳሰሳ ጥናት መደረጉን የጠቆሙት አቶ አታላይ ስልጠናው በጥናቱ የተለዩ ክፍተቶችን መሰረት በማድረግ መዘጋጀቱን ገልጸዋል፡፡ በተቋሙ የስድስት ወር ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ ላይ የተነሱ ሀሳቦች ለስልጠናው መሰጠት መነሻ እንደሆነም ሥራ አስፈጻሚው ተናግረዋል፡፡ ተቋሙ መልካም የሚባሉና መሻሻል ያለባቸው ባህሎች እንዳሉት ያነሱት አቶ አታላይ ጠንካራ ባህሎችን ለማስቀጠልና ክፍተቶችን ለማስተካከል ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡ ለተቋማዊ ባህል ግንባታ የሥራ መሪዎች ድርሻ የጎላ ቢሆንም ሠራተኛውም የበኩሉን ሚና እንዲወጣ አስገንዝበዋል፡፡ የኮርፖሬት ቢዝነስ የተላበሰ ተቋማዊ ባህል ለመገንባት የሁሉንም ሠራተኛ ተሳትፎ የሚጠይቅ በመሆኑ በቀጣይ ከሠራተኞች ጋር የተለያዩ ውይይቶች  እንደሚካሄዱም ነው ሥራ አስፈጻሚው የተናገሩት፡፡ ስልጠናውን የሰጡት በጀርመኑ ፍራንክፈርት የፋይናንስና አስተዳደር ት/ቤት (Frankfurt school of finance and management, Germany) ከፍተኛ አሰልጣኝና አማካሪ የሆኑት ጃኪ ካሲኩ እንደተናገሩት በአንድ ተቋም ላይ ተቋማዊ ባህልን ለማጠናከር ትብብርን እና ኮርፖሬሽንን መገንባት፣ የሠራተኛውን አቅም ማሳደግ፣ ውስብስበ የሆኑ አሰራሮችን ማስተካከል፣ ለሥራ የሚያገለግሉ ግብዓቶችን ማሟላትና በጋራ መጠቀም፣ እንዲሁም የአጋርና ባለድርሻ አካላትን ሃሳብና አስተያየትን በግብዓትነት መጠቀም ይገባል፡፡ ለጠንካራ ተቋማዊ ባህል ግንባታ የአመራሩ ድርሻ ከፍተኛ በመሆኑ አመራሩ ብቃት ያለው እና በስነ-ምግባሩ የታነጸ እንዲሆን እንዲሁም ውሳኔዎችን ምክንያታዊ በሆነ መልኩ መስጠት እንዲችል ተቋማዊ ባህልን ለማስረጽ የተለያዩ የኮሙዩኒኬሽን ዘዴዎችን መጠቀም አንደሚገባ አሰልጣኟ ተናግረዋል፡፡ ከመንግስት የልማት ድርጅቶች ተቆጣጣሪ ባለስልጣን ጋር በመተባበር በተዘጋጀውና ለሁለት ቀናት በቆየው ስልጠና ላይ የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አሸብር ባልቻን ጨምሮ የዘርፍ ሥራ አስፈጻሚዎች፣ የመምሪያ ዳይሬክተሮች እና አንዳንድ የቢሮ ሥራ አስኪያጆች ተሳትፈዋል፡፡ “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 28 ቀን 2015 ዓ.ም

እንኳን ለ127ኛው የአድዋ ድል በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን!
እንኳን ለ127ኛው የአድዋ ድል በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን!

ለማከፋፈያ ጣቢያ ኃላፊዎችና ለሪጅን ቢሮ ሥራ አስኪያጆች የሥራ አመራር ስልጠና ተሰጠ ……..///…….. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን የስራ ዘርፍ
ለማከፋፈያ ጣቢያ ኃላፊዎችና ለሪጅን ቢሮ ሥራ አስኪያጆች የሥራ አመራር ስልጠና ተሰጠ ……..///…….. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን የስራ ዘርፍ ሥር ለሚገኙ የሪጅን እና የማከፋፈያ ጣቢያ ኃላፊዎች የሥራ አመራር ክህሎት ላይ ያተኮረ ስልጠና ተሰጠ፡፡ የማዕከላዊ ሪጅን መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ጋሻው እንድርያስ እንደገለፁት ሥልጠናው የማከፋፈያ ጣቢያ ኃላፊዎችን የአመራር ብቃት ለማሳደግና ከጊዜ ወደ ጊዜ እጅግ እየሰፉና እያደገ የመጣውን ሠራተኛ ለማስተዳደር የአመራር አቅም ለመገንባት ነው፡፡ ሥልጠናው የተቋሙ የሥራ መሪዎች መፅሀፈ ዕድ የተብራራበት፣ የአገልጋይነት አመራር ጽንሰሀሳብ የተተነተነበት እና ሁሉም ሠራተኞች መዳረሻ ጎላቸውን ለማሳካት ማድረግ ምን መስራት እንደሚጠበቅባቸው ማሳየት የተቻለበት መሆኑን አስረድተዋል፡፡ የሥራ አመራር ክህሎት ሥልጠናው አዲስ የሪጅኖች አደረጃጀት መፈጠሩን ተከትሎ ሥራዎችን በተገቢው ሪፎርም ለማቀላጠፍ በተቋሙ የሰው ሀብት ተቋማዊ ትራንስፎርሜሽን ቢሮ መሰጠቱን ገልፀዋል፡፡ በስልጠናው ላይ 18 የማዕከላዊ ሪጅን 3 የሰብስቴሽን ጣቢያ ኃላፊዎች እና 5 የሪጅን ቢሮ ኃላፊዎች ተሳትፈዋል፡፡ “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 22 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content

ተቋሙ የሚያከናውናቸው ግንባታዎች ገቢ ማመንጨት እስኪጀምሩ ድረስ ባንኩ በአጋርነቱ እንደሚቀጥል ገለፀ ........///....... የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሚያደርገውን የፋይናንስ ብድር አቅርቦት አጠናክሮ እንደሚቀጥል  አስታወቀ። በባንኩ የፐብሊክና ኢንስቲትዩሽናል ባንኪንግ ዳይሬክተር ወ/ሮ መልካም በለጠ እንደገለፁት ሁለቱ ተቋማት ከ17 ዓመት በላይ የዘለቀ ጠንካራ አጋርነት አላቸው። ባንኩ በሀገሪቱ ውስጥ ለሚገኙ ለሁሉም የመንግሥት ተቋማት ከ80 በመቶ በላይ የብድር አገልግሎት መስጠቱንና ከዚህ ውስጥ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከ50 በመቶ በላይ ድርሻ እንዳለው ገልፀዋል። ባንኩ እስካሁን ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከ400 ቢሊየን ብር በላይ የብድር አገልግሎት ማቅረቡን ወ/ሮ መልካም ተናግረዋል። ከዚህ ውስጥ ከ191 ቢሊየን ብር በላይ የሚሆነው ብድር ወደ ዕዳና ሀብት አስተዳደር ኮርፖሬሽን እንዲዛወር መደረጉን አስታውሰዋል።  የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በኢነርጂ ዘርፍ ለሀገሪቱ ዕድገት ትልቅ ሚና ያላቸውን ግንባታዎች እያከናወነ እንደሚገኝ የጠቀሱት ወ/ሮ መልካም ባንኩ በቀጣይ ሊገነቡ ለታቀዱ ግዙፍ የኃይል መሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች የብድር አቅርቦቱን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል። እንደ ዳይሬክተሯ ገለፃ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሚያከናውናቸው ግንባታዎች ወደ ገቢ መቀየር  እስኪጀምሩ ድረስ ባንኩ በአጋርነቱ ይቀጥላልም  ብለዋል። በኃይል ልማት ዘርፉ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለዓመታት የዘለቀ ድጋፍ ሲያደርግ መቆየቱን የገለፁት ወ/ሮ መልካም ባንኩ ሀገራዊ ግዴታውን እየተወጣ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል። ባንኩ ለአራት የተቀናጀ የግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ፓርኮች የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ ከአራት ቢሊየን ብር በላይ የፋይናንስ ብድር ማመቻቸቱን የጠቀሱት ዳይሬክተሯ በቂና አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት ተደራሽ መሆኑ ባለሃብቶች መዋዕለ ንዋያቸውን በማፍሰስ የኢንዱስትሪ ዘርፉን ለማሳደግ ዕድል ይፈጥርላቸዋል ሲሉ ተናግረዋል። በቀጣይም የሁለቱ ተቋማት የትብብርና የቅንጅት ሥራ ይበልጥ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ያረጋገጡት ዳይሬክተሯ ተቋሙ ወደፊት በሚያገኛቸው ገቢዎች የብድሮቹን የመክፈል አቅም እንደሚኖረው እምነታቸውን ገልፀዋል። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ  www.eep.com.et የካቲት 22 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+4

ለግብርና ማቀነባበሪያ ፓርኮች የኃይል አቅርቦት ግንባታ የሚውል የብድር ስምምነት ተፈረመ ....///...... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ፓርኮች የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት የሚውል የብድር ስምምነት ተፈራረሙ። ስምምነቱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ እና የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የፐብሊክና ኢኒስቲትዩሽናል ባንኪንግ ዳይሬክተር ወ/ሮ መልካም በለጠ ተፈራርመዋል፡፡ ስምምነቱ በዋናነት ለአራቱ የግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ፓርኮች የኃይል ማከፋፈያ እና ማስተላለፊያ መስመር ግንባታ ለማካሔድ የብድር አቅርቦት ላይ ያተኮረ ነው። የብድር አቅርቦቱ የቡሬ፣ ቡልቡላ፣ ይርጋለም እና ባአከር የተቀናጀ የግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ፓርኮች ከዋናው የግሪድ ቋት ጋር የሚያገናኛቸውን የኃይል ማከፋፈያ እና ማስተላለፊያ መስመር ለመገንባት የሚያስችል እንደሆነም ነው በስምምነቱ ላይ የተገለፀው። ባንኩ ለአራቱ የግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ፖርኮች የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ ከአራት ቢሊየን ብር በላይ የፋይናንስ ብድር ማመቻቸቱ ተገልጿል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና በተወሰነ ድርሻ የገንዘብ ሚኒስቴር ለግንባታ የሚውለውን የፋይናንስ ብድር በ10 ዓመት ውስጥ ከፍለው ለማጠናቀቅ የሚችሉበት የብድር ውል ስምምነት ነው። ለአምራች ኢንዱስትሪዎች እየቀረበ ያለው የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት በሒደት እየተሻሻለ መምጣቱ የተጠቆመ ሲሆን ባንኩ ለተቋሙ ያቀረበው ብድር ሊገነቡ ለታሰቡት ፕሮጀክቶች ማስፈፀሚያ ወሳኝ መሆኑተገልጿል። ተቋሙ በሦስት ዓመት ውስጥ ለአራቱ የተቀናጀ የግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ፓርኮች የኃይል አቅርቦት የሚውሉ መሠረተ ልማቶችን ገንብቶ ለማጠናቀቅ ማቀዱን ለማወቅ ተችሏል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ለአምራች ኢንዱስትሪ ማህበራት አዘጋጅቶት በነበረው የውይይት መድረክ ላይ ለቡሬ፣ ለቡልቡላ፣ ለይርጋለምና ለባአከር የተቀናጀ የግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ የኢንዱስትሪ ፓርኮች የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ እንደሚሰራ መናገራቸው ይታወሳል። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 21 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+1

ተቋሙ ለሁለት ፕሮጀክቶች ከ50 ሚሊየን ብር በላይ ግምት ያለው የማማከር አገልግሎት እየሰጠ ነው …….///……. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኢንጂነሪንግ ዘርፍ ከ50 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ገንዘብ ለሁለት ፕሮጀክቶች የማማከር አገልግሎት ለመስጠት መስማማቱን በዘርፉ የሱፐርቪዥን እና ኮንትራት አስተዳደር መምሪያ አስታወቀ፡፡ የመምሪያው ዳይሬክተሩ አቶ ግርማ ዘለቀ እንደገለፁት በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት በሞጆ ከተማ አቅራቢያ ለሚገነባው የገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን የኃይል አቅርቦት ፕሮጀክት የማማከር አገልግሎት ለመስጠት ስምምነት ተፈርሞ የካቲት 9 ቀን 2015 ዓ.ም. በይፋ ሥራ ጀምሯል፡፡ የኃይል አቅርቦት ፕሮጀክቱን በ18 ወራት ውስጥ ለማጠናቀቅ ውል መገባቱን ተናግረዋል፡፡ የማማከር አገልግሎቱ የጨረታ ዶክመንት ማዘጋጀት፣ የክትትልና ቁጥጥር ሥራን ማከናወን እና የሥራ ማጠናቀቂያ ሪፖርት ዝግጅት ማጠናቀቅ እንደሚያካትት ዳይሬክተሩ አብራርተዋል፡፡ አቶ ግርማ እንዳስረዱት ተቋሙ በተመሳሳይ ከአባይ ሲሚንቶ ፋብሪካ ጋር ከ6 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ የሚያስገኝ የማማከር አገልግሎት ስምምነት ተፈራርሞ ወደ ሥራ ገብቷል፡፡ “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 15 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+2

ባለፉት ስድስት ወራት አምስት የኃይል ማመንጫ ጣቢያቢዎች ከመቶ ፐርስንት በላይ ኃይል አመንጭተዋል …….///……. በ2015 በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ስድስት ወራት አምስት የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ከዕቅዳቸው በላይ ኃይል ማመንጨታቸውን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጫ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ አስታወቀ፡፡ በዘርፉ የፕላኒንግ ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ጥሩወርቅ ሽፈራው እንደገለፁት ፊንጫ፣ አዋሽ 3ኛ፣ ጢስ አባይ 2ኛ ፣አዳማ 1 እና አዳማ 2 የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ከታቀደላቸው በላይ ኃይል ማመንጨታቸውን ሥራ አስኪያጇ አስረድተዋል፡፡ ጣቢያዎቹ ከታቀደላቸው በላይ ኃይል ማመንጨት የቻሉት በኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ላይ ሳምንታዊ፤ ወርሃዊና ዓመታዊ የኢንስፔክሽን እና ጥገና ሥራዎች በዕቅዱ መሰረት መከናወን በመቻሉ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡ እንደ ስራ አስኪያጇ ገለፃ በኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች የቅደመ መከላከል የጥገና ሥራዎች በመከናወናቸው እና ጣቢያዎች ኃይል ለማመንጨት ዝግጁ በመደረጋቸው ከታቀደው በላይ ኃይል ማመንጨት ተችሏል፡፡ በዘንድሮ የክረምት ወቅት ኃይል ማመንጫ ግድቦቹ በበጀት ዓመቱ የታቀደውን ኢነርጂ ለማሳካት የተቻሉት በቂ ውሃ እንዲይዙ በመደረጉና የውሃ አስተዳደር ሥራዎች በተሳካ ሁኔታ በመሰራታቸው ነው ብለዋል፡፡ በ6 ወራት ውስጥ የነበረውን የንፋስ ፍጥነት ታሳቢ ያደረገ ሥራ በመሰራቱ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎቹ ዕቅዳቸውን ማሳካት እንደቻሉ ተናግረዋል፡፡ “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 14 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+1

በምስራቅ አፍሪካ የዓለም ባንክ ቀጣናዊ ቢሮ የሥራ ኃላፊዎች የአዘዞ - ጭልጋ ፕሮጀክትን ጎበኙ .......///…… በምስራቅ አፍሪካ የዓለም ባንክ ቀጣናዊ ቢሮ የሥራ ኃላፊዎች የአዘዞ - ጭልጋ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ እና ማስተላለፊያ መስመር ግንባታ ያለበትን ደረጃ መጎብኘታቸውን ፕሮጀክት ጽ/ቤቱ አስታውቋል። በምስራቅ አፍሪካ የዓለም ባንክ ቀጣና ዳይሬክተር ሚስተር ኦስማን ዲዮን የተመራው የልዑካን ቡድን የፕሮጀክቱ ግንባታ ያለበትን ደረጃ በመስክ በመገኘት ገምግሟል። የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ አቶ አሸናፊ ሙሉብርሃን እንደገለፁት የጉብኝቱ ዋና ዓላማ በዓለም ባንክ የፋይናንስ ድጋፍ የሚገነባውን ፕሮጀክት ለመገምገም ነው። በፕሮጀክቱ ዕቃዎች ላይ ተደጋጋሚ የሆኑ የስርቆት ወንጀሎች መፈፀማቸውና የከተማ አስተዳደሩ ለካሳ ጥያቄዎች አፋጣኝ መፍትሔ መስጠት ባለመቻሉ በግንባታው ሂደት ላይ አሉታዊ ጫና ማሳደሩን ለልዑካን ቡድኑ አስረድተዋል። አጠቃላይ የፕሮጀክቱ ግንባታ ከ90 በመቶ በላይ መድረሱን የገለፁት ሥራ አስኪያጁ ሥራውን በተያዘለት ጊዜ ለመጨረስ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገልፀዋል። በዓለም ባንክ የምስራቅ አፍሪካ ቀጣና ዳይሬክተር ሚስተር ኦስማን ዲዮን በበኩላቸው ፕሮጀክቱ በተያዘው በጀት፣ የጊዜ ሰሌዳና የጥራት ደረጃ እንዲጠናቀቅ ያሳሰቡ ሲሆን ከወሰን ማስከበር ጋር ተያይዘው ለሚነሱ ጉዳዮች የከተማ አስተዳደሩ አፋጣኝ ምላሽ እንዲሰጥ ጠይቀዋል። በኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ላይ ከሚተከሉት 105 የብረት ምሰሶዎች መካከል የ81 ምሰሶዎች ተከላ እና የኮንዳክተር ዝርጋታ መጠናቀቁን ለማወቅ ተችሏል። የጭልጋ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ የፍተሻ ስራ የተጠናቀቀ ሲሆን የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ዝርጋታው ሙሉ በሙሉ ሲጠናቀቅ የሙከራ ሥራ ይጀመራል ተብሎ ይጠበቃል። ዓለም ባንክ ለፕሮጀክቱ ማስፈፀሚያ የሚሆነውን የፋይናንስ ወጪ የብድር አቅርቦት ያመቻቸ መሆኑን ሥራ አስኪያጁ አስታውቀዋል። በጉብኝቱ ላይ በምስራቅ አፍሪካ የዓለም ባንክ የመሠረተ ልማት ዳይሬክተርን ጨምሮ የጎንደር ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ተገኝተዋል። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 10 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+7

ለኢኮኖሚ ዞኑ ኤሌክትሪክ አቅርቦት ግንባታ ፕሮጀክት በይፋ ተጀመረ …….///……. በሞጆ ከተማ አካባቢ ለሚነባው የገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን አገልግሎት የሚሰጥ ባለ 230/33 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት የግንባታ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ተካሄደ። በግንባታ ማስጀመሪያ ሥነ ሥርዓቱ ላይ ንግግር ያደረጉት የገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ኮርፖሬሽን ተጠባባቂ ሥራ አስኪያጅ አቶ ደመላሽ ሙሉ እንደገለፁት የሚገነባው ፕሮጀክት ለ40 ዓመት የታቀደና በአራት ምዕራፎች ተከፋፍሎ የሚከናወን ሀገራዊ ራዕይ የሰነቀ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ነው። ለአራቱ ምዕራፎች አጠቃላይ ከሁለት ጊጋ ዋት በላይ የኤሌክትሪክ ኃይል እንደሚያስፈልግ የገለጹት አቶ ደመላሽ ኮርፖሬሽኑ በአምስት ዓመት ለሚገነባው የመጀሪያው ምዕራፍ ፕሮጀክት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል 340 ሜጋ ዋት ኤሌክትሪክ እንዲያቀርብለት መጠየቃቸውንም ገልፀዋል፡፡ እንደርሳቸው ገለጻ በመጀመሪያው ምዕራፍ ከተጠየቀው የኃይል ፍላጎት ውስጥ አሁን በተጀመረው ፕሮጀክት 230 ኪሎ ቮልት ኤሌክትሪክ ለማቅረብ የሚያስችል ስምምነት ተደርጓል፡፡ በየምዕራፎቹ ለሚካሄደው ግንባታ የሚያስፈልገውን የኃይል ፍላጎት ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በዝርዝር ማቅረባቸውን የጠቆሙት ተጠባባቂ ሥራ አስኪያጁ የግንባታውን ወጭ ጨምሮ የሚያስፈልገውን ማንኛውም ድጋፍ ለማድረግ ኮርፖሬሽኑ ዝግጁ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታ የራስ ኃይል መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ሰለሞን ኃይለጊዮርጊስ በበኩላቸው ፕሮጀክቱ የጠየቀውን የኤሌክትሪክ ፍጆታ ለማቅረብ ባለፉት 6 ወራት በቂ ዝግጅት ሲደረግ መቆየቱን አንስተዋል፡፡ በዝግጅቱም ምን ዓይነት የኢንዱስትሪ ዞኖች እንደሚገነቡና የሚያስፈልጋቸውን የኃይል መጠን መረጃ ሰብስቦ በመተንተን ወደ ሥራ ለመግባት ከተቋሙ የኢንጅነሪንግ ዘርፍ ጋር በመሆን ሰፊ ሥራ መሰራቱን ገልጸዋል፡፡ አሁን ላይ የሚገነባውን የባለ 230/33 ኪሎ ቮልት የማስተላለፊያና ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ በ18 ወራት ውስጥ በሚፈለገው ጥራት አጠናቆ ለማስረከብ በትጋት እንደሚሰሩ ዳይሬክተሩ አረጋግጠዋል፡፡ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኢንጂነሪንግ ዘርፍ የሱፐርቪዥንና ኮንትራት ዳይሬክተር እና የፕሮጀክቱ አማካሪ አቶ ግርማ ዘለቀ በበኩላቸው የሚገነባውን የማስተላለፊያና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት ለማማከር የ45 ሚሊዮን ብር ስምምነት መፈራረማቸውን ገልጸዋል፡፡ የፕሮጀክቱ ግንባታ በተቋሙ የራስ ኃይል መምሪያ የሚገነባ ሲሆን የማከፋፈያ ጣቢያና ማስተላለፊያ መስመር የዕቃ አቅርቦቱን ሳይጨምር ለማከፋፈያ ጣቢያው የሲቪል ሥራ 226 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር፣ ለኤሌክትሮ መካኒካል ሥራ 22 ነጥብ 3 ሚሊዮን ብር እና ለማስተላለፊያ መስመሩ ደግሞ 10 ነጥብ 7 ሚሊዮን ብር በድምሩ 259 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር የተመደበለት ሲሆን ወጪውም ሙሉ በሙሉ በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት የሚሸፈን ይሆናል፡፡ “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 10 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content

ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮይሻ የውኃ ማመንጫ ፕሮጀክት ጽ/ቤት በጂኦሎጂ 1ኛ ክፍት የሥራ መደብ ተወዳዳሪዎችን አወዳድሮ ለመቅጠር በቀን 03/05/2015 ዓ.ም በደብዳቤ ቁጥር ኢ.ኤ.ኃ/8.4/135/15 በማስታወቂያ መግለፁ ይታወቃል። በመሆኑም ከዚህ በታች ስም ዝርዝራችሁ የተገለፀው አመልካቾች ባቀረባችሁት የትምህርት ማስረጃ እና የሥራ ልምድ መሰረት ለፅሁፍና ለቃል ፈተና ያለፋችሁ በመሆኑ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና መስሪያ ቤት 20ኛ ፎቅ በሚገኘው የስብሰባ አዳራሽ ውስጥ አርብ በቀን 10/06/2015 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት በአካል በመቅረብ እንድትፈተኑ እናሳውቃለን፡

photo content
+8

ፕሮጀክቱን በተያዘለት ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው …….///…… የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የግንባታ ሥራን በተያዘለት ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን የፕሮጀክት ጽ/ቤቱ አስታወቀ፡፡ የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ አቶ ተሰማ ኡርጌቻ እንደገለፁት የግንባታው አጠቃላይ አፈፃፀም ከ38 በመቶ በላይ ደርሷል፡፡ የካሣ ክፍያ ሥራ፣ የዲዛይን ግምገማ፣ የውስጥ ለውስጥ እና መጋቢ መንገዶች ግንባታ፣ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ እና የተርባይን መሰረት ቁፋሮ ሥራዎች እየተካሄዱ እንደሚገኙ ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡ በአሁኑ ሰዓት የተርባይን ዕቃዎች ሙሉ በሙሉ ጅቡቲ ወደብ መድረሳቸውን የጠቀሱት ሥራ አስኪያጁ የማከፋፈያ ጣቢያ ዕቃዎች በአብዛኛው ተመርተው በመጓጓዝ ላይ እንደሚገኙም ገልፀዋል፡፡ የሲቪል ሥራዎች ላይ የግንባታ ጥራት ችግር እንዳይፈጠር ከፍተኛ ቁጥጥር በማድረግ ላይ እንደሚገን የተናገሩት አቶ ተሰማ የኮንክሪት ጥንካሬ፣ የሲ-15 እና ሲ-37 ሲሚንቶ ዓይነቶች ጥራት ፍተሻ፣ የመንገዶች የታችኛው አፈር ንጣፍ፣ የሙሊት አፈር ጥራት፣ የፌሮ እና የኮንክሪት ቅይጥ ዲዛይን ሥራዎች ክትትል እየተደረገባቸው ከሚገኙ ዋና ዋና ሥራዎች መካከል ተጠቃሽ መሆናቸውን አብራርተዋል፡፡ ከወረዳ መስተዳድር እና ከባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት ለመሬት ባለይዞታ አርሶአደሮች በቴክኖሎጂ የታገዘ የካሳ ክፍያ የአሰራር ሥርዓት በመዘርጋት ክፍያ መፈፀሙን ጠቁመዋል፡፡ እንደ አቶ ተሰማ ገለፃ በጅቡቲ ድንበር በኩል የሚገኙ መንገዶች በጎርፍ በመጎዳታቸው ምክንያት ጅቡቲ ወደብ የደረሱትን የተርባይን ዕቃዎች ወደ ሳይት ማጓጓዝ ባለመቻሉ የሚመለከታቸው አካላት ድጋፍ ተጠይቋል፡፡ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ 100 ሜጋ ዋት ተጨማሪ ኃይል ወደ ብሔራዊ የኃይል ቋት በማስገባት አስተዋፅኦ ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 08 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+2

EEP Communication - Статистика и аналитика Telegram-канала @eepcommuication