ru
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Открыть в Telegram

📈 Аналитический обзор Telegram-канала EEP Communication

Канал EEP Communication (@eepcommuication) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 15 534 подписчиков, занимая 8 338 место в категории Технологии и приложения и 2 162 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 15 534 подписчиков.

Согласно последним данным от 29 июня, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 6, а за последние 24 часа — -1, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 25.10%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 16.85% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 3 901 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 2 619 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 8.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
EEP Communication

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 30 июня, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Технологии и приложения.

15 534
Подписчики
-124 часа
-167 дней
+630 день
Архив постов
የፕሮጀክቱ አጠቃላይ ሥራ ከ61 በመቶ በላይ ደርሷል ………//………. የበቆጂ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ ፕሮጀክት አጠቃላይ ሥራ 61 ነጥብ 6 በመቶ መድረሱ ተገለፀ። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የራስ ኃይል ኮንስትራክሽን መምሪያ የበቆጂ ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት የሳይት አስተባባሪ አቶ እንዳልካቸው ጃምቦ እንደገለፁት ፕሮጀክቱ የዲዛይን ሥራ፣ የሲቪል ግንባታ፣ የኤሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎች አቅርቦትና ተከላ፣ የፍተሻና ሙከራ ሥራዎች አሉት፡፡ በሲቪል ግንባታ ከሚከናወኑት ሥራዎች መካከል የትራንስፎርመር መሰረት የመገንባት ሥራ ሲጠናቀቅ የመቆጣጠሪያ ክፍል ግንባታው ሥላብ የመሙላት ደረጃ ላይ መድረሱን አቶ እንዳልካቸው ተናግረዋል፡፡ የጣቢያው የግቢ አጥር፣ የመኖሪያ ቤትና የጥበቃ ክፍል የመሰረት ሥራ ቁፋሮ እንዲሁም በጊዜያዊነት የሚያገለግል የውስጥ ለውስጥ እና መጋቢ መንገዶች ጠረጋ ተጠናቋል ብለዋል። የፕሮጀክቱ የሲቪል ሥራ አፈፃፀም 36 ነጥብ 6 በመቶ መድረሱን ነው ያስታወቁት፡፡ በተቋሙ የበቆጂ ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት ሳይት ሥራ አስኪያጅ አቶ ተኮላ ተሾመ በበኩላቸው በአሁኑ ወቅት የፕሮጀክቱ ወሳኝ ሥራዎች የሆኑት የጣቢያው መቆጣጠሪያ ክፍል ግንባታ፣ የትራንስፎርመር ማስቀመጫና የስዊች ያርድ እንዲሁም የሠራተኞች መኖሪያ ቤት የመሠረት ሥራቸው በመጠናቀቅ ላይ መሆናቸውን ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል። እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ በአሁኑ ወቅት በስዊች ያርዱ ላይ ቀሪ የቁፋሮና የመሠረት ሥራዎች በመከናወን ላይ ሲሆኑ የትራንስፎርመር ተከላ፣ የመቆጣጠሪያ ክፍል እንዲሁም የመኖሪያ ቤቶች የግድግዳና ጣሪያ ማጠናቀቂያ ሥራዎች በቀጣይ የሚከናወኑ ይሆናል። ማከፋፈያ ጣቢያው ኃይል የሚያገኘው ከመልካዋከና ወደ ቆቃ ከሚያልፈው ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ መሆኑን የጠቀሱት ሥራ አስኪያጁ ለዚህም 1 ነጥብ 1 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን አራት የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች የግንባታ ሥራ በቅርቡ እንደሚጀመር ተናግረዋል፡፡ እያንዳንዳቸው 50 ሜጋ ቮልት አምፒር አቅም ያላቸው ሁለት ትራንስፎርመሮችን ጨምሮ ሙሉ የፕሮጀክቱ ዕቃዎች በ15 ቀናት ውስጥ ወደ ግንባታ ሳይቱ የሚደርሱ ሲሆን ይህም የኤሌክትሮ መካኒካል ሥራውን በፍጥነት ለማጠናቀቅ ያግዛል ብለዋል። አሁን ባለው ነባራዊ ሁኔታ ከዕቃ አቅርቦትም ሆነ ከካሳ ክፍያ ጋር የሚስተዋሉ ችግሮች ባለመኖራቸው ፕሮጀክቱን በተያዘለት ጊዜ ለማጠናቀቅ እንደሚያስችል ነው የገለፁት። የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው ሲጠናቀቅ ለበቆጂና አካባቢው ማህበረሰብ አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ ያስችላል። ግንባታው የሚከናወነው በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የራስ ኃይል ኮንስትራክሽን መምሪያ ሲሆን የማማከር ሥራውን ደግሞ የተቋሙ ኢንጅነሪንግ ክፍል እያከናወነው ይገኛል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 12 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+9

የኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት አጠቃላይ ግንባታ 62 በመቶ ደርሷል ………..///………. ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ወደ ሥልጣን ከመጡ ወዲህ የኮይሻ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክትን ለ12ኛ ጊዜ ጎበኙ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ ባሰፈሩት ጽሑፍ “ከ2013 ዓ.ም. ጀምሮ ለ12ኛ ጊዜ ባካሄድኩት የኮይሻ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ግምገማ በለወጥነው የፕሮጀክት አስተዳደር እና ክትትል ሥርዓት የተነሣ የአጠቃላይ ግንባታው ሂደት 62% ላይ መድረሱን በመመልከቴ ደስታ ተሰምቶኛል” ብለዋል። ኢትዮጵያ በግዙፍነታቸው በአፍሪካ አንደኛ እና ሦስተኛ የሆኑትን የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ እና የኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ግድቦች ባለቤት መሆኗ የንፁህ የኃይል ማመንጨት አቅሟን እና ጥረቷን አቻ የሌለው ያደርገዋል ሲሉ ገልፀዋል። የኮይሻ ግድብ በጨበራ ጩርጩራ ብሔራዊ ፓርክ በተገነባው የጨበራ የዝሆን ዳና ሎጅ በቅርብ ርቀት ላይ የሚገኝ በመሆኑ ለአካባቢው የቱሪዝም ዕድል ተጨማሪ አስተዋፅኦ እንደሚያደርግም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አስታውቀዋል። ግድቡ በዓመት በአማካይ 6460 ጊጋ ዋት ሰዓት ኤሌክትሪክ የሚያመነጭ ሲሆን በዓመት እስከ አንድ ሚሊየን ቶን የካርበን ልቀት የመቆጣጠር አቅም አለው። የኮይሻ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ሲጠናቀቅ 180 ሜትር ቁመት፣ 250 ሜትር ርዝመትና 41 ሜትር ስፋት ይኖረዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 12 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+6

ሪጅኑ ያሉት ማከፋፈያ ጣቢያዎች ካላቸው ኃይል የመጫን አቅም ጥቅም ላይ እየዋለ ያለው 32 በመቶ ብቻ ነው ……….///……….. በምስራቅ ሁለት ሪጅን የሚገኙ አምስቱ የኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች መጫን ከሚችሉት 155 ሜጋ ዋት ኃይል ለህብረተሰቡ እየቀረበ ያለው 50 ሜጋ ዋት ብቻ እንደሆነ የሪጅኑ የማስተላለፊያ መስመሮች እና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ አስታወቀ። የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ አብዱላሂ አብሽር እንደተናገሩት የሱማሌ ክልልን የሚሸፍነው የምስራቅ ሁለት ሪጅን ከቆቀቃ እና ከመልካ ዋከና የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች በሁለት አቅጣጫ ኃይል ያገኛል። ሪጅኑ የሚያስተዳድራቸው አምስት ማከፋፈያ ጣቢያዎች በአጠቃላይ 155 ሜጋ ዋት የመሸከም አቅም ቢኖራቸውም ለህብረተሰቡ እየቀረበ ያለው ግን 32 በመቶ ወይም 50 ሜጋ ዋት ብቻ ነው ብለዋል። በማከፋፈያ ጣቢያዎቹ ተጨማሪ ደንበኞችን ማስተናገድ የሚያስችል 105 ሜጋ ዋት ትርፍ የኤሌክትሪክ ኃይል እንዳለም አመልክተዋል። በክልሉ ካሉ ማከፋፈያ ጣቢያዎች አብዛኛው ደንበኛ ኃይል የሚያገኘው ከክልሉ ርዕሰ መዲና ከተማ ከሚገኘው የጅግጅጋ ማከፋፈያ ጣቢያ እንደሆነ ያነሱት ዳይሬክተሩ ሌሎች ጣቢያዎች ደግሞ ካላቸው አቅም አገልግሎት ላይ እየዋለ ያለው ከ20 በመቶ እንደማይበልጥ ነው የተናገሩት። ያለውን ኃይል ጥቅም ላይ ለማዋል ከክልሉ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር በቅንጅት እየተሰራ እንደሆነም አቶ አብዱላሂ አስታውቀዋል። በኦፕሬሽን ሥራው ላይ የኃይል መቆራረጥ ሳይከሰት የቅድመ መከላከል እና የጥገና ሥራዎች በወቅቱ እየተከናወኑ ይገኛሉ ያሉት ዳይሬክተሩ ሥራው ውጤታማ በሆነ መልኩ እንዲከናወን ለማድረግ የሠራተኛውን አቅም መገንባት ላይ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ ነው ብለዋል። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሱማሌ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጽ/ቤት የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ማንደፍሮ ታደሰ በበኩላቸው በሪጅኑ በቂ የኤሌክትሪክ ኃይል እንዳለ ገልፀዋል፡፡ ይሁንና በክልሉ ያለው የህዝብ አሰፋፈር የተበታተነ በመሆኑና በአካባቢው ኢንዱስትሪዎች ባለመስፋፋታቸው ያለውን ኃይል በአግባቡ መጠቀም አልተቻለም ብለዋል። በክልሉ በአሁኑ ወቅት ያለው የኃይል ተደራሽነት ከ20 በመቶ እንደማይበልጥ የጠቆሙት አቶ ማንደፍሮ ይህን ለማሳደግ የተለያዩ አማራጮች መነደፋቸውን ጠቁመዋል። እንደ አቶ ማንደፍሮ ገለፃ ባለሃብቱ በክልሉ ኢንቨስትመንት እንዲሳተፍ በቂ ኃይል እንዳለ በማሳወቅ የመቀስቀስ እና የህብረተሰቡን የኤሌክትሪክ ኃይል የመጠቀም ልማድ ለማሳደግ የተለያዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ። የምስራቅ 2 ሪጅኑ ራሱን ችሎ በአዲስ መዋቅሩ የኃይል መቆራረጥ ችግሮች ሲያጋጥሙ በወቅቱ መፍትሔ ለመስጠት እና በአገልግሎቱ ላይ የነበሩ ጫናዎቹን ለማቃለል እንደሚያግዝ የሥራ ኃላፊዎቹ አንስተዋል፡፡ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ ሁለቱ ተቋማት በቅንጅት እየሠሩ መሆኑንም አስታውቀዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 12 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+3

የማከፋፈያ ጣቢያው ግንባታ ከ72 መቶ በላይ ተጠናቋል ……....///…….... የወልዲያ ባለ 400/230/33/15 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ አፈፃፀም 72 ነጥብ 5 በመቶ መድረሱን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪከ ኃይል የፕሮጀክቱ ሪዚደንት መሐንዲስ አቶ ሀብታሙ ተሾመ አስታወቁ። አቶ ሀብታሙ እንዳስታወቁት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው የሲቪል ሥራ 85 በመቶ እንዲሁም የኤሌክትሮሜካኒካል ሥራ 60 በመቶ ተጠናቋል። የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያውን በተያዘው በጀት ዓመት አጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ ለማድረግ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ነው የገለፁት። በአሁኑ ወቅት የባዝባር ተከላ፣ የመቆጣጠሪያ እና ለኃይል ማሰተላለፍ የሚያገለግሉ የመሬት ውስጥ ገመድ ዝርጋታዎች እንዲሁም የቀበራ ሥራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኙ መሐንዲሱ ተናግረዋል። የትራንስፎርመር እና ሻንት ሪአክተር ዕቃዎችን የገጠማ ሥራ ለማከናወን ዕቃዎቹን ካመረተው ኩባንያ ባለሙያዎች እስኪመጡ እየተጠበቀ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። እንደ አቶ ሀብታሙ ገለፃ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው ስምንት ባለ 15 እና ስምንት ባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች አሉት። በ15 እና 33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች ላይ የሚኖረውን የኦፕሬሽን ሥራ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተደገፈ ለማድረግ በጋዝ የሚሰራ የጂ.አይ.ኤስ መቆጣጠሪያ (Gas Insulated System) የገጠማ ሥራ እንደሚከናወን ሪዚደንት መሐንዲሱ ጠቁመዋል። የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው 500 ሜጋ ቮልት አምፒር አቅም ያላቸው ሁለት ባለ 250 እና 126 ሜጋ ቮልት አምፒር አቅም ያላቸው ሁለት ባለ 63 ሜጋ ቮልት አምፒር ትራንስፎርመሮች እንዲሁም ሁለት ባለ 60 ሜጋ ቫር ሻንት ሪአክተሮች እንደሚኖሩት ገልፀዋል። የወልዲያ ባለ 400/230/33/15 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት የመተማመኛ ሰነድ በጊዜው ባለመከፈቱ፣ በኮሮና ወረርሽኝ እና መስመሩ በሚያልፍባቸው አካባቢዎች በተከሰቱ የፀጥታ ችግሮች ሳቢያ ሲጓተት መቆየቱን አብራርተዋል። የማከፋፈያ ጣቢያውን ግንባታ አጠናቆ ለአገልግሎት ለማብቃት ከ913 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት ተይዞለታል፡፡ ማከፋፈያ ጣቢያው ሲጠናቀቅ ለወልዲያ ከተማና በአካባቢው ለሚገኙ የኢንዱስትሪ መንደሮች እንዲሁም ለአዋሽ-ወልዲያ- ሐራ ገቢያ የባቡር መስመር አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ተደራሽ ለማድረግ ያግዛል። የወልዲያ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታን ሻንጋይ ኤሌክትሮ ግሩፕ የተባለ የቻይና ኩባኒያ እያከናወነው ሲሆን በአማካሪነት ደግሞ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኢንጅነሪንግ ቢሮ እየተሳተፈበት ይገኛል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 11 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+8

የፕሮጀክቱን የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታ በተያዘው በጀት ዓመት ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው …......////............ የባህር ዳር – ወልዲያ – ኮምቦልቻ ባለ 400 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክትን በሁለት የግንባታ ምዕራፍ ከፍሎ ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የፕሮጀክቱ ሪዚደንት መሐንዲስ አቶ ሀብታሙ ተሾመ አስታወቁ። አቶ ሀብታሙ እንዳስታወቁት የመጀመሪያው የግንባታ ምዕራፍ ከባህርዳር እስከ ወልዲያ የሚደርሰውን የኃይል ማስተላለፊያ መስመር የሚያጠቃልል ሲሆን ሁለተኛው ምዕራፍ ደግሞ ከወልዲያ እስከ ኮምቦልቻ ድረስ ያለውን ይሸፍናል። የመጀመሪያውን የግንባታ ምዕራፍ በተያዘው በጀት ዓመት አጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ከባህርዳር እስከ ወልዲያ እንደሚተከሉ ከሚጠበቁት 640 የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ውስጥ የ620 የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች ተከላ ተጠናቋል፤ ቀሪ ምሰሶዎችን ለመትከል የሚያስችሉ ሥራዎችም እየተከናወኑ ነው ብለዋል። ከባህርዳር እስከ ወልዲያ የኮንዳክተር ገመድ ለመዘርጋት ከታሰበው 295 ነጥብ 87 ኪሎ ሜትር ውስጥ 222 ኪሎ ሜትር ማጠናቀቅ መቻሉንም ነው አቶ ሀብታሙ የተናገሩት። የ640 የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎችን ተከላ ሥራ ለማከናወን ከሚያስፈልገው የመሠረት ቁፋሮ ሥራ ውስጥ የ632 የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች የመሠረት ቁፋሮ ሥራ መጠናቀቁንም አመልክተዋል። 25 ኪሎ ሜትር የሚሸፍኑ 50 የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች መሠረት የማውጣት፣ የተከላ እና የኮንዳክተር ገመድ ዝርጋታ እንደሚቀሩ የተናገሩት ሪዚደንት መሐንዲሱ ከዚህ ውስጥ 15 የሚደርሱ የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች በወሰን ማስከበር ችግር ሳቢያ ግንባታቸው ሳይከናወን መዘግየቱን ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት የፕሮጀክቱ አጠቃላይ አፈፃፀምም 85 በመቶ መድረሱን መሐንዲሱ ጠቅሰዋል። እንደ አቶ ሀብታሙ ገለፃ የወሰን ማስከበር ችግርና በፕሮጀክቱ ሠራተኞች ላይ የሚያጋጥመው የደህንነት ስጋት እንዲሁም በኃይል ተሸካሚ ምሰሶ ብረቶችና ሽቦዎች ላይ የሚፈፀሙ ተደጋጋሚ የስርቆት ወንጀሎችን በመከላከል ፕሮጀክቱን በተያዘለት ጊዜ ለማጠናቀቅ ሁሉም ሊረባረብ ይገባል፡፡ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ በሚያልፍባቸው የባህርዳር፣ ዘንዘልማ እና ንፋስ መውጫ አካባቢዎች የወሰን ማስከበር ችግሮች መከሰታቸውን የገለፁት አቶ ሀብታሙ በተለይም በንፋስ መውጫ የአንድ የኃይል ተሸካሚ ምሰሶ ተከላ ሥራ ባለመከናወኑ ምክንያት የ3 ኪሎ ሜትር የኮንዳክተር ገመድ ዝርጋታ ሥራ ለመስራት እንቅፋት መፍጠሩን ተናግረዋል። በባህርዳር ዙሪያ እና በደብረታቦር አካባቢዎች በኃይል ተሸካሚ ምሰሶ ብረቶችና ሽቦዎች ላይ ተደጋጋሚ የስርቆት ወንጀሎች እየተፈፀሙ እንደሚገኙም ጠቁመዋል። የባህርዳር - ወልዲያ ባለ 400 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት ግንባታ ሥራ የመተማመኛ ሰነድ በጊዜው ባለመከፈቱ፣ በኮሮና ወረርሽኝ እና መስመሩ በሚያልፍባቸው አካባቢዎች በተከሰቱ የፀጥታ ችግሮች ሳቢያ ሲጓተት መቆየቱን ገልፀዋል። ፕሮጀክቱ የባህርዳር፣ የደቡብ ጎንደር እና የሰሜን ወሎ ዞኖችን የሚያካልል በመሆኑ በየደረጃው ያሉ አመራሮች ችግሮቹን በመፍታት ለግንባታው መፋጠን የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ጥሪ አቅርበዋል። የፕሮጀክቱን የግንባታ ሥራ ታታ ፕሮጀክትስ ሊሚትድ (TATA PROJECTS LTD) የተባለው የህንድ ኩባንያ እያከናወነው ሲሆን በአማካሪነት ደግሞ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኢንጂነሪንግ ቢሮ እየተሳተፈበት ይገኛል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 10 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+9

ተዘግተው የቆዩ መጋዘኖችን በካይዘን ፍልስፍና የማደራጀት ሥራ እየተከናወነ ነው ……..///…….. ኮተቤ የሚገኘውን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማሰልጠኛ ማዕከል መጋዘን በካይዘን ፍልስፍና መሰረት የማደረጃት ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የተቋሙ የስልጠናና ልማት ማዕከል አስታወቀ፡፡ የማዕከሉ ሥራ አስኪያጅ አቶ ደምስ ሰይፉ እንዳስታወቁት በመጋዘኑ ውስጥ የሚያገለግሉና የማያገለግሉ ዕቃዎች በአንድ ላይ ከመቀመጣቸውም ባለፈ በውስጡ ያሉት ንብረቶች ለረጅም ዓመታት አይታወቁም ነበር፡፡ ዕቃዎችን ለማወቅና በካይዘን ፍልስፍና ለማደራጀት በተቋማዊ ለውጥ ቢሮ በኩል የዳሰሳ ጥናት ተደርጎ ወደ ሥራ መገባቱን ሥራ አስኪያጁ ጠቁመዋል፡፡ የጥናቱን ውጤት መሰረት በማድረግ መወገድ ያለባቸው እንዲወገዱ፣ አገልግሎት የሚሰጡት ወደሚያገለግሉበት የሥራ ክፍል እንዲተላለፉ እንዲሁም ሌሎቹ በሰነድ ተመዝግበው ወደዋናዉ የተቋሙ መጋዘን እንዲገቡ የተቋሙ ከፍተኛ አመራር አቅጣጫ ማስቀመጡን ተናግረዋል፡፡ በዚህም ዕቃዎችን ለመለየትና በአግባቡ ለማደራጀት በማዕከሉ የካይዘን ቡድን በማቋቋም ወደ ሥራ መገባቱንና ዕቃዎችን የመለየትና የማደራጀት ሥራ መጀመሩን ነው አቶ ደምስ የገለጹት፡፡ በመጋዘኑ ውስጥ ተቋሙ ከዚህ በፊት ሲጠቀምባቸው የነበሩ ለታሪክ መቀመጥ ያለባቸው በርካታ ዕቃዎችና ማሽነሪዎች መገኘታቸውም አስታውቀዋል፡፡ በማዕከሉ የሰው ኃይል አስተዳደርና የካይዘን ቡድን ሰብሳቢ አቶ ባትሪ ደረሰ በበኩላቸው መጋዘኑ ለረጅም ዓመት ተዘግቶ በመቆየቱ ሥራው ሲጀመር በርካታ ፈታኝ ነገሮች አጋጥመው እንደነበር አንስተዋል፡፡ በማዕከሉ ላይ ከ25 ዓመታት በላይ ያገለገሉት ወ/ሮ መሰረት ተሰማ ደግሞ ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ በኃላፊነትና በታማኝነት ያቆዩዋቸው የመጋዘኑ ቁልፎች ተከፍተው ተረካቢ በመገኘቱ እንደተደሰቱ ገልፀዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 9 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

የቴክኒክ ድጋፍ ሥራዎች እያደጉ ነው …….///……… በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማሻሻያ ሥራ የሚፈልጉ የማስተላለፊያ መስመሮች እና ማከፋፈያ ጣቢያዎችን በማጥናት ምክረ ሀሳብ አቅርቦ እያገዘ መሆኑን የማስተላለፊያ መስመሮች እና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ዘርፍ አስታወቀ፡፡ በዘርፉ የቴክኒክ ድጋፍ ቢሮ ኃላፊ መሀንዲስ አበባው ያለው እንዳስታወቁት በጥናቱ መሰረት ዝርዝር ዲዛይን የማዘጋጀት እና የእሴት ምዝገባ በማከናወን ቢሮው የድጋፍ ሥራ እያከናወነ ነው፡፡ ለሥራው እንዲያግዝ የመመዝገቢያ ሶፍትዌር መበልፀጉንና ለጣቢያዎች በቂ መለዋወጫ መኖሩን በማረጋገጥ አልያም ለግዢ አፈፃፀም ምቹ መስፈርት በማዘጋጀት የማሻሻያና የጥገና ሥራዎች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲከናወኑ እየተደረገ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ አቶ አበባው እንደገለፁት ለማከፋፈያ ጣቢያ ዕቃዎች ኢንሹራንስ እንዲገባና የኦፕሬሽን ፖሊሲ እንዲኖር የማድረግ የቴክኒክ ድጋፍ ሥራ ተሰርቷል፡፡ የኃይል አቅርቦትን አስተማማኝ ለማድረግ ጥናት ማከናወንና በጤናና ደህንነት ጉዳዮች ላይ ፖሊሲና ፕሮሲጀሮች በመዘጋጀታቸው የኦፕሬሽን ሥራዎች እንዲቀላጠፉ ማገዙን አብራርተዋል፡፡ ከኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች እና ከሪጅኖች በስልክ፣ በደብዳቤና በዋትስአፕ ቡድን በሚገኙ መረጃዎች መሰረት አስፈላጊ ድጋፉ እየተደረገ መሆኑን ዳይሬክተሩ ተናግረዋል፡፡ የድጋፍ ስራቸውን ይበልጥ ለማሳደግም ከኦሞቲክ አፍሪካና አር ቲ ኢ ኢንተርናሽናል ድርጅቶች ጋር የልምድ ልውውጥ መደረጉን ተናግረዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 08 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+5

ስትራቴጂክ ዕቅዱን ለመተግበር ተቋማዊ የእኔነት ባህል መፍጠር እንደሚገባ ተገለጸ .........///.......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ያዘጋጀውን የሶስት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ ለመተግበር ተቋማዊ የኔነት ባህል መፍጠር እንደሚገባ የዋና ሥራ አስፈጻሚ ተወካይና የኮርፖሬት ፕላኒንግ ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚ አቶ አንዱዓለም ሲዓ አሳሰቡ። የተቋሙ ከፍተኛ እና መካከለኛ አመራሮች ሱሉልታ በሚገኘው የአፍሪካ አመራር አካዳሚ ከታህሳስ 5 እስከ 6 ቀን 2016 ዓ.ም. የአስተሳሰብ፣ ሳይንሳዊ እና ስትራቴጂያዊ የውሳኔ አሰጣጥ፣ ችግርን መለየት፣ መተንተን፣ መፍትሄ መስጠትና ማቀድ ላይ ያተኮረ ስልጠና ወስደዋል። በስልጠናው ማጠቃለያ  ላይ የዋና ሥራ አስፈፃሚው ተወካይ ባደረጉት ንግግር ስልጠናው ያስፈለገው ተቋሙ ባዘጋጀው ስትራቴጂክ ዕቅድ ላይ ለአመራሩ  በየደረጃው ግንዛቤ ለመፍጠር፣ ለማነቃቃትና የአስተሳሰብ ለውጥ ለማምጣት ነው። በስልጠናው የተገኘውን ዕውቀት መነሻ በማድረግ ለውጠን ከራስ በመጀመር ለተቋማዊ ለውጥ መስራት አስፈላጊ መሆኑን አቶ አንዱዓለም ገልፀዋል። ስትራቴጂክ ዕቅዱን ማስተዋወቅና ገጽታ ግንባታ ላይ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባም አቶ አንዱዓለም አሳስበዋል። የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኸኝ በበኩላቸው በስልጠናው የተገኘውን ዕውቀት በስራ መተግበር እና በተነሳሽነት ወደ ሠራተኛ  ማውረድ ለስትራቴጂክ ዕቅዱ ስኬት ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰዋል። ወደሠራተኛ በማውረድ በኩል በተነሳሽነት መስራትና ሠራተኛውን ያሳተፈ ንቅናቄ መፍጠር ይገባል ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል። የሰው ኃይል ሥራ  አስፈፃሚ  አቶ አታላይ አበበ ደግሞ ስልጠናው ራስንና ሰውን ለመቀየር የሚያስችል በመሆኑ ቀደም ሲል የነበረውን አሰራር ቆም ብሎ በማየት ለተሻለ ውጤት መነሳት እንደሚገባ ተናግረዋል። የተቋሙ የሰው ሀብት ልማት መምሪያ ዳይሬክተር  ዶክተር ወንድወሰን ካሳ በበኩላቸው ስትራቴጂክ ዕቅዱን ለመተግበር በተደረገው የዳሰሳ ጥናት የአመራሩን ግንዛቤ ማሳደግና መነቃቃት መፍጠር እንደሚያስፈልግ በተገኘው ግብዓት መሰረት ስልጠናው መዘጋጀቱን ገልፀዋል ። ስትራቴጂክ  ዕቅዱን ለመተግበር አመራሩ እና ሠራተኛው ከመቼውም ጊዜ በተሻለ በእኔነት ስሜት ወደተግባር እንዲገቡ የጠየቁት የተቋሙ መሰረታዊ የሠራተኛ ማህበር ሊቀመንበር አቶ መኮንን ክፍሌ ናቸው። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 07 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+5

ሪጅኑ ለሀገር ኢኮኖሚ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ለሚያበረክቱ ዘርፎች አስተማማኝ ኃይል እያቀረበ ነው ........///……... በኢትዮጵያ ኤሌክትረክ ኃይል የምስራቅ አንድ ሪጅን ለሀገር ኢኮኖሚ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ለሚያደርጉ የተለያዩ ዘርፎች አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል እያቀረበ እንደሚገኝ የሪጅኑ የማስተላለፊያ መስመሮችና የማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ አስታወቀ። የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ወርዲ መሐመድ እንዳስታወቁት በሪጅኑ አራት ባለ 230 እና አምስት ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች እንዲሁም 3 ሺህ 400 ኪሎ ሜትር ከፍተኛ የኃይል የማስተላለፊያ መስመሮች ይገኛሉ። ሪጅኑ ወደ ጂቡቲ የሚላከውን ኃይል ጨምሮ ለድሬዳዋ ነፃ የንግድ ቀጠና እና በሌሎች አካባቢዎች ለሚገኙ ከፍተኛ ኢንዱስትሪዎች አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል እያቀረበ እንደሚገኝ ገልፀዋል። ሪጅኑ አገልግሎት በሚሰጥባቸው አካባቢዎች የኢንዱስትሪዎች መስፋፋትን ተከትሎ የኃይል ፍላጎት ጥያቄ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ በመምጣቱ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎቹ ላይ የአቅም ማሳደግና የማሻሻያ ሥራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኙ አቶ ወርዲ ተናግረዋል። ከአቅም ማሳደግ ሥራው ጎን ለጎን የኃይል መቆራረጥን ለመከላከልና የኦፕሬሽንና የጥገና ሥራዎችን ለማዘመን የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኙም ነው ዳይሬክተሩ የጠቀሱት። በሐረር ቁጥር ሦስት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ የኦፕሬሽን ሥራውን በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተደገፈ ለማድረግ በጋዝ የሚሰራ የጂ.አይ.ኤስ መቆጣጠሪያ (Gas Insulated System) ቅየራ እየተከናወነ እንደሚገኝ የጠቀሱት አቶ ወርዲ የመቆጣጠሪያ ቅየራ ሥራው በድሬዳዋ ቁጥር ሦስት እና በአዲጋላ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይም እንደሚከናወን ጠቁመዋል። በሪጅኑ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ከድር አብደላ በበኩላቸው በራስ አቅም የተለያዩ የጥገና ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ጠቅሰዋል። ሪጅኑ ለጥገና የሚያስፈልጉ ዕቃዎች ላይ የማሻሻያ (Modification) ሥራዎችን በማድረግ እየተጠቀመ እንደሚገኝ የጠቆሙት ሥራ አስኪያጁ ይህም ተቋሙን ከተጨማሪ ወጪ ለማዳን እንደሚያግዝ አመልክተዋል። የሪጅኑ የጥገና ባለሙያዎች በኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ ከሚያገኟቸው የቴክኖሎጂና የዕውቀት ሽግግሮች ባለፈ በተለያዩ ዘርፎች ክህሎት እንዲኖራቸው እየተደረገ እንደሚገኝም አቶ ከድር ገልፀዋል። በሪጅኑ በሚገኙ በሁሉም የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎችና ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ በየጊዜው የፍተሻና የጥገና ሥራዎች እንደሚካሄድም ነው ሥራ አስኪያጁ የጠቆሙት። እንደ አቶ ከድር ገለፃ በአሁኑ ወቅት አገልግሎት እየሰጡ ከሚገኙት በተጨማሪ የምስራቁን ግሪድ የሚያጠናክሩ ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ለመገንባት እንቅስቃሴ ተጀምሯል። ሪጅኑ በአካባቢው ከሚገኙ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጽ/ቤቶች ጋር በቅንጅት የተለያዩ ጥገናዎችን እያከናወነ እንደሚገኝም ነው አቶ ከድር ያስታወቁት። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 06 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+1

ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በኮሙዩኒኬሽን ኦፊሰር 3ኛ እና ዌብሳይት ኤክስፐርት 2ኛ የስራ መደቦች ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር በአዲስ ዘመን ጋዜጣ መጋቢት 02 ቀን 2015 ዓ.ም የውጪ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወሳል፡፡ ስለሆነም መስፈርቱን አሟልታችሁ ከተመዘገባችሁት ተወዳዳሪዎች መካከል የስም ዝርዝራችሁ ከዚህ በታች የተገለጸው በተሰጠው የጽሁፍ ፈተና ብልጫ ያመጣችሁ ስለሆነ ከታህሳስ 08 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 5 (አምስት) የስራ ቀናት ውስጥ ኮተቤ ብረታ ብረት ፊት ለፊት በሚገኘው የተቋሙ ዋና መ/ቤት የሰው ኃይል ምደባ ቢሮ በመገኘት የትምህርት ማስረጃችሁን ዋናዉን እና ኮፒ በመያዝ እየቀረባችሁ የቅጥር ሂደት እንድትፈጽሙ እናሳውቃለን፡፡ ማሳሰቢያ፡- ስማችሁ ያልተጠቀሰ ተወዳዳሪዎች የማለፊያ ነጥብ ያላገኛችሁ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 05 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+9